Borkena Times- ቦርከና ታይምስ

Borkena Times- ቦርከና ታይምስ ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ እንሆናለን ይህ ልሳን የህዝብ ልሳን ነ?

(ዘ-ሐበሻ ዜና) የራያ ሴቶች በአሸንዳ በአል ላይ እጃቸውን በማጣመር ተቃውሞ ማሰማታቸው ተገለፀ፡፡ የአሸንዳ በአል በተለያዩ አካባቢዎች በደመቀ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን በደቡባዊ ትግራይ ግን ለ...
23/08/2025

(ዘ-ሐበሻ ዜና) የራያ ሴቶች በአሸንዳ በአል ላይ እጃቸውን በማጣመር ተቃውሞ ማሰማታቸው ተገለፀ፡፡ የአሸንዳ በአል በተለያዩ አካባቢዎች በደመቀ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን በደቡባዊ ትግራይ ግን ለየት ያለ ይዘት እንደነበረው ትግራይ ሄራልድ ዘግቧል፡፡ እንደዘገባው በመሆኒና ሌሎችም የደቡባዊ ትግራይ ዞን ከተሞች ላይ ልጅ አገረዶች ከጨዋታና ጭፈራ በተጨማሪ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ሴቶቹ ‹‹አትግደሉን፣ አታፍኑን፣ አታሸብሩን›› የሚሉ ድምፆችን ማሰማታቸውንና እጃቸውን ከፍ አድርገው በማጣመር ተቃውሟቸውን መግለፃቸውን ዘግቧል፡፡ አንዲት የመሆኒ ነዋሪ የሆነች ሴት ለትግራይ ሄራልድ ስትናገር ‹‹የዘንድሮው አሸንዳ አዲስ ልብስ አድርገን የምንጨፍርበት በአል ብቻ ሳይሆን የታሰርንበት ሰንሰለት እንዲበጠስ ጥያቄ ያቀረብንበት ነው፡፡

የህወሀት የጦር አዛዦች እያደረሱብን ያለው ጥቃት እንዲቆም ድምፃችንን አሰምተናል›› ብላለች፡፡ በደቡባዊ ትግራይ ዞን የህወሀት ከኮር በላይ የሆኑ ወታደራዊ አመራሮች በዘረጉት ኔትወርክ ነዋሪው እንደሚገደል፣ እንደሚታፈንና ፆታዊ ጥቃት እንደሚደርስበት ዘገባው አውስቷል፡፡
#ዘገባው የ ዘሀበሻ ነው

እኝህ ጳጳስ በምእመኖቻቼው ፊት የሚያነቡት እንደሌላው ጊዜ ስብከት አይደለም። እኝህ ጳጳስ የሚያነቡት ጋዛ ላይ በወራሪዋ የተጨፈጨፉ 12,211 የጋዛ ህፃናትን ስምና እድሜ ነው። ወር ያክል እ...
23/08/2025

እኝህ ጳጳስ በምእመኖቻቼው ፊት የሚያነቡት እንደሌላው ጊዜ ስብከት አይደለም። እኝህ ጳጳስ የሚያነቡት ጋዛ ላይ በወራሪዋ የተጨፈጨፉ 12,211 የጋዛ ህፃናትን ስምና እድሜ ነው። ወር ያክል እድሜ እንኳ ካልሞላቸው ገና ለአይን የሚያሳሱ ህፃናትን ጭፍጨፋ።
ጳጳሱ በግፍ የረገፉ የጋዛ ህፃናትን ስምና እድሜ አንብቦ ለመጨረስ ከ 7 ሰአታት በላይ ፈጀባቸው። በ 479 ገፅ መፅሀፍ የሰነዱትን የግፍ ዶሴ ከፍተው ለአለም አሰሙ። ለ ሰባት ሰአታት ሲያነቡ አልደከማቸውም አልሰለቻቼውም !
ይህን ሁሉ ግፍ ካነበቡ በሗላ የህፃናቱ ሞት ያበቃ ዘንዳ አለምን ተማፅነው ወደ ፈጣሪያቸውም ፀልየው በሀዘን ንባባቸውን አጠናቀቁ።
እኝህ አባት ጣልያናዊው ካርድናል አባ ማቲዮ ዙፒ ናቸው።
እኝህ አባት የተጨፈጨፉ የጋዛ ህፃናት ስምና እድሜ ዝርዝርን ሰንደው ለአለም አሰሙ። ተማፀኑ ። ይሄ ከትልቅ አባትነት የሚመነጭ እንጅ ከቶ ሌላ አይደለም።

የኛዎቹ ሀይማኖት መራዎች ስለ ጋዛ ትንፍሽ በማይሉበት አሳዛኝ ታሪካችን የካቶሊክ አባቶች የሀዘን ተማፅኖን እያየን መተአጀብ ይዘናል።

የህያ አላህ ይዘንለትና እንዳለው ጋዛ መለያ ማበጠሪያ ነች።

"በጋዛ የተከሰተው እና ሰው ሠራሽ የሆነውን የረሐብ ፍጅትና ዕልቂት ጉዳይ፣ አሁን በዓለም ዐይኖች ፊት ለመጋረድ የማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል። [ሰው ሠራሽ የረሐብ ፍጅቱ] እንደሚከሰት ቀድ...
23/08/2025

"በጋዛ የተከሰተው እና ሰው ሠራሽ የሆነውን የረሐብ ፍጅትና ዕልቂት ጉዳይ፣ አሁን በዓለም ዐይኖች ፊት ለመጋረድ የማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።

[ሰው ሠራሽ የረሐብ ፍጅቱ] እንደሚከሰት ቀድመን ዐውቀን ነበር። ስለርሱ ስናስጠነቅቅ ቆይተናል። እናስቆመው ዘንድ አልተፈቀደልንም።

በየዕለቱ የሰው ሕይወት እየቀጠፈ ስላለው ይኼንን ዓለም አቀፍ ቸነፈር አስመልክቶ አሁን የዓለም አገራት መሪዎችን የምንጠይቀው አንድ ያፈጠጠ ጥያቄ አለን፤

እርሱም 'ሰብዓዊነት ሆይ! ከወዴት አለህ?' ስንል እንጠንቃለን።

ሰብዓዊ ዕርዳታ ላይ እየተደረገ ያለው ዕቀባ ዛሬውኑ ይቁም!!

ተኩስ አቁም አሁኑኑ!"

ቴዎድሮስ አድሐኖም (ዶ/ር)
በተባበሩት መንግሥታት የዓለም የጤና ድርጅት ፕሬዝዳንት

የአዋሽ - ኮምቦልቻ - ሐራ ገበያ እና የሐራ ገበያ - መቐለ የባቡር መስመሮች ግንባታ ሊጀምር ነው ተባለ    | 🚆 የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ በ2013 ዓ.ም በሰሜን ኢትዮጵያ በተ...
23/08/2025

የአዋሽ - ኮምቦልቻ - ሐራ ገበያ እና የሐራ ገበያ - መቐለ የባቡር መስመሮች ግንባታ ሊጀምር ነው ተባለ

| 🚆 የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ በ2013 ዓ.ም በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት ምክንያት ግንባታቸው ተቋርጠው የነበሩትን የባቡር መንገዶች ግንባታ ለማስጀመር የሚያስችሉ ግምገማዎች ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

ማዕከላዊ ኢትዮጵያን ከሰሜን ጋር ለማገናኘት የተነደፉት የባቡር መስመሮቹ፦

🔶 የአዋሽ - ኮምቦልቻ - ሐራ ገበያ 392 ኪሎ ሜትር፣
🔶 የሐራ ገበያ - መቀሌ 268 ኪሎ ሜትር ርዝመት አላቸው፡፡

ፕሮጀክቶቹ፣ የቻይና የፋይናንስ ተቋማትን ጨምሮ በአብዛኛው በውጭ ብድር የሚሠሩ መሆናቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡

🛤 ኮርፖሬሽኑ በዓመቱ ውስጥ ከግንባታ ፕሮጀክቶች እና ከሌሎች የንግድ እንቅስቃሴዎች 710 ሚሊዮን ብር ገቢ ቢያገኝም፣ ከባቡር ሐዲድ ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ በውጭ ዕዳ ጫና ውስጥ እንደሚገኝ ግምገማው ላይ ተጠቅሷል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

የአባቴን ቤት እሸጣለሁ እንጅ አልቆምም!!የአዲስ አድማስ ጋዜጣ መስራችና ባለቤት አሰፋ ጎሳዬ    | ሽቅርቅሪት ቅዳሜ ላይ ቆመን ዕለቷን ያስናፍቋት ስለነበሩት አንዷ "አዲስ አድማስ" ጋዜጣ ...
23/08/2025

የአባቴን ቤት እሸጣለሁ እንጅ አልቆምም!!

የአዲስ አድማስ ጋዜጣ መስራችና ባለቤት አሰፋ ጎሳዬ

| ሽቅርቅሪት ቅዳሜ ላይ ቆመን ዕለቷን ያስናፍቋት ስለነበሩት አንዷ "አዲስ አድማስ" ጋዜጣ ትንሽ ብናወራስ!?

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ህልው ሆኖ ወደ አንባቢ የመጣው በወርሃ ጥር 1991 አ.ም የዛሬ 26 አመት ግድም ነበር።

አዲስ አድማስ የንባብ ዐውዱን ከመቀላቀሏ በፊት ይዘትና ቅርጿን በተመለከተ ብዙ ዝግጅት፣ ብዙ ጥንቃቄ፣ ብዙ ምክክር፣ ብዙ ሙያዊ ርብርብ ተደርጎባታል። ይህንን ጥንቃቄና ዝግጅት አሳምረው የሚያውቁት ባለቤቷ አሰፋ ጎሳዬና ጓደኞቹ ጋዜጣዋን "እንከን የለሽ" በሚል እርግጠኝነት የንባብ ዐውዱን ቢቀላቀሉም፤ እንደታሰበውና እንደተለፋበት ያህል ግን ወዲያው ምላሽ አላገኘም። ይልቁንም በሸክም የወጣው ጋዜጣ በሸክም እየተመለሰ፤ በጋዜጣው ዝግጅት ላይ የአቅም አቅማችንን እንተጋ የነበርነውን ሁሉ ልብ የሚያርድ ሁኔታ ተፈጠረ።

እንዴት? ለምን? በሚል ግራ መጋባት ራሳችንን እስከመጠራጠር አደረሰን!

ከዚህ የተነሳም 'ቢሆን፣ ቢደረግ፣ የምንለውን ሃሳብ እያነሳን እየጣልን ተነጋገርን። ብዙዎቻችን ከአንባቢው አለመብሰልና ፈጣን መረጃ ፈላጊነት እንጅ በይዘቱ አንዳች እንከን እንደሌለው እንገምታለን።

ከይዘት ባሻገር አውጥተን አውርደን ቶሎ ተቀባይነት እንዳያገኝ እንቅፋት የሆነበት ሌላው ምክንያት 'ቅርፁ ሊሆን ይችላል' በሚል ግምት ባልተለመደው ብርቱካናማው የስያሜው ቀለም መደብና የጽሑፉ ቅርፅ ላይ አተኮርን። እናም አሰፋን "በቃ ችግሩ ይሄ ብርቱካናማ ቀለም ያለው ስያሜና ጽሑፍ ሊሆን ስለሚችል እንቀይረው" አልነው። አሰፋም ያቺን ሽራፊ ፈገግታውን እያሳዪን "በመቃብሬ ላይ" በፈረንጅ አፍ On my dead body ወዶ ሳይሆን ተገዶ ይለምዳታል አለን።
"ኪሳራውስ?" ብንለው "የአባቴን ቤት እስኪያስሸጠኝ ሊቀጥል ይችላል እንጅ አላደርገውም" አለን!

አሰፋ "ስኬትህን በመዳፍህ መጨበጥ ካሻህ በያዝከው ነገር ፀንተህ ግፋ፤ እንዳትዝልም ፀንተህ ወጥር Push and Persist" የሚባለው ጽንሰ-ሃሳብ ቀድሞ የገባው ነበር። እናም እንዳለው ሆነ "አዲስ አድማስ" በይዘቱም ይሁን በዝግጅቱ በየሳምንቱ በጉጉት የሚጠበቅና የሚነበብ ተወዳጅ ጋዜጣ ለመሆን በቃ!!

ዛሬ ይህንን ከ26 አመታት በፊት የሆነ ትውስታ ያስመዘዘኝ ትላንት ያነበብኩት የ ናፍቆት ዮሴፍ የቁጭትና መብሰክሰክ ጽሑፍ ነው።

እናም ከእሷ ቁጭትና መብሰክሰክ ተነስቼ "እውን አሰፋ በህይወት ቢኖር አዲስ አድማስ ከህትመት ትወጣ ነበር?" ብዬ እንዳስብ አድርጋኝ ነው!

ሞት ቀደመው እንጅ አሴ ቢኖርማ እንኳን ጋዜጣው ሊቆም ይቅርና ዛሬ በሀገራችን ቁጥር አንድ የሚባለው የቴሌቪዥን ጣቢያ ስም "አዲስ አድማስ ቲቪ" የሚባል በሆነ ነበር!!

ቸር ቀዳሚት ትሁንላችሁ!

ሀረር ልምዷን ለአዲስ አበባ በደንብ አጋርታለች!! -----"የሌሊት አናብስት" (ጅቦች) በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ  ከ አፈንዲ ሙተቂ
22/08/2025

ሀረር ልምዷን ለአዲስ አበባ በደንብ አጋርታለች!!
-----
"የሌሊት አናብስት" (ጅቦች) በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ
ለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ
ከ አፈንዲ ሙተቂ

 ....❗በአንድ ውሃ የተሞላ ማሞቂያ ውስጥ አንድ እንቁራሪት ያስቀምጡ። ከዚያም እቃውን እሳት ላይ ይጣዱት። የውሃው የሙቀት መጠን በጨመረ ቁጥር እንቁራሪቱም የሰውነት ሙቀቱን ያስተካክላል። ...
22/08/2025

....❗

በአንድ ውሃ የተሞላ ማሞቂያ ውስጥ አንድ እንቁራሪት ያስቀምጡ። ከዚያም እቃውን እሳት ላይ ይጣዱት። የውሃው የሙቀት መጠን በጨመረ ቁጥር እንቁራሪቱም የሰውነት ሙቀቱን ያስተካክላል። የውሃው ሙቀት ከፍ እያለ ሲመጣም አሁንም እንቁራሪቱ ሙቀቱን እያስተካከለ ይቀጥላል።

የውሃው ሙቀት የመፍለቅለቅ ደረጃ ላይ ሲደርስ ግን እንቁራሪቱ ከዚህ በላይ ሙቀቱን ማስተካከል ያቅተዋል። በዚህን ጊዜ እንቁራሪቱ ከእቃው ዘሎ ለመውጣት ይወስናል። ሆኖም ግን መውጣት አይችልም። ምክንያቱም የነበረውን ጥንካሬ የሰውነት ሙቀቱን በማስተካከል ጨርሶታል። ወዲያውኑ እንቁራሪቱ ይሞታል።

? አስቡ! 🤔

አዎ ብዙዎቻችን የምንለው የሞቀው ውሃ እንደሆነ ነው። ነገር ግን እውነታውና እንቁራሪቱን የገደለው የራሱ የእንቁራሪቱ መቼ ዘሎ መውጣት እንዳለበት ያለመወሰን ችግር ነው። #ምቾት

ሁላችንም በሕይወታችን ከሰዎችና ከሁኔታዎች ጋር ራሳችንን ማስተካከል አለብን። ነገር ግን መቼ ማስተካከል እንዳለብንና መቼ ትተን መሄድ እንዳለብን እርግጠኞች መሆን አለብን።



ሰዎችን በአካል፣ በስሜት፣ በገንዘብ፣ በመንፈስ ወይም በአዕምሮ እንዲበዘብዙን ከፈቀድንላቸው ሁልጊዜም ይቀጥሉበታል።

ይህም ብቻ ሳይሆን አንድ እኛን እየጎዳና ቀስ በቀስ እየጎተተን፣ የሚመች መስሎ ሙሉ ኢነርጂያችንን የሚመጥና ኋላ ላይ ከማንወጣበት አዘቅት ውስጥ ከሚከተን ልማድ፣ ሥራ፣ ወይም ግንኙነት በጊዜ ለማምለጥ መወሰን መልካም ነው።

እናም፤
መቼ ከዚህ ነገር ማምለጥ እንዳለብን ጊዜ ሳናጠፋ እንወስን!

! 🙏

አፋር ክልል - አፋምቦ
22/08/2025

አፋር ክልል - አፋምቦ

አንድ ኮሎምቢያዊ ገበሬ በእርሻው ላይ  ሲሰራ 600 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ተቀብሮ አገኘ📌ገንዘቡ የሟቹ አደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ የነበረው ፓብሎ ኤስኮባር ሊሆን ይችላል ተብሏል።  | የኮሎምቢ...
22/08/2025

አንድ ኮሎምቢያዊ ገበሬ በእርሻው ላይ ሲሰራ 600 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ተቀብሮ አገኘ

📌ገንዘቡ የሟቹ አደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ የነበረው ፓብሎ ኤስኮባር ሊሆን ይችላል ተብሏል።

| የኮሎምቢያ ሚዲያን ዋቢ በማድረግ ማርካ የተባለ የየቀን ጋዜጣ ድረ-ገፅ ከቀናቶች በፊት እንደዘገበው አንቲዮኪያ በተባለ ቦታ የተገኘው ገንዘብ ማንነቱ እንዳይገለጽ የፈለገው ገበሬ፣ የእርሻ ቦታውን ሲያሰፋ ከመሬት አንድ ሜትር በላይ ጥልቀት ላይ የተቀበሩ በርካታ የዛገ የብረት በርሜሎች አገኝቷል።

በርሜሎቹ በመቶዎች የሚቆጠሩ በጥቅል የታሰሩ በዋነኝነት የአሜሪካ ዶላር የባንክ ኖቶች የያዙ ሲሆን፣ እነዚህም በጥሩ ሁኔታ ተጠብቀው ተገኝተዋል።

የኮሎምቢያ ባለስልጣናት ግኝቱ እንደተነገረ ወዲያውኑ ገብተው የገንዘቡን ትክክለኛ ምንጭ ለመወሰን ምርመራ ጀመሩ። የመጀመሪያው ግምት እንደሚያሳየው፣ ገንዘቡ የ1980ዎቹ እና 1990ዎቹ የሜደሊን ካርቴል ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በቀላሉ ህጋዊ ማድረግ ወይም ማንቀሳቀስ ስላልተቻለ ለማከማቸት ይጠቀሙባቸው ከነበሩት መደበቂያዎች አንዱ ሊሆን ይችላል ተብሏል።

ይህ የፓብሎ ኤስኮባር ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘበት አይደለም። ዝናው በከፍተኛ ደረጃ በነበረበት ጊዜ፣ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪው ራሱ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በእርሻ ቦታዎችና በጫካ ውስጥ ደብቆ ነበር። ከእነዚህ ውስጥ ብዙዎቹ በ1993 ከሞተ በኋላ ተረስተው ነበር።

ይህ ግኝት ስለ አፈ ታሪካዊው "ፓብሎ ኤስኮባር ሀብቶች" ፍላጎትን እንደገና አነሳስቷል፣ ነገር ግን የገበሬውን እና የቤተሰቡን ደህንነት በተመለከተም ስጋትን ፈጥሯል።

የጉስታቮ ፔድሮ መንግስት አሁን ገንዘቡን መውረስ ወይም ለገበሬው ሽልማት መስጠት እንዳለበት እያጤነ ነው።

ፍ/ቤቱ ለተማሪዎቹ ወሰነ‼📌የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እስላማዊ አለባበሳቸውን ለብሰው መማር ህገ-መንግስታዊ መብታቸው መሆኑ ተወስኗል።📌በጥቅምት 2017 በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን የአ...
21/08/2025

ፍ/ቤቱ ለተማሪዎቹ ወሰነ‼

📌የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እስላማዊ አለባበሳቸውን ለብሰው መማር ህገ-መንግስታዊ መብታቸው መሆኑ ተወስኗል።

📌በጥቅምት 2017 በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች "ሂጃባችሁን ካላወለቃችሁ አትማሩም" በሚል ከትምህርት ገበታ መታገዳቸው ይታወሳል።

📌ተማሪዎቹ በዚህ ምክንያት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ሳይፈተኑ ቀርተዋል።

📌አሁን የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሴት ተማሪዎቹ እስላማዊ አለባበሳቸውን ጠብቀው (ለብሰው) ማማራቸው ህገ-መንግስታዊ መብታቸው መሆኑን ገልፆ የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በእስላማዊ አለባበሳቸው ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ውሳኔ አስተላልፏል።
መረጃው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ህ/ግ ነው።
================

‘ጥንካሬ የሚለካው ምን ያህል ሰዎች ልትገድል እንደምትችል በማሳየት አይደለም’ ሲሉ የአውስትራሊያ ባለስልጣን ተናገሩ  | የአውስትራሊያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ቶኒ ቡርክ በሁለቱ መንግ...
20/08/2025

‘ጥንካሬ የሚለካው ምን ያህል ሰዎች ልትገድል እንደምትችል በማሳየት አይደለም’ ሲሉ የአውስትራሊያ ባለስልጣን ተናገሩ

| የአውስትራሊያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ቶኒ ቡርክ በሁለቱ መንግስታት መካከል እየተባባሰ በመጣው የቃላት ጦርነት በእስራኤል ላይ ምላሽ ሰጥተዋል።

እስራኤል በመንግስታቸው ላይ ለሰነዘሩችው ትችት ምላሽ ሲሰጡ ቡርክ ጥንካሬ የሚለካው ምን ያህል ሰው ልታፈነዳ እንደምትችል ወይም ስንት ልጆችን በረሀብ መግደል እንደምትችል በማሳየት አይደለም ብለዋል።

ቀደም ሲል የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የአውስትራሊያ አቻቸውን አንቶኒ አልባኔስን "እስራኤልን የከዳ እና የአውስትራሊያን አይሁዶች የተወ ደካማ ፖለቲከኛ" ሲሉ መጥራታቸው አይዘነጋም።

አልባኒዝ ረቡዕ ዕለት አስተያየቶቹን ተከትሎ ለጋዜጠኞች በሰጡት አጭር መግለጫ ላይ “እነዚህን ነገሮች በግሌ አልወስድም ፣ ከሰዎች ጋር በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እገናኛለሁ” ብለዋል።

የፍልስጤም ግዛትን እውቅና ለመስጠት ያቀደው የአውስትራሊያ መንግስት የእስራኤል ፖለቲከኛ ሲምቻ ሮትማንን ቪዛ ከሰረዘ በኋላ ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ውስጥ ገብቷል።

ከሰዓታት በኋላ፣ እስራኤል የፍልስጤም ባለስልጣን የአውስትራሊያ ተወካዮችን ቪዛ ሰርዛ ወደፊት ማንኛቸውም የአውስትራሊያ ቪዛ ማመልከቻዎች ምርመራ እንደሚደረግባቸው ተናግራለችያሉ ዳጉ ነው ።

የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት ጉምቱ ፖለቲከኛ አቶ በረከት ስምኦን ስለኢትዮ ኤርትራ ተናገሩ‼አቶ በረከት ስምኦን መቀመጫውን አሜሪካ አገር ላደረገ ኢትዮ ሪቪው ለተባለ ድህረገጽ ሰጠው...
20/08/2025

የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት ጉምቱ ፖለቲከኛ አቶ በረከት ስምኦን ስለኢትዮ ኤርትራ ተናገሩ‼

አቶ በረከት ስምኦን መቀመጫውን አሜሪካ አገር ላደረገ ኢትዮ ሪቪው ለተባለ ድህረገጽ ሰጠው በተባለው ትንታኔ ስለ ኢትዮ ኤርትራ እና ስለ ህወሓት ቤት ስለ ተፈጠረው ሹኹቻ አንዳንድ ነገር ብሏል።

➛በኢትዮጵያና በኤርትራ መሃል ጦርነት ቢቀሰቀስ አስመራ ጫፍ ደርሶ አይቆምም
➛የኤርትራ ሉዐላዊነት ያበቃለታል
➛ጦርነት ከመጀመሩ በፊት የሻዕቢያ ስርዓት ከተገረሰሰ በኋላ በኤርትራ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር መጀመሪያ ማሰላሰል መቅደም አለበት
➛በህወሓት እና በኤርትራ መካከል የተፈጠረው ግንኙነት ከሁሉም አቅጣጫ መዘጋት የለብንም የሚል የተስፋ እርምጃ ነው ብሏል
➛ግን የህወሓት አመራሮች ኢሳይያስ አፈወርቂ በዓለም ደረጃ የተጠሉ መሪ መሆናቸውን የዘነጉ ይመስለኛል ብሏል።
➛በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ከተነሳ ግን እንደ ራሻ እና ዩክሬን የመሬት ልውውጥ ሊያስከትል ይችላል። ይህ ብቻ ሳይሆን ኤርትራ ሙሉ በሙሉ አሰብን ታጣለች ብሏል።
➛ህወሓት ከዚህ በኋላ ልታደስም ቢል የመታደስ ግዜው ያለፈ መስሎ ነው የሚታየኝ ብሏል።
➛የቀድሞው ጠ/ሚ ሀይለማርያም ደሳለኝንም ወቅሷል ጥሩ ጅማሮና ማበብ ላይ የነበረውን የደቡቡን ፖለቲካ እንዲፈርስ አድርጓል ብሏል።

Address

Borkena
Kombolcha

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Borkena Times- ቦርከና ታይምስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Borkena Times- ቦርከና ታይምስ:

Share