29/06/2025
በአማራ ክልል ሰላምን የሚደግፉ ህዝባዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ደሴ እና ደብረ ብርሃንን ጨምሮ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች መንግስት እየወሰደ ያለውን የህግ ማስከበር ርምጃ የሚደግፉ ህዝባዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው፡፡
በድጋፍ ሰልፉ ላይ ሰላምን እንፈልጋለን፣ መንግስት በተደጋጋሚ የሚያቀርበውን የሰላም ጥሪ እንዲሁም የህግ ማስከበር ርምጃ እንደግፋለን የሚሉ መልዕክቶች ተስተጋብተዋል፡፡
ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ ከተደረገባቸው አካባቢዎች መካከል የደቡብ ወሎ ዞን መቀመጫ የሆነችውን ደሴ ከተማን ጨምሮ ኮምቦልቻ እና ሀርቡ ይጠቀሳሉ፡፡
በተመሳሳይ በክልሉ የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው ደብረ ብርሃን ከተማ ህዝባዊ ሰልፍ የተደረገ ሲሆን የከተማዋ ነዋሪዎች የሰላም መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡
በከድር መሐመድ፣ ሰብለ አክሊሉ፣ ስንታየሁ አራጌ እና አላዩ ገረመው
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/ በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!