Gibe Daily Post

Gibe Daily Post tiktok.com/

telegram👉https://t.me/mohagi2114

14/11/2025

የሆናችሁ እና single mom የመሆን ሃሳብ ያላችሁ ሴቶች ካላቹም ከዚህ ቪዲዮ ብዙ የምትማሩ ነገር ይኖራል ብዬ ላጋራችሁ ወደድኩ። #ይደመጥ

13/11/2025
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የሞባይል ስልክ ስርቆት ፈፅመው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡...
13/11/2025

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የሞባይል ስልክ ስርቆት ፈፅመው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው በተለምዶ "ሿሿ” የተባለውን ወንጀል በመፈፀም ሞባይል ስልክ ሰርቀው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ናትናኤል አለሙ ፣ አቤል ኮርሳ ፣ ዕድላዊት መላከ፣ መቅደስ አቡሽ፣ ኢዛና ባህሩ፣ ፀጋ ታደሰ እና መቅደስ አምዴሳ የተባሉ ሲሆኑ ሽፈራው ገበየሁ በተባለ ግለሰብ ላይ ወንጀሉን የፈፀሙት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ኮዬ ቂሊንጦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡

ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ተጠርጣሪዎቹ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 89261 ኦ.ሮ በሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የግል ተበዳይን ጭነው እየተጓዙ ሞባይል ስልኩን ከኪሱ ከሰረቁ በኋላ "ትራፊክ ይቀጣናል ጋቢና ግባ ብለው" እንዳስወረዱት እና ከወረደ በኋላ ጥለውት እንዳመለጡ ተገልጿል፡፡

በግል ተበዳይ ላይ ወንጀል እንደተፈፀመ የተመለከቱ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ፖሊስ በጋራ ባደረጉት ክትትል ወንጀሉን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 5 ሴቶች እና 2 ወንዶች ሳሪስ አቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ ከተሽከርካሪው ወርደው ሊሰወሩ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በወቅቱ በተሽከርካሪው ላይ በተደረገ ፍተሻ ከተለያዩ ግለሰቦች ላይ በተመሳሳይ መልኩ የተሰረቁ ዘጠኝ ሞባይል ስልኮች የተያዙ ሲሆን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ በተጠርጣሪዎቹ ላይ የጀመረውን የምርመራ ስራ አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ በተጠቀሰው ተሽከርካሪ እና በተያዙት ተጠርጣሪዎች ተመሳሳይ ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚል ግለሰብ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመቅረብ ከተያዙት ስልኮች መካከል የእሱ ንብረት ስለመኖሩ በማረጋገጥ እንዲወስድ እና ለፖሊስ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል፡፡

መሰል የወንጀል አፈፃፀሞችን ለመከላከል በየጊዜው የሚገለፁ የጥንቃቄ መልዕክቶችን ተግባራዊ በማድረግ በከተማችን ሊፈፀሙ የሚችሉ ወንጀሎችን አስቀድሞ መከላከል እና መቆጣጠር እንደሚቻል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውሶ አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥም ህብረተሰቡ ለፖሊስ መረጃ በመስጠት ተባባሪነቱን ማጠናከር እንደሚጠበቅበት ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
*

Via AAP

ጥጋብ እና ስረአት አልበኝነት በሻሸመኔ ከተማ ጎዳናዎች ላይ !🤔🤔 #ሻሸመኔ
12/11/2025

ጥጋብ እና ስረአት አልበኝነት በሻሸመኔ ከተማ ጎዳናዎች ላይ !🤔🤔

#ሻሸመኔ

11/11/2025


#አዶናይ

11/11/2025

አዶናይ የ ሾው ላይ መቅረብ የማይፈልግበትን ምክንያት በዚህ መልኩ አብራርቷል!👂👂

በደንብ አድምጡ እና በጨዋነት የራሳችሁን አስታያየት ስጡበት ።

የመስከረም ወር ተፅዕኖ ፈጣሪ አዶናይ በሰይፉ ሾው ላይ ላለመቅረብ ወሰነ! የመስከረም ወር የሶሻል ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ አሸናፊ የሆነው አዶናይ፣ በታዋቂው 'ሰይፉ ሾው' ላይ እንዲቀርብ የቀረበ...
11/11/2025

የመስከረም ወር ተፅዕኖ ፈጣሪ አዶናይ በሰይፉ ሾው ላይ ላለመቅረብ ወሰነ!

የመስከረም ወር የሶሻል ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ አሸናፊ የሆነው አዶናይ፣ በታዋቂው 'ሰይፉ ሾው' ላይ እንዲቀርብ የቀረበለትን ግብዣ እንደማይቀበል አስታወቀ።

አዶናይ ይህን ውሳኔ ያሳለፈበትን ምክንያት ሲገልጽ፣ የዝግጅቱ አዘጋጅ ሰይፉ ፋንታሁን በአሽሙር እንደተናገረው ተሰምቶኛል ብሏል።

ሰይፉ በዝግጅቱ ላይ፣ አዶናይ ሾው ላይ መቅረብ ከፈለገ "ይህ ሾው ለሁሉም ክፍት ስለሆነ" መቅረብ እንደሚችል በመግለጽ የጋበዘው ሲሆን፣ ንግግሩን ሲያጠቃልልም "ዶናይ" የሚል ቃል ተጠቅሟል።

አዶናይ ይህን "ዶናይ" የሚል አጠራር እንደ አሽሙር እና እንደ “ቅኔ” ነው ወስዶታል።

በብዝ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ሰይፉ የተጠቀመው ቃል 'ዶናይ' ወይም 'ዶናዬ' የሚለው ከአዶናይ ቀደም ሲል ሰዎችን ለማስተማር ሲጠቀምባቸው ከነበሩት ቃላት መጨረሻ ላይ ካለችው 'ዬ' ከምትለው ፊደል ጋር ተመሳሳይነት ስላለው እንደ አሽሙር ተወስዷል።

አዶናይ በመጨረሻ ምላሹን ሲሰጥ፣

ሾው ላይ መቅረብ እንደማይፈልግ በማያሻማ ሁኔታ ገልጿል። ለዚህም ምክንያቶች ሲዘረዝር፦

* በአካል አግኝቼው ነበር፣ በክብር አላወራኝም" ብሏል።

* የምርጫ ቅስቀሳ እያስፈለገኝም" በማለት፣ ሾው ላይ መቅረብ ሽንፈቴን ወይም ድሌን አይለውጠውም የሚል አቋም አንጸባርቋል።

ሰይፉንም እንዲሚያከብረው እና እሱን እያየ እንዳደገም ገልፇል::

በዚህ ጉዳይ ላይ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?

* የሰይፉን አጠራር እንደ አሽሙር ትመለከቱታላችሁ?
* አዶናይ የሰጠውን ምላሽ ትደግፋላችሁ?

አስተያየታችሁ አካፍሉ ?

🙏🙏🙏

Via Gursha

ዳዊት ድሪምስ ፤ እንኳን ደስ ያለህ !! 💍❤️ Dawit Dreams " የኔ ህልም 1 ብርን ከ 1 ዶላር እኩል ማድረግ ነው " በሚለው ድንቅ መፈክሩ ይታወቃል ። Dawit Dreams ባለፍት ...
10/11/2025

ዳዊት ድሪምስ ፤ እንኳን ደስ ያለህ !! 💍❤️

Dawit Dreams " የኔ ህልም 1 ብርን ከ 1 ዶላር እኩል ማድረግ ነው " በሚለው ድንቅ መፈክሩ ይታወቃል ። Dawit Dreams ባለፍት ዓመታት ከግል እስከ መንግስት ተቋማት አነቃቅቷል ።

ከታዋቂ እስከ አዋቂ ግለሰቦች ተነቃቅተዋል ፤ በርካቶችንም በእርሱ የተስፋ እንጀራን ተመግበዋል። ሕይወታቸውን መቀየር እንደቻሉ ምስክርነት ሲሰጡ ተመልክተናል ።

ታዋቂ እና አነቃቂው ዳዊት ድሪምስ ትናንት በጋብቻ የተቀደሰውን የፍቅር ቃልኪዳን ፈፅሟል ። እኛም "ሰው ብቻውን ይኖር ዘንድ መልካም አይደለም " እና ለሙሽራው Dawit Dreams እና ለሚወዳት ባለቤቱ መልካም ጋብቻ እንመኛለን!!❤️🙏❤️

ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ   ሕዳር 1፣ 2018  በተቀናጀ መንገድ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ የተደረሰባቸ...
10/11/2025

ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ

ሕዳር 1፣ 2018 በተቀናጀ መንገድ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ ፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለፋና ዲጂታል እንደገለጸው ÷ መንግሥት ተግባራዊ ያደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በመጻረር በተደራጀ መንገድ በሚፈጽሙ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮች ዙሪያ በተቀናጀ መልኩ ምስጢራዊ የመረጃ ስምሪት ሲከናወን ቆይቷል፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የክልል የፀጥታ አካላትና በሕብረተሰቡ ጥቆማ በተደረገ የተቀናጀ ሥምሪት በፋይናንስ አሻጥር የተሰማሩ 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገልጿል፡፡

ከሕገ ወጥ ተግባሩ ጋር ትስስር የነበራቸው 519 የባንክ አካውንቶች የታገዱ ሲሆን ÷ የተለያዩ ኤግዚቢቶች መያዛቸውም ተጠቅሷል፡፡

ሕገ ወጥ ሃዋላዎች ፣ የገንዘብ ዝውውሮች፣ የውጭ ምንዛሪ ስወራዎች ፣ የግብር ስወራዎች፣ ሕገ ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ የማስመሰልና ሌሎች ተመሳሳይ ወንጀሎች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ እንዲሁም አሸባሪዎችንና የታጠቁ ቡድኖችን ለመደገፍ ሲውሉ መቆየታቸውን መግለጫው አመልክቷል፡፡

በተለይም ሕገ ወጥ በሆኑ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች፣ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎች፣ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያዎች፣ ሕገ ወጥ የሃዋላ አዘዋዋሪዎችና ደላላዎች፣ በወጪና ገቢ ንግድ ላይ አሻጥር የፈፀሙ አስመጪዎችና ላኪዎች እንዲሁም ሕጋዊ ንግድ ሳይኖራቸው በሕገ ወጥ ሃዋላ ላይ በመሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ በማንቀሳቀስ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ባደረሱ አካላት የማያዳግም ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱ ተጠቁሟል፡፡

በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሚልኩት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የብሔራዊ ባንክን መመሪያ በሚጥስ ሁኔታ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ የቆዩ ሕጋዊ ፈቃዳቸው በፈጸሙት ተደጋጋሚ ጥፋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰረዘባቸው ዓለም አቀፍ የሃዋላ አስተላላፊዎችና ሕገ ወጥ የሃዋላ ድርጅቶችም ርምጃው የተወሰደባቸው ናቸው።

በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ሀብትን ከሀገር በማሸሽ ላይ ያሉ ድርጅቶች ባለቤቶችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

የብሔራዊ ባንክ ሕግን በሚጥስ ሁኔታና ያለምንም ፈቃድ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይም ርምጃ ተወስዷል፡፡

በሀገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም ላይ በማነጣጠር ሲፈጸም የነበረው ኢኮኖሚያዊ አሻጥር ትላልቅ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ለማስተጓጎል፣ ሕዝብ በመንግሥት ላይ ቅሬታ እንዲያድርበት እንዲሁም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እንዳያንሰራራ በተቀናጀ መንገድ ሲፈጽሙት እንደነበረ ነው የተገለጸው፡፡

የሀገርን ደኅንነት ስጋት ላይ በሚጥሉ እና የሀገርን ኢኮኖሚ በሚጎዱ አሻጥሮች ላይ ተሳታፊ የሆኑ አካላትን በመከታተል የማያዳግም ርምጃ ለመውሰድ የተጀመረው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡

መላው ሀገር ወዳድ ዜጋ መሰል ወንጀሎችንና ወንጀለኞችን በማጋለጥ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርቧል፡፡

FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)

በዛሬው እለት ህዳር 1/2018 ዓ.ም በአፋር ክልል አብዓላና ዙሪያዋ የሚኖሩ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።ሰላማዊ ሰልፉን አስመልክቶ ከክልሉ ኮሚኒኬሽን ባገኘነው መረጃ ነዋሪዎቹ በህወሓ...
10/11/2025

በዛሬው እለት ህዳር 1/2018 ዓ.ም በአፋር ክልል አብዓላና ዙሪያዋ የሚኖሩ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።

ሰላማዊ ሰልፉን አስመልክቶ ከክልሉ ኮሚኒኬሽን ባገኘነው መረጃ ነዋሪዎቹ በህወሓትና በሻዕብያ “ ትብብር “ በአከባቢያቸው ተቃጥቷል ያሉትን ጥቃት ክፉኛ አውግዘዋል።

“ ህዝቡ ወደ ቀዩ ይመለስ የትግራይ ኃይል ከያዘው የዓፋር መሬት ይውጣ “ ያሉት ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ፤ ይህን ሳይሆን ከቀረ ከዓፋር እና ከፌደራል መንግስታት ጋር ተሰልፈው መብታቸው ለማስከበር እንደሚንቀሳቀሱ ዝተዋል።

  ላሥታ ወረዳ መሽጎ በነበረው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ ተወሰዷል።       በሰሜን ወሎ ዞን ላሥታ ወረዳ መሽጎ የነበረውን ፅንፈኛ ቡድን መደምሰስ መቻሉን የሰንጥቅ ክፍለ ጦር ምክትል አዛ...
10/11/2025

ላሥታ ወረዳ መሽጎ በነበረው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ ተወሰዷል።

በሰሜን ወሎ ዞን ላሥታ ወረዳ መሽጎ የነበረውን ፅንፈኛ ቡድን መደምሰስ መቻሉን የሰንጥቅ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሻለቃ አብዲ መሀመድ ገልፀዋል።

በፅንፈኛው ቡድን ላይ ቁሳዊ እና ሰብዓዊ ኪሳራ በማድረሥ በርካታ የፅንፈኛው ቡድን ሲደመሰሥ ፅንፈኛዉ ዘርፎ ሲጠቀምበት የነበረ ተሽከርካሪ፣ ሞተር ሳይክል እና የተለያዩ ዓይነት መሣሪያዎች እንዲሁም የህክምና ቁሳቁሶች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ዘጋቢ ቢላል ገሰሰ ነው።

Via የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ 🙏

Address

Jimma City
Jimma

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gibe Daily Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gibe Daily Post:

Share