ABU AMMAR TEMAM

ABU AMMAR TEMAM Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ABU AMMAR TEMAM, Digital creator, JIMMA, Jimma.

29/04/2026
በሆርሙዝ ወሽመጥ የኢራን ጀልባዎች በጭነት መርከቦች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው ተገለጠየብሪታንያ የባህር ላይ ደህንነት ተቆጣጣሪ (UKMTO) ረቡዕ ዕለት እንደገለጸው፤ የኢራን የጦር ጀልባዎች በ...
22/04/2026

በሆርሙዝ ወሽመጥ የኢራን ጀልባዎች በጭነት መርከቦች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው ተገለጠ

የብሪታንያ የባህር ላይ ደህንነት ተቆጣጣሪ (UKMTO) ረቡዕ ዕለት እንደገለጸው፤ የኢራን የጦር ጀልባዎች በሆርሙዝ ወሽመጥ ውስጥ ቢያንስ በአንድ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል።

UKMTO እንዳለው፤ አንድ የጭነት መርከብ ከኦማን በስተሰሜን ምስራቅ 15 የባህር ማይል ርቀት ላይ፣ ወደ ወሽመጡ መግቢያ አካባቢ፣ በኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) ጀልባ ጥቃት እንደተሰነዘረበት ሪፖርት አድርጓል። በጥቃቱ በመርከቡ መሪ ክፍል (bridge) ላይ ጉዳት የደረሰ ቢሆንም፣ የሰው ሕይወት ግን አልጠፋም።

የኢራን የዜና ወኪል "ታስኒም" በበኩሉ፤ መርከቡ ስልታዊ የውሃ መስመሩን በከበቡት የኢራን የታጠቁ ኃይሎች የተሰጠውን "ማስጠንቀቂያ ችላ ብሏል" ብሏል። ሆኖም "ቫንጋርድ ቴክ" የተሰኘው የብሪታንያ የደህንነት ተቋም መርከቡ የላይቤሪያ ባንዲራ የለበሰ መሆኑንና "በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ለማለፍ ፈቃድ እንዳለው ተነግሮት ነበር" ሲል መረጃውን አስተባብሏል።

በተጨማሪም ከኢራን ዳርቻ ስምንት የባህር ማይል ርቀት ላይ ሌላ የጭነት መርከብ ጥቃት ደርሶበት በባህር ላይ እንዲቆም መደረጉን UKMTO ገልጿል። "ቫንጋርድ" ይህ መርከብ የፓናማ ባንዲራ የለበሰችው "ኢውፎሪያ" (Euphoria) የተሰኘች የጭነት መርከብ መሆኗንና ከሆርሙዝ ወሽመጥ ወጥታ እየተጓዘች እንደነበር አረጋግጧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ የባህር ኃይል ክፍሎች የሆርሙዝ ወሽመጥን ለማለፍ የሞከሩ ሁለት መርከቦችን አስቁመው ወደ ኢራን ግዛት የውሃ ክልል እንዲገቡ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።

#ኢራን #ወደአማርኛ

የአሜሪካ የኑክሌር ሰርጓጅ መርከብ ጠፋ! በፋርስ ባህረ ሰላጤ (Persian Gulf) 3.4 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የአሜሪካ ሰርጓጅ መርከብ መውደሙ ተነገረ። መረጃው እንደሚያመለክተው፤ ሚያዝ...
22/04/2026

የአሜሪካ የኑክሌር ሰርጓጅ መርከብ ጠፋ!

በፋርስ ባህረ ሰላጤ (Persian Gulf) 3.4 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የአሜሪካ ሰርጓጅ መርከብ መውደሙ ተነገረ።

መረጃው እንደሚያመለክተው፤ ሚያዝያ 17 (April 17) ኢራን አንድ የአሜሪካ የኑክሌር ሰርጓጅ መርከብን በፋርስ ባህረ ሰላጤ ውስጥ በተሳካ ሁኔታ አጥቅታ አጥቅታ ሰጥማለች።

ከዚህ ክስተት 24 ሰዓታት አስቀድሞ "ቨርጂኒያ ክላስ" (Virginia-class) የተሰኘ የአሜሪካ ባህር ኃይል ሰርጓጅ መርከብ በባህር ላይ መጥፋቱ ተገልጿል።

ይህ አስከፊ አደጋ በሚከሰትበት ወቅት 140 ገደማ አሜሪካውያን መርከበኞች በመርከቧ ውስጥ እንደነበሩ ይገመታል።

ፔንታገን (የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር) ለሙሉ ቀን ዝምታን መርጧል። ምንም ዓይነት ጋዜጣዊ መግለጫም ሆነ ማብራሪያ አልተሰጠም።

የ140ዎቹ መርከበኞች እጣ ፈንታ እስካሁን አልታወቀም። በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገነባውና 3.4 ቢሊዮን ዶላር የወጣበት ሰርጓጅ መርከብ ወድሞ፣ አደገኛ ከሆነው የኑክሌር ሬአክተሩ ጋር በፋርስ ባህረ ሰላጤ ግርጌ ይገኛል።

ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ወዲያውኑ የአስቸኳይ ጊዜ ቡድን ልኳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የአሜሪካ ባህር ኃይል ሁሉንም ሰርጓጅ መርከቦቹን ከፋርስ ባህረ ሰላጤ በፍጥነት ያስወጣ ሲሆን፤ ይህም የዛቻውን አሳሳቢነት ያሳያል ተብሏል።

ኢራን ይህንን ሰርጓጅ መርከብ ለማውደም የተራቀቀ የሩሲያ ቴክኖሎጂን እንደተጠቀመች ተጠቅሷል።

News Media — ከመረጃ ባሻገር!

15/04/2026

ፍትህ ለአክሱም ሙስሊሞች‼
#ፍትህ #ትግራይ #አክሱም #ተጋሩ ゚viralシalシ

የአክሱም ሙስሊሞች ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር ተጠየቀ!በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ከተማ ታላቅ የዳዕዋ እና የቁርዐን ሂፍዝ ተማሪዎች ምርቃት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት የተከ...
13/04/2026

የአክሱም ሙስሊሞች ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር ተጠየቀ!

በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ከተማ
ታላቅ የዳዕዋ እና የቁርዐን ሂፍዝ ተማሪዎች ምርቃት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት የተከበሩ አሊሞችና የመጅሊስ አመራሮች፣ ታዋቂ ዱዐቶች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና የክብር እንግዶች በተገኙበት በሺዎች በሚቆጠሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ደምቆ ውበ በሆነ መልኩ ተከናውኗል።

የምዕራብ ወለጋ ዞን ሙስሊም ማህበረሰብ በነቂስ በመውጣት የክብር እንግዳው የሆኑትን የዲን መምህሮቹን ልዩ በሆነ ክብርና ሞገሰ አጅቦ የተቀበለ ሲሆን፤ መርሀ ግብሩ በቁርዐን የተዋበ፣ የአንድነት ፋናው የጎላ፣ በአክሱም ለሚገኙ ሙስሊም ወገኖቹ የአጋርነት መልዕክት የተሰተጋባበት መድረክ እንዲሆን አድርጓል።

በዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ የቁርዐን ወዳጆች በተገኙበት በዚህ መድረክ ከ1400 አመታት በፊት የእምነት ነፃነታቸው በአምባገነኖች በመገፈፉ ምክኒያት ፍትህን ፍለጋ ለተሰደዱ ከለላ በሆነው ፍትሀዊ መሪ ስትመራ በነበረችው አክሱም ዛሬ የህዝባቸውን ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ የሆነውን የእምነት ነፃነት የሚጋፉ በዳዬችን በማውገዝ ለወገኖቻችን የአጋርነት ድምፅ መሆን ተችሏል።

በመድረኩም ሀገራችን ብዘሀ ሀይማኖት እንደመሆኗ ሰብዐዊና ህጋዊ የሆኑ የሀይማኖት ነፃነቶችን ማክበር የጋራ ሰላማችንን የምናሰጠብቅበት ብቸኛ አማራጭ መሆኑ ተገልጿል። የአክሱም ሙስሊሞች ዘመናት የተሻገረ ጥያቄ ምላሽ ተነፍጎ ባለበት ተጨባጭም መሰል ጥቃቶችን መደረብ አብሮነትን የሚያቃቅርና ለዘላቂ ሰላም እንቅፋት የሚሆን ትንኮሳ ነው። የዜጎችን ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ መብት ማክበር የአብሮነት እሴት ሲሆን በአንድ ሀገርና በአንድ አካባቢ ለሚኖሩ ዜጎች ደግሞ የማህበራዊ ትስስራቸው መሰረት ነው።

በዚህ አጋጣሚ በአክሱም አካባቢ ሙስሊሞች ላይ የሚፈፀሙ የተለያየ መልክ ያላቸው ጥቃቶች በህግም፣ በሀይማኖትም ሆነ በሞራል ውግዝ የሆኑ ተግባራት መሆናቸው አፅንዖት ሊሰጠው ይገባል። እነዚህን ውግዝ ተግባራት ለማሰቆም የአካባቢው አሰተዳደሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ሁሉም በየፊናው ከማህበረሰቡ ጎን በመቆም ሀላፊነቱን ይወጣ ዘንድ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዝዳንት ኡስታዝ ሀይደር ኸድር ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ረመዳን ሙባረክ! Ramadaan Mybaarak! 🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙እንኳን ለ1447ኛ ዓመተ ሂጅራ የረመዳን ወር በሰላም አደረሳችሁ!አላህ፥ ወሩን የኢባዳ፥የመረዳዳት እና ተቅዋ የምንጎናጸፍበ...
17/02/2026

ረመዳን ሙባረክ! Ramadaan Mybaarak!
🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙🌙

እንኳን ለ1447ኛ ዓመተ ሂጅራ የረመዳን ወር በሰላም አደረሳችሁ!

አላህ፥ ወሩን የኢባዳ፥የመረዳዳት እና ተቅዋ የምንጎናጸፍበት የለውጥ ወር ያድርግልን።
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥

Baga baatii Ramadaanaa bara hijraa 1447tiin isin gahe!

Rabbiin ji'a jijjiramaa, ji'a ibaadaa, wal galgargaarsaa, fi kan taqwaa itti argannu nuuf ha godhu.

Address

JIMMA
Jimma

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ABU AMMAR TEMAM posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share