
21/08/2025
የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል አንድ አመራሩ በታጣቂዎች መገደላቸውን አስታወቀ
በአማራ ክልል ሰላም ካውንስል የሰሜን #ጎጃም ዞን የካውንስሉ መሪ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ አመራሩ በታጣቂዎች መገደላቸውን አስታወቀ።
መልዓከ ምህረት ነቃጥበብ ገነት የተባሉ የካውንስሉ የሰሜን ጎጃም ዞን አመራሩ “የታጠቁ ኃይሎች ከመንግሥት ጋር እንዲወያዩ፣ ሰላም እንዲሰፍን እና የክልሉ ሕዝብ ስቃይም እንዲያበቃ ሲማጸኑ መቆየታቸውን” ካውንስሉ የጻፈለትን ደብዳቤ ዋቢ በማድረግ የክልሉ ቴሌቪዢን ባሰራጨው ዘገባ አስታውቋል።
በአከባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች “ሐምሌ 01 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ እኒህ አባት ከሚያገለግሉበት ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታጥቀው በመግባት አፍነው ወስደዋቸዋል” ሲል መግለጫው ማውሳቱን ዘገባው አካቷል።
ታጣቂዎቹ የካውንስሉን አመራር “ዳህና ማርያም ወደተባለው የታጣቂዎች ምሽግ በመውሰድ ለስቃይ ሲዳርጓቸው መቆየታቸውን” እና “ነሐሴ 06 ቀን 2017 ዓ.ም ደግሞ በታጣቂዎቹ መገደላቸውን” የካውንስሉ መግለጫ ማስታወቁን ዘገባው አካቷል።
https://addisstandard.com/Amharic/?p=8976