Borkena Times- ቦርከና ታይምስ

Borkena Times- ቦርከና ታይምስ ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ እንሆናለን ይህ ልሳን የህዝብ ልሳን ነ?

«በጦርነት የሚመለስ የአማራ ሕዝብ ጥያቄ የለም፣ ከግጭትና ጦርነት የምናገኘው ትርፍ የለም" በሚል መሪ ቃል በመላው አማራ ክልል   ህዝባዊ  ሰልፍ ተካሂዷል ።
29/06/2025

«በጦርነት የሚመለስ የአማራ ሕዝብ ጥያቄ የለም፣ ከግጭትና ጦርነት የምናገኘው ትርፍ የለም" በሚል መሪ ቃል በመላው አማራ ክልል ህዝባዊ ሰልፍ ተካሂዷል ።

በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙ  | በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መ...
25/06/2025

በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙ

| በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መታየታቸውን አናዶሉ እና የኢራን የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።

እስራኤል ከሰኔ 13 ጀምሮ የኢራን የጦር ጀኔራሎችን መግደሏን ያስታወቀች ሲሆን፤ ሦስቱ የኢራን የጦር መሪዎች በትናንትናው ዕለት ኢራን የድል በዓሏን ስታከብር ከህዝቡ ጋር በመገኘት አክብረዋል ብለዋል ምንጮቹ።

ከዚህ ውስጥ አንዱ የሆኑት የእስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፕስ ቁድስ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኢል ቃኣኒ በዓሉን ከሕብ ጋር ማክበራቸውን የኢራቅ የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።

በኢራን ታስኒም የዜና አገልግሎት የተለጠፈ ቪዲዮ ቃአኒ በዝግጅቱ ላይ ከተሰበሰቡት መካከል አሳይቷል።

ኤጄንሲው በኤክስ ላይ ኮማንደር ቃአኒ ዛሬ በተካሄደው የቴህራን የድል በዓል ላይ ይገኛሉ ሲል ተናግሯል።

በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ቃአኒ በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት የኢራን ጦር መሪዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ዘግቦ እንደነበር የሚታወስ ነው።

በተመሳሳይ የወቅቱ የመከላከያ ሚኒስትር እና የአየር ኃይል አዛዥ የነበሩ ብርጋዴር ጄኔራል አዚዝ ናስርዛዴህ በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ በመከላከያ ሚኒስቴር ላይ በተፈፀመ የአየር ጥቃት ተገድለዋል ተብለው የነበረ ቢሆንም በሕይወት እንዳሉ እና አሁንም በስልጣን ላይ እንደሚገኙ ተስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።

የአያቶላህ አሊ ኻሚኒ ከፍተኛ አማካሪ እና የደህንነት ዋና አማካሪ አድሚራል አሊ ሻምካኒ እ.ኤ.አ ሰኔ 13 ቀን 2025 በእስራኤል የአየር ጥቃት መሞታቸው ከተነገሩት አንዱ የነበሩ ናቸው።

አድሚራል አሊ ሻምካኒ በድል በዓሉ ላይ በመገኘት የድል በዓሉን አክብረዋል ሲሉ የኢራን የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።

የኮምቦልቻው ማይክል ፊሊፕስ 💙💙💙ማይክል ፊሊፕስ በአንድ የኦሎምፒክ ውድድር 8  የወርቅ ሜዳሊያ በማምጣት የተያዘውን ሪከርድ በመስበር 12 ወርቅ ያሸነፈው የኮምቦልቻው ክስተትየመላ ኢትዮጵያ ...
24/06/2025

የኮምቦልቻው ማይክል ፊሊፕስ

💙💙💙

ማይክል ፊሊፕስ በአንድ የኦሎምፒክ ውድድር 8 የወርቅ ሜዳሊያ በማምጣት የተያዘውን ሪከርድ በመስበር

12 ወርቅ ያሸነፈው የኮምቦልቻው ክስተት

የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች በጅማ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በ26 የስፖርት አይነቶች ሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተሳተፉበት መድረክ ወደ ፍጻሜው እየተቃረበም ነው፡፡

በዚሁ የስፖርት መድረክ በውሀ ዋና ስፖርት አንድ ወጣት ክስተት የሆነበትን ውድድር አሳልፏል፤ በኮምቦልቻ ከተማ የተወለደው ተምኪን ጌታቸው፡፡

የውሀ ዋና ስፖርትን በኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ የጀመረው ወጣቱ በአማራ ክልል ከታዳጊዎች እስከ ዞን ውድድሮች በመሳተፍ ያለውን አቅም በሚገባ አሳይቷል፡፡

በቅርቡ በተደረገው የመላ አማራ ጨዋታዎች ድንቅ ብቃቱን በማሳየት ክልሉን ለመወከል የበቃው ዋናተኛው፤ እየተካሄደ በሚገኝው የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ላይም ክሰተት መሆን ችሏል፡፡

ተምኪን ከተወዳደረባቸው 13 የውሀ ዋና ስፖርቶች 12 የወርቅ ሜዳልያ አግኝቷል፤ በአንድ ውድድር ደግሞ የብር ሜዳሊያ በማግኘት ታሪክ ሰርቷል፡፡

ኢትዮጵያ ስኬታማ ባልሆነችበት የስፖርት አይነት ብዙ ርቀት መጓዝ እንደሚፈልግ የገለጸው ተምኪን፤ በተለይ በኦሎምፒክ መድረክ የሀገሩን ስም ማስጠራት ትልቁ ግቡ መሆኑንም ተናግሯል፡፡

ከአሁን በፊት በአህጉርና አለም አቀፍ መድረኮች ኢትዮጵያን መወከል የቻሉ ዋናተኞችን ያፈረችው ኮምቦልቻ አሁን ደግሞ ተምኪን ጌታቸውን አስተዋውቃለች።

በጅማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኝው የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ከተምኪን ጌታቸው በተጨማሪ ሌላኛው ከኮምቦልቻ የተገኝው አብዱ ሁሴን በውሀ ዋና ስፖርት 9 የወርቅ ሜዳልያ አግኝቷል።

አማራ ክልል በመድረኩ ካስመዘገባቸው ሜዳልያዎች 50 በመቶ የሚሆነው ወርቅ የተገኘው በውሀ ዋና ስፖርት ነው።

የመካከለኛው ምስራቅ በአዲስ ውጥረት ውስጥ: አሜሪካ ኢራን ላይ ጥቃት ፈፅማለች! የቴህራን ምላሽስ ምን ሊሆን ይችላል? ቅዳሜ ዕለት ምሽት፣ አሜሪካ በሦስት የኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ያል...
22/06/2025

የመካከለኛው ምስራቅ በአዲስ ውጥረት ውስጥ: አሜሪካ ኢራን ላይ ጥቃት ፈፅማለች! የቴህራን ምላሽስ ምን ሊሆን ይችላል?

ቅዳሜ ዕለት ምሽት፣ አሜሪካ በሦስት የኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ያልተጠበቀ የአየር ጥቃት በመፈጸም፣ አሜሪካን በቀጥታ በእስራኤል እና በኢራን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ውስጥ አስገብቷታል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳሉት፣ የአየር ጥቃቶቹ የኢራንን የኒውክሌር ማበልፀጊያ አቅም ለማሰናከል በሚደረገው ጥረት፣ የፎርዶው (Fordow)፣ ናታንዝ (Natanz) እና ኢስፋሃን (Isfahan) ጣቢያዎችን "ሙሉ በሙሉ ወድመዋል"። ሆኖም፣ በተራራ ስር በጥልቀት የተቀበረው እና በአየር መከላከያ የተጠበቀው የፎርዶው ተቋም ሙሉ በሙሉ ወድሟል ወይም በከፊል የሚለው እስከ አሁን ግልጽ አይደለም።

አልጀዚራ አረብኛ እንደዘገበው፣ ዋሽንግተን ለቴህራን ስለ ጥቃቱ አስቀድማ ያሳወቀች ሲሆን፣ የተጠቁት ጣቢያዎችም ባዶ እንደነበሩ የሚያመላክቱ መረጃዎች እየወጡ ነው። በተጨማሪም፣ አምዋጅ ሚዲያ የኢራንን የፖለቲካ ምንጭ ጠቅሶ እንደዘገበው፣ አብዛኛው የኢራን የበለፀገ ዩራኒየም ክምችት ከሦስቱ የተጠቁ አካባቢዎች ውጭ ባሉ ደህንነቱ በተጠበቁ ስፍራዎች እንደሚገኙ እየተነገረ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢራን በአሜሪካ ጥቃቶች ላይ የመልሶ ማጥቃት ዛቻ ያሰማች ሲሆን፣ እሁድ ዕለትም "በቀጠናው ያለ እያንዳንዱ የአሜሪካ ወታደር እና ዜጋ ህጋዊ ኢላማ ነው" የሚል ማስጠንቀቂያ አውጥታለች። ሁኔታው አሁንም እየተለወጠ ባለበት ወቅት፣ ኢራን ምን አማራጮች አሏት የሚለውን እንመልከት።

ኢራን ልትወስዳቸው የምትችላቸው አማራጮች:

• በአሜሪካ ንብረቶች ላይ ጥቃት መፈጸም: አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ውስጥ በኩዌት፣ በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ በኳታር፣ በሶሪያ፣ በባህሬን እና በኢራቅ የሚገኙ በርካታ ወታደራዊ ካምፖች አሏት። ኢራን በእነዚህ የአሜሪካ ካምፖች ወይም ንብረቶች ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የመልሶ ማጥቃት ልትፈጽም ትችላለች። የኢራን የመንግስት ሚዲያ ተንታኝ "እናንተ ጀመራችሁት እኛ እንጨርሰዋለን" በማለት የአሜሪካ ካምፖችን የሚያሳይ ካርታ አሳይቷል። ኩዌትም በሀገሯ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ግቢ ውስጥ ለ900 ሰዎች መጠለያ እንዳዘጋጀች አስታውቃለች።

• ከኒውክሌር ስርጭት መከላከል ስምምነት (NPT) መውጣት: አሜሪካ በኢራን ላይ በፈጸመችው ጥቃት ምክንያት አንዳንድ የኢራን የፓርላማ አባላት ሀገሪቱ ከኒውክሌር ስርጭት መከላከል ስምምነት (NPT) እንድትወጣ ጥሪ እንዲያቀርቡ አድርጓል። ይህ ስምምነት የኒውክሌር ትጥቅ ማስፈታትን እና ሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል አጠቃቀምን የሚያበረታታ ነው። የፓርላማው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ ኃላፊ አባስ ጎልሮ የዩኤስ ጥቃቶች ኢራን በአንቀጽ 10 መሰረት ከስምምነቱ የመውጣት ህጋዊ መብት እንደሰጧት ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ከዚህ ስምምነት የወጣችው ሰሜን ኮሪያ (በ2003) ብቻ ስትሆን፣ እስራኤል፣ ፓኪስታን እና ህንድ ደግሞ የNPT አባል አይደሉም።

• የሆርሙዝን የባሕር ወሽመጥ መዝጋት (Strait of Hormuz): የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ ለአለም አቀፍ ንግድ ቁልፍ የሆነ የትራንስፖርት መስመር ሲሆን፣ ለአለም የቀን ዘይት ፍሰት አንድ አምስተኛ የሚሆነውን የሚያስተላልፍ "የመተላለፊያ ቀዳዳ" ነው። ኢራን ቀደም ሲል ለአሜሪካ ጥቃት ምላሽ መስመሩን ልትዘጋ እንደምትችል ስትዛበት የነበረ ሲሆን፣ እሁድ ዕለትም የኢራን የበላይ መሪ አሊ ካሜኒ ተወካይ ይህ እርምጃ በፍጥነት መወሰድ እንዳለበት ተናግረዋል። ይህ የባሕረ ሰላጤው መዘጋት በአለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ ከባድ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል።

• የተለያዩ ባካባቢው የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን መደገፍ : በየመን፣ በኢራቅ እና በሊባኖስ ያሉ በርካታ ኢራን የሚደግፋቸው የታጠቁ ቡድኖች በክልሉ በሚገኙ የአሜሪካ ንብረቶች ላይ የመልሶ ማጥቃት የመፈጸም ዕድላቸው ሰፊ ነው። የየመን ሁቲዎች ባለስልጣን እሁድ ዕለት፣ ቡድናቸው በአሜሪካ ጥቃቶች ላይ የሚሰጠው ምላሽ "የጊዜ ጉዳይ" ብቻ ነው ብለዋል። ከእነዚህ ቡድኖች ውስጥ ብዙዎቹ ከጥቅምት 2023 የጋዛ ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በእስራኤል እና በአሜሪካ ኢላማዎች ላይ በትናንሽ ጥቃቶች ሲሳተፉ ቆይተዋል።

የአለም ትኩረት በመካከለኛው ምስራቅ ላይ ሲሆን፣ ሁኔታው ምን አይነት አቅጣጫ ይዞ እንደሚሄድ ለማወቅ ጊዜ ይወስዳል። ታዲያ ወዳጄ፣ በእነዚህ አሳሳቢ ክስተቶች ላይ ምን ታስባለህ? ኢራን የትኛውን አማራጭ ትወስዳለች ብለህ ትገምታለህ? ይህ ግጭትስ ወደ ምን ያመራል?

ምንጭ Middle East Eye

ለዶናልድ ትራምፕ የቀረበው ጥሪበአሜሪካ መቀመጫውን ያደረገው "የአይሁድ ድምጽ ለሰላም" /ጅዊሽ ቮይስ ፎር ፒስ (JVP)፣ ዶናልድ ትራምፕ እስራኤልን ማስታጠቅ እንዲያቆሙ ጥሪ አቀረበ።ተሟጋች ...
20/06/2025

ለዶናልድ ትራምፕ የቀረበው ጥሪ

በአሜሪካ መቀመጫውን ያደረገው "የአይሁድ ድምጽ ለሰላም" /ጅዊሽ ቮይስ ፎር ፒስ (JVP)፣ ዶናልድ ትራምፕ እስራኤልን ማስታጠቅ እንዲያቆሙ ጥሪ አቀረበ።

ተሟጋች ቡድኑ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም እና እስራኤል በኢራን ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንድታቆም በግልጽ ጠይቋል ፡፡

ይህ ተሟጋች ቡድን ግራ ዘመም አይሁድ አሜሪካዊ "ጸረ-ጽዮናዊ " ሲሆን፣ እስራኤል በፍልስጤም የምታደርገውን መስፋፋት በጥብቅ በመቃወም ይታወቃል።

አሁን የተጀመረው ውጥረት ሙሉ ቀጠናውን እንዳያዳርስ ስጋት አለኝ ያለው ጅዊሽ ቮይስ ፎር ፒስ፣ የእስራኤል መንግስት ለአስርት ዓመታት በሚደረግለት ዓለም አቀፍ ድጋፍ "በፍልስጤማውያን ላይ የጦር ወንጀል እንዲፈጽም እድል ተሰቶታል፡፡ ያለመንም ሁኔታ ከአሜሪካ መንግስት የሚደረግለት ድጋፍም እዚህ ደረጃ ላይ አድርሶናል።" ሲልም ወቅሷል።

የአሜሪካ መንግስት ለእስራኤል በዓመት 3.8 ቢሊዮን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ ያደርጋል።

“ከኢራን ጋር ውጥረቱ ከፍ ባለበት ሰዓት የእስራኤል መንግስት በአሜሪካ መንግስት ድጋፍ በፍልስጤም የሚፈጽመውን ግፍ እና ማስራብ ቀጥሏል" ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ አጋርቷል ጄ ቪ ፒ።

“እስራኤል የዘር ፍጅት እየፈጸመች እና ቀጠናዊ ጦርነትን እያነሳሳች ነው፡፡ አሜሪካ እስራኤልን ማስታጠቅ አሁኑኑ ማቆም አለበት፡፡" ብሏል።

ዘገባው የአልጀዚራ ነው፡፡

ቢኒያም ካሴ

በትራፊክ መጨናነቅ ከአስቃቂው የአውሮፕላን አደጋ የተረፈችው ሕንዳዊት… ቡሚ ቹሃን በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ከበረራ ሰዓት በ10 ደቂቃ ዘግይታ በመድረሷ ከአሰቃቂው የአውሮፕላን መከስከስ አ...
13/06/2025

በትራፊክ መጨናነቅ ከአስቃቂው የአውሮፕላን አደጋ የተረፈችው ሕንዳዊት…

ቡሚ ቹሃን በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ከበረራ ሰዓት በ10 ደቂቃ ዘግይታ በመድረሷ ከአሰቃቂው የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ መትረፍ ችላለች፡፡

ቡሚ ቹሃን የቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ተማሪ ስትሆን ከባለቤቷ ጋር በእንግሊዝ ብሪስቶል ኑሮዋን አድርጋለች፡፡

በቅርቡም የእረፍት ጊዜዋን ከቤተሰቦቿ ጋር ለማሳለፍ ወደ ምዕራብ ሕንድ አቅንታ ነበር፡፡

የእረፍት ጊዜዋ ሲጠናቀቅም ወደ ለንደን ለመመለስ በበረራ ቁጥር 171 አውሮፕላን ትኬት መቁረጧን ትናገራለች፡፡

የበረራ ሰዓቱ ሲደርስም ቦሆሚ ቻውሃን ወደ አህመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ ማቅናት ትጀምራለች፡፡

ይሁን እንጂ ወደ አውሮፕላን ማረፊያው እየሄደች ባለችበት ወቅት ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያጋጥማታል፡፡

አሕመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያም ከበረራ ሰዓት በ10 ደቂቃ ዘግይታ ትደርሳለች፤የሚመለከታቸው አካላትም ወደ ውስጥ እንዳትገባ ከለከሏት፡፡ይህን ተከትሎም በረራው አመለጣት፡፡

ትረፊ ያላት ነፍስ እንዲሉ… በረራ ያመለጣት ቡሚ ቹሃን ከንዴቷ ሳትወጣ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ወደለንደን ልትጓዝበት የነበረው አውሮፕላን መከስከሱን በሥፍራው ተገኝታ አይታለች፡፡

ቡሚ ቹሃን የትራፊክ መጨናነቅ ሕይወቴን ታደገው ስትል መናገሯንም ቢቢሲ በዘገባው አስፍሯል፡፡

(ኤፍ ኤም ሲ)

01/06/2025

በ72ኛው ሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር ከፍተኛ ተፎካካሪ ሆና በ2ኛነት ያጠናቀቀችው ኢትዮጵያዊት ኃሴት ደረጀ ።
#🇪🇹

"እምባ የሚደርቀው በፍርድ ብቻ ሳይኾን በፍቅርም ነው"  አበጋር በወሎ አካባቢ በስፋት አገልግሎት ላይ የሚውል ባሕላዊ የዳኝነት እና የእርቅ ሥነ ሥርዓት ነው፡፡ በሀገራችን ሰዎች በሚያደርጓቸ...
29/05/2025

"እምባ የሚደርቀው በፍርድ ብቻ ሳይኾን በፍቅርም ነው"

አበጋር በወሎ አካባቢ በስፋት አገልግሎት ላይ የሚውል ባሕላዊ የዳኝነት እና የእርቅ ሥነ ሥርዓት ነው፡፡

በሀገራችን ሰዎች በሚያደርጓቸው ማኅበራዊ መስተጋብሮች ውስጥ ግጭት የማይቀር አንድ ክስተት ሲኾን ይህንን የሚፈቱ በርካታ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች አሉ፡፡

እውቁ የሥነ-ማኅበረሰብ ሊቅ ጆርጅ ሲመል ”ግጭት ምንም እንኳን ከሁለት የተጋጩ ወገኖች ውስጥ በአንደኛው ላይ ጠባሳን ጥሎ ቢያልፍም ሁለት የማይጣጣሙ ፍላጎቶችን በማስታረቅ ወደ አንዳች ዓይነት መቀራረብ መድረስ የሚያስችል መንገድ ነው" ይላል፡፡

ባሕላዊ የእርቅ ሥነ ሥርዓቶች ግጭቶች በማኅበረሰቡ ሕይዎት፣ አካል እና ንብረት ላይ አደጋ ከማድረሱ እና የበለጠ ውድመት ከማስከተሉ በፊት ለመቆጣጠር የሚረዱ ናቸው፡፡ ለዛሬም የአበጋር ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓትን እንቃኛለን፡፡

አበጋር የሽምግልና ሥነ ሥርዓት በአብዛኛው የወሎ አካባቢ ማኅበረሰቡ የሚጠቀምበት የዳኝነት እና የእርቅ ሥነ-ሥርዓት ነው፡፡ አበጋር የሚለው ቃልም አስታራቂ የሚል ፍቺ እንዳለው ይነገርለታል፡፡

አበጋር የተጣላን የሚያስታርቅ፣ ክፉ እንዳይሠራ በሀገር ሽማግሌዎች ፊት ተው የሚባልበት እና መጥፎ ነገሩን ዱአ ወይም ጸሎት አድርገው ወደ ፈጣሪ በመለመን በተጣሉት ሰዎች መካከል ጥላቻን የሚያርቁበት ሥርዓት መኾኑን ነው ከአማራ ክልል ባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ የተገኘው መረጃ የሚያመላክተው፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን ባሕል እና ቱሪዝም መምሪያ የባሕል እሴቶች እና ኢንዱስትሪ ልማት ቡድን መሪ የኾኑት ኃይሉ ታደሰ አበጋር በወሎ አካባቢ የሚተገበር የሽምግልና ሥርዓት ሲኾን ከሌሎች ለየት የሚያደርገው በዘር የሚወረስ መኾኑ ነው ይላሉ፡፡

አንድ አበጋር የኾኑ አባት ማዕረጋቸውን ከልጆቻቸው ውስጥ በአስተሳሰብ መልካም ለኾነው፣ የተሻለ አቅም እና ቀና አመለካከት ላለው ልጃቸው መርቀው እንደሚያስተላልፉ ነው የገለጹልን፡፡

አበጋር ላይ የሚስተናገዱ የግጭት ዓይነቶች ከትንሽ እስከ ትልቅ ማለትም ዛቻ፣ የንብረት ውድመት፣ ድብደባ፣ የግድያ ወንጀሎች እና ሌሎችም ናቸው ብለዋል፡፡ ሁሉም የግጭት ዓይነቶች ወደ አበጋር ከቀረቡ ይፈታሉ ነው ያሉት፡፡ ይሁን እንጂ ግጭቶች እንዲፈቱ ወደ አበጋር የሚሄዱት በጎረቤት እና በዘመድ ካልተፈታ እና ግጭቱ ጠንክሯል ተብሎ ሲታሰብ እንደኾነም አቶ ኃይሉ ይገልጻሉ፡፡

በአበጋር ሥርዓት በዳዩ በድያለሁ አስታርቁኝ ብሎ ሲጠይቅ እና የአካባቢው ማኅበረሰብ ችግሩን ተረድቶ ወደ ከፋ ደረጃ ከመድረሱ በፊት ወደ አበጋር ሄደው ይታረቁ ብሎ በእድር መሪዎች እና በታዋቂ ሽማግሌዎች አማካኝነት ሲጠይቅ መኾኑንም ጠቅሰውልናል፡፡

እርቅ እንዲከናወን ጥያቄው ከቀረበ በኋላ አበጋሮች ችግሩ ከተፈጠረበት ቦታ ሄደው ድንኳን ይጥላሉ፤ ማኅበረሰቡ እንዲገባ ድቢ ወይም ከበሮ ይመታሉ ነው ያሉት፡፡ ከዚያም የአካባቢው ማኅበረሰብ አበጋር መጣ በማለት የሚበላ እና የሚጠጣ ይዘው ይቀርባሉ፤ እየበሉ እና እየጠጡ ዱኣ ወይም ጸሎት ያደርጋሉ ነው ያሉት፡፡

በመቀጠልም ችግሩን በመረዳት ያንን ሊፈቱ የሚችሉ ሽማግሌዎች ከበዳይም ከተበዳይም ይመረጣሉ፡፡ ሁለት አበጋሮች ከማኅበረሰቡ ሽማግሌ ሊኾኑ የሚችሉ ከሁለቱም ወገን ዘመድ፣ የሀገር ሽማግሌ እና የሃይማኖት አባቶች ተመርጠው በቀጠሮ ወደ እርግማን ከመገባቱ በፊት እውነቱን እንዲያወጡ ይጠየቃሉ ነው ያሉን፡፡

ከዚያም የበደለ ሰው አምኖ ይገባል፤ በዚህ ጊዜ ከፍተኛ የኾነ የምረቃ ሥርዓት ይከወናል ነው ያሉት። ምረቃው ወንዝ ያሻግራል፤ አምኖ ካልገባ ግን በአንጻሩ እርግማን ይኾናል ብለዋል አቶ ኃይሉ፡፡ ይህም "አርከባስ" ይባላል፡፡ በዳዩ ያደረገውን ነገር ከዋሸ የሚደርስበት እርግማን ሲኾን ይህ እርግማን የደረሰበት ሰው እስከ ሰባት ትውልድ ይጎዳል፤ ዘር አይወጣለትም፤ አዝመራው አይዝለትም፤ ከብት አይረባለትም ተብሎ ስለሚታሰብ አይደብቅም ነው ያሉት።

አበጋር በማኅበራዊ ዘርፍ በቀል እና ቂምን ከስሩ በመንቀል በኩል ሚናው ከፍተኛ ነው፡፡ ለአብነት አንድ ወንጀለኛ ጥፋት አጥፍቶ በፍርድ ቤት ቅጣቱን ጨርሶ ከወጣ በኋላ የተበደለው ሰው በተመሳሳይ ደም ሲመልስ ይስተዋላል፡፡ ነገር ግን በአበጋር የታረቀ ሰው ቂም በቀል እንደሌለው እና በፍቅር አብረው እንደሚኖሩ አንስተውልናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ‘’እምባ የሚደርቀው በፍርድ ብቻ ሳይኾን በፍቅርም ነው’’ የሚል ፍቅርን እና መዋደድን የሚያበረታታ ባሕል ይዘው አንዳንድ በጣም ከባድ የኾኑ ግጭቶችን ለማስቆም ሲባል ሁለቱ ግጭት ውስጥ የገቡ ወገኖች በጋብቻ እንዲተሳሰሩ፣ እንዲወልዱ እና እንዲዛመዱ በማድረግ ደም እንዲደርቅ የማድረግ ሥራ እንደሚሠራም ነው የገለጹልን፡፡

የእርቅ ሥነ-ሥርዓቱ ከሦስት እስከ አራት ቀናት ውስጥ የሚጠናቀቅ በመኾኑ የሚባክን ጊዜ እና ጉልበት የለም፡፡ በፍርድ ቤት ብዙ ጊዜ፣ ጉልበት እና ገንዘብ የሚወስደው ችግር በአጭር ይቋጫል ብለዋል፡፡

ሼህ ሱልጣን ለይሱን ደግሞ በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ የሚኖሩ አበጋር ናቸው፡፡ እርሳቸውም እንደሚሉት አበጋር ማለት አስታራቂ ማለት ሲኾን የአስታራቂ ሽማግሌዎች የማዕረግ ስምም ነው ብለዋል፡፡

በአበጋር የተበደለን በመካስ እና በዳይ ይቅርታ እንዲጠይቅ በማድረግ ቂም በቀል እንዲጠፋ ይደረጋል፡፡ ለተለያዩ የወንጀል ዓይነቶች የተለያዩ ካሳዎችንም እንደሚተገብሩ ገልጸውልናል፡፡

ለአብነትም ለሰው ሕይዎት መጥፋት 2 መቶ ሺህ ብር፣ ለአካል ጉዳት እና ለሌሎች የንብረት ውድመቶች በየደረጃው የተቀመጡ ቅጣቶችን በዳይ ለተበዳይ እንዲክስ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡ የታረቁ ወገኖችም እርቁን አክብረው በሰላም ይኖራሉ፡፡

ከዚህ በተቃራኒው እርቁን አፍርሶ የተገኘ ሰው ከማኅበራዊ ሕይዎት በማግለል አካባቢውን እስከማስለቀቅ የሚደርስ ቅጣት ስላለው ማንም ከባሕሉ አፈንግጦ የሚወጣ የለም ነው ያሉት፡፡

የዞኑ ባሕል እና ቱሪዝም መምሪያ ይህንን ባሕላዊ እሴት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ በጽሑፍ እና በዶክመንታሪ ፊልም መሰነዱን ከዞኑ ባሕል እና ቱሪዝም መምሪያ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

አበጋሮችም ከወረዳ ጀምሮ እስከ ክልል ድረስ እውቅና እንዲያገኙ፣ ማበረታቻዎችን በመስጠት እና በተለያዩ መድረኮች እየተገኙ ተሞክሯቸውን እንዲያጋሩ እየተደረገም ነው፡፡

(አሚኮ)

ኮምቦልቻ እንደምን ናት? ===============     ==========         =====የመቻቻል እርስት የፍቅር ከተማ፣የአንድነት ቆሌ የአብሮነት ከራማ፣በህብር ያፀኗት ቄስና ቃልቻ፤አ...
27/05/2025

ኮምቦልቻ እንደምን ናት?
===============
==========
=====

የመቻቻል እርስት የፍቅር ከተማ፣
የአንድነት ቆሌ የአብሮነት ከራማ፣
በህብር ያፀኗት ቄስና ቃልቻ፤
አርቆ አስተዋይዋ እንዴት ናት ኮምቦልቻ?
❤❤❤❤
ኮምቦልቻ እንደምን ናት?
================
ካድማ የዘገነች የንቃት ዋሪዳ፣
ቀድማ የባነነች ከወፍ ጬኸት ማልዳ፣
የፍቅር ከተማ የመቻቻል ገንዳ፣
አግኝታ እማትኮራ አጥታ እማትቸገር፣
የመምሬ ይማም የሸህ ሰብስቤ አገር፣
የእምነት አንድነቷ ጎልብቶና ገዝፎ፣
የምትለዋወጥ ጉልባን እና ገንፎ።
ከአብሮነት ሀር ፈትል አምላክ የሸመናት፣
የወሎ ምሳሌ አድርጎ ያፀናት፣
ከግጭቱ ይልቅ እርቁ የሚቀናት፣
ኮምቦልቻ እንደምን ናት?
"""""
ኮምቦልቻ እንደምን ናት እንዴት ናት ባያሌው፣
ሙስሊም ክርስቲያኑ ወጣት ሽማግሌው፣
ክፍለ ከተማዋ በሙሉ ቀበሌው?
በአምነት አባቶቿ ፀብን ያስታረቀች፣
የተጣመመውን በምክር ያረቀች፣
የመቻቻልን ውል አንቀፅ ያረቀቀች፣
ኮሞቦልቻ እንደምን ነች?
❤❤❤❤❤
በእምነት፣በባህል ህዝቧን አስተሳስራ፣
መቀነቷን ታጥቃ ለለውጥ የምትሰራ፣
የመቻቻል ጫጉላ የሰላም ሙሺራ፣
ግራ የገባውን እያሰለጠነች፣
ሴራ ሲወጥኑ ስራ እየወጠነች፣
ቁጭ ብሎ እሚያማውን ሰርታ እያሳመነች፣
ባሩድ የጠማውን እጣን እያጠነች፣
በእምነቷቿ ህብረት ለስኬት ፈጠነች።
ኮምቦልቻ እንደዚህ ነች።
❤❤❤
ገና ከጅምሩ የእኛዋ ኮንበልሻ፣
ተብላለችና የሁሉ መሻሻ፤
ሠላሙን ያብዛልን እስከ መጨረሻ!!!
❤❤❤❤❤❤
መሃመ mal d

ሁሉም ዜጋ የኢትዮጵያን የባህር በር ጉዳይ የጋራ አጀንዳ ሊያደርግ ይገባል*********************የባህር በር የማግኘትን ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አንዱ አካል አድርጋ እየሰራችበት የምት...
25/05/2025

ሁሉም ዜጋ የኢትዮጵያን የባህር በር ጉዳይ የጋራ አጀንዳ ሊያደርግ ይገባል
*********************

የባህር በር የማግኘትን ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አንዱ አካል አድርጋ እየሰራችበት የምትገኘው ኢትዮጵያ ከቀጠናው ሀገራት ጋር ትብብር በመፍጠር ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገች ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ቀነአ ያደታ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣችን፣ በሕዝብ ብዛታችንና በታሪካችን የባህር በር ማግኘት ይገባናል ያሉት አማካሪው፤ "ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያለ ምንም ክፍፍልና ልዩነት በመተባበር የተጀመረውን የባህር በር አጀንዳ ወደ ፊት ማስኬድ አለበት" ብለዋል፡፡

በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ ኢትዮጵያ እየሰራችበት የሚገኘው የባህር በር ጥያቄው ቅቡልነት ያለው መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ቀጣና ከሚገኙ ሀገራት ጋር ረጅም ዘመን ያስቆጠረ የታሪክ፣ የባህል፣የእምነትና የቋንቋ ግንኝነት እንዳላት የተናገሩት ደግሞ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የውጭ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ናቸው።

ኢትዮጵያ በቀጠናው የሚከሰቱ የፀጥታና የደህንነት ችግሮችን ለመፍታት የጎላ ሚና እንዳላት ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያን ዕድገትና ልማት የማይሹ እንዲሁም በባህር በር ጉዳይ ታሪካዊ ሐቅ የማይዋጥላቸውን ሀገራት ሀሳብ በማስቀየር ዕውነታውን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ እየተሰራ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ ገልጸዋል፡፡

ከሰሞኑ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ያዘጋጀው 3ኛው የቀይ ባህር ቀጣናዊ ጂኦ ፖለቲካዊ ፎረም በቀይ ባህርና በኤደን ባህረሰላጤ ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ሲሆን፤ የባህር በር ጉዳይ የኔም ጉዳይ ነው የሚለውን አጀንዳ ወዳጅም ጠላትም እንዲያውቀው መድረኩ ወሳኝ ምክክርና ውይይት የተካሄደበት መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ጃፋር በድሩ አንስተዋል፡፡

ebc

እናቷም የእንጀራ አባቷም በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ። ወላጅ እናት ወ/ሮ ሀና በየነ ትባላለች የድሬዳዋ ከተማ ገንደቆሬ ሰፈር ነዋሪ ስትሆን ከቀድሞ ባሏ ጋር  የተፈታችው ይህቺ ሴት ከእሷ ጋር እ...
23/05/2025

እናቷም የእንጀራ አባቷም በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ።

ወላጅ እናት ወ/ሮ ሀና በየነ ትባላለች የድሬዳዋ ከተማ ገንደቆሬ ሰፈር ነዋሪ ስትሆን ከቀድሞ ባሏ ጋር የተፈታችው ይህቺ ሴት ከእሷ ጋር እየኖረ ባለው ሌላ ወንድ ከአብራኳ የወጣችውን የገዛ ሴት ልጅዋ ተገዳ መደፈሯን ስታውቅ እጮኛዋን በወንጀል እንዲቀጣ ማድረግ ሲገባት የ11 ዓመት ልጇ ላይ ፈርዳ መረጃ ለማድበስበስ በማሰብ ልጇን ላይ ጫና በመፍጠር በድብደባ አካላዊ ጉዳት ከማድረስ በተጨማሪ ከ5ተኛ ክፍል የትምህርት ገበታ እና ከጎረቤቶቿ በመነጠል ከማንም ሰው ጋር ምንም ግንኙነት እንዳታረግ በማድረግ ለብዙ ጊዜ ቤት ተዘግቶባት እና ስራ ቦታ ድረስ ከስሯ ሳትነጥላት ብትንቀሳቀስም መረጃ ለመደበቅ በቂ ሆኖ ስላላገኘችው በመጨረሻ በአብራኳ በወጣችው የገዛ ልጇ ላይ የሰራችው ተደጋጋሚ የአረመኔ ሥራ ሳያንሳት እጮኛዋን ከወንጀል ለማትረፍ መረጃ ለማጥፋት ህዳር 1 ቀን 2015 ዓም ከእጮኛዋ ጋር በመተባበር ቀጥቅጠው ህፃን በአምላክ ግርማን ገደሏት።

በወላጅ እናቷ እና እንጀራ አባቷ ሕይወቷ ያለፈው ሕፃን በአምላክ ግርማ አበጋዝ ጉዳይ ዛሬ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት የቅጣት ውሣኔ ሰጥቷል።በዚህም መሠረት እናቷ ሀና በየነ እና የእንጀራ አባቷ ብሩክ በሞት እንዲቀጡ ተወስኗል

በመላው አማራ ስፖርታዊ ውድድር ኮምቦልቻ ከተማ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።  በደሴ ከተማ ለተከታታይ 12 ቀናት በተካሄደው የመላው አማራ ስፖርታዊ ውድድር  ኮምቦልቻ ከተማ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።...
22/05/2025

በመላው አማራ ስፖርታዊ ውድድር ኮምቦልቻ ከተማ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።

በደሴ ከተማ ለተከታታይ 12 ቀናት በተካሄደው የመላው አማራ ስፖርታዊ ውድድር ኮምቦልቻ ከተማ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።

ሰሜን ሸዋና ደቡብ ወሎ ዞኖች ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

ውድድሩ በእግርና መረብ ኳስ፣ አትሌቲክስን ጨምሮ በ19 የስፖርት አይነቶች ተካሂዷል።

የአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ እርዚቅ ኢሳ በማጠናቀቂያ ስነ ስርአቱ ላይ እንደገለፁት፥ ውድድሩ በክልሉ የተቀዛቀዘውን ስፖርት በማነቃቃት ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።

የተጀረውን መነቃቃት በማስቀጠል ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በማስፋፋትና በማልማት ላይ በማተኮር ይሰራል ብለዋል።

በውድድሩ ከ5 ሺህ በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ጠቁመው የእርስ በእርስ ግንኙነትን በማጠናከር ስለሰላም መስበክ ተችሏል ብለዋል።

ለመላው ኢትዮጵያ ጨዋታ ክልሉን የሚወክሉ ስፖርቶችን መምረጥ መቻሉን ጠቁመው፥ ጨዋታው በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

በውድድሩ ኮምቦልቻ ከተማ በ47 ወርቅ፣ በ29 ብርና በ25 ነሀስ 1ኛ በመሆን አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል።

ሰሜን ሸዋ ዞን በ30 ወርቅ፣በ20 ብርና በ18 ነሀስ 2ኛ እንዲሁም ደቡብ ወሎ ዞን በ30 ወርቅ፣ በ19 ብርና በ25 ነሀስ 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።

ዛሬ በተካሄደው የማጠቃለያ የእግር ኳስ የፍጻሜ ጨዋታ ሰሜን ወሎ ዞን የእግር ኳስ ቡድን የደሴ ከተማ አቻውን በማሸነፍ ዋንጫ አንስቷል።
ኮምቦልቻ ኮሙኒኬሽን

Address

Borkena
Kombolcha

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Borkena Times- ቦርከና ታይምስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Borkena Times- ቦርከና ታይምስ:

Share