Belachew Belay - በላቸው በላይ

Belachew Belay - በላቸው በላይ Journalist
👉Follow me🌹

የኮንታ ዞን መንግስት ከቀርጫንሼ ኃ/የተ/የግል ማህበር ጋር ከ197 ሚሊዮን 528 ሺ ብር በላይ በሆነ ወጪ የመንገድ ስራ ማሽነሪ ግዢ የውል ስምምነት ተፈራረመ።    የመንገድ ስራ ማሽነሪዎች...
13/05/2024

የኮንታ ዞን መንግስት ከቀርጫንሼ ኃ/የተ/የግል ማህበር ጋር ከ197 ሚሊዮን 528 ሺ ብር በላይ በሆነ ወጪ የመንገድ ስራ ማሽነሪ ግዢ የውል ስምምነት ተፈራረመ።

የመንገድ ስራ ማሽነሪዎች ግዢ ስምምነቱን የኮንታ ዞን ፋ/ኢ/ል/መምሪያ ኃላፊ አቶ አግደው አሰፋ ከቀርጫርሼ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ም/ል ስራ አስኪያጅ ከሆኑት ከአቶ አቡበከር ይማም ጋር ተፈራርመዋል::

በፍርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ ለእንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኮንታ ዞን ም/ል አስተዳዳሪ አቶ ገዛኸኝ ገዝሙ የዞኑን ህዝብ የመንገድ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የግንባታ ማሽኔሪዎችን በራስ አቅም ገዝቶ መጠቀም ተገቢ መሆኑን በመግለፅ ለተግባሩ ስኬት ርብርብ ላደረጉ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

አያይዘውም አቅራቢው ድርጅት ማሽነሪዎችን በወቅቱ እንደሚያቀርብም እምነታቸውን ገልፀዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ ረዳት የመንግስት ተጠሪና በብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ የዘማናት የህዝብን የመልማት ጥያቄ ለመመለስ የዞኑ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመበጀት ማሽነሪ ፍላጎትን ለማሟላት ያደረገው ጥረት የሚደነቅና ለሌሎች አካባቢዎችም ምርጥ ተሞክሮ ሊሆን የሚችል መሆኑን ተናግረዋል።

የዋቻ ንጹህ መጠጥ ዉሃ ፕሮጀክት ነገ ይመረቃል  በዋቻ ከተማ አስተዳደር የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑም ታውቋል።በካፋ ዞን ዋቻ ከተማ አስተዳደር ...
13/05/2024

የዋቻ ንጹህ መጠጥ ዉሃ ፕሮጀክት ነገ ይመረቃል

በዋቻ ከተማ አስተዳደር የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑም ታውቋል።

በካፋ ዞን ዋቻ ከተማ አስተዳደር ተገንብቶ የተጠናቀቀው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከፍተኛ የፌደራልና የክልል የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነገ ተመርቆ ስራ ይጀምራል ተብሏል።

በባስኬት ፈንድ በተገኘ ብድርና ከክልል እስከ ከተማ አስተዳደሩ በተከናወነው የማቺንግ ፈንድ በጨና ወረዳ ቦባበላ ቀበሌ ላይ በተቆፈረ ጥልቅ ጉድጓድና ምንጭ በማጎልበት የተጠናቀቀው ይኸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በነገው ዕለት እንደሚመረቅ የክልሉ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው ተናግረዋል ።

“ሁሉም የእጁን ያገኛል''------------------------------አንዲት እናት ሁልጊዜም ዳቦ ስትጋግር የዳቦው ቁጥር ለቤተሰቡ ሁሉ አዳርሶ አንድ ተጨማሪ እንዲተርፍ አድርጋ ነበር። እ...
13/05/2024

“ሁሉም የእጁን ያገኛል''
------------------------------
አንዲት እናት ሁልጊዜም ዳቦ ስትጋግር የዳቦው ቁጥር ለቤተሰቡ ሁሉ አዳርሶ አንድ ተጨማሪ እንዲተርፍ አድርጋ ነበር። እናም አንዱን ትርፍ ዳቦ በቤታቸው አቅራቢያ የሚያልፍ የተራበ ሰው እንዲወስደው በሚል በዳንቴል ጠቅልላ በር ላይ ታስቀምጠዋለች። አንድ ጀርባው የጎበጠ ሰውም ዘወትር እየሄደ ዳቦውን ወስዶ ይበላ ነበር። ለብዙ ወራት ያቺ ሴት ዳቦ ማስቀመጧን፣ ሰውዬም ወስዶ መብላቱን ቀጠሉ።

የሚገርመው ነገር ያ ዳቦውን የሚወስደው ሰው አንድም ቀን ምስጋና አቅርቦላት ስለማያውቅ ሴትዬዋ ትበሳጭ ጀመር። ይባስ ብሎ ሰውዬው በማመስገን ፋንታ “ሁሉም ሰው የእጁን ያገኛል'' ማለትን ያዘወትር ነበር። ይሄን ሲል ሴትዬዋ “ምናባቱ ለማለት ፈልጎ ነው?'' እያለች መበሳጨቷ አልቀረም። “ይሄ ውለታ ቢስ፣ ማመስገን ሲገባው ጭራሽ ‹የእጇን ይስጣት› እያለ ያሟርትብኛል? ቆይ ልኩን ባላሳየው..'' እያለች ትዝት ጀመር።

በንዴት ስሜት ውስጥ ሆናም በቀጣዩ ቀን ዳቦ
ስታስቀምጥ በውስጡ መርዝ ልትነሰንስበት ትወስናለች።
እንዳይነጋ የለም ቀጣዩ ማለዳ ሲመጣ የጋገረችው
አንደኛው ዳቦ ውስጥ መርዝ አድርጋበት ልታስቀምጥ ስትል እጇ መንቀጥቀጥ ጀመረ። ራሷን እንደምንም ልታደፋፍር ብትታገልም አልቻለችም። ከዚያም “ምን ማድረጌ ነው'' እያለች ለጥቂት ደቂቃዎች ራሷን ወቀሰች።

ወዲያው ከጋገረቻቸው ዳቦዎች መካከል የራሷን ፋንታ አንስታ እንደተለመደው በዳንቴል አድርጋ በሩ ላይ አስቀመጠችው። መርዝ ተደርጎበት የነበረውን ዳቦም ማንም እንዳይደርስበት ብላ ወስዳ ሽንት ቤት ከተተችው። የዚያን እለት የገዛ ቁርሷን ለዚያ ተመጽዋች ስላስረከበት ጾሟን መዋል ግድ ሆኖባት ነበር።

እንደዚያው ባዶ ሆዷን እንዳለች ልክ ዘወትር
እንደምታደርገው ጸሎት ቤቷ ገብታ ለወንድ ልጇ ጸሎት አደረገች። ልጇ ወደ ጦር ግንባር ከዘመተ ረጅም ዘመን አስቆጥሯል። ፈጣሪ ልጇን በሕይወት ይመለስላትም ዘንድ የእናት አንጀቷ ስፍስፍ እስኪል እያለቀሰች ጸለየች። የዚያን እለት ማታ ግን ያለወትሮው የቤቱ በር ተንኳኳ።

እርሷም ግር እየተሰኘች ሄዳ ስትከፍተው ጦር ሜዳ የሄደው ልጇ በሩ ላይ ቆሟል፡፡ ስታየው በጣም ተደሰተች። እልልታዋንም አቀለጠችው። ትከሻው ላይ ተጠምጥማ ደስታ እንባ እያነባች አገላብጣ ስትስመው ቆየች። ልጇ በጣም ከስቶ ነበር። የጉንጩ አጥንት ፈጥጦ፣ ሰውነቱ መንምኖ ሲታይ ምግብ ከቀመሰ ወር ያለፈው ይመስላል። ቤት ገብቶ ራት ከተበላ በሁዋላ ስላሳለፈው ታሪክ ለእናቱ ተረከላት። በትረካውም መሀል እንዲህ አለ።

“መቸም ተዓምር ነው! ወደዚህ ከተማ በእግሬ እየመጣሁ
ሳለ መንገድ ላይ አቅም አንሶኝ ወድቄ ነበር። ቦታው ምናልባት ከዚህ ስድስትና ሰባት ኪሎ ሜትር ቢርቅ ነው። ዐቅሜን ስገምተው እዚህ ቤት የሚያደርሰኝ መስሎኝ ነበር፤ ነገር ግን ጥቂት ሲቀረኝ ርሀብ አዝለፍልፎ ጣለኝ። እናም ከጦርነት ተርፌ በርሀብ ስለመሞቴ እርግጠኛ ወደመሆን ደረጃ ስሸጋገር በድንገት አንድ አልፎ ሂያጅ ደረሰልኝ። ጀርባው ላይ ጎበጥ ያለ ደግ ሰው ዳቦ ይዞ መጥቶ ሲያበላኝ ነብሴ መለስ አለችልኝ። ታዲያ ዳቦውን ሲሰጠኝ ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ?''

እናት እንባዋ በጉንጯ ኮለል ብሎ እየፈሰሰ “ምን አለህ ልጄ? እኔ ምን አውቃለሁ አንተው ንገረኝ!'' አለች። ልጁም እንዲህ ሲል መለሰ። “‹በየቀኑ አንድ ዳቦ እየበላሁ ነው የምኖረው። አሁን እንደምታየው እጄ ላይ አንድ ዳቦ ነው ያለው። ግዴለም ለዛሬ እኔ ሳልበላ ልቅር፤ ጦሜን አድራለሁ። ከእኔ የበለጠ ይሄ ዳቦ ላንተ ያስፈልግሃል› አለና ቅንጣት ታህል ቅር ሳይለው ሰጠኝ። ይሄው እኔም በእሱ ደግነት ከሞት ዳንኩ።

የእናቴንም ዐይን ለማየት በቃሁ!'' ይሄን ሲናገር እናት እንባዋን ፍጹም መቆጣጠር አቃታት። ያ ሰው “ሁሉም የእጁን ያገኛል'' ሲል የተናገረው አሁን ገባት። ይሄኔ በንዴት ዳቦው ላይ መርዙን እንዳደረገችበት ቢሆን ኖሮ የገዛ ልጇን በመርዝ ገድላው ነበር። እሷ ጦሟን ውላ ለሰውዬው ዳቦ በማስቀመጧ ምክንያት ያስቀመጠችው ዳቦ ምንም ሳይሸረፍ ሄዶ የልጇን ሕይወት ታደገ።

አንዳንዴ ክፋት ስንሠራ በየት ዞሮ ወደ እኛ እንደሚመጣ አናውቀውም። ቀጥታ እኛን ባይነካንም በልጆቻችንና በምንወዳቸው ሰዎች በኩል ሒሳብ እንድናወራርድ ያደርገናል። በተቃራኒው ደግ ስንሠራ ለጊዜው የአዕምሮ ርካታ ብቻ የሚያስገኝልን ይመስለናል። ነገር ግን እሱም ተዟዙሮ ከብዙ አደጋ፣ ከብዙ መዓት ሊያወጣን ይችላል። ወገኔ ሐሰት እንዳይመስልህ፤ የእውነትም “ደግነት ይከፍላል'፤ ፈጽሞ እንዳትጠራጠር!!!

(መሳፍንት ተፈራ)

እናትነት በራሱ ጀግንነት ነው::  የእናቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር ከጀመረ 120 ዓመት ሊሞላው ነው::የመንግስታቱ ድርጅት በየዓመቱ በፈረንጆች ግንቦት ወር ከገባ ሁለተኛው እሁድ የ...
12/05/2024

እናትነት በራሱ ጀግንነት ነው::

የእናቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር ከጀመረ 120 ዓመት ሊሞላው ነው::

የመንግስታቱ ድርጅት በየዓመቱ በፈረንጆች ግንቦት ወር ከገባ ሁለተኛው እሁድ የእናቶች ቀን ሆኖ እንዲውል በወሰነው መሰረት እለቱ ይከበራል።

እናቶች ለዓለማችን የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ለማስታወስ በሚል ከፈረንጆቹ ከ1907 ጀምሮ በየዓመቱ በመከበር ላይ ነው።

መልካም የእናቶች ቀን!!

380 ሜትር ርዝማኔ እና 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለውና በ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በጀት  የተገባው  ዓባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ጠ/ሚ ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በይፋ ተመረቀ ...
12/05/2024

380 ሜትር ርዝማኔ እና 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለውና በ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በጀት የተገባው ዓባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ጠ/ሚ ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በይፋ ተመረቀ

በሀገሪቱ ታሪክ በዓይነቱ ልዩ የኾነው ይኽ ድልድይ 380 ሜትር ርዝማኔ እና 43 ሜትር የጎን ስፋት አለው። በአንድ ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን በግራ እና በቀኝ የማስተናገድ አቅም ያለው ከመኾኑም ባለፈ የብስክሌተኞች መተላለፊያን ጨምሮ 5 ሜትር የእግረኛ መንገድ አካትቷል።

እያንዳንዱ የድልድዩ ገመድ አቃፊ ማማዎች ቁመት 27 ሜትር ከፍታ ሲኖረው፣ ከውኃ እና ከመሬት በታች እስከ 24 ሜትር ጥልቀት ባላቸው በርካታ ፓይሎች የተዋቀረ ነው፡፡

169 ሜትር ርዝመት ያለው ነባሩ የዓባይ ወንዝ ድልድይ ከስልሳ ዓመታት በላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲኾን፣ ጠባብ እና ለከፍተኛ የትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ባለመኾኑ ነበር አዲስ ድልድይ እንዲገነባ በመንግስት የተወሰነው።

አሁን ላይ ግንባታው የተጠናቀቀው አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ የባሕር ዳር ከተማን በመሐል አቋርጦ የሚያልፍ ሲኾን፣ በተንጠልጣይ ገመዶቹ እና ምሶሶዎቹ ላይ ዘመናዊ መብራት የተገጠመለት በመኾኑ ለአካባቢው ልዩ ድምቅት ከመስጠቱም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያሳልጥ ነው።

ግንባታውን ከፌደራል መንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በጀት ዓለም አቀፉ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ (cccc) አከናውኖታል፡፡ የቱርኩ ቦቴክ እና ሀገር በቀሉ ስታዲያ ኢንጅነሪንግ የግንባታውን የቁጥጥር እና የማማከር ሥራ በጥምረት ሠርተዋል።

የድልድዩ መገንባት ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ ተጠቃሽ የቱሪስት መስህብ በመሆን አዎንታዊ ሚና ይጫወታል። ከካይሮ እስከ ኬፕታውን የሚደርሰው የትራንስ አፍሪካ አውራጎዳና ላይ ያረፈ በመኾኑም ሀገሪቱ የዚህ ሀይዌይ መስፈርትን የሚያሟሉ ከፍተኛ ክብደት ያላቸውን ተሽከርካሪዎች የሚሸከሙ አስተማማኝ ድልድዮች እንዳሏት ማሳያ ነው።

ለድልድዩ መዳረሻ በሁለት አቅጣጫ ከሄኒ ጋርደን አደባባይ እስከ ዘንዘልማ መገንጠያ ድረስ የሚዘልቀው የ4 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የባሕር ዳር ዓባይ ወንዝ ድልድይ መዳረሻ መንገድ ሀገር በቀሎቹ ሀፍኮን ከክሮስላንድ ኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር በመጣመር ግንባታውን ያከናውናሉ፡፡ የመንገድ ግንባታው ቀሪ ውስን ሥራ በቅርቡ ይጠናቀቃል።

ይኽ የመሠረተ-ልማት አውታር በከፍተኛ የሀገር መዋለ-ንዋይ የተገነባ እንደመኾኑ ሁሉም ዜጋ ሊንከባከበው እና በባለቤትነት ስሜት ሊጠብቅው እንደሚገባ ማስገንዘቡን ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መረጃ ያመለክታል።

ለትውልድ ተሻጋሪ አሻራ
12/05/2024

ለትውልድ ተሻጋሪ አሻራ

የካፋን ባህል በድንቅ ዘፈኖቹ ከፍ ካደረጉት ብርቅዬና ተወዳጅ  ዘፋኞች መሀከል አንዱ የሆነዉ ምትኩ በቀለ (ቸዉሲ ) አሁን በአዲስና ዘመናዊ ሙዚቃ ሊያዝናናን በነገዉ ዕለት በአዲስ አበባ ከተ...
11/05/2024

የካፋን ባህል በድንቅ ዘፈኖቹ ከፍ ካደረጉት ብርቅዬና ተወዳጅ ዘፋኞች መሀከል አንዱ የሆነዉ ምትኩ በቀለ (ቸዉሲ ) አሁን በአዲስና ዘመናዊ ሙዚቃ ሊያዝናናን በነገዉ ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ አዲሱን አልበም ያስመርቃል ።

ለድምፃዊ ምትኩና አድናቂዎቹ እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ እኔ በስራ መደራረብ ምክንያት በነገዉ ዕለት በምረቃዉ ፕሮግራም ላይ መገኘት ባልችልም በቅርብ ጊዜያት ቦንጋ ላይ በሚደረገዉ ፕሮግራም ይህንን የካፋ ህዝብ ባለዉለታ በድምቀት እንደምንቀበል ተስፋ አደርጋለሁ ።

የዞኑ አስተዳደር ከጎንህ መሆኑን እያረጋገጥኩ በድጋሚ ቸዉሲ እና አድናቂዎቹ በሙሉ እንኳን ደስ አለን እላለሁ ።

አቶ እንዳሻው ከበደ
የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

የምትኩ በቀለ (ቸዉሲ ) አዲሱን አልበም በተመለከተ ያስተላለፉት መልዕክት🙏🙏

የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና መርሃ ግብር ይፋ ሆነ  ከትግራይ ክልል ውጭ በሁሉም ክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ላሉ ተፈታኞች በወረቀትና በበይነ መረብ ...
11/05/2024

የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና መርሃ ግብር ይፋ ሆነ

ከትግራይ ክልል ውጭ በሁሉም ክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ላሉ ተፈታኞች በወረቀትና በበይነ መረብ የሚሰጠው የፈተና መርሃ ግብር----

ከ 1 መቶ 22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው ባለ 5 ወለል  የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህንጻ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተጣለ  ከ 1 መቶ 22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የ...
11/05/2024

ከ 1 መቶ 22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው ባለ 5 ወለል የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህንጻ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተጣለ

ከ 1 መቶ 22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው ባለ 5 ወለል የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህንጻ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ በላይ ተሰማ፣ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፣ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ከበደን ጨምሮ ሌሎች በተገኙበት ተጥሏል።

በ7 መቶ 20 ቀናት የሚጠናቀቀውን ይህን ግንባታ የወንድሙ ወ/ሚካኤል ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ እንደምሰራ ተገልጿል።

በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአረጋዊያን  የተገነባው  የመኖሪያ ማዕከል ተመረቀ  በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከ 21 ሚሊየን  ብር በላይ ወጪ ወጥቶበት  በአጭር ጊዜ የተገነባው የአረጋዊያን መኖሪያ ማዕከል  ...
11/05/2024

በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአረጋዊያን የተገነባው የመኖሪያ ማዕከል ተመረቀ

በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከ 21 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ወጥቶበት በአጭር ጊዜ የተገነባው የአረጋዊያን መኖሪያ ማዕከል ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ በቅቷል።

በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ጴጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ ይህ የአረጋዊያን መኖሪያ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ ለምረቃ በመብቃቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው ግንባታው ለምረቃ እንድበቃ ከውስጥና ከውጪ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ልባዊ ምስጋና አቅርቧል።

ለግንባታው መሳካት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሚና ለተጫወቱት አካላት የምስክር ወረቀትና ዕውቅና ተበርክቶላቸዋል።

በምረቃው ስነ - ስርዓቱ ላይ ከፌዴራል ፣ ከክልል፣ ከዞንና ከወረዳ የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ መሆናቸዉን የካፋ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።

አትሌት ታደሰ ወርቁን ያፈራ ያልተዘመረለት ጀግና   በቦንጋ ከተማ የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ የችቦ ማብራት ፕሮግራም ከመካሄዱ በፊት በተደረገው የሩጫ ውድድር የተሳተፈው የ74 ዓመቱ  መለሰ ወ...
11/05/2024

አትሌት ታደሰ ወርቁን ያፈራ ያልተዘመረለት ጀግና

በቦንጋ ከተማ የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ የችቦ ማብራት ፕሮግራም ከመካሄዱ በፊት በተደረገው የሩጫ ውድድር የተሳተፈው የ74 ዓመቱ መለሰ ወልዴ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።

መለስ ወልዴ የጠሎ ወረዳ ኦዳ አትሌቲክስ ፕሮጀክት አሰልጣኝ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ከመንግሥት ስራ በጡረታ ቢገለልም በዘርፉ እያገለገለ ይገኛል፡፡

በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የሩጫ ውድድር አጠናቆ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል፡፡

መለሰ ወልዴ አትሌት ታደሰ ወርቁንና ሞሳድ ጌታቸውን ያፈራ አንጋፋ አሰልጣኝ ነዉ::

ልዩ ተሸላሚ በመሆኑ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማውና ይብልጥ ጠንክሮ ለመስራት እንዳነሳሳዉ ተናግሯል።(Fm 97.4)

Address

Bonga Kaffa
Jimma
WORLD

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Belachew Belay - በላቸው በላይ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share