ወሎ ሚዲያ ኔትወርክ- Wollo Media Netwerk

ወሎ ሚዲያ ኔትወርክ- Wollo Media Netwerk በዚህ ፔጅ ሀገራዊ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮ?

አዲስ ተመራጩ የኬንያ ፕሬዚዳንት ለበዓለ ሲመታቸዉ ኢትዮጵያን ጋበዙአዲስ ተመራጩ የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የፊታችን ማክሰኞ መዲና ናይሮቢ ላይ በሚካሄደዉ በዓለ ሲመት ላይ የኬንያ 5ኛው...
08/09/2022

አዲስ ተመራጩ የኬንያ ፕሬዚዳንት ለበዓለ ሲመታቸዉ ኢትዮጵያን ጋበዙ

አዲስ ተመራጩ የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የፊታችን ማክሰኞ መዲና ናይሮቢ ላይ በሚካሄደዉ በዓለ ሲመት ላይ የኬንያ 5ኛው ፕሬዝዳንት በመሆን መንበረ ሥልጣኑን ከፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ይረከባሉ።
ዊሊያም ሩቶ ማክሰኞ መስከረም 3 ቀን 2015 ዓ.ም በሚካሄደዉ በዓለ ሲመ ት ላይ ከ40 በላይ የሃገራት መንግሥታት እና የመንግሥታት ተጠሪዎችን መጋበዛቸዉን የኬንያዉ ዴሊኔሽን ዘግቧል። በሥነ-ስርዓቱ ላይ እንዲገኙ ከተጋበዙት መካከል፤ የኢትዮጵያ፤ ግብጽ፤ ዩጋንዳ፤ ናይጀሪያ፤ ጋና እና፤ የደቡብ አፍሪቃ መሪዎች ይገኙበታል።

ከዚህ በተጨማሪም የአውሮጳ ህብረት፣ የአፍሪቃ ህብረት እና መንግሥታዊ የልማት ጉዳይ ባለሥልጣናት ተወካዮች በሥነ-ስርዓቱ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ወቅታዊ ሀገሪዊ እና አለማቀፋዊ መረጃዎችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
👇👇
Telegram channel :-https://t.me/wollomedianet

በ2022 የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና   ለአሸናፊዎች የሚከፈለው ክፍያ ስንት ነው?   የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና   ሪከርድ  የሰበረ ተወዳዳሪ   ሪከርድ ለሰበረበት ብቻ  የውድድሩ ስፖንሰ...
17/07/2022

በ2022 የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለአሸናፊዎች የሚከፈለው ክፍያ ስንት ነው?

የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሪከርድ የሰበረ ተወዳዳሪ ሪከርድ ለሰበረበት ብቻ የውድድሩ ስፖንሰር የጃፓኑ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃ አምራቹ TDK 100 ሺ ዶላር የሚከፍል ሲሆን ከአንድ እስከ ስምንት የሚወጡ የፍፃሜ ተወዳዳሪዎች የሚከተለውን የገንዘብ ሽልማት ያገኛሉ;

ወርቅ: 70,000 የአሜሪካ ዶላር
ብር፡ 35,000 ዶላር
ነሐስ: 22,000 ዶላር
አራተኛው : 16,000 ዶላር
አምስተኛ : 11,000 ዶላር
ስድስተኛ : 7,000 ዶላር
ሰባተኛ : 6,000 ዶላር
ስምንተኛ : 5,000 ዶላር
ከ192 ሀገራት የተውጣጡ 1,900 አትሌቶች በ2022 የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዩጂን ኦሪገን እየተወዳደሩ ይገኛሉ።
ወድድሩ ከትናንት ወዲያ የተጀመረ ሲሆን በአጠቃላይ ለዘጠኝ ቀን ይቆያል።

ቴሌግራም ቻናል :-https://t.me/wollomedianet

ፎቶ ፦ አትሌታችን ታምራት ቶላ 2:05:35 በሆነ ሰዓት በመግባት ለሀገሩ ወርቅ ከማስገኘት በተጨማሪ የሻምፒየንስ ሺፑን ሪከርድ የግሉ አድርጓል ።ታምራት ቶላ በድምሩ 170,000 ዶላር በሽል...
17/07/2022

ፎቶ ፦ አትሌታችን ታምራት ቶላ 2:05:35 በሆነ ሰዓት በመግባት ለሀገሩ ወርቅ ከማስገኘት በተጨማሪ የሻምፒየንስ ሺፑን ሪከርድ የግሉ አድርጓል ።

ታምራት ቶላ በድምሩ 170,000 ዶላር በሽልማት መልክ የሚበረከትለት ይሆናል ።

ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው አትሌታችን ሞስነት ገረመው 35,000 ዶላር ያገኛል።

ሻምፒየን ሺፕ ሪከርድ :- 100,000 ዶላር
1ኛ ደረጃ :- 70,000 ዶላር

ቴሌግራም:-https://t.me/wollomedianet

ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/Banteamla/

እንኳን ደስ አለሽ ሀገሬ 🇪🇹❤️ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹በማራቶን ወርቁ ተደግሟል! 🥇 ታምራት ቶላ ወርቅ !!!🥈ሞስነት ገረመው  🥇በማራቶን ታምራት ቶላ አሁን ለኢትዮጵያ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝ...
17/07/2022

እንኳን ደስ አለሽ ሀገሬ 🇪🇹❤️ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በማራቶን ወርቁ ተደግሟል!

🥇 ታምራት ቶላ ወርቅ !!!

🥈ሞስነት ገረመው

🥇በማራቶን ታምራት ቶላ አሁን ለኢትዮጵያ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል።

እንኳን ደስ አለን 🇪🇹❤️ !!

ቴሌግራም ቻናል :-https://t.me/wollomedianet

የ“አል አይን ኒውስ” የኢትዮጵያ ዘጋቢ   በፀጥታ ኃይሎች  እንደተወሰደ ተነገረየተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መገናኛ ብዙሃን ለሆነው “አል አይን ኒውስ” በዘጋቢነት የሚሰራው ጋዜጠኛ አልዓዛር ተ...
14/07/2022

የ“አል አይን ኒውስ” የኢትዮጵያ ዘጋቢ በፀጥታ ኃይሎች እንደተወሰደ ተነገረ

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መገናኛ ብዙሃን ለሆነው “አል አይን ኒውስ” በዘጋቢነት የሚሰራው ጋዜጠኛ አልዓዛር ተረፈ ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 7 ከሰዓት በጸጥታ ኃይሎች መያዙን ባለቤቱ እና ባልደረባው ገለጹ። ጋዜጠኛው በጸጥታ አካላት ከተያዘ በኋላ በአዲስ አበባ ላምበረት አካባቢ ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ተናግሯል።

አልዓዛርን በታሰረበት ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ የጎበኘው ባልደረባው ዳዊት በጋሻው፤ ጋዜጠኛው የተያዘው ላምበረት መናኸሪያ አካባቢ ከሚገኝ ካፌ እንደሆነ ገልጿል። የሲቪል ልብስ የለበሱ ሁለት ግለሰቦች ጋዜጠኛውን መታወቂያ እንዲያሳያቸው እንደጠየቁት እና “እንፈልግሃለን” ብለው እንደወሰዱት የዓይን እማኞች ነግረውኛል ብሏል።

ሁለቱ ግለሰቦች አልዓዛርን በያዙበት ወቅት “ለችግኝ ተከላ ጥሩ አመለካከት የለህም፤ ‘ቤተ መንግስት ገብተን፤ በደም የበቀለውን ችግኝ እንነቅላለን’ ብለሃል” በሚል ሲወነጅሉት መሰማታቸውን ጋዜጠኛ ዳዊት ተናግሯል።

Ethiopian Insider

ቴሌግራም ቻናል :-https://t.me/wollomedianet

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብፅ ላይ ያስመዘገበውን ጣፋጭ ድል ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ ባስተላለፉት መልዕክት " ይህ ከእግር ኳስ በላይ ብዙ ትርጉም...
09/06/2022

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብፅ ላይ ያስመዘገበውን ጣፋጭ ድል ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ ባስተላለፉት መልዕክት " ይህ ከእግር ኳስ በላይ ብዙ ትርጉም ያለውን ጨዋታ በድል በማጠናቀቃችሁ ኩራት ተሰምቶናል። ከስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጋር በአስቸኳይ ተነጋግረን ለዛሬው ድል እና ባለፈው ጨዋታ ላደረጋችሁት ሁሉ 2 ሚልየን ብር ሽልማት ለቡድኑ አባላት እናበረክታለን። " ብለዋል።

ቴሌግራም ቻናልላችንን ቤተሰብ ይሁኑ :-https://t.me/joinchat/5_a59ayWYPw0OWQ0

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) በአስደደማሚ ብቃት ግብጽን 2 ለ0 አሸነፈለአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ የምድብ ግጥሚያውን ሐሙስ፤ ሰኔ 2 ቀን፣ 2014 ዓም ማላዊ ቢንጉ ብሔራዊ ስታዲ...
09/06/2022

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) በአስደደማሚ ብቃት ግብጽን 2 ለ0 አሸነፈ

ለአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ የምድብ ግጥሚያውን ሐሙስ፤ ሰኔ 2 ቀን፣ 2014 ዓም ማላዊ ቢንጉ ብሔራዊ ስታዲየም ውስጥ ያካኼደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የግብጽ አቻውን አሸነፈ።

ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ግብ በ21ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ዳዋ ሆቴሳ ነው። ሁለተኛውን ግብ ደግሞ በ40ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ያሳረፈው ሽመልስ በቀለ ነው። ሁለቱም ግቦች የኢትዮጵያ አጥቂዎች ድንቅ ብቃት የታየበት ነው። አሁን ባለው ውጤት መሰረት ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር በነጥብ እኩል ኾና በግብ ክፍያ ግን ትበልጣለች። ያም በመሆኑ የሁለተኛ ደረጃን ይዛለች። የመጀመሪያው አጋማሽ ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማግኘት የነበረውን የፍጹም ቅጣት ምት ሳይሰጠው ቀርቷል።

ሰሞኑን ባቀረብነው ጽሑፍ በርካቶች የግብጽ ቡድን በሰፋ የግብ ልዩነት ያሸንፋል ሲሉ ገምተው ነበር። ውጤቱም ኾነ የጨዋታው ብልጫ ግን የተገላቢጦሽ ኾኗል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) ባለፈው በዛሬው ጨዋታ የግብጽን ቡድን በሚገባ በልጠው ታይተዋል።

እሁድ በተከናወነው የመጀመሪያው የአፍሪቃ ዋንጫ የማጣሪያ ግጥሚያ የኢትዮጵያ ቡድን በማላዊ ቡድን የ2 ለ1 ሽንፈት አስተናግዶ ነበር። የዛሬው ድሉ በዋሊያዎቹ ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥሯል።
በሌላ ግጥሚያ ተመሳሳይ ምድብ ውስጥ የሚገኙት ማላዊ እና ጊኒ ያለምንም ግብ ተለያይተዋል። በስታዲየሙ የተገኙ የማላዊ ደጋፊዎች ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ድጋፋቸው ሲገልጡ ታይተዋል። ፎቶ፦ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

[DW]
ቴሌግራም ቻናልላችንን ቤተሰብ ይሁኑ :-https://t.me/joinchat/5_a59ayWYPw0OWQ0

09/06/2022

የወልቃት የበጀት ጉዳይን መንግስት ያለውን አቋም ለትግራይ ክልል በማድረግ ታማኝነቱን አረጋግጧል

ላካዜት የቀድሞ ክለቡን ተቀላቀለ፡፡ የአርሰናሉ አጥቂ አሌክሳንደር ላካዜት በነጻ ዝውውር የቀድሞ ክለቡን ሊዮን ተቀላቅሏል ፡፡ ከአምስት ዓመት በፊት አርሰናል ፈረንሳዊውን ለማስፈረም 46.5 ...
09/06/2022

ላካዜት የቀድሞ ክለቡን ተቀላቀለ፡፡

የአርሰናሉ አጥቂ አሌክሳንደር ላካዜት በነጻ ዝውውር የቀድሞ ክለቡን ሊዮን ተቀላቅሏል ፡፡
ከአምስት ዓመት በፊት አርሰናል ፈረንሳዊውን ለማስፈረም 46.5 ሚ.ፓ ከፍሏል ፡፡
ላካዜት የፈረንሳዩን ክለብ መልሶ የተቀላቀለው እስከ ሰኔ 2025 በሚዘልቅ የሶስት ዓመት ውል ነው ፡፡

ፈረንሳዊው በፕሪምየር ሊጉ 158 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 54 ጎሎችን አስቆጥሯል ፡፡ መድፈኞቹ የ2020 ውን ኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫ ሲያነሱ አስተዋጽኦ አበርክቷል ፡፡

ቴሌግራም ቻናልላችንን ቤተሰብ ይሁኑ :-https://t.me/joinchat/5_a59ayWYPw0OWQ0

አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ተሾሙ!አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ።አምባሳደር ተስፋዬ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዘርፍ...
09/06/2022

አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ተሾሙ!

አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ።

አምባሳደር ተስፋዬ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዘርፍ ሚኒስትር ዴአታ ሆነው ተሹመዋል።

አምባሳደር ተስፋዬ ሰኔ 01 ቀን 2014 ዓ/ ም ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እስከተሾሙ ድረስ በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቋሚ መልክተኛ ሆነው በማገልገል ላይ እንደነበሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት መረጃ ያሳያል።

ቴሌግራም ቻናልላችንን ቤተሰብ ይሁኑ :-https://t.me/joinchat/5_a59ayWYPw0OWQ0

Address

Kembolcha

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ወሎ ሚዲያ ኔትወርክ- Wollo Media Netwerk posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category