Agew Unity Press

Agew Unity Press Voice for the Voiceless! Like/follow our page ✔️
በዚህ ሊንክ እየገባችሁ Subscribe አድርጉ 👇
https://www.youtube.com/

04/07/2025
በአገው ህዝብ ላይ የምትቆምር ቁማርተኛ‼️የአገው ህዝብ እንዲያውቅ የምንፈልገው ነገር ቢኖር ሰኔ /2012 ዓ/ም አቡኔ ዓለም የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አፈ-ጉባኤ ነበርች። የአገው ህዝብ...
04/07/2025

በአገው ህዝብ ላይ የምትቆምር ቁማርተኛ‼️

የአገው ህዝብ እንዲያውቅ የምንፈልገው ነገር ቢኖር ሰኔ /2012 ዓ/ም አቡኔ ዓለም የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አፈ-ጉባኤ ነበርች። የአገው ህዝብ የክልልነት ጥያቄውን ደብቃ ለዛሬው የአገው ህዝብ ዘረፈ ብዙ በደሎች ዋነኛ ምክንያት እሷ መሆኗን እንድታውቁ ለማለት እወዳለሁ።

በሰኔ /2012 ዓ/ም የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የክልልነት ጥያቄ የብሔረሰብ ዞኑ ም/ቤት ለአጀንዳ አቅርቦ ውሳኔ እንዲሰጥበት ለአፈ-ጉባኤ ጽ/ቤት ቀሪ ላይ አስፈርመን አስገብተን የነበርን ቢሆንም አቡኔ ዓለም አልደረሰንም በማለት የክልልነት ጥያቄው ውድቅ እንዲደረግበት አድርጋ የነበረች ቢሆንም እንደገና በአስቸኳይ ኮፒ በማድረግ አፈ-ጉባኤ ጽ/ቤት አስገብተን የደረሰ መሆኑን ብናረጋግጥም ከአቶ ባይነሳኝ የወቅቱ የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ ጋር በመመሳጠር ሆን ብላ የክልልነት ጥያቄውን ለአዊ ብሔረሰብ ዞን ም/ቤት ባለማቅረቧ የተነሳ የአገው የክልልነት ጥያቄ በእሷ አሻጥር ሳይቀርብ እንዲቀር ያደረገች ግለሰብ መሆኗን አብዛኛው የአገው ህዝብ ያውቃውል።

ይህ የሚያሳየው አቡኔ ዓለም በአገው ህዝብ ላይ ያደረገችው ታሪክ የማይሽር ጠበሳ ከ2012 ዓ/ም የጀመረ ቢሆንም በእሷ ፀረ አገውነት የተነሳ አሁን ላይ የአገው ህዝብ የሚፈልገው የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጥያቄ አጣብቂኝ ውስጥ ይገኛል።

የክልልነት ጥያቄ በቀረበበት ወቅት 2012 ዓ/ም አቡኔ ዓለም የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትን ጥያቄ ለም/ቤት አቅርባ ብታስወስን ኑሮ ዛሬ የአገው ህዝብ ከጨቋኝ ክልል ተላቆ የራሱ የአገው ክልል ይኖረው ነበር።

በወቅቱ አቡኔ ዓለም ባደረገችው ፀረ አገውነት ውሳኔ የተነሳ አሁን ላይ የአገው ህዝብ የክልልነት ጥያቄን በየመድረኩና በየገፆቹ እያንሸራሸረ ቢሆንም የክልልነት ጥያቂያችን እስከ አሁን ሰሚ አጦ የህልውና ጥያቂያችን ሆኖብናል።

የአቡኔ ዓለም በአገው ህዝብ ላይ ጨዋታዋ ዛሬም የቀጠለ ሲሆን ዛሬ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በ4ኛ ዓመት በ42ኛው መደበኛ ስብሰባ የ2017 በጀት ዓመት ሪፖርት ላይ ጠቅላይ ሚ/አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከም/ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት በተገኙበት ሰዓት አቡኔ ዓለም በፓርላማ የመናገር ዕድል ያገኘች ቢሆንም አንዲት ጥያቄና ሃሳብ ከውስጥ በቴዎድሮስ እንዳለው አሻጥር ከውጭ በአማራ ፋኖ 360 ዲግሪ ተከቦ አጣብቂኝ ውስጥ ስለሚገኘው የአገው አዊ ህዝብ ሳት ብላ እንኳ የአገው ህዝብ ስም አለመጥራቷና እንደተወካይነቷ ድምፅ አለመሆና አሳዛኝም አሳፋሪም ተግባር ነው።

በጀግናው የዚገም ወረዳ ህዝብ ስም ከፍ ሲል በአገው ህዝብ ስም ተወካላ በ4 ዓመታት ውስጥ 42 ጊዜ በተካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተንተባተበች 1 ደቂቃ ባልሞላ ንግግሯ ውስጥ ሌሎች የፓርላማ ተወካይዮ ከ10 እስከ 15 ደቂቃ ወስደው በተላይ የጌድዮን ህዝብ ተወካይ ለጌድዮን ህዝብ የረቀቁ ጥያቄዎችን ሲያቀርብ ባየንበት የፓርላማ መድረክ የኛዋ ጉድ አቡኔ ዓለም ስለህዝባችን ያለመተንፈሷ ምን ያህል ህዝባችንን የከዳች ካህዲ መሆኗን ያየንበት የፓርላማ ውሎ ስለመሆኑ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ/ም ቆሽጣችን እያረረ፤ ጨጓራችን እየተቃጠለ፣ የደም ግፊቴ እየጨመረ፣ የልብ ትርታዬ ከመደበኛው በላይ እየመታ ለማዳመት ችያለሁ። ያሳዝናል!

ከአገው የፓርላማ ተወካይ ተብዬ የአቡኔ ዓለም ንግግር እኔን እንደ አንድ የአገው ተወላጅ የሰማሁትና ያየሁት ነገር አሳፍሮኛል፤ አሳዝኖኛል። አሁን እኔ አቡኔ ዓለምን የምጠይቀው ነገር ቢኖር እውነት አንቺ አገው ነሽ? እውነት አንቺ የአገው ህዝብ ተወካይ ነሽ? አልመሰለኝም። የህዝባችን ህልውና በመጥፋት አዳጋ ውስጥ እያለ ድምፅ አለመሆንሽን እንዴት ታይዋለሽ? የሚለውን ጥያቄ ማቅረብ እወዳለሁ።

በመጨረሻ የአገው አዊ ህዝብን በመወከል በፓርላማ 8 ተወካዮች ቢኖሩንም አንዳቸውም ለህዝባችን ድምፅ ባለመሆናቸው ከልቤ አዝናለሁ። የአገው ምሁራን፣ ማህበራዊ አንቂዎች፣ ፖለቲከኞች፣ ነጋዴዎችና አርሶ አደሮች በ2018 ዓ/ም ለሚደረገው ሀገራዊ ፣ ክልላዊና አካባቢያዊ ምርጫ ትክክለኛ ተወካዮችን ለመምረጥ ከአሁኑ እንድታስቡበት ለማስገንዘብ እወዳለሁ።

አገውነት ወይም ሞት!!!
አመሰግናለሁ!!

© Addisu Mekonnen : 26/10/2017 E.C.

የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበት አዋጅ ፀደቀየህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት...
01/07/2025

የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበት አዋጅ ፀደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበትን አዋጅ አጽድቋል።

ከዚህ ቀደም የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት እንዲሆኑ የሚፈቅደው ረቂቅ አዋጅ ስያሜ የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት አዋጅ ወደ ሚል ስያሜው ተቀይሮ ነው የፀደቀው።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው በአዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በአራት ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል።

አዋጁ በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ፣ የሪል ስቴት ዘርፉን ለማነቃቃት፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ ዲፕሎማሲን ለማጠናከር እና ሌሎች ጥቅሞች እንዳሉትም ተገልጿል።

30/06/2025

የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ፡ መስሪያ ቦታ ከአገው ዞኖች ውጭ ለተውጣጡ የአማራ ተወላጅ የልዩ ኃይልና አድማ ብተና ተመላሽ ወታደሮች ለመስጠት እየተዘጋጀ ነው!
መቆም አለበት‼️

በአማራ ክልል የረድኤት ሰራተኛ መገደሏን ተመድ አወገዘየረድኤት ድርጅት ሰራተኞች ከለላ እንዲሰጣቸው ጠይቋልየተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ)፤ በአማራ ክልል የእ...
30/06/2025

በአማራ ክልል የረድኤት ሰራተኛ መገደሏን ተመድ አወገዘ

የረድኤት ድርጅት ሰራተኞች ከለላ እንዲሰጣቸው ጠይቋል

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ)፤ በአማራ ክልል የእርዳታ ድርጅት ሰራተኛ መገደሏን አስታወቀ፤ ድርጊቱን በማውገዝ የረድኤት ድርጅቶች ሰራተኞች ከለላ እንዲሰጣቸው ጠይቋል።

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን “አንጎት” ወረዳ በመንግስት ሃይሎችና በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች መካከል ተከስቶ በነበረው ግጭት በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስላ የነበረች የረድኤት ድርጅት ሰራተኛዋ ማህሌት ስጦታው አበራ መሞቷን ያስታወቀው ኦቻ፤ ድርጊቱን አውግዟል።

የማስተባበሪያ ቢሮው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ተወካይ አቢባቶ ዋኔ፤ “ማህሌት በክልሉ ለሚንቀሳቀሰው የአማራ መልሶ ማቋቋምና ልማት ድርጅት (ORDA) ሰራተኛ መሆኗን በመጠቆም፣ ድርጊቱ በማውገዝ መግለጫ ማውጣታቸውን አስታውቋል።

የማስተባበሪያ ቢሮው ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፤ "ማህሌት በተኩስ ልውውጡ ጉዳት የደረሰባት በአካባቢው የእርዳታ እህል አቅርቦት የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች በተመለከተ መረጃ እያሰባሰበች፣ በስራ ላይ በነበረችበት ወቅት ነው” ብሏል።

ሃላፊዋ፤ “ማህሌት ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ረፋድ አራት ሰአት አከባቢ በጥይት ተመትታ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባት” ጠቁመው፣ “በዕለቱ በዞኑ ወደሚገኘው የወልድያ ሆስፒታል ተወስዳ የህክምና እርዳታ እንድታገኝ ጥረት መደረጉን” አመላክተዋል። “ነገር ግን ማትረፍ አለመቻሉን” ገልጸዋል።

የመንግስታቱ ድርጅት በተያዘው የፈረንጆቹ 2025፣ በኢትዮጵያ በስራ ላይ እያለ የተገደለ የመጀመሪያ ሰራተኛውን ነው ሪፖርት ያደረገው።

ባሰለፍነው የፈረንጆቹ አመት 2024 በመላ ሀገሪቱ 10 የረድኤት ሰራተኞች መገደላቸውን የመንግስታቱ ድርጅት ሪፖርት ማድረጉ ይታወሳል፤ ከተገደሉት የእርዳታ ሰራተኞች መካከል ስምንቱ በአማራ ክልል መሆኑን ጠቁሟል።

አዲስ ስታንዳርድ

የኢራን መሪ አሜሪካን አስጠነቀቁ!የኢራን ሁለንተናዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ አሜሪካ ዳግም በኢራን ላይ ጥቃት ካደረሰች የከፋ ምላሽ እንደሚሰጡ አስታወቁ።ከኢራንና እስራኤል የተኩስ አቁም ስም...
27/06/2025

የኢራን መሪ አሜሪካን አስጠነቀቁ!

የኢራን ሁለንተናዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ አሜሪካ ዳግም በኢራን ላይ ጥቃት ካደረሰች የከፋ ምላሽ እንደሚሰጡ አስታወቁ።

ከኢራንና እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አያቶላህ ንግግር አድርገዋል።

በቴሌቭዥን በሰጡት መግለጫ "በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ የፈፀምነው ጥቃት ዋሺንግተን ዳግም ጥቃት ከሰነዘረች ልትጠብቀው የሚገባ ምሳሌ ነው ብለዋል።

በኳታርና ኢራቅ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ኢራን ድብደባ መፈጸሟ ይታወሳል ።

27/06/2025

መግለጫዉን ኤርትራ ተቃዉማዋለች

የኤርትራን አቋም ሱዳን፣ ሩሲያና ኢራን ሲደግፉት፣የአዉሮጳ ሕብረትና ብሪታንያ ግን ተቃዉመዉታል።

የኤርትራ መንግሥት በሐገሪቱ ዉስጥ ይፈፀማል የሚባለዉን የመብት ረገጣን የሚመረምረዉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሙያ ኃላፊነት እንዲሰረዝ ጠየቀ። ሮይተርስ ዜና አገልግሎት የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ሰነድን ጠቅሶ እንደዘገበዉ ኤርትራ ምርመራዉ እንዲቋረጥ መፈለጉ ምዕራባዉ መንግሥታትን አሳስቧል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሙያዎች ኤርትራ ዉስጥ ይደርሳሉ የሚባሉ የመብት ጥሰቶችን መመዝገብ፣ መከታተልና መመርመር የጀመሩት እንደ ጎርጎረሳዉያኑ አቆጣጠር በ2012 ነዉ።

በአሁኑ ወቅት የልዩ መርማሪነቱን ኃላፊነት የያዙት ሱዳናዊዉ የሰብአዊ መብቶች ጠበቃ መሐመድ አብዱሠላም ባቢኬር ባለፈዉ ወር ባቀረቡት ዘገባ የኤርትራን የሰብአዊ መብት ይዞታ «አሳሳቢ» ብለዉታል። በባለሙያዉ ዘገባ መሠረት ሰዎች በዘፈቀደ ይታሠራሉ፣ይሰወራሉ፣ የረጅም ጊዜ ወታደራዊና ብሔራዊ አገልግሎት ለመስጠት ይገደዳሉ።

ክትትሉን ለረጅም ጊዜ የምትቃወመዉ ኤርትራ ባለፈዉ ሰኞ የመርማሪዎቹ ሥልጣን እንዲሰረዝ የሚጠይቅ ረቂቅ ለድርጅቱ አቅርባለች። የኤርትራን አቋም ሱዳን፣ ሩሲያና ኢራን ሲደግፉት፣የአዉሮጳ ሕብረትና ብሪታንያ ግን ተቃዉመዉታል።

ፎቶ ፤ አስመራ ከተማ

ዜና፡ የ  #ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር የክልሉን “ግዛት በማስመለስ” እና በተፈናቃዮች ጉዳይ ላይ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚወያዩ ገለፁየትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተ...
27/06/2025

ዜና፡ የ #ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር የክልሉን “ግዛት በማስመለስ” እና በተፈናቃዮች ጉዳይ ላይ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚወያዩ ገለፁ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ከጠ/ሚ አብይ አህመድ ጋር በመገናኘት ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማስቻል እና "በወራሪ ሀይሎች" የተያዙ ያሏቸውን የክልሉ አካባቢዎችን ነጻ ማውጣት በሚሉ አጀንዳዎች ዙሪያ ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚወያዩ አስታወቁ።

ሌተናል ጀነራል ታደሰ "በክልሉ እያጋጠሙ ያሉ ተደጋጋሚ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ከፌዴራል መንግስት ጋር የፖለቲካ ውይይት እንዲደረግ እንጠይቃለን" ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት የተባበሩት መንግስታት ደርጅት የልማት ፕሮግራም የአደጋ እና ዝግጁነት ቢሮ ምክትል ዳይሬክተር ቱርባን ሳሌህ የተመራ ልዑክን ትናንት በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።

ፕሬዝዳንቱ ከልዑካኑ ጋር በነበራቸው ውይይት፤ “ወደ ጦርነት እንድንገባ የሚያደርገን ምክንያት የለም” ሲሉ ገልጸው “ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማድረግ እና የክልሉን የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ ከፌደራል መንግስት ጋር በቀጣይ ተቀራርቦ መስራት ያስፈልጋል” ብለዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=8242

Addis Standard

ትራምፕ ቤንዚን እየጨመሩ ነው ! / ቻይና /የቻይና መንግስት በዛሬው እለት በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በኩል ባወጣው መግለጫ አምስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የኢራን እና የእስራኤል ጦርነት ላይ አሜሪካ...
17/06/2025

ትራምፕ ቤንዚን እየጨመሩ ነው ! / ቻይና /

የቻይና መንግስት በዛሬው እለት በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በኩል ባወጣው መግለጫ አምስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የኢራን እና የእስራኤል ጦርነት ላይ አሜሪካ ቤንዚን እየጨመች ማለቷ ነዉ የተነገረዉ።

በመግለጫው በእስራኤል እና በኢራን መካከል እየተባባሰ ባለው ግጭት “በእሳት ላይ ቤንዚን ጨምረዋል” ስትል ፕሬዝዳንቱን ከሳለች።

ይህንም ያሉት በዛሬው እለት ስለ መካከለኛው ምስራቅ ጉዳይ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ጉኦ ጂያኩን በኩል በሰጡት መግለጫ ላይ ነዉ ።

ጂያኩን ስለ አሜሪካ ተሳትፎ ለቀረበላቸው ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፤ እሳቱን ማቀጣጠል፣ ማገዶ መጨመር፣ ማስፈራራት እና ግፊት መጨመር ሁኔታውን ለማረጋጋት አይረዳም። ብለዋል ።

እስራኤል እና ኢራን የአየር እና የሚሳኤል ጥቃት መለዋወጣቸውን የቀጠሉ ሲሆን፤ ቴል አቪቭ በተለያዩ የኢራን ጦር ሃይሎች እና ወሳኝ ኢላማዎች ላይ ጥቃት ስትሰነዝር ኢራን በበርካታ የእስራኤል ከተሞች የባስቲክ ሚሳኤሎችን ማስወንጨፏን ቀጥላለች ቢቢሲ ዛሬ ከሰዓት ባወጣወ ዘገባ እንደሚያሳየዉ ትራምፕ፣ ኢራንና እስራኤል ስምምነት ላይ እንዲደርሱ እንደማይፈልጉ ያሳያል።

ይህ ቀናትን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ከቀጠናው አልፎ በፋርስና በኦማን ባህረ ሰላጤዎች መካከል ያለው ሰርጥ እንዲሁም የመን፣ ጅቡቲና ኤርትራን የሚያዋስነው ባብ ኤል-ማንዳብ ሰርጥ ወሳኝ የንግድ መርከቦች መተላለፊያና ባሕረ ሰላጤ እንዲሁም ቀይ ባሕር ላይ ያለዉን የአለም የንግድ ልዉዉጥ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚረዳ እየተነገረ ይገኛል ።

የኔታ ትዩብ

Address

Lalibela

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Agew Unity Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Agew Unity Press:

Share

አገውነት!!

ዓላማችን አገውነቱን በልቡ ከትቦ፣ ለወግና ባህሉ፣ ለታሪኩና ማንነቱ ዘብ የቆመና ራሱን በራሱ የሚያስተዳድር አዲስ የአገው ትውልድ መፍጠር ነው!! ፔጁን "Like" ስላደረጉ እናመሰግናለን!!