Gibe Daily Post

  | በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ቁጥራቸው ከ190 በላይ የሆኑ የኦነግ ሻኔ ታጣቂዎች ተሰልፈው በመግባት እጃቸውን ሰጡ።ሰላም ለኢትዮጵያ ሰላም ለኦሮሚያ ክልል እና ህዝብ
15/08/2025

| በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ቁጥራቸው ከ190 በላይ የሆኑ የኦነግ ሻኔ ታጣቂዎች ተሰልፈው በመግባት እጃቸውን ሰጡ።

ሰላም ለኢትዮጵያ ሰላም ለኦሮሚያ ክልል እና ህዝብ

የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ልደትን ሳስብ...(በላይነህ አቅናው) በአመራርነታቸው እና በርዕዮት ላይ እንዳሰላስል አነሳስቶኛል። እንኳን ተወለዱ ለማለት ስሰናዳ  አእምሮዬ በአንድ ወቅት ...
15/08/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ልደትን ሳስብ...
(በላይነህ አቅናው)

በአመራርነታቸው እና በርዕዮት ላይ እንዳሰላስል አነሳስቶኛል። እንኳን ተወለዱ ለማለት ስሰናዳ አእምሮዬ በአንድ ወቅት ስላነበብኩት የጥንቱን አለም ስለ ለወጠዉ ወጣቱ የመቄዶንያ ንጉስ ስለ ታላቁ እስክንድር በታሪክ መም ወደኋላ በመመለስ እያውጠነጠነ ነበር።

በዘመናት እና በሁኔታዎች ቢለያዩም በአካሄዳቸው መካከል ያለው ተመሳሳይነት በገሃድ ይታያል። ሁለቱም በሕዝባቸዉ ታሪክ ውስጥ ወሳኝ በሚባል ጊዜ ላይ ብቅ ያሉ መሪዎች ናቸዉ። ሁለቱም ብርቅዬ ስትራቴጂስት፣ የአዳዲስ እሳቤዎች ፈለግ፣ ቆራጥ ውሳኔ አሰጣጥ እና ሰዎችን ከትልቅ ራዕይ ጀርባ የማሰባሰብና የመምራት ችሎታን የተካኑ ናቸው። ይህች አጭር ጽሑፍ ከዚህ እውነታ የተፀነሰች የዚሁ ሃቅ ነጸብራቅ ናት።

ዐብይ አህመድ በመጋቢት 2010 ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዉ በትረ ስልጣኑን ሲጨብጡ በኢትዮጵያ ታሪክ የብሩህ ዘመን ጮራ መፈንደቅ መባቻ ሆነ። ዝነኛ የወታደራዊ መረጃ መኮንን የነበሩት ጠቅላዩ የለውጥ አራማጅና አብሳሪ ፖለቲከኛ ለመሆንም ብቃታቸዉ ከሚገመተዉ በላይ ሆኖ ተገኘ።

ከቀደሙት መሪዎች በጎሣ ፖለቲካ የተተበተበ ፌዴሬሽንንና የላሸቀ ኢኮኖሚያዊ መሰናክሎችን ቢወርሱም ወዲያው ካቢኔያቸውን በአዲስ መልክ አዋቅረዉ፣ ሴቶችን ወደ አመራርነት ከፍ በማድረግ በይዘቱም በአደረጃጀቱም ለየት ያለ ቅርፅ ያለዉን መንግስት አዋቀሩ። በዚህ እምብዛም ጊዜ ያልፈጀባቸዉ ነገር ግን ስር-ነቀል መንግስታዊ ውቅር የቆራጥ አመራር ባህሪያትን በሚገባ አሳይተዋል።

“ታላቁ እስክንድር” በመባል የሚታወቀው የመቄዶንያው ሳልሳዊ አሌክሳንደር በተመሳሳይ መልኩ ነበር የተንኮታንኮተን ግዛት በ336 የወረሰዉ። እሱም ታዲያ በወራት ውስጥ በግሪክ የነበረውን አመጽ አስወግዶ ግብፅ ሲገባ የነጻ አውጭነት ሰያሜን ለማግኘት ጊዜ አልፈጀበትም። የአካባቢውን ልማዶች ተቀብሎና አክብሮ በግሪክ ስታይል ተቋማትን በማስተዋወቅ እስክንድርያን መሰረተ።

የነኚህ ብርቱ መሪዎች ግብር የሚመሳሰለዉ እንግዲህ በአመራር ክህሎታቸዉ ሲሆን ሁለቱም ወታደራዊ ችሎታ እና አዳዲስ የአስተዳደር ዓይነቶችን የመሸመን አቅም አሳይተዎል። ሌላዉ ተመሳሳይነታቸዉ ወደ መሪነት ዙፋን የመጡበት መንገድና የወጡበት መስመር ነው። በአመራር ዲ ኤን ኤ ውስጥ: ሁለቱም ሰዎች ወደ ቢሮ የገቡት ከመንግስት መዋቅር ሲሆን ስለ መንግስት አደረጃጀት ሙሉ እዉቀት ከጨበጡ በኃላ ነበር። እስክንድር አልጋ ወራሽ እና ጄኔራል ሲሆን ዐብይ በወታደራዊ መረጃ ኦፊሰርነት አገልግሎ ነው። ሁለቱም ቀድሞ ለተፈጠረዉ አገራዊ ቀውሶች በድፍረት እና በቁርጠኝነት ጥም ቆራጭ የሆነ ምላሽ ሰጥተዋል። የአሌክሳንደር የከተሞች መሠረት የሄለኒክ ባህል እና አስተዳደር ማዕከል ሆኖ አገልግሏል። ዐብይ የካቢኔ ማሻሻያ እና ተምሳሌታዊ ሹመቶች ለተሃድሶ ራዕያቸውን እንደ ዘመናዊ ተቋማት ሆነው ያገለግላሉ።

የዐብይ የቀይ ባህር ስልታዊ አቀራረብ የአሌክሳንደርን እስትራቴጂካዊ የአሌክሳንደሪያን ምስረታ ያሳያል። ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የባህር በር አልባ ሆና ኖራለች። ይህም ለውጭ ንግድ እንቅፋት ነው። ዐብይ ኢትዮጵያን ከአለም አቀፍ ንግድ ጋር ለማስተሳሰር በማሰብ በቀይ ባህር ዳርቻ ላይ የወደብ መዳረሻን ለማስጠበቅ ዲፕሎማሲያዊ እና ሎጂስቲካዊ እርምጃዎችን ጀምሯል። እስክንድር በስትራቴጂ ከባህር ዳርቻ ላይ ከተሞችን እንደሚገነባ ሁሉ፣ ዐብይም ኢትዮጵያን ከመገለል ከፍ ለማድረግ የመንገድ፣ የጉምሩክ እና የንግድ ግንኙነቶችን ይገነባል። ሁለቱም መሪዎች ተምሳሌታዊነትን ከቁስ ጋር ይጠቀማሉ። አሌክሳንደር በግብፅ እንደ ፈርዖን ንግስና መለኮታዊ እና ፖለቲካዊ ህጋዊነትን አዋህዷል። የሄለኒክ እና የአካባቢ ባህሎችን በአምልኮ ሥርዓቶች፣ በሥነ ሕንፃ እና በአስተዳደር አዋህዷል። ዐብይ ዘመናዊ አቻዎችን ይጠቀማል፡ ህዝባዊ ምረቃዎችን፣ አካታች ንግግሮችን እና ከፍተኛ ተፅእኖ ያላቸውን የመሠረተ ልማት ማስጀመሪያዎች። የብሔር ብሔረሰቦችን ተሻግሮ ዘመናዊ፣ የተዋሃደች ኢትዮጵያን የሚያመላክት ሀገራዊ ትረካ ቀርጿል።

ስልታዊ ራዕይ፣ ተቋማዊ ፈጠራ እና ተምሳሌታዊ ድርጊቶች እስክንድርንና ዐብይን የሚያገናኙት የአመራር ምሰሶዎች ናቸው። የአሌክሳንደር ኢምፓየር በአህጉራት ውስጥ ብዙ መቶ ዘመናትን እና ረጅም ባህላዊ ተፅእኖን አሰድሯል። የአብይ ፕሮጀክት የተለየ ነው፡ ኢኮኖሚያዊ እድሳት፣ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር፧ እና ክልላዊ መደመርን እዉን በማድረግ የተሰበረ ፓሊቲውን ወደ አንድ ወጥ የሆነና ወደፊት የሚመለከት አካል የመቀየር ፍላጎት አለዉ።

በአሌክሳንደር ዘመን ኃይል ኢምፓየርን ገነባ። በዐብይ ዘመን ግን መግባባት እድገትን ማጠናከር አለበት። የወደብ ተደራሽነት በመደራደር፣ ተቋማትን ማሻሻል እና የእርስ በርስ ግጭት አደጋን በማስቀረት ሰላምን ማስጠበቅ አለበት። የተረጋጋ የመንግስት ኡደት፣ የተግባር ሎጂስቲክስ፣ ኮሪደሮችን እና አካታች አስተዳደርን ካሳካ፣ ትሩፋቱ የሚለካው በተሃድሶ ፅንሰ-ሀሳቦች ብቻ ሳይሆን በተሻሻለ ህይወት እና በኢኮኖሚ ለውጦችም ላይ ነው። ታሪክ ዘላቂ ተቋማትን የሚገነቡ እና የሰዎችን አድማስ የሚያሰፉ መሪዎችን ይሸልማል። እስክንድር ሲታወስ ሥልጣኔን የፈጠረ ኢምፓየር መገንባቱ ነዉ። ዐቢይ በዘመኑ ተቋሞች ዜጎቿን በብልጽግናና በሰላም የሚያስተሳስር ኢትዮጵያን ለመገንባት ይፈልጋል። ከተሳካለት, ከታላቁ እስክንድር ጋር ያለው ንፅፅር ለዉዳሴ ፍጆታ ሳይሆን በርግጥም የሚገባዉ ይሆናል።

ሕዝበ-ሙስሊሙ መሪውን በሚመርጥበት ምርጫ ዛሬ የዑለማ ምርጫ ተካሂዷልየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ባወጣው መርሐ-ግብር መሰረት ዛሬ የዑለማ (የሃይማኖ...
15/08/2025

ሕዝበ-ሙስሊሙ መሪውን በሚመርጥበት ምርጫ ዛሬ የዑለማ ምርጫ ተካሂዷል

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ባወጣው መርሐ-ግብር መሰረት ዛሬ የዑለማ (የሃይማኖት ሊቃውንት) ምርጫ ተካሂዷል።

ኢቢሲ በተገኘበት በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለከተማ ወረዳ 3 ሀምዛ መስጂድ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ ድምፅ ሰጥተዋል።

ፕሬዚዳንት አስቀድመው ለመራጭነት በተመዘገቡበት መስጂድ ተገኝተው ነው ድምፅ የሰጡት።

ዛሬ በዑለማ (በሃይማኖት ሊቃውንት) የተጀመረው ምርጫ በቀጣይ ሁለት ቀናት በወጣቶች፣ በሴቶች፣ በምሁራን እና በሠራተኛ ማሕበረሰብ ዘርፍ ይካሄዳል።

ነሐሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ል የተጀመረው የመጅሊስ ምርጫ ነሐሴ 30 ቀን 2017 ዓ.ል የፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን በማዋቀር እና መሪዎችን በመምረጥ ይጠናቀቃል።

የመራጭነት ምዝገባ የተመዘገቡ ሙስሊሞች በቀሪዎቹ ቀናት በተመዘገቡበት ዘርፍ በነቂስ ወጥተው ወኪሎቻቸውን እንዲመርጡም ፕሬዚዳንቱ ጥሪ አቅርበዋል።

በሀብታሙ ተክለስላሴ

እንኳን ተወለድክ!!Baga Dhalatte!!My PM Dr. Abiy Ahmed Ali  Happy Birthday
15/08/2025

እንኳን ተወለድክ!!
Baga Dhalatte!!

My PM Dr. Abiy Ahmed Ali Happy Birthday

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሲዳማ ክልል ሲገቡ የተደረገላቸው አቀባበል - (በምሥል) #ሲዳማ
15/08/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሲዳማ ክልል ሲገቡ የተደረገላቸው አቀባበል - (በምሥል)

#ሲዳማ

ወደ ውጭ ሀገር እልካለሁ በማለት ከተለያዩ ግለሰቦች ከ1.3 ሚሊየን ብር በላይ አጭበርብሮ የተሰወረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታወ...
14/08/2025

ወደ ውጭ ሀገር እልካለሁ በማለት ከተለያዩ ግለሰቦች ከ1.3 ሚሊየን ብር በላይ አጭበርብሮ የተሰወረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ጌትነት እንዳሻው የተባለ ተከሳሽ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው መገናኛ ሠላም ታወር ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይቶ ‹‹ ኤልያና የጉዞና አማካሪ ድርጅት ›› የሚል ህጋዊ እውቅና የሌለው ድርጅት በመክፈት ሰዎችን ወደ ውጭ ሀገር እልካለሁ በሚል ከተለያዩ ግለሰቦች እስከ 1 ሚሊየን 360ሺህ ብር ድረስ በመቀበል የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም እንደነበረ ፖሊስ ገልጿል።

ግለሰቡ ግንቦት 09 ቀን 2017 ዓ/ም የግል ተበዳይ ብርቱካን እመብርሀን የተባለች ግለሰብን ወደ ውጭ ሀገር እልክሻለሁ በማለት 340ሺህ ብር በመቀበልና ቼክ እንደማታለያ በመስጠት ግለሰቧንም በተባለው ቀን ወደ ውጪ ሊልክ ባለመቻሉ ለፖሊስ ሪፖርት አድርገዋል፡፡

ከግለሰቧ ክስ በተጨማሪም ሰናይት ተክላይ፣ ሠናይት ገ/ኪዳን እና አብረኀት የተባሉ ግለሰቦች ከእያንዳቸው 340ሺህ ብር በመቀበልና ወደ ውጪ ሀገር እልካችኋለሁ በማለት መሰወሩን በመግለፅ ተጨማሪ ሪፖርት ለፖሊስም ደርሶታል፡፡

የክ/ከተማው ፖሊስ የቀረበለትን ክስ መሰረት በማድረግ ባደረገው መረጃ የማሰባሰብ ተግባር ተጠርጣሪው ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገር የመላክ ምንም ዓይነት ህጋዊ ፈቃድ የሌለው ከመሆኑም በተጨማሪ በተለያዩ ክ/ከተሞች በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ክስ ተመስርቶበት እየተፈለገ እንደሆነም ለመረዳት ተችሏል፡፡

ግለሰቡን ሲፈለግና ሲያፈላለግ የነበረው ፖሊስም ነሐሴ 07 ቀን 2017 ዓ/ም ባደረገው ብርቱ ክትትል ተከሳሽ ይኖርበታል በተባለው ለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 14 ልዩ ቦታው የካ አባዶ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከጠዋት 12፡00 ሠዓት ላይ በቁጥጥር ስር ሊውልም ችሏል፡፡

ፖሊስ በግለሰቡ ላይ ተጨማሪ ምርመራ የማስፋት ተግባሩን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ከዚህ ቀደም በዚህ ግለሰብ ተመሳሳይ የማጭበርበር ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚል አካል ካለም የካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመቅረብ መረጃ መስጠት የሚችል መሆኑም ተመላክቷል፡፡

በተለያዩ ጊዜያት ወደ ውጭ ሀገር እንልካለን የሚሉ አንዳንድ አካላት ተግባራቸው ህጋዊነትን የተከተለ መሆኑን በሚገባ ማረጋገጥ ለመሰል የወንጀል ድርጊቶች ተጋላጭ ከመሆን ያድናል ሲልም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን ያስተላልፋል፡፡
*

AAP 🙏

በቁጥጥር ስር ውሏል‼️ማንም ከህግ በላይ አይሆንም:: ማንንም
14/08/2025

በቁጥጥር ስር ውሏል‼️

ማንም ከህግ በላይ አይሆንም:: ማንንም

"ሂሳብ እንስራ ከተባለ....‼የትውልድ ስብራት ጠግኖ ያራመደ፣በውለታው መጠን ደሞዝ ያልወሰደ፣በአሻራው ቁስል ልክ ዋጋ ያልተከፈለው፣የዚች ሀገር ሐኪም አብይ አህመድ ነው። 👑 Abiy Ahmed...
14/08/2025

"ሂሳብ እንስራ ከተባለ....‼

የትውልድ ስብራት ጠግኖ ያራመደ፣
በውለታው መጠን ደሞዝ ያልወሰደ፣
በአሻራው ቁስል ልክ ዋጋ ያልተከፈለው፣
የዚች ሀገር ሐኪም አብይ አህመድ ነው።


👑 Abiy Ahmed Ali 👑

13/08/2025

ተጋጭተን አይተነዋል ፣ ተዋግተንም አይተነዋል....


Abiy Ahmed Ali 👑

ጫካ የደረሰ ስርዓት አልበኝነት  በኢትዮጵያ የተስፋፋው  ቀድመው የተፈጠሩ ጥቂት ስርዓት አልበኞችን በህግ አግባብ ስርዓት ባለማስያዝ አልያም ለይስሙላ ለቀናት አስሮ በመልቀቅ ዝንጉ አሰራር ም...
13/08/2025

ጫካ የደረሰ ስርዓት አልበኝነት በኢትዮጵያ የተስፋፋው ቀድመው የተፈጠሩ ጥቂት ስርዓት አልበኞችን በህግ አግባብ ስርዓት ባለማስያዝ አልያም ለይስሙላ ለቀናት አስሮ በመልቀቅ ዝንጉ አሰራር ምክንያት ነው። ለዚህም አሁን በየጫካው በብሔር ስም የእከሌ ክ/ጦር መሪ ነኝ ሚሉ በእንዝላልነት በህግ ሳይጠየቁ የቀሩ አልያም የተለቀቁ ሽፍታ አጋች ዘራፊዎችን መመልከት በቂ ነው።

አሁን ደግሞ የጫካው ሳይበቃ እነኝህን የከተማ ጋንግ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሱ ፣ ለሌሎችም መጥፎ ልምድ እያስፋፉ የሚገኙ ማናለብኝ ባይ ቦዘኔዎችን በግዜ በህግ በመጠየቅ ስርዓት ማስያዝ ያስፈልጋል። ህግና ስርዓት እንዲናቅ እንዲረገጥ የሚያደጉ መዘናጋቶች ዋጋ ያስከፍላሉ ።

ሳይቃጠል በቅጠል !

ከህግ በላይ የሆነው ዳለቻ! ለሚደግፋችሁና ለቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ክብርና ህሊናስ አትጨነቁም ወይ? በዚህ ልጅ ጉዳይ በድጋሜ ለመፃፍ ተገደድኩ። ከዚህ በላይ ህሊናዬ ሊያስተኛኝ አይችልም።  ...
13/08/2025

ከህግ በላይ የሆነው ዳለቻ!

ለሚደግፋችሁና ለቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ክብርና ህሊናስ አትጨነቁም ወይ?

በዚህ ልጅ ጉዳይ በድጋሜ ለመፃፍ ተገደድኩ። ከዚህ በላይ ህሊናዬ ሊያስተኛኝ አይችልም። አንድ ግለሰብ መንግስት ባለባት ሐገር እንዴት ነው ከህግ በላይ ሆኖ የሚኖረው? ህዝብን እንደህዝብ መሃል አዲስ አበባ ላይ ሆኖ ቀን ከሌት እየተሳደበ፣ እያዋረደ፣ መሳሪያ እያወጣ ውጪ ሐገር ያሉ ሰዎችን ዘር ማንዘራችሁን እጨርሳለሁ እያለ፣ አማራን ትግሬን ፣ ደቡብን፣ እራሱ የኦሮሞን ህዝብ በፀያፍ ስድብ እየሰደበና እያንቋሸሸ አዲስ አበባ መሃል ጫፉ ሳይነካ የሚኖረው በምን ህግ ነው?

ባለጊዜ ነን ቀጥቅጠን እንገዛችኋለን እያለ፣ ሃይማኖትን ለመናገር በሚቀፍ ስድብ እየሰደበና እያንቋሸሸ፣ ባለስልጣናትን እየጠራ የግል እስርቤት አለኝ የፈለኩትን አስራለሁ የፈለኩትን አስገድላለሁ እያለ መንግስት ባለባት ሐገር ምን እየተሰራ እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም።

ህዝቡ እንዲህ እስኪማረር ድረስ፣ ህዝብ በሱ ምክኒያት እስኪያለቅስ ድረስ፣ ማነው ለሱ protection እየሰጠው ያለው? እውነት የህግ አካላት የዚህ ልጅ ጉዳይ ሳይደርሳቹህና ሳታይት ቀርታችሁ ነው ወይ? ስንቱን ሰው በአንዲት ስህተት በቁጥጥር ስር ስታውሉ ይሄ ሰውዬ ኢትዮጵያዊ እንኳን አይደለም አሜሪካዊ ነው። በዚህ ደረጃ በህዝብ ላይ እንዲህ ነውር እየሰራና እየተናገረ ሐገሪቱ መንግስት አልባ ሐገር እንድትመስል እያደረገ ደረቱን ነፍቶ ሲኖር በሱ የተነሳ የኦሮሞ ህዝብ ባለጊዜ እየተባለ፣ በሱ የተነሳ መንግስትን የሚደግፍ ህሊና ያለው ሰው ሁሉ አንገቱን ደፍቶ እየኖረ ይሄ አንድ ተራ ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውላችሁ በህግ መጠየቅ ያልቻላችሁት ለምንድነው?

በስሚ ስሚ የሚያውቃቸውን ባለስልጣናት ዝምድና እንዳለው እያስመሰለ፣ የኮሚሽነሮችን፣ የባለስልጣናትን ስም እየጠራ፣ የግል እስር ቤት አለኝ እያለ ቀን ተሌት ታርጌት አድርጎ ህዝብን የሚያማርርና የሚያስለቅስን ልጅ እጁን መያዝ ያልቻላችሁትና የፈራችሁት በምን ምክኒያት ነው? ህዝቡስ በዚህ ልጅ የተነሳ ቢማረር ይፈረድበታል ወይ? እኛ አንዳች ነገር ባላገኘነው “ተከፋይ” እየተባልን ሐገራችንን በአቅማችን እያገለገልን የተሰበረውን ለመጠገን ሌት ተቀን እንለፋለን እንዲህ አይነቱን አሜሪካ ውስጥ ትራክ እየነዳ ሲሳደብ የኖረን መሃይም የአእምሮ ህመምተኛ ከተማ መሃል ህዝብ እያባላና ህዝብ በመንግስት ላይ ጥላቻ እንዲኖረው ቀን ከሌት እየሰራ በነፃነት እንዲኖር የፈቀዳችሁት በምን ህሊናችሁ መዝናችሁት ነው?

እኔ የዚህን ልጅ ቪዲዮ እዚህ ለጥፌ የሰው ጭንቅላት አላበላሽም። አሁንም ይሄ ልጅ በህግ ይጠየቅልን። በኢትዮጵያ ታሪክ በዚህ ልጅ ደረጃ ህዝብ የተሳደበ፣ የግድያ ዛቻ ያደረሰ፣ የተራበች እናትን ፎቶ ለጥፎ ያዋረደ፣ ሰዎችን እንደሚገድል የበግልፅ የሚያወራ፣ ከዚህም በላይ እጅግ አፀያፊ ነገሮችን ለአመታት በአደባባይ የፈፀመ ግለሰብ የተከበረውን የኦሮሞን ህዝብ የሚያዋርድ፣ ማህበረሰቡን ገዳይ ጨፍጫፊ ባለጊዜ እንዲባል ቀን ከሌት የሚሰራ ሰው ሳይያዝ ለሁሉም እኩል ህግ አለ ብሎ ለማውራት ይከብደኛል።

ልጁ አባቱ የተከበሩ ሐገር የሚያግዙ እንደሆኑ አጣርቻለሁ። ነገር ግን የማንም ሰው ልጅ ቢሆንም በዚህ ደረጃ ነውር ሐገርና ህዝብ ላይ ከፈፀመ ይጠየቃል። ይታሰራል። ይመረመራል። ሐገርን ሐገር የሚያደርጋት የህግ የበላይነት ነው። ከዚህ ልጅ ምን ለማትረፍስ ነው ይሄ ሁሉ ትእግስትና ዝምታ። ለሌላው ለሚደግፋችሁና ለቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ክብርና ህሊናስ አትጨነቁም ወይ?

በዚህ ልጅ ምክኒያት ኦሮሞ አማራ ትግሬ ሳይባል የሚደርሱኝ ቪዲዮዎችና ምሬቶች ከአቅም በላይ ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ የህግ አካል ካለ ከዚህ ልጅ በላይ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለአመታት ወንጀል የሰራ ሰው የለምና ለህግ ይቅረብልን ስል የኢትዮጵያን ህዝብ ወክዬ ጥያቄዬን አቀርባለሁ። ይሄ የሁሉም ህዝብ የጋራ ጥያቄ ነው።

አክቲቪስት ናትናኤል መኮንን

Address

Jimma

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gibe Daily Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gibe Daily Post:

Share