Agew Unity Press

Agew Unity Press Voice for the Voiceless! Like/follow our page ✔️
በዚህ ሊንክ እየገባችሁ Subscribe አድርጉ 👇
https://www.youtube.com/

የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል አንድ አመራሩ በታጣቂዎች መገደላቸውን አስታወቀበአማራ ክልል ሰላም ካውንስል የሰሜን  #ጎጃም ዞን የካውንስሉ መሪ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ አመራሩ በታጣቂዎች...
21/08/2025

የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል አንድ አመራሩ በታጣቂዎች መገደላቸውን አስታወቀ

በአማራ ክልል ሰላም ካውንስል የሰሜን #ጎጃም ዞን የካውንስሉ መሪ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ አመራሩ በታጣቂዎች መገደላቸውን አስታወቀ።

መልዓከ ምህረት ነቃጥበብ ገነት የተባሉ የካውንስሉ የሰሜን ጎጃም ዞን አመራሩ “የታጠቁ ኃይሎች ከመንግሥት ጋር እንዲወያዩ፣ ሰላም እንዲሰፍን እና የክልሉ ሕዝብ ስቃይም እንዲያበቃ ሲማጸኑ መቆየታቸውን” ካውንስሉ የጻፈለትን ደብዳቤ ዋቢ በማድረግ የክልሉ ቴሌቪዢን ባሰራጨው ዘገባ አስታውቋል።

በአከባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች “ሐምሌ 01 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ እኒህ አባት ከሚያገለግሉበት ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታጥቀው በመግባት አፍነው ወስደዋቸዋል” ሲል መግለጫው ማውሳቱን ዘገባው አካቷል።

ታጣቂዎቹ የካውንስሉን አመራር “ዳህና ማርያም ወደተባለው የታጣቂዎች ምሽግ በመውሰድ ለስቃይ ሲዳርጓቸው መቆየታቸውን” እና “ነሐሴ 06 ቀን 2017 ዓ.ም ደግሞ በታጣቂዎቹ መገደላቸውን” የካውንስሉ መግለጫ ማስታወቁን ዘገባው አካቷል።

https://addisstandard.com/Amharic/?p=8976

መንግስት ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ ወሰነ* ከፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ ***የኢፌዴሪ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ...
18/08/2025

መንግስት ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ ወሰነ

* ከፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ
***

የኢፌዴሪ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘመናት የገጠሟትን የኢኮኖሚ ስብራቶች ለመጠገንና ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ግስጋሤ ለማፋጠን አዲስ የኢኮኖሚ ልማት ዕይታ እና መንገድ እየተከተለች ትገኛለች። በተያዘው ብዝኃ ዘርፍ፣ ብዝኃ ተዋናይ እና ብዝኃ ተጠቃሚ የኢኮኖሚ ዕድገት አቅጣጫ፣ ለኢኮኖሚ ጥራትና አሳታፊነት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡

እንደሚታወቀው፣ ሀገራችን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባቶችን በመሠረታዊነት ለመፍታት ልዩ ልዩ ሪፎርሞችን ጀምራ እያሳካች ትገኛለች፡፡ የእነዚህ ሪፎርሞች ዓላማ ሁለት ነው፡፡ በአንድ በኩል ነባር ሀገራዊ ስብራቶችን መጠገንና የተንከባለሉ ዕዳዎችን ማቃለል ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የዛሬንና የነገን ትውልድ ጥያቄዎች በመመለስ፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና በአስተማማኝ መሠረት ላይ መገንባት ነው፡፡

ሪፎርሙን በመተግበር በተገኙ ውጤቶችና ትሩፋቶች፣ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች፣ የቢዝነስ አንቀሳቃሾችና በግል ክፍለ ኢኮኖሚ የተሠማሩ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የገቢ ሁኔታ ከኢኮኖሚ ዕድገቱ ጋር እየጨመረ መጥቷል፡፡ ነገር ግን የቋሚ ደመወዝተኞች በተለይም የመንግሥት ሠራተኞች ገቢ በተገቢው መጠን ሊጨምር አልቻለም፡፡

በአንድ በኩል በየጊዜው እየጨመረ በመጣው ሰፊ የመንግሥት ሠራተኛ ቁጥር ምክንያት የመንግሥት አጠቃላይ የደመወዝ ወጪ ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ምክንያት የኢትዮጵያ መንግሥት ለደመወዝ የሚያውለው ወጪ ከአጠቃላይ የመንግሥት ወጪ አንጻር ያለው ድርሻ ከ30 እስከ 32 በመቶ ይደርሳል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለእያንዳንዱ የመንግሥት ሠራተኛ የሚከፈለው ደመወዝ በሚፈለገው መልክ መጨመር ባለመቻሉ አሁንም የሚከፈለው አነስተኛ ነው፡፡

ይሄንን በመረዳት እና በየጊዜው በመንግሥት ሠራተኛው በተለይም ዝቅተኛ ተከፋይ በሆነው ላይ እየደረሰ ያለውን የኑሮ ጫና ለማቃለል፣ በ2017 በጀት ዓመት 91 ቢሊየን ብር ወጪ በማድረግ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ እንዲሻሻል ተደርጓል። ያለፈው የበጀት ዓመት እንደ ሀገር ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የገባንበትና በመንግሥት ወጪ ላይ ከፍተኛ ጫና የነበረበት ዓመት ቢሆንም፣ መንግሥት ባለው ቁርጠኛ ሰው ተኮር አቋም፣ የዝቅተኛ ተከፋይ ሠራተኛውን ደመወዝ ትርጉም ባለው ሁኔታ አሻሽሏል።

ደመወዝ ከመጨመር ባለፈ ቋሚ ገቢ ያለውን ሠራተኛ የመግዛት ዐቅም ለማሳደግ፣ መንግሥት ከ1994 ዓም ጀምሮ ሥራ ላይ በቆየው የቁርጥ ገቢ ግብር ዐዋጅ ውስጥ በተካተቱት የግብር ማስከፈያ ምጣኔ እና በተለያየ ደረጃ ግብር በሚጣልበት የገቢ ቅንፍ (income bracket) ላይ ማስተካከያ አድርጓል፡፡ በዚህም ሰፊ ማሻሻያ የተደረገ ሲሆን፣ በተለይም ከታክስ ነጻ የሆነውን የተቀጣሪ ገቢ ከብር 600 ወደ ብር 2000 ለማሳደግ ተችሏል።

መንግሥት ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውን የመንግሥት ሠራተኛ ዝቅተኛ የክፍያ ሁኔታ እና ተያይዞ የመጣውን የኑሮ ጫና በአንድ ጊዜ በሚደረግ የደመወዝ ማሻሻያ ሊቀርፈው እንደማይችል ይገነዘባል። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ መንግሥት ከእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ብልጽግና ምዕራፍ ሁሉም ዜጋ ተጠቃሚ መሆን አለበት ብሎ ደግሞ ያምናል። ስለሆነም ከሚወሰዱ ሌሎች ማሻሻያዎች በተጨማሪ፣ ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

በዚህ ማሻሻያ፦

1. ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

2. ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000 እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

3. የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6,940 ወደ ብር 11, 500 ይሻሻላል።

4. ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ ይደረግበታል፡፡

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል፡፡ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል። ይህ የደመወዝ ጭማሪ ካለን የልማት ፍላጎት አንጻር አገልግሎቶችና መሠረተ ልማት ለማስፋፋት የሚያስፈልገንን ሀብት የሚሻማ ቢሆንም፣ የመንግሥት ሠራተኛውን ኑሮ ማሻሻል ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ የተወሰነ ነው። ከዚህም ባሻገር የመንግሥት ሠራተኛው ችግር በደመወዝ ማሻሻያ ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ በቀጣይ የቤት አቅርቦትን እና የጤና መድን ሽፋንን ጨምሮ የተለያዩ መፍትሔዎች ይወሰዳሉ፡፡

መንግሥት ይሄንን የደመወዝ ማሻሻያ ሲያደርግ ጭማሪው በቂና የመጨረሻ ነው ብሎ በማመን አይደለም፡፡ በቀጣይነት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ማሻሻያው እየተተገበረ ሲሄድ ውጤትን መሠረት ያደረጉ ማሻሻያዎች ይደረጋሉ፡፡ በተጨማሪም የጀመርነው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ይበልጥ ውጤት እያስመዘገበ በሄደ ቁጥር፣ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የትሩፋቱ ተቋዳሽ ይሆናል፡፡

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም በተገቢ ደረጃና መጠን ለመክፈል ከተፈለገ፣ ያንን የሚሸከም ሀገራዊ ኢኮኖሚ መገንባት አለብን፡፡ ኢትዮጵያ ለአገልጋዮቿ ተገቢውን ክፍያ እንድትከፍል የሚያስችላትን ኢኮኖሚ የመገንባት ኃላፊነት ደግሞ፣ በመንግሥት ሠራተኛው ላይ ጭምር የተጣለ ብሔራዊ ግዴታ ነው፡፡ ካልተከልነው ዛፍ ፍሬ፣ ካልዘራነው ሰብል ምርት ልናገኝ አንችልምና፡፡ ኢኮኖሚያችን ካላደገ፣ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ሊያድግ አይችልም፡፡ ለአብነት የታክስ ገቢያችንን በአንድ በመቶ ብናሳድግ እንኳን፣ ከ3ዐዐ ቢሊዮን በላይ ተጨማሪ ሀገራዊ ገቢ እናገኛለን፡፡ ይሄንን ለማሳካት ደግሞ በየመስኩ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ከፍተኛውን ሚና ይጫወታሉ፡፡

በአጠቃላይ ዘላቂና ትርጉም ያለው የኑሮ ደረጃ መሻሻል እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዓይናችንን ለአፍታም ቢሆን ከሀገራዊ ሕልማችን ሳንነቅል መረባረብ አለብን። በዚህ ሂደት ውስጥ ኢትዮጵያውያን የሚከፍሉት የውዴታ መሥዋዕትነት አለ፡፡ ይህ መሥዋዕትነት ለነገ ሲባል የሚከፈል መሥዋዕትነት ነው፡፡ ለተሻለ ነገ ስንል የተወሰኑ ፍላጎቶቻችንን እንተዋለን፡፡ ውድ ዕውቀታችንን፣ ጊዜያችንን እና ጉልበታችንን እንሠዋለን፡፡ ያደጉ ሀገራት ሁሉ የከፍታ ማማ ላይ የደረሱት በአንድ ወቅት መሥዋዕትነት በከፈሉ ትውልዶቻቸው ትከሻ ላይ ነው፡፡

እኛ ኢትዮጵያውያን በነጻነት የምንኖረው፣ ከመኖር ለሚበልጥ ሀገራዊና ሕዝባዊ ክብር ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን በሠው ዐርበኞቻችን ምክንያት ነው፡፡ የኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞች የድካማቸውን ያህል ክፍያ እንደማያገኙ ይታወቃል፡፡ ይሄም ለተሻለች ኢትዮጵያ እየተከፈለ ያለ መሥዋዕትነት እንደሆነ መንግሥት ዕውቅና ይሰጣል። ስለሆነም በዚሁ አጋጣሚ፣ በአነስተኛ ክፍያ ሕዝብና መንግሥት የሰጣቸውን ኃላፊነት በመወጣት ላይ ለሚገኙ አገልጋዮች መንግሥት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

በመጨረሻም ሕዝባችንን በንጽሕናና በትጋት በማገልገል፤ ከሚገባንና ከሚጠበቅብን በላይ በመሥራት፤ ሙስናና ብልሹ አሠራርን በመታገል፤ ከዕቅዶቻችን በላይ በማከናወን፤ የኢትዮጵያን ብልጽግና እንደምናረጋግጥ መንግሥት ጽኑ እምነት አለው፡፡ የብልጽግና ጉዟችን በቀጠለ መጠን፣ በየምዕራፉ ሁላችንም የብልጽግናን ትሩፋት መቋደሳችን አይቀሬ ነው፡፡ ለዚያ ደግሞ ሁላችንም ወገባችንን አጥብቀንና ታጥቀን መትጋት አለብን፡፡

ይህ ሲሳካ ነጻነታችንን በደማቸው እንዳጎናጸፉን ቀደምት አባቶቻችን እና እናቶቻችን ሁሉ፣ እኛም ሀገራቸውን ለማበልጸግ ዋጋ የከፈሉ ትውልዶች ተብለን ታሪክ ሲዘክረን ይኖራል።

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን

ህወሓት የፌደራል መንግሥቱን ከሰሰየስምምነቱ አደራዳሪዎች በመንግሥት ላይግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋልህወሓት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አተገባበር ተቆጣጣሪ ቡድን በአ...
16/08/2025

ህወሓት የፌደራል መንግሥቱን ከሰሰ

የስምምነቱ አደራዳሪዎች በመንግሥት ላይ
ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል

ህወሓት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አተገባበር ተቆጣጣሪ ቡድን በአፋጣኝ የስምምነቱን አፈጻጸም እንዲገመግም ዛሬ ባወጣው ሳምንታዊ መልዕክቱ ጠይቋል።

ፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ተፈናቃዮች ላይ እያደረሰ ያለውን አደጋ ተረድቶ በስምምነቱ መሠረት ግዴታውን ከመወጣት ይልቅ፣ በተፈናቃዮች ሞትና ሥቃይ "የፖለቲካ ትርፍ" ለማግኘት በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል በማለት ሕወሓት ከሷል።

ህወሓት አያይዞም፣ የስምምነቱ አደራዳሪዎች፣ አውሮፓ ኅብረት፣ አፍሪካ ኅብረትና የአሜሪካ መንግሥት ስምምነቱ ተግባራዊ ባለመኾኑ የሚከሠተውን አደጋ በመረዳት፣ መንግሥት ለችግሩ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈልግ ግፊት እንዲያደርጉም አሳስቧል።

(ዋዜማ)

በኢትዮጵያ ብሮድካሲቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) ውስጥ ግለሰቦች ተደራጅተው ከፍተኛ ምዝበራና ዘረፋ እየፈፀሙ መሆናቸውን ውስጠአዋቂ ምንጮች ገለፁ።ምንጮች የላኩልን ሰነዶች በደርጅቱ ውስጥ እየተፈ...
13/08/2025

በኢትዮጵያ ብሮድካሲቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) ውስጥ ግለሰቦች ተደራጅተው ከፍተኛ ምዝበራና ዘረፋ እየፈፀሙ መሆናቸውን ውስጠአዋቂ ምንጮች ገለፁ።

ምንጮች የላኩልን ሰነዶች በደርጅቱ ውስጥ እየተፈፀመ ያለው ዘረፋ የተቋሙን ህልውና አደጋ ላይ መጣሉን ያሳያል።

ከዚህ በተጨማሪ ድርጅቱን በዘመድ አዝማድና የቅርብ ሰዎች ሪኮመንዴሽን በሚል ኢፍትሐዊ አሰራር እየሞሉት ነው ብለዋል።

በኢቢሲ ከፍተኛ የሥነ ምግባርና የሙስና ወንጀሎች በተደራጁ አመራሮች እየተፈፀመ ይገኛል ያሉት ምንጮች፣ የመንግስት ሀይባይነት ያጣውና በተደጋጋሚ ኢቢሲ እንዲስተካከል ለበላይ አመራር ቦርዶችና በብልጽግና ዋና ጽ/ቤት ውስጥ ለሚገኙና ጉዳዩን ለጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እንዲያደርሱ ቢነገራቸውም የተነገራቸውን መረጃ በሙሉ መንግስት ሰምቶ ችግሩን እንዲፈታ ከማድረግ ይልቅ ለኢቢሲ ዋና ስራአስኪያጅ ለአቶ ጌትነት ታደሰ በመንገር በኮርፖሬሽኑ ውስጥ ተረጋግተን እንዳንሰራ አድርገውናል ብለዋል፡፡
በዋና ስራአስኪያጁና በእሳቸው መዋቅር ድርጅቱ የህልውና አደጋ ተጋርጦበታል ነው ያሉት።

የመንግስትን ሥራ አለአግባብ በመምራት ለምዝበራ ምቹ በሆነ መንገድ ለአንድ ሰው ሥራው የማይመለከተው ለአቶ ማማሩ ተስፋ እስከ ብር 600ሺህ ብር ሥራ ማስኬጃ እንዲሁም ለወ/ሪት ሰናይት ሀይሌ ብር 425,000 በመስጠት ግለሰቦቹ የሚያቀርቡት ደረሰኝ የሪፎርም ሥራ ስለሆነ ማንም ማጣራት እንደለሌበት መመሪያ በአቶ ሞላልኝ መለሰ ትእዛዝ ለሁሉም ሥራው የሚመለከታቸው በመስጠት ሂሳቡ እንዲወራረድ ተደርጓል ነው ያሉት፡፡

በኮርፖሬሽኑ ውስጥ ባሉት ማኔጅመንት አባላት በውሎ አበል ስም ለተለያዩ ወጪዎች መሸፈኛ እየተባለ ከፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ ከአቶ ደረጄ ዳዲ ጀምሮ በየወሩ እስከ ብር 40,000.00 ድረስ ወጪ በማድረግ እያወራረዱ እንደሚገኝ ሰነዱ አመላክቷል፡፡

ስምንት የዲቪዥን ኃላፊዎች ኮርፖሬሽኑ በኤሌክትሪክ የሚሰራ መኪና ሰጥቶአቸው ያለመመሪያ ከየካቲት ወር 2017 ጀምሮ በየወሩ የ250 ሊትር የቤንዚን ዋጋ ብር 24500.00 እየወሰዱ መሆናቸው ያስረዳው ሰነዱ፣ ስም ዝርዝራቸውም ደረጄ አለማየሁ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ፤ ሞላልኝ መለሰ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ፤ ደረጄ ዳዲ የሰው ሃብት ሥራ አስፈፀሚ፤ ነቢዩ ወንድወሰን፤ ጌትነት ታደሰ ዋና ሥራ አስፈፀሚ፤ ገናናው ለገሰ ሌሎች መሆናቸውን ጠቅሷል።

በሌላ በኩል ሶስት ባህላዊ ጎጆ ቤቶችን ለመገንባት በፕሮፎርማ ግዥ ብር 29 ሚሊዮን ወጪ የተደረገ መሆኑን ሰነዱ አስረድቷል።

ከዚህ በተጨማሪ በሕጋዊ አለም አቀፍ ጨረታ መገዛት የነበረባቸው የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ግዥ ዱባይ ከሚገኙ ደላላዎች በብር 687ሚሊዮን ወይም 5.6 ሚሊዮን ዶላር በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ግዥ ለመፈፀም ታስቦ ከውስጥ ጉዳዩ ይመለከተናል ብለው በሥራው የተፀፀቱ የሥራ ኃላፊዎች ከሥራ እንኳን ቢባረር ይሻለኛል በማለት ለሚመለከተው ጥቆማ ሰጥቶ ምርመራ ከተካሄደ በኃላ እንዲቆም ቢደረግም አሁንም በተመሳሳይ መንገድ ከሚያውቁት ድርጅቶች የግል ጥቅማቸውን በሚያስከብር መልኩ ድርድር በማደረግ ላይ መሆናቸውን አስረድቷል።

ከዚህ በተጨማሪ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈትቤት ከ2011 ጀምሮ በማንኛውም በበጀት በሚተዳደሩትና በውስጥ ገቢያቸውና ከመንግስት ከሚሰጣቸው ድጋፍ በሚተዳደሩ አስፈፀሚ አካላት ላይ ያለ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፈቃድ የውጭ ጉዞ ክፍያ እንዳይፈፀም የተላለፈውን መመሪያ በመተላለፍ በዋና ሥራ አስፈፀሚ ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ሞላልኝ መለሰ ፈቃጅነት፣ ለዱባይ ከደላላዎች ለቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ግዥ ፕሮፎርማ ማሰባሰብ ለስድስት ኃላፊዎች 1. አቶ ሞላልኝ መለሰ 2. አቶ በለጠ እሱባለው 3. አቶ ማማሩ ተስፋ እና ሌሎች አመራሮች ለእያንዳንዳቸው 4700 ዶላር በድምሩ 28,200 ዶላር ከግል ባንክ በመፍቀድ ወጪ ማድረጋቸውን ጠቅሷል።

ለራሺያና ለቻይና ጉዞ ለአቶ ጌትነት የ17 ቀናት በቀን 4590 ዶላር ከግል ባንክ አካውንትና መንግስት የፈቀደውን የ4ቀናት ጉዞ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000 ዶላር መከፈሉን ሰነዱ ያስረዳል።

በቻይና መንግስት ለሥልጠና ሁለት ሠራተኞችን ሙሉ ወጪያቸውን ሸፍኖ እያለ ከግል ባንኮች 10,600 ዶላር መከፈሉ ያስረዳው ሰነዱ፣ የቻይና መንግስት ለሁሉም ተቋማት ባዘጋጀው የ12 ቀናት ሙሉ ወጪ ሸፍኖ እያለ ለአምስት በምክትል ማእረግ ያሉ 1. ሰናይት ሀይሌ 2. አሰፋ በቀለ 3. ታሪኩ ብርሃኑ 4. መሀመድ አወል 5. ፍቅሩ ካሳ ያለአግባብ ለእያንዳንዳችው በአቶ ሞላልኝ መለሰ ፈቃጅነት ከመንግስት አካውንት ባለመፈቀዱ ከግል ባንክ 23,400 ዶላር ክፍያ መፈፀሙን ይገልፃል።

ወደ ጣሊያን ጉዞ ለአራት ሰዎች 1. አቶ ሞላልኝ መለሰ 2. አቶ በለጠ እሱባለው 3. አቶ አብዱራሂማን ሩቤ 4. አቶ ፍቃዱ ገሰሰ ያለ ጠቅላይ ሚኒስቴር የውጭ ጉዞ ፍቃድ ተጉዘው በዚያው ሶስቱ ከአቶ ፍቃዱ ገሰሰ በስተቀር ጌትስአይር ከሚባል የአሜሪካን ኩባኒያ ግብዣ ተደርጎላቸው ወደ አሜሪካ ጉዞ በለመፈቀዱ በአጋጣሚ ከጣሊያን ወደ አሜሪካ በረራ በማድረግ ደርሶ መመለሳቸው ለዚሁ ጉዞ ከብር 10,000,000.00 በላይ ወጪ መደረጉን ሰነዱ ያስረዳል።

የክልል ስቱዲዮ ግንባታ እየተባለ ግልጽ ጨረታ ወይም በውስን ጨረታ እንኳን ሳይካሄድ ለአሶሳ፤ ለጂማ፤ ለወላይታ ሶዶ፤ ለሰመራ ፤ ለጅግጅጋ እና ለዳውሮ ተርጫ በፕሮፎርማ ብቻ ከብር 107 ሚሊዮን በላይ በአንድ አመት ውስጥ የተፈፀመ ሲሆን ለግዥ እንዲያመቻቸው በአንድ ግዥ እስከ ዘጠኝ መቶ ሺህ ብር እየቆራረጡ ግዥዎች መፈጸሙና ስቱዲዮዎቹም በገለልተኛ አካላት ኦዲት ቢደረግ አንድም መሳሪያ የሌለውና ለምርቃት ብቻ በሠራተኛው ዘንድ የጎደፈ ስማቸውን ለመገንባት ከዋናው መ/ቤት መሳሪያዎቹን በመንቀል ካስመረቁ በኃላ ወደ ቦታው የሚመልሱት መሆኑን ገልጿል።

ከዚህ በፊት ተገዝቶ ገብቶ ከነበሩት 25 ካሜራዎች ውስጥ በአንድ አመት የሥራ ቆይታ እንኳን ሳይኖራቸው 12 ተበላሽተው ያለ ሥራ መቀመጣቸው ከእነዚህ ውስጥ በቢሮ ውስጥ መጥፋቱ ተረጋግጦ እያለ ርምጃ አለመወሰዱን ጠቅሷል።

የአቶ ጌትነት ታደሰ ኔትዎርክ ኮርፖሬሽኑን ማሰራት አለመቻሉንና የመንግስት ሀይባይነት መታጣቱና አቶ ጌትነት ታደሰ በራሳቸው ሾፌር ስድስት መኪኖች ከንብረት አስተዳደር ወጪ አድርገው እየተጠቀሙበት መሆኑንና ለእነዚህ መኪኖች ነዳጅ በሙሉ ከኮርፖሬሽኑ መሆኑን ሰነዱ ያስረዳል።

ለኃላፊዎች ለሰርቪስ አገልግሎት የሚሆኑ ስምንት የኤክትሪክ መኪኖች ሲገዙ የገበያ ዋጋቸው ብር 3,200,000 ሆኖ እያለ በብር 4,200,000.00 መገዛቱን ገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪ በአቶ ሞላልኝ መለሰ መሪነት የኮርፖሬሽኑ ሠራተኛ ላልሆኑ 13 ግለሰቦች ፓስፖርት እንዲያወጡ በማድረግ ከአገር እንዲወጡ ማደረጋቸውን ሰነዱ ያስረዳል።

የኮርፖሬሽኑ ውስጥ ኦዲተሮች ከ2016 ጀምሮ ያሉትን ወጪዎች ኦዲት እንዳያደርጉና የወጪዎቹን ሚስጢር እንዲጠብቁ ማስጠንቀቂያ በአቶ ሞላልኝ መለሰ በኩል ተስጥቶአቸው ምንም አይነት የግዥ ወጪዎች ኦዲት እንዳያደርጉ እንዲሁም ሥራ እንዳይፈቱ በተሰብሳቢ ገቢዎችና ከ2004 ጀምሮ ያሉትን ሰነዶች ኦዲት አድርገው ባለፈው የአመራር ዘመን ችግሮች ነበሩባቸው ብሎ እንዲያቀርቡ ለአቶ ብርሃኑ ቻላቸው በአቶ ሞላልኝ መለሰ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ተስጥቶ ይህ ሚስጢራዊነቱ መጠበቅ እንዳለበት አስጠናቅቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ያለ አግባብ የአንድ ኣካባቢ ሰዎችን ብቻ የመንግስትን ፖልሲ በምፃረር መንገድ ከ172 በላይ በአንድ አመት ውስጥ ቅጥርና ዝውውር የፈፀመ መሆኑን ውስጠአዋቂዎች በላኩት የስም ዝርዝር አስረድተዋል።

Oromia Media Network

የኦሮሞ ምሁራንና የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ስምምነትና ውሳኔዎችሲያትል ፣ ዋሽንግተንሐምሌ 31 ቀን 2025 (እ.ኤ.አ.)የኦሮሞ ምሁራና የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች እ.ኤ.አ. ህዳር 31 ቀን 20...
01/08/2025

የኦሮሞ ምሁራንና የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ስምምነትና ውሳኔዎች

ሲያትል ፣ ዋሽንግተን
ሐምሌ 31 ቀን 2025 (እ.ኤ.አ.)

የኦሮሞ ምሁራና የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች እ.ኤ.አ. ህዳር 31 ቀን 2025 በሲያትል: ዋሽንግተን ግዛት በመገናኘት በኦሮሚያ፣ ኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይትና ትንተና ካደረግን በኋላ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ጉዳዮች ላይ ተስማምተን ውሳኔዎች ላይ ደርሰናል።

አንደኛ፡ አሁን በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ የኦሮሞን ህዝብ ከዚህ በፊት ታይቶ ለማይታወቅ ሰቆቃ እና ጭቆና እንዳጋለጠው ተገንዝበን ይህ አገዛዝ መወገድ እንዳለበት ተስማምተናል። ይህ ቡድን ፀረ ኦሮሞ ተግባራትንና ፖሊሲዎችን እየፈፀመ በዚህ ብሄር ውስጥ ለመደበቅ የሚያደርገውን ሙከራ አጥብቀን እናወግዛለን። በተመሳሳይ አንዳንድ ወገኖች ይህን ቡድን በተሳሳተ መንገድ "የኦሮሞ መንግሥት" ብለው መጥራታቸው ከነባራዊው እውነታ የራቀና ተቀባይነት የሌለው ነው።

ሁለተኛ ፡ የአብይ አህመድ ጨቋኝ አገዛዝ በሁሉም የሀገሪቱ ብሄረሰቦች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት አጥብቀን እናወግዛለን።

ሶስተኛ ፡ የኦሮሞ ፖለቲካ ድርጅቶች (ኦነግ-ኦነሠ: ኦፌኮ እና ኦነግ) አስፈላጊውን ለውጥ ለማምጣትና መጪውን ሽግግር ስኬታማ ለማድረግ በተደራጀ መንገድ የሚየደርጉትን እንቅስቃሴ በሁሉም ዘርፍ ለመደገፍ ተስማምተናል።

አራተኛ፡ የአብይ አህመድ መንግስት በሥልጣን ላይ ለመቆየት ከተጠቀመባቸው ስልቶች አንዱ በሕዝቦች መካከል ግጭቶችን መፍጠር ነው። በዚህም መሰረት በኦሮሞና በወንድማማች ሕዝቦች መካከል ጥርጣሬና ግጭት ለመፍጠር ያለመ መሆኑን በመረዳት ሁሉም የሀገሪቱ ሕዝቦችና ዜጎች ይህንን እኩይ አገዛዝ ለመለወጥ ከመቼውም ጊዜ በላይ ወቅታዊ ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

አምስተኛ፡ የአብይን ብልፅግና መንግስት የሚያገለግሉ ወታደራዊና የፖለቲካ ሃይሎች የአገዛዙን ሥልጣን ከመጠበቅ የህዝብን ጥቅም ወደ ማስከበር እንዲሸጋገሩ ጥሪ እናደርጋለን።

ስድስተኛ ፡ በኦሮሞ የፓለቲካ ኃይሎች መካከል የተጀመረው ውይይት እንዲቀጥልና ከሌሎች የአገሪቱ ሕዝቦችና ዜጎች ጋር ምክክር ለማድረግ ተስማምተናል።

ሰባተኛ፡ የአብይ አህመድ አገዛዝ እድሜውን ለማራዘም በህዝቦች መካከል ግጭት በመፍጠር መፈናቀልን ሲፈጥር የቆየና በመፍጠርም ላይ ያለ መሆኑን በመረዳት ህዝቡም ይህንን ስልት ተገንዝቦ በመካከሉ ያለውን አንድነትና ወንድማማችነት እንዲጠብቅ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ስምንተኛ ፡ የአብይ አህመድ አገዛዝ ከላይ የተዘረዘሩትን ወንጀሎች የኦሮሞን ሕዝብ ጨምሮ
በሁሉም የአገሪቱ ሕዝቦችና ዜጎች ላይ እየፈጸመ ያለ መሆኑን በመረዳት መጪው ለውጥና ሽግግር ስኬታማ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ አጎራባች አገሮችና የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብና ተቋማት አስፈላጊውን ጫና እንዲያደርጉ እንጠይቃለን።

በመጨረሻም የተጀመሩት ውይይቶችን የሚያካሂድና የተደረጉትን ውሳኔዎችን ለማሳካት አስተባባሪ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሥራ እንዲጀምር ተደርጓል።

አንድነታችን በነፃነት ይፀናል፣
ድል በትግላችን ይመጣል!

Jawar Mohammed

አትራፊ ጦርነት፣ አክሳሪ ሠላም የለምና -- ጦርነት ያብቃ፤ ሠላምና ዲሞክራሲ ይስፈን!ክተቃዋሚ ፖለቲካ ፓረቲዎቸ ኮክሰ  በወቅታዊ ሁኔታ ላይ   የተሰጠ መግለጫ👇ሀምሌ  21/2017ዓ.ም፣ አዲ...
28/07/2025

አትራፊ ጦርነት፣ አክሳሪ ሠላም የለምና -- ጦርነት ያብቃ፤ ሠላምና ዲሞክራሲ ይስፈን!
ክተቃዋሚ ፖለቲካ ፓረቲዎቸ ኮክሰ በወቅታዊ ሁኔታ ላይ የተሰጠ መግለጫ👇

ሀምሌ 21/2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ።

በሀገራችን የተለያዩ ክልሎች፟፟ በዋናነት በኦሮሚያ፣ አማራ፣ ትግራይ፣ እንዲሁም በሌሎቸም፣ በሀዝብና መንግስት መካከል ያለው ግንኙነት ተዛብቶ አለመግባባቶቸ ወደ ሀዘባዊ የህልውናና ዲሞክራሲ ትግል ከተሸጋግሩ ዓመታት ተቆጥረዋል ፡፡ ይህ የውስጥ ውጥረት ድንበር ተሻግሮ ትናንተ አጋር የነበሩ ጎረቤታሞች መካከል ከፖለቲካና ዲፕሎማሲ መርሆዎች የወረደ ሰቀጣጭ የጦርነት አታሞ ሲደለቅ እያደመጥን ነው፡፡ በተለይ ከኤርትራ ጋር የተገባው እሰጥ አገባ ያሳፍራል፤ያነዣበበወ አደጋ በእጀጉ ያስፈራል፡፡ ከሁለቱም ወገን አሸናፊና ተሸናፊ ስሌለለው የወንድማማቾች ጦርነት የሚስማው ሽለላና ቀረርቶ የዜጎች ህይወት፣ሃብትና ንብረት ፣ ማኅበራዊ ቀውስ ማስፋት፣ማስቀጠልና ችግሮችን ማባባስ እንጂ መፍትሄ አያመጣም፣ ለማንም የድል ብሥራት አይሆንም፡፡ ቀንጫራውን የሰብዐዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻችን የፖለቲካ ነጻነታችን የበለጠ ለአደጋ አጋልጦ ወደከፋ አምባገነንነት ሲያልፍም አገር ማፍረስ ሊያደርሰን ይችላል፡፡ ድል በደምና በጥፋት አይለካም፡፡

በእንዲህ ያለው ምስቅልቅሎሽ ውስጥ እያለን ስለ መጪው 7ተኛ (ምርጫ 2018) እየተነገረ ነው፤ያለፉት ስድስት ምርጫዎች ( ከ97ቱ ምርጫ በከፊል በስተቀር) በአገር ውስጥም ሆን በአእለም አቀፍ ደረጃ ፍትሃዊ፣ታማኘነትና የህዝብ አመነታ የጎደላቸው በብዙዎች ዘንድ ተቀባይንት አለው፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ መራጩ ህዝብና በነጻና ገለልተኛ ተዋናዮቸ በሂደቱ ላይ ያለውን እምነት የት እንዳደረሰው በዓለም አደባባይ የተሰጣ ሃቅ ነው፡፡ቦርዱ እንደተቋም ያለበት የነጻና ገለልተኝነት ጥያቄና የገዢው ፓርቲ ጉዳይ አስፈጻሚነት ክስ በዕድሜው እየቀረፈው የመጣው ችግር ሣይሆን እየተባባሰ የመጣ ነው፡፡ ይባስ በሚያስብል ለምርጫው ከዓመት ያነሰ ጊዜ በቀረበት ጊዜ ከገማሽ በላይ (60 ከመቶ) አባላቱ በአዲስ ተሹመዋል፡፡ ይህን በሚያጠናክር መልክ የምርጫ ህግ ለማሻሻል በሚል ቦርዱ እንደ ነጻ የዲምክራሲ ተቋም የተቃዋሚ ፓርቲዎችንና የባለድርሻ አካላትን የማሻሻያና የትኩረት ነጥቦች ከማገናዘብ፣ ከተጨባጭና ነባራዊ ሁኔታው አንጻር መመመዘን ይልቅ በተቃራኒው ተገኝቷል፡፡

ከመጪው ምርጫ በፊት የቦርዱ ሀጋዊ የአሰራርና ተቋማዊ ችግር እስካልተፈታ ድረስ ለምርጫ መዘጋጀት የሚለው ሃሳብ ትርጉም አልባ ይሆናል፡፡ በእነዚህ ሁኔታዎቸ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም፡፡እውነተኛ ሪፎርም ከሌለ በኢትዮጵያ ተኣማኒ፣ አካታች፣ነጻና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም፡፡

በአገሪቱ ውስጥ የሚታዩትን እነዚህን ነባራዊና ወቅታዊ ሁለንተናዊ ምስቅልቅሎች መፍትሄ ያዋልዳል የተባለለት የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንም ከልደቱ ጀምሮ የተሰናከለ በሂደቱም ክሽፈቱን ያረጋገጠ መሆኑ መጻኢ ዕድላችን አገርን ሊያሳጣን ከሚችል እጅግ ፈታኝ ሁኔታ የተጋለጥን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ብመሆኑም ማንንም በምንም ምክንያት ከማንም የማይለይ ያገር ህልውና የማስቅጠል የጋራ ተግባር ከፊታቸን ተደቅኗል፡፡

ስለዚሀ ክዚሀ ነባራዊና ተጨባጭ ሁኔታዎቸ የሚመነጨወነ ሁለንተናዊ ቀውስና በቀጠናችን፣ በአሀጉራችን አልፎም በአለማችን የሚደቅነውን ጥፋትና ውድመት፣ አደጋና ስጋት ለመቀልበስ ባለድርሻዎች ብሙሉ ያለልዩነት ፦ ኢሀአደግ በምከር አልሰማባይነቱና ንቀቱ ለከፋው ዛሬ እንዳደረሰን፣ በብልጽግና ግትርነትና እብሪት ፍንትው ብሎ ከሚታየው ኢትዮጵያነ ከዚህም የባሰ አዘቅት የመክተት አደጋ ለመታደግ በአነድነትና በቁርጠኝነት እንድንነሳ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን//
በመሆኑም ፡-

1/መራጭ ህዝባችን በአገራችን ያንዣበበው አደጋ ለመቀልበስ ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍንና መጪው ምርጫ ነጻ፣ ዲሞክራሲያዊና ተዓማኒ ይሆን ዘንድ በገዢው ፓርቲ/መንግስት ላይ ተገቢውን ጫና ላመፍጠር በአገር ቤትና ዓለምአቀፍ መድረክ ለምናደርገው ትግል የምናቀርበውን ጥሪ እንድትከታተሉና ከጎናችን እንድትቆሙ፤

2/የሠላማዊ ትግል አራማጅ ፓርቲዎች ያነሳናቸው ጥያቄዎች ለነገ የማይባሉ፣ የፓርቲ ፕሮግራምና ፍላጎት ጥያቄ የማያስነሱ ግን በተናጠል የማይመለሱ ናቸውና በነዚህ ጥያቄዎች ዙሪያ ያለቅድመ ሁኔታ እንድንሰባሰብ ፤

3/የሲቪል ማኅበረሰብ አባላት ጥያቄዎቻችን ከፖለቲካ ጥያቄ ባሻገር የአገር-አድን ፣የህዝብ መድህንነት አጀንዳ ናቸውና በሁሉም መድረኮች፣ በሙሉ አቅማችሁ ከጎናችን እንድትሰለፉ፤

4/የአገሪቱና ህዝቦቿ ወዳጅ ቀጠናዊ.አህጉራዊና ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶችና ወዳጅ አገራት ከጎናችን በመቆም ለዲሞክራሲና ዘላቂ ሠላም ለምናደርገው ትግል ተገቢውን ህጋዊና ዲፕሎማሲያዊ የትግል አጋርነታችሁን በተግባር እንድታሳዩን ፣አፍራሽ ጣልቃ ገቦችም እጃችሁን እንድትሰበስቡ፤... አበክረን እንጠይቃለን፡፡

በመጨረሻም ገዢው ፓርቲ /መንግሰት የህግ የበላይነትን ማስከበር፣የአገር ሠላምና መረጋጋት ማስፈን ቀዳሚና ዋና ተግባርና ኃላፊነትህ መሆኑን ተገንዝቦ፣ የውጪ ደጋፊዎችን አፍራሽ ድርጊት ራሱን አግልሎ፣ ከተያያዘው የጥፋት አቅጣጫ እንዲታረም/እንዲመለስና ለጥሪያችን አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ አካታች፣ .አሳታፊ፣ ተዓማኒና ተቀባይነት ያለው ከሃቀኛ ብሄራዊ መግባባትና ድርድር የሚመነጭ መፍትሄ እንዲዘጋጅ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

የተባበረ ትግል ያሸንፋል//
የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎቸ ኮክሰ /ኮከስ/

21/2017ዓ.ም፣ አዲስ አበባ።

ፋኖ ይሄንን አዲስ የጦር መሳሪያ ከየት አገኘው?
26/07/2025

ፋኖ ይሄንን አዲስ የጦር መሳሪያ ከየት አገኘው?

ፕሬዝደንት ኢሳያስ ኢትዮጵያ 'ከጠብ አጫሪነት ይልቅ በውስጥ ችግሮቿ ላይ ታተኩር' ሲሉ ተናገሩየኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከአገራቸው ጋር ውዝግብ ውስጥ የገባችው ጎረቤታቸው ኢትዮጵ...
24/07/2025

ፕሬዝደንት ኢሳያስ ኢትዮጵያ 'ከጠብ አጫሪነት ይልቅ በውስጥ ችግሮቿ ላይ ታተኩር' ሲሉ ተናገሩ

የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከአገራቸው ጋር ውዝግብ ውስጥ የገባችው ጎረቤታቸው ኢትዮጵያ ከምታሰማው የጠብ አጫሪነት ንግግር ተቆጥባ በአንገብጋቢ የውስጥ ችግሮቿ ላይ ታተኩር ሲሉ ተናገሩ።
ፕሬዝደንቱ ይህንን የተናገሩት ትናንት ረቡዕ ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም. ከአገራቸው ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢው ጋር ባደረጉት ሁለተኛ ክፍል ቃለ ምልለሳቸው ነው።
ባለፈው ቅዳሜ በቀረበው ክፍል አንድ ላይ በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ስላለው ውዝግብ አንስተው የነበረ ሲሆን፣
ፕሬዝደንቱ በዚሁ ንግግራቸው ኢትዮጵያን በመጥቀስ ጠብ አጫሪ ንግግሮችን ከመስማት ይልቅ አንገብጋቢ የውስጥ ችግሮቿን ለመፍታት ትኩረት እንድታደርግ በድጋሚ አሳሰበዋል።
ፕሬዝደንቱ በመጀመሪያው ክፍል ቃለ ምልልስ ላይም ኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግሥታት የላከችውን ደብዳቤ ጠቅሰው "አስገራሚ የውሸት ክስ" በማለት ማጣጣላቸው ይታወሳል።

ትናንት ረቡዕ ምሽት በተላለፈው ምልልሳቸው ላይም አገራቸው የጦርነት ፍላጎት እንደሌላት ተናግረዋል። የአዲስ አበባው መንግሥት ሌሎች ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮች አሉት፤ መስራት ከፈለገ። ማስቀደም ያለበት ጉዳይ ትቶ አላስፈላጊ ነገር ውስጥ ገብቶ አለመረጋጋት የሚፈጥርበት ምክንያት ምንድን ነው? አያስፈልግም" ሲሉም ተደምጠዋል።
በዚሁ ቃለ ምልልሳቸው ላይ "ኤርትራን መወንጀል ሌላ ጣጣ ማምጣት ነው" ያሉት ፕሬዝደንቱ "የከፋ ውጤት ከመጣ ማቆም አይቻልም። አሁኑኑ አስቁሙ" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል

ፕሬዚዳንቱ "ዲፕሎማሲ . . . በአጋጣሚዎች ድግስ ላይ ስትገናኝ ሰላም ሰላም ስለተባባልክ፣ ፎቶግራፍ ስለተነሳህ አይደለም። እንደዚህ ያሉ አደጋዎች ሲመጡ አይሆንም፤ አያስፈልግህም ስትል፣ እዚህ ላይ ነው ዲፕሎማሲ መስራት ያለብህ" ብለዋል።
ኤርትራ ጦርነት ለማድረግ እየተዘጋጀች ነው የሚለውን ክስ በመጥቀስም "ስም ማጥፋት ነው። ዋሽተህ ማሳሳት የለብህም። ነገ ሌላ ችግር ሲመጣ፣ ያን ችግር ማጋነን ተገቢ አይደለም። ችግር ሳይመጣ ግን ማስቆም አለብህ" ብለዋለ።
ይሄ ሁሉ ቀጣናውን እያመሰች ያለችውን ኤማሬትስ ነች ሲሉ የከሰሱት ፕሬዝደንቱ፣ "ከኤምሬትስ በየቀኑ ወደ ኢትዮጵያ እየተጓዘ ያለውን መሳሪያ እያየን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
"ይሄ በባሕር ሳቢያ እየተባለ ያለውን የብልጽግና አጀንዳ አይደለም" ሲሉ የተናገሩት የኤርትራው ፕሬዝደንት "ሥራቸውን መሥራት አለባቸው" ብለዋል።
ፕሬዝደንቱ ሌሎች ቀጣናውን ይበጠብጣሉ በማለት እስራኤልን፣ ፈረንሳይን እና አሜሪካንንም ከስሰዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ፍላጎቷን ይፋ ካደረገች በኋላ ተሻሽሎ የነበረው የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት ሻክሮ አሁን ወደ መካሰስ ደርሷል።
ሁለቱ አገራት አገራት መካከል የሚሰማው መካሰስ እና የቃላት ልውውጥ ወደ ግጭት ሊያመራ ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል። አንዳንድ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት በሁለቱም ወገን ወታደራዊ ዝግጅት እየተካሄደ ነው።

Via BBC

ዜና፡  #ኢትዮጵያ በከፍተኛ ደረጃ ከአይኤምኤፍ ከተበደሩ 10 የአፍሪካ ሀገራት ተርታ መመደቧ ተጠቆመአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) በከፍተኛ ደረጃ ብድር ከሰጣቸው 10 የአፍሪ...
23/07/2025

ዜና፡ #ኢትዮጵያ በከፍተኛ ደረጃ ከአይኤምኤፍ ከተበደሩ 10 የአፍሪካ ሀገራት ተርታ መመደቧ ተጠቆመ

አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) በከፍተኛ ደረጃ ብድር ከሰጣቸው 10 የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ ተገለጸ። በተያዘው አመት 2017 ዓ.ም ሐምሌ ወር ላይ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ብድር ከአይኤምኤፍ እንደምታገኝም ተጠቁሟል።

እንደ አፍሪካን ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘገባ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የአይኤምኤፍ ብድር እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ አንድ ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ተጠግቷል፤ ከአፍሪካ በሰባተኛ ደረጃ ተቀምጣለች።

ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት አለምአቀፉ የገንዘብ ተቋም ብድር እያገኙ ያሉት በውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ መተንፈስ ያቃተውን ኢኮኖሚያቸውን ትንፋሽ እንዲቀጥል ለማድረግ ነው በሚል መሆኑን የጠቆመው አፍሪካን ቢዝነስ ኢንሳይደር ድረገጽ ይሁን እንጂ ከፍተኛ የአይኤምኤፍ ዕዳ የረዥም ጊዜ መዘዞች ይዞ በመምጣት በአህጉሪቱ ላይ ስጋት እየፈጠረ ይገኛል ሲል አመላክቷል።

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16/ 2017 ዓ/ም፦ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) በከፍተኛ ደረጃ ብድር ከሰጣቸው 10 የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ ተገለጸ። በተያዘው አመት ...

09/07/2025

ዜና

መቃ ላይ የተሰማራው የመከላከያ ሠራዊት ዛሬም የከተማውን ሕዝብ በከፍተኛ ደረጃ ማስፈራራቱን ተያይዞታል።

"ታጣቂው የወሰደብንን መሳሪያ አንድም ሳይቀር ካሉበት ሄዳችሁ ካላመጣችሁ፣ ከተማውን እናወድመዋለን፣ እናንተንም እንገድላችኋለን" እያለ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ሕብረተሰቡም፣ "ታጣቂው ሃይል ታጣቂ እንጂ ሕዝብ አይደለም፣ በተለያዩ ጊዜያት እኛንም ሲገድለን ነው የነበረው፣ እራሳች ያሉበት ድረስ ሄዳችሁ ቀሙዋቸው እንጂ እኛን ተውን" እያለ ይገኛል።

የመከላከያው ወታደር በተደጋጋሚ ፋኖው ጥቃት እያካሄደበት መሳሪያውን ሲማርከው "ለምን የአማራውን ሕዝብ መሣሪያ ካላስመለሳችሁ አላለም?" የሚሉ ወገኖች በበኩላቸው፣ ይሄን እያደረጉ ያሉት በከላከያው ውስጥ ያሉ የአማራ ጽንፈኞችና ሙሰኞች ናቸው ብለዋል።

በታጋዮች በኩል "እና የወሰድነው መሳሪያ የለም፣ ይልቁን ሕዝባችን ባያንገላቱት መልካም ነው" የሚል መልስ ተሰጥቱዋል።

Address

Lalibela

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Agew Unity Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Agew Unity Press:

Share

አገውነት!!

ዓላማችን አገውነቱን በልቡ ከትቦ፣ ለወግና ባህሉ፣ ለታሪኩና ማንነቱ ዘብ የቆመና ራሱን በራሱ የሚያስተዳድር አዲስ የአገው ትውልድ መፍጠር ነው!! ፔጁን "Like" ስላደረጉ እናመሰግናለን!!