Visit Agaw Midir/አገው ምድርን እንጎብኝ

Visit Agaw Midir/አገው ምድርን እንጎብኝ The Department of Awi Nationality ADM.Culture & Tourism Dept. is always promoting Agaw peoples culture,History , tourism ,language.

አዲስ አበባ  ባለፈው ሳምንት  ሦስት ታላላቅ ዓለም አቀፍ ኹነቶች አስተናግዳለች፤ ከሕዳር 16- 21 ዓ.ም ባሉት ቀናት ሦስት ታላላቅ  ዓለማቀፍ ኹነቶችን አስተናግዳለች ይኽም ኢትዮጵያ በአፍ...
02/12/2025

አዲስ አበባ ባለፈው ሳምንት ሦስት ታላላቅ ዓለም አቀፍ ኹነቶች አስተናግዳለች፤

ከሕዳር 16- 21 ዓ.ም ባሉት ቀናት ሦስት ታላላቅ ዓለማቀፍ ኹነቶችን አስተናግዳለች ይኽም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚ የMICE (Meeting, Incentive, Conference, and Exhibition) መዳረሻ መሆኗን ከሚያረጋግጡ በርካታ ተግባራት አንዱ ነው።

እነዚህም የምስራቅ አፍሪካ የህግ ባለሙያዎች ማህበር (EALS) 30ኛው ዓመታዊ ጉባዔና ጠቅላላ ጉባዔ፤ 4ኛው ዓለም አቀፍ የአፍሪካ ሕገ-መንግስታዊ ፍርድ ቤቶች ሲምፖዚየም እና 3ኛው የኢጋድ (IGAD) ሚዲያ ሽልማትና ሲምፖዚየም ናቸው።

የአፍሪካ ከፍተኛ ዳኞች፣ የሕገ-መንግስት ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊቃነ መናብርት፣ የህግ ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች አዲስ አበባ የከተሙበት ሳምንት እንደመሆኑ ልዑካኑ የአዲስ አበባ የሚገኙ ታሪካዊ እና አዲስ የተገነቡ መስህቦችን ለመጎብኘት ዕድል አግኝተዋል።

ይህ የስብሰባዎች መጠን እና ጥራት እንዲሁም እንግዶች በከተማዋ የመቆየት ፍላጎት አዲስ አበባ ለትላልቅ የዓለም አቀፍ ዝግጅቶች ያላትን ጠንካራ አቅም ያሳያል።

ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት 𝐆𝐨𝐫𝐠𝐨𝐫𝐚 𝐄𝐜𝐨 𝐑𝐞𝐬𝐨𝐫𝐭ጎርጎራ በሰሜን የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የምትገኝ ውብ ከተማ ናት፡፡ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ደግሞ ተፈጥሯ አብዝቶ ባደለው አካባቢ ለተመሰረተችው...
01/12/2025

ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት 𝐆𝐨𝐫𝐠𝐨𝐫𝐚 𝐄𝐜𝐨 𝐑𝐞𝐬𝐨𝐫𝐭

ጎርጎራ በሰሜን የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የምትገኝ ውብ ከተማ ናት፡፡ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ደግሞ ተፈጥሯ አብዝቶ ባደለው አካባቢ ለተመሰረተችው ከተማ ልዩ ጌጥ እና ዋና መዳረሻ ሁኗል፡፡

Gorgora Eco Resort is a sustainable getaway formed to highlight the gorgeousness of 𝐆𝐨𝐫𝐠𝐨𝐫𝐚, a scenic town on the northern shore of Lake Tana in Amhara region

ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያውን ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ፡፡ባህር ዳር፤ ህዳር 21/2018 ዓ.ምየአብክመ ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የመ...
30/11/2025

ቢሮው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያውን ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ፡፡

ባህር ዳር፤ ህዳር 21/2018 ዓ.ም
የአብክመ ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያውን ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ከዞንና ከተማ አስተዳደር የባህል ቱሪዝም እና ስፖርት መምሪያ ኃላፊዎች ጋር በጋራ በባህር ዳር ከተማ ገምግሟል፡፡

በመርሃ ግብሩ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በሁሉም ዘርፎች የተሻለ አፈጻጸም ያሳየንበት በመሆኑ ይህን አጠናክርን መቀጠልና ዘርፉን ውጤታማና ግንባር ቀደም ማድረግ ይገባናል ሲሉ የአብክመ ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋዬ ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም በቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ፣ በቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት፣ በቋንቋ ልማትና አጠቃቀም ዙሪያ፣ መዳረሻዎችን የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም በማስተዋወቅ እንዲሁም ወቅቱን የጠበቀ ድጋፍና ክትትል ከማድረግ አኳያ በሩብ ዓመቱ ውጤታማ በሆነ መልኩ የተከናወኑ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡

ከሩብ ዓመቱ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ በተጨማሪ በባህልና ቱሪዝም መዋቅር በዞኖች፣ ከተማ አስተዳደሮችና ወረዳዎች በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተደረገውን የድጋፍና ክትትል ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል፡፡

ይህም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ጥንካሬያቸውን እንዲያስቀጥሉ እና ከድክመቶቻቸው ደግሞ በመማር ለቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት እንደሚያግዛቸው ሪፖርት አቅራቢዎቹ ተናግረዋል፡፡

ሪፖርቱ የሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች መምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት በጋራ መገምገሙ ልምድ እንዲለዋወጡና ተሞክሮዎችን እንዲለዋወጡ እንደሚያግዛቸው ተመላክቷል፡፡
Culture,Tourism and Sport Bureau

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር በዚገም ወረዳ ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት በሚል መሪ ሀሳብ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ጀመር።ቅላጅ ፦ ህዳር 19...
28/11/2025

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር በዚገም ወረዳ ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት በሚል መሪ ሀሳብ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ጀመር።

ቅላጅ ፦ ህዳር 19/2018ዓ/ም ዚገም ኮምኒኬሽን በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር በዚገም ወረዳ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ከ5 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች በሚገኙባት፣ የበርካታ የተፈጥሮ ሀብት ፀጋ ባለቤት እንዲሁም ብራንድ በርበሬ አብቃይ በሆነችው በውቢቷ ዚገም ወረዳ እየተከበረ ይገኛል።
ምንጭ፦ zigem communication

በአእምሮ ንብረት፣የፈጠራ ስራዎች፣ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃና መከበር ዙሪያ የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡ባህር ዳር፣ ህዳር 19/2018 ዓ.ምየአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖ...
28/11/2025

በአእምሮ ንብረት፣የፈጠራ ስራዎች፣ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃና መከበር ዙሪያ የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
ባህር ዳር፣ ህዳር 19/2018 ዓ.ም
የአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ከሠላም ኢትዮጵያ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በአእምሯዊ ንብረት /በፈጠራ ስራዎች፣ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች/ ጥበቃ ዙሪያ ለኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ህዳር 19/2018 ዓ.ም. በባህር ዳር ከተማ ተሰጥቷል፡፡ በስልጠናው የተለያዩ አርቲስቶችና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የባህል ልማት ባለሙያዎችና የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ዙሪያ ከሚሰሩ ተቋማት ተወካዮች እና ሌሎችም ተሳትፈዋል፡፡
ስልጠናው እውቀትን፤ጉልበትን እና ጥበብን ተጠቅመን የምናመርተው አእምሯዊ ንብረት በአግባቡና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመጠቀም ይረዳናል ሲሉ ሰልጣኞች አስተያየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ በኪነ ጥበብ ዘርፍ የሚሰሩ የፈጠራ ሥራዎች ተገቢ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች መከበር የፈጠራ ባለቤቶችን ከማበረታታት ባለፈ የኪነጥበብ ዘርፉን ለማሳደግ እና ሀገራዊ አንድነትን ለመገንባት ከፍተኛ ድርሻ አለው ብለዋል፡፡
ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በኪነ ጥበብ ስራዎች እንደቀዩ የሚናገሩት አቶ በምናቡ ከበደ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአእምሯዊ ንብረት መብቶችን የሚያስጠብቁ ተቋማትና የሙያ ማህበራት በመኖራቸው የተሻለ መሆኑን ገልጸው የዘርፉ ባለሙያዎች /የኪነ ጥበብ ቤተሰቡ/ ግንዛቤ አለማደግ የፈጠራ መብቶች እንዳይከበሩ አድርጓል ብለዋል፡፡

የኪነጥበብ ሥራዎች እርስበርስ የሚያስተሳስሩ፣ ራስን ፣ቤተሰብን ፣ሕዝብን እና አገርን በበጎ የሚቀርጹ፣የለማ አእምሮና ማህበረሰብ እንዲፈጠር የሚያግዙ በአጠቃላይ ያደገ አገርን ስለሚፈጥሩ የጥበብ ስራዎች የቅጅና ተዛማጅ መብቶች እንዲከበሩ መደረጉ ድርሳ ጉልህ መሆኑን ተሳታፊዎቹ አስተያየታቸውን ተናግረዋል፡፡
በዕለቱ የአማራ ክልል ባህል፣ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ እምቢአለ የተገኙ ሲሆን ክልሉ ያለውን እምቅ የቱሪዝም ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም ከኪነጥበብ ባለሙያዎች ጋር እየሰራ እንደሆነ ገልጸው የዘርፉ ባለሙያዎችም መብታቸው እንዲከበርም ተመሳሳይ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡ እና ቢሮው የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture ፤Tourism & Sport Bureau
bureau
# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ

======= ===የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በጃዊ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በአጠቃላይ የፓርኩ የቆዳ ስፋት 51‚796 ሄክታር ተከልሎ በጥበቃ ላይ ያለ የተፈጥሮ ደን ...
28/11/2025

======= ===
የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በጃዊ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በአጠቃላይ የፓርኩ የቆዳ ስፋት 51‚796 ሄክታር ተከልሎ በጥበቃ ላይ ያለ የተፈጥሮ ደን ነው፡፡
የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ በምዕራብ ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በምስራቅ ባኩሳ ኪዳነ-ምህረት ቀበሌ በሰሜን ባኩሳ ማርያም ቀበሌ በደቡብ ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልልና ባኩሳ ማርያም ቀበሌ ያዋስኑታል፡፡ ፓርኩ ከባህር ወለል በላይ ከ710–1200 ሜትር ከፍታ ላይ ይገኛል፡፡ አማካኝ የዝናብ መጠኑ 900–1288 ሚ.ሜ ነው፡፡ ዝቅተኛና ከፍተኛ የሙቀት መጠኑ 15.7-31.5 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ አማካኝ የሙቀት መጠኑ ደግሞ 23.6 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ሲሆን 100% የቆላ የአየር ቀጠና ውስጥ ይገኛል፡፡
የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ በሀገራችን በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ የተመናመነ የበረሃ ብዝሀ ህይወት ውስጥ ወካይ ስርዓተ-ምህዳር የተፈጥሮ ደኑን ይወክላል፡፡ የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ ከ80% በላይ ተፈጥሮሯዊነቱን የጠበቀ ሲሆን
– ከ28 በላይ ታላላቅ አጥቢ የዱር እንስሳት
– ከ31 በላይ አዕዋፋት
– ከ58/63 በላይ የዛፍና ቁጥቋጦ በርካታ የሳር ዝርያዎች እንዲሁም ተሳቢና ተራማጅ እንደ ዘንዶ፣ አዞ፣ የተለያዩ የእባብና የአሳ ዝርያዎች ይገኙበታል፡፡
የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ የተፈጥሮ ደን በሀገሪቱና በክልሉ እንደልብ የማይገኙ ለመጥፋት የተቃረቡ እፅዋት እንደ ሽመል፣ ጥቁር እንጨት፣ የቆላ ዋንዛ፣ኮመር፣የጣን ዛፍ፣ ዶቅማ፣ ላሎ ፣ዋርካ፣ሾላ ዛፎችና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡
በፓርኩ የሚገኙ የዱር እንስሳት መካከል እንበሳ፣የቆላ አጋዘን፣ ድኩላ፣ ከርከሮ፣ ዝንጀሮ፣ ፌቆ፣ ነብር፣ ጉሬዛ፣ ቀይ ጦጣ፣ ተኩላ፣ አሳማ፣ ሚዳቋ፣ ጅብ፣ ጀርባው ጥቁር ቀበሮ፣ ጃርት፣ ጥርኝ የመሳሰሉት ሲገኙ ቀደም ሲል የነበሩ አሁን ግን የተሰደዱ ውድንቢ፣ ደፈርሳ፣ ጨሌ ባለጋሜ፣ ቶራቆርኬ በአካባቢው ኑዋሪዎች ዘንድ የሚታወቁ የቅርብ ጊዜ ታሪኮች ናቸው፡፡
💝💝ሌላኛ የአዊ ፀጋ ባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ💝💝

" ቱሪዝምን ከቅርስነት ወደ ቁርስነት  ለውጦ መጠቀም ይገባል "ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ  " ዘመኑን እንገንዘበው፣ያለንን እንወቅ፣ ቅርስ ስላለህ ብቻ አይጎበኝም ፤ ሰላምና ተመጣጣኝ አገልግሎት በ...
27/11/2025

" ቱሪዝምን ከቅርስነት ወደ ቁርስነት ለውጦ መጠቀም ይገባል "
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

" ዘመኑን እንገንዘበው፣ያለንን እንወቅ፣ ቅርስ ስላለህ ብቻ አይጎበኝም ፤ ሰላምና ተመጣጣኝ አገልግሎት በማቅረብ መስህብ ሀብቶችን ወደ መዳረሻነት መቀየር ያስፈልጋል።

አሁን ጊዜው የጋስትሮኖሚ ነው - ቱሪስቱን ባህላዊ ምግብ ሰርተህ እንዲበላ ሳይሆን እራሱ አብስሎ እንዲበላ ማድረግ ፣ባህላዊ አልባሳትንና ቁሳቁሶችን መሸጥ ብቻ ሳይሆን እንዲሰራ ወዘተ - ማድረግ ይገባል"
በአጠቃላይ ቅርሶቻችንን ቁርስ የምናደርግበት ጊዜ ላይ ነን "

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ‘‘አንታጉ”የአገውኛ ፊልምን ተረከበ፡፡ህዳር 18/2018ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲየእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአንታጉ ፊልምን ደህንነት ጠብቆ በመያዝ ለመማር ማስተማር፣ለምምርና...
27/11/2025

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ‘‘አንታጉ”የአገውኛ ፊልምን ተረከበ፡፡
ህዳር 18/2018ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአንታጉ ፊልምን ደህንነት ጠብቆ በመያዝ ለመማር ማስተማር፣ለምምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ለማዋል ከአዊ ብሄረሰብ አስታዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ተረክቧል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝኣንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው የአገው ባህል ፣ታሪክ እና ቋንቋ እንዲያድግ የትኩረት መስክ አድረጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸው ለመጀመሪያ ጊዜ በአገወኛ ቋንቋ የተሰራውን ታሪካዊ ፊልም በመረከቡ መደሰቱን ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ክንዴ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው የአገው ባህል ፣ታሪክ እና ቋንቋን ለማሳዳግ የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ተቋቁም በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው ይህን ታሪካዊ ፊልም በመረከብ ፊልሙ ከመማር ማስተማር እና ምርምር በተጨማሪ ለህዝቡ ተደራሽ እንዲሆን ደህንነቱ ተጠብቆ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች እንደሚሰራጭ ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ክንዴ አክለውም የአዊ ብሄረሰብ አስተደዳር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አንታጉ ፊልምን ካለምንም ክፍያ ማስረከቡን ጠቅሰው ይህ ፊልም እንዲሰራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለነበራቸው አካላትም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የአዊ ብሄረሰብ አስተደዳር ቱሪዝም መምሪያ ተወካይ ኃላፊ ወለሊ ጌቴ የአንታጉ ፊልም የአገው ህዝብ ታሪክ፣ቋንቋ እና ባህልን ለማሳደግ የተሰራ የህዝብ ፊልም መሆኑን ገልጸው ፊልሙ ደህንነቱ ተጠብቆ ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንዲሆን ዩኒቨርሲቲውን መምረጣቸውን ተናግረዋል፡፡ ኃላፊው አያዘውም አንታጉ ፊልም ሲሰራ ህብረተሰቡ በሁሉም ነገር ያገዘ መሆኑን አስታውሰው ፊልሙን ወደ ህብረተሰቡ ለማድረስ የተለያዩ ውስንነቶች ያጋጠሙ መሆኑን አስታውሰው ይህን ችግር ለመቅረፍ ለዩኒቨርሲቲው ማስረከብ አማራጭ መሆን ገልጸዋል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ብርሃኑ አሳየ(ረ/ፕሮፌሰር) አንታጉ ፊልም የአገውን ባህል፣ ቋንቋና ታሪክን የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲው በመማር ማስተማሪያነት እና ለምርምር እንዲሁም ዩኒቨርስቲው ለቀጣይ የቴያትርና የፊልም ስራ ለመስራት ጭምር የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ተተኪ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉነህ አሸነፍ አንታጉ ፊልም የመጀመሪያው በአገወኛ ቋንቋ የተሰራው ፊልም ባለቤቱ ህዝብ መሆኑን ገልጸው መምሪያው ለእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ያስረከበው ለጥናትና ምርምር እንዲጠቀም ፣ ማህበራዊ ሚዲያን ተጠቅሞ ለህዝብ ተደራሽ እእንዲያደርግ እና ደህንነቱ ተጠብቆ ለትውልድ እንዲያስተላልፍ መሆኑን ተናግረዋል ።
በርክክብ ስነ ስርዓቱ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እና የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡
ያለህን ዕምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

27/11/2025
በጎንደር የቱሪዝም ልማቱና የከተማው ማስዋብ ስራዎች የጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል በጎንደር እየተከናወነ ያለው የቱሪዝም ልማትና የከተማው ማስዋብ ስራዎች የውጭና የሀገር ው...
26/11/2025

በጎንደር የቱሪዝም ልማቱና የከተማው ማስዋብ ስራዎች የጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል

በጎንደር እየተከናወነ ያለው የቱሪዝም ልማትና የከተማው ማስዋብ ስራዎች የውጭና የሀገር ውስጥ የጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ ተገለጸ።

የዘንድሮ የጎንደር የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ የሕዝቦችን አብሮነትና አንድነትን በሚያስተሳስስር መንገድ ከዋዜማው ጀምሮ በተለያዩ ሁነቶች ለማክበር ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ ነው።

የአማራ ክልል ባሕል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ዝግጅቱን በመገምገም ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተመልክቷል።

የቢሮው ሃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋዬ በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ስራ የጎንደር ከተማን ዳግም ትንሳኤ ያበሰረ ታላቅ ታሪካዊ ክዋኔ ነው፡፡

እንጅባራ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ በሚሰራው ሥራ አቅም እየሆነን ስለሆነ እናመሰግናለን
24/11/2025

እንጅባራ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ በሚሰራው ሥራ አቅም እየሆነን ስለሆነ እናመሰግናለን

23/11/2025

Address

Injibara
09

Telephone

+251582270376

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Visit Agaw Midir/አገው ምድርን እንጎብኝ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Visit Agaw Midir/አገው ምድርን እንጎብኝ:

Share