Borkena Times- ቦርከና ታይምስ

Borkena Times- ቦርከና ታይምስ ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ እንሆናለን ይህ ልሳን የህዝብ ልሳን ነ?

17/10/2025

#ተጠንቀቅ

💚💚💚

17/10/2025

ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ እና በዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ ነው

ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እና ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑን የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ገልጸዋል።

የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የኅልውና ጉዳይ መሆኑንም ነው በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ለኢዜአ የተናገሩት።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑንም በአጽንኦት አንስተዋል።

እስካሁን ባለው ሂደትም በብዙ መመዘኛዎች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እንዳለው መገንዘባቸውን ገልጸዋል።

ለውጤታማነቱም ኢትዮጵያ ያላትን ሕጋዊ መሠረት፣ ታሪካዊና የሠነድ ማስረጃ በመጠቀም በሰላማዊ የዲፕሎማሲ ልዕልና ስልት ጥረቷን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅባትም መክረዋል።

ለዚህም አጋዡ መሣሪያ ለጎረቤት ሀገራት፣ ለአፍሪካ ኅብረት፣ ለምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለሥልጣን(ኢጋድ)፣ ለዓለም አቀፍ ተቋማትና ተጽዕኖ ፈጣሪ የጋራ ዕድገት ደጋፊ ሀገራት የአቋሟን ትክክለኛነት በልኩ ማስገንዘብ መሆኑን አስረድተዋል።

የባሕር በር ለተሻለ ሁለንተናዊ ዕድገት ቁልፍ መሆኑን አስገንዝበው፤ ከሕግና ከሕዝብ ፍላጎት ውጭ በሆነ መንገድ እንድታጣ የተደረገችውን የባህር በር ማግኘት እንደሚገባትም ነው የተናገሩት።

#ኢዜአ

17/10/2025

#ወሎ

ቼጉቬራ በሆነ የበግ እረኛ አቃጣሪነት ከተደበቀበት ቦታ ተያዘ። አንድ ሰውዬ የተፈጠረው ነገር ግርምት ጭሮበት እረኛውን ጠየቀው፦“እድሜ ልኩን ላንተ መብት ጠበቃ ሆኖ ሲዋጋ የኖረን ሰው ለምን ...
17/10/2025

ቼጉቬራ በሆነ የበግ እረኛ አቃጣሪነት ከተደበቀበት ቦታ ተያዘ። አንድ ሰውዬ የተፈጠረው ነገር ግርምት ጭሮበት እረኛውን ጠየቀው፦“እድሜ ልኩን ላንተ መብት ጠበቃ ሆኖ ሲዋጋ የኖረን ሰው ለምን አቃጠርክበት?”

እረኛውም እንዲህ ሲል መለሰ፦“ይህ ነፃ አውጪ ነኝ የሚለን ሰውዬ እደበቃለሁ ሲል በጎቼን አስንደንብሮ ከበረት ሰደደብኝ”

ከአመታት በኋላ በግብፅ ታላቁ አዛዥ ሙሀመድ ከሪም በስሩ መቶ ሺህዎችን ያሰለፈ የፈረሳዩን መሪ ናፖልዮን በመቃወም ደረጃ ብቻውን የቆመ ብቸኛ ሰው ነበር። ቢሆንም በመጨረሻም ሙሀመድ ከሪም በናፖሊዮ እጅ ወደቀና የሞት ፍርድ ተፈረደበት። ናፖሊዮ ግን ሙሀመድን ጠርቶ እንዲህ አለው፦“እንደ አንተ ዓይነት ሰው ከስንት አንድ ቢገኝ እንጂ የለም። ለእኔ ደግሞ አገሩን ብሎ የተዋጋን ጀግና መግደል በታሪክ የማይረሳ ጠበሳ ነው የሚሆንብኝ። ስለዚህ አላስገድልህም። ነገር ግን አንድ ቅድመ ሁኔታ አለ፤ እንደ መካሻ ይሆን ዘንድ መቶ ዐሥር ሺህ የወርቅ ሳንቲም ክፍያ ታቀርባለህ። እኔም እርህራሄዬን እሰጥሃለሁ።”

ሙሐመድ ከሪምም ፈገግ አለና እንዲህም አለ፦“ለጊዜው የዛን ያህል የሚበቃ የወርቅ ሳንቲም በእጄ የለኝም፤ ነገር ግን ለነጋዴዎች ከመቶ ሺህ በላይ የወርቅ ሳንቲም አበድርያለሁ።”

ናፖሊዮ ይህን ሲሰማ ጥቂት እንዲቆይ ፈቀደለት። እናም ሙሀመድ ከሪም በወታደሮች ተከቦ ገበያ ወጣ። መስዋት የከፈለላቸው የአገሩ ነጋዴዎች ተስፋን ከሰጡት ብሎ ያበደረውን የወርቅ ሳንቲም ጠየቀ። አንድ ነጋዴ ግን ሊሰማው አልፈቀደም፤ እንደውም የታላቁ እስክንድር መጥፋት እና የኢኮኖሚ መውደቅ መንስኤ ነው ሲል ከሰሰው።

መሐመድ ከሪም ወደ ናፖሊዮን በተሰበረ ልብ ተመለሰ። ናፖሊዮም እንዲህ አለው፦“ተስፋ አላስቆርጥህም አላስገድልህምም ጭምር። ምክንያቱም ከእኛ ጋር ጦርነት መግጠምህ ብቻ ሳይሆን፤ ሕይወትህን ለሕዝብ ስትል አሳልፍህ መስጠትህ ትልቅ ክብር ነው። እነሱ ግን ነፍሳቸውን በሸቀጥ የለወጡ ግብዞች ናቸውና ነፃነት ከንግድ እንደሚበልጥ ፈጽሞ አልተገነዘቡትም።”

የአረቡ ታላቅ ባለቅኔ ሙሀመድ ራሺድ ረዛ እንዲህ ይላሉ፦“ደናቁርት ማኀበረሰብን ለማሳወቅ የተነሳ አዋቂ፤ ለዕውር መንገድ ያበራለት ዘንድ እራሱን በእሳት ያቃጠለን ሰው ይመስላል።”

 #የእርዳታ ጥሪየኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት መምሪያ የስራ ባልደረባ የሆኑት አቶ አብዱልአዚዝ በቀለ ኃ/ማሪያም በደረሰባቸው ድንገተኛ የነርቭ ህመም በደሴ ከተማ  በተ...
16/10/2025

#የእርዳታ ጥሪ

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሰረተ ልማት መምሪያ የስራ ባልደረባ የሆኑት አቶ አብዱልአዚዝ በቀለ ኃ/ማሪያም በደረሰባቸው ድንገተኛ የነርቭ ህመም በደሴ ከተማ በተለያዩ የህክምና ማዕከላት ህክምና ሲከታተሉ ቢቆዩም ህመሙ ሊሻለው ባለመቻሉ ለአስቸኳይ ህክምና ወደ አዲስ አበባ ሪፈር ተብለዋል።

አዲስ አበባ የሚገኘው የህክምና ማዕከልም የቀዶ ህክምና ማድረግ እንደለባቸው ስለተነገራቸው ለቀዶ ህክምናው ወጭ 300ሽህ ብር በላይ በመሆኑ የተጠየቀውን ወጭ በራሳቸው ለመሸፈን አቅም ስለሌላቸው የገንዘብ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተቋቁሞ ገንዘብ እየተሰባሰበ ይገኛል።

በመሆኑ የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴው ሁሉም የቻለውን የገንዘብ ድጋፍ እንድታደርጉለት እና ፈጣሪ እንዲያነው በዱአና በፀጥሎት እናድታግዙት ጠይቀዋል ።

የማሰባሰቢያ አካውንቱ አብዱልአዚዝ በቀለ ኀ/ ማሪያም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000192471827፣
አባይ ባንክ 6067411072141013
መሆኑን የተቋቋመው ገቢ አሰባሳቢ ከሚቴ ገልጿል።

" የወላዷን ስቃይ ሳይ ግን አልቻልኩም፣ በጣም ደከመኝ እንባዋን ሳይ እኔም ባለሁበት ቁጭ ብየ አለቀስኩ ፤ የእኔ ማልቀስ ግን ህፃኑን ማትረፍ አልቻለም፣ በዚህም በጣም አዝኛለሁ " - የአምቡ...
16/10/2025

" የወላዷን ስቃይ ሳይ ግን አልቻልኩም፣ በጣም ደከመኝ እንባዋን ሳይ እኔም ባለሁበት ቁጭ ብየ አለቀስኩ ፤ የእኔ ማልቀስ ግን ህፃኑን ማትረፍ አልቻለም፣ በዚህም በጣም አዝኛለሁ " - የአምቡላንስ ሹፌር

በጎፋ ዞን መሎ ጋዳ አካባቢ አንድ የአምቡላንስ ሹፌር አንዲት ወላድ እናትን ወደ ሆስፒታል ይዞ ሲጓዝ አምቡላንሷ በጭቃ ተውጣ እና ሹፌሩ መኪናዋን ለማውጣት የቻለውን በሙሉ አድርጎ ሲያቅተው በጭቃው ላይ ቁጭ ብሎ ሲያለቅስ የሚያሳይ ምስል በተለያዩ የማህበራዊ ገጾች ላይ ተዘዋውሮ ነበር።

ይህ ሹፌር ሀብታሙ ደርጉ ደረሰ ይባላል።

ሹፌር ሀብታሙ ደርጉ ደረሰ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አለ ?

" ችግሩ የተፈጠረው ከመሎ ጋዳ ወረዳ አንዲት ወላድ እናት በወሊድ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላት ወደ ጎፋ ዞን ሆስፒታል ይዤ እየሄድኩ እያለ ልዩ ስሙ ጃውላ መንገድ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 8 ስአት ላይ ነው።

ከወላዷ ጋር የነበሩ ሰዎች ከእኔ ጋር በመሆን መኪናዋን ከጭቃው ለማውጣት እየታገልን እያለ ወላዷ በዚሁ ቦታ ላይ ወለደች፣ የሚያሳዝነው ግን የተወለደው ህጻን ሞቷል።

በመቀጠልም ስለተፈጠረው ነገር ለሃላፊዬ ደወልኩና ነገርኩት፣ እናትየዋ የደም ካንሰር ስላለባት በህይወት ለመቆየት ወደ ሆስፒታል መድረስ አለባት አልኩት። ከዛም ከቡልቄ ወረዳ ሌላ አምብላንስ መጥቶ እናትየዋን እንድወስዳት ተደረገ።

ይህ ነገር ከመሆኑ በፊት ግን እናትየዋን እና ህፃኑን በህይወት ለማዳን የግድ አምብላንሷን ከጭቃው ማላቀቅ ስለነበረብኝ ብዙ ስቆፍር ነበር። ነገር ግን አልሆነም፣ እኔም በዚያ ብርድ ላይ ስቆፍር አድሬ ሰኞ እለት ጠዋት 2:30 አካባቢ ላይ ወደ ጋዳ ተመልስኩ።

በሰአቱ የተሰማኝ ስሜት ከባድ ነው፣ ቆፍሬ፣ ቆፍሬ ሲደክመኝ በአካባቢው ያሉ ሰዎች እንዲረዱን አምቡላንሷን ሳስጮሀት ነበር። ግን መጀመሪያ ላይ ማንም አልመጣልንም። አብረውኝ የህክምና ባለሙያን ጨምሮ የወላዷ ባለቤት እና አማቿ ነበሩ።

በሰአቱ የወላዷን ስቃይ ሳይ አልቻልኩም፣ በጣም ደከመኝ፣ እንባዋን ሳይ እኔም ባለሁበት ቁጭ ብየ አለቀስኩ ፤ የእኔ ማልቀስ ግን ህፃኑን ማትረፍ አልቻለም፣ በዚህም በጣም አዝኛለሁ።

በህይወት የሌለ ልጅ የወለደችው እናት በስአቱ በጣም ደክሟት ነበር፣ ምክንያቱም የደም ካንሰር አለባት። ሌለኛው አምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ወስዶ ካደረሳት በሗላ ወደ ጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር ተጽፎላታል፣ ነገር ግን ለህክምናው የተጠየቀችው ገንዘብ ወደ 800 ሺህ ብር ስለሆነ ገና እርዳታ እያሰባሰብን ነው።

በአምቡላንስ ሹፍርና እያገለገልኩ ሁለት አመት ቆይቻለሁ፣ ብዙ ጊዜም ተመሳሳይ ችግር ይገጥመኛል፣ ሁለት እና ሶስት ቀን መንገድ ላይ የማድርባቸው አጋጣሚዎችም ነበሩ። በተደጋጋሚ የእናቶችን ከፍተኛ የሆነ ሲቃይ አይቻለሁ። በዚህኛው ግን በጣም ተስፋ ቆርጨ ከዚህ በሗላ መኪና ላለማሽከርከር አስቤ ነበር። በፌስቡክ የእኔን ምስል ብዙዎች ሲቀባበሉት ስመለከት እና ብዙዎች ለእናቶች ያላቸውን ፍቅር ሲገልፁ ሳይ ግን በጣም ደስ ብሎኛል።

ሁሌም በመንገድ ጉዳይ እንደተሰቃየን ነው፣ ችግሩ ጫፍ የወጣ ነው። የእናቶችን እና የህፃናቶችን ሞት ለማቆም ሁሉም ሰው ለመሎ ጋዳ መንገድ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል " ሲል ተናግሯል።
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ የተወሰደ

16/10/2025

#ዓዲግራት የተቃውሞ ሰልፉን ተቀላቅላለች። ተመላሽ ታጋዮች ወይ በትክክል ምሩን አሊያም ውረዱ እያሉ ነው ።

በተመሳሳይ የአርሚ 13 ታጣቂዎች ከሽረ ወደ ሽራሮ የሚወስደውን መንገድ ዓዲ ሃገራይ ከተማ ላይ በመዝጋት ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።

የፅንፈኛው ህወሓት ቡድን የግፍ ቀንበር ከትግራይ ህዝብ ጫንቃ ላይ መውረዱ አይቀሬ ነው።

ለኢትዮጵያ ሕዝብ ወደብ የማግኘት ጥያቄ የህልውና ጉዳይ ነው!!የባሕር በር አስፈላጊነት ጥያቄ የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የአንዳንድ ጎረቤት ሀገራት ጥያቄ ጭምር ነ...
16/10/2025

ለኢትዮጵያ ሕዝብ ወደብ የማግኘት ጥያቄ የህልውና ጉዳይ ነው!!

የባሕር በር አስፈላጊነት ጥያቄ የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የአንዳንድ ጎረቤት ሀገራት ጥያቄ ጭምር ነው::ኢትዮጵያ የጠየቀችው የባህር በር ጥያቄ የህልውና ከመሆኑ ባሻገር ጥቅሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራት የሚጠቅም ነው::ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር አካባቢ ሰላምና መረጋጋትን በማስፈን ረገድ የነበራ የታሪክ ሚና ቀላል አልነበረም:: የባሕር በር አስፈላጊነቱ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የጎረቤት ሀገራም ጭምር ነው፡፡ የባሕር በር የኢትዮጵያውያን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የምግብ ዋስትና እና የውኃ ችግር እያጋጠማቸው ላሉ ሀገራትም አስፈላጊ ነው፡፡ኢትዮጵያ በተፈጥሮ አቀማመጥዋ እና ባላት ምቹ የአየር ፀባይ ምክንያት የተለያዩ ምርቶችን አምርታ በባሕር በማሻገር ለጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ሀገራትም ማቅረብ ትችላለች ወደ ሚል ሀሳብም እየተደረሰ ይገኛል::
#የባህርበር
#ቀይባህር

15/10/2025

#ታላቁ ባለ ቅኔ እና ማዲህ #ሀጂ ሸህ ሁሴን ማዲህ ይህን ብለዋ ! ! !

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከሶሪያ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ ጋር በሞስኮ ተወያዩ*********************የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሶሪያ አረብ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት...
15/10/2025

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከሶሪያ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ ጋር በሞስኮ ተወያዩ
*********************

የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሶሪያ አረብ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በክሬምሊን ውይይት አድርገዋል።

ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በሀገራቱ መጻዒ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሶሪያ የሚገኙ የሩሲያ ጦር ሠፈሮች ጉዳይ ላይ ትኩረት አድርገው መምከራቸው ተገልጿል፡፡

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለረዥም ዘመናት የቆየ ወዳጅነትና ግንኙነት እንዳለ አንስተው፤ በአልሻራ የሚመሩት ኃይሎች በሶሪያ ድል መቀዳጀታቸው ለሀገሪቱና ለህዝቡ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በበኩላቸው፤ አዲሱ የሶሪያ መንግሥት ከሩሲያ ጋር ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ማደስ እንደሚፈልግ ተናግረዋል፡፡

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ በዛሬው ዕለት በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ውይይት ለሩሲያ እና ሶሪያ ግንኙነት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን መጥቀሳቸውን ስፑቲንክ ዘግቧል።

"በጋዛ ከእምነትና የመኖር ፍላጎት በስተቀር የቀረ ነገር የለም"በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ወደ ቤታቸው የተመለሱ ፍልስጤማውያን፣ ህመምና ኪሳራ ቢገጥማቸውም፤ እንደ አዲስ ለ...
15/10/2025

"በጋዛ ከእምነትና የመኖር ፍላጎት በስተቀር የቀረ ነገር የለም"

በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ወደ ቤታቸው የተመለሱ ፍልስጤማውያን፣ ህመምና ኪሳራ ቢገጥማቸውም፤ እንደ አዲስ ለመጀመር ቁርጠኛ መሆናቸውን ይናገራሉ።

“እጅ አንሰጥም። በሀገራችን እንኖራለን” ብሏል ከእስራኤል እስር የተፈታው አህመድ አሊ።

"ጋዛን ስናይ ሞተን ቢሆን ብለን ነበር" የሚሉት ነዋሪዎቹ፤ ቢሆንም ግን ከተማችንን መልሰን እንገነባታለን፤ ብለዋል፡፡

የጋዛ ነዋሪዎች ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ስለተሰማቸው ስሜት፣ ከሚወዷቸው ጋር ስለነበረው ግንኙነት፣ ከእምነትና የመኖር ፍላጎት በስተቀር ምንም የቀረ ነገር ወደሌለበት ሥፍራ መመለስ ምን ማለት እንደሆነ ከስፑትኒክ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።

በጠና ታመዋል "በዱዓም ሆነ በፆለት አትርሷቸው"ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) በጠና መታመማቸው ተሰምቷል። የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ ...
15/10/2025

በጠና ታመዋል "በዱዓም ሆነ በፆለት አትርሷቸው"

ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) በጠና መታመማቸው ተሰምቷል።

የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) የጤና እክል ገጥሟቸዉ ለህክምና ወደ ቱርክ ሀገር መሄዳቸውም ተነግሯል።

ሀጅ ዑመር ኢድሪስ ያጋጠማቸው የጤና እክል ምንነት እስካሁን በይፋ አልተነገረም።

ሙፍቲ ከገጠማቸው የጤና እክል አላህ አፊያ እንዲያረጋቸው ዱዓ እንዲደረግላቸው ጥሪ መቅረቡን ጠቅሶ የዘገበው ነጃሺ ቴሌቪዥን ነው ::

Address

Borkena
Kombolcha

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Borkena Times- ቦርከና ታይምስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Borkena Times- ቦርከና ታይምስ:

Share