Agew Unity Press

Agew Unity Press Voice for the Voiceless!
(1)

13/03/2026

እውነትኛ ፍቅር❤

27/02/2026

እናት ውለታዋ ❤

ኤርትራ ሰራዊቷን በአስቸኳይ ከግዛቴ ታስወጣ ስትል ኢትዮጵያ ጠየቀች---------አውራምባ ታይምስ [አዲስ አበባ] - የኤርትራ ሰራዊት የኢትዮጵያን ሉአላዊ ግዛት በመጣስ በሰሜን ምስራቅ አቅጣ...
08/02/2026

ኤርትራ ሰራዊቷን በአስቸኳይ ከግዛቴ ታስወጣ ስትል ኢትዮጵያ ጠየቀች
---------
አውራምባ ታይምስ [አዲስ አበባ] - የኤርትራ ሰራዊት የኢትዮጵያን ሉአላዊ ግዛት በመጣስ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ ግልጽ ወረራ ፈጽሞብኛል ሲል የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የተጻፈውና ለኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳላህ በተላከው በዚህ ደብዳቤ፣ የኤርትራ ሰራዊት የኢትዮጵያን ሉአላዊ ግዛት በመጣስ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ ግልጽ ወረራ መፈጸሙንና እዛ ከሚገኙ በደብዳቤው ላይ በስም ካልተጠቀሱ ታጣቂዎች ጋር ወታደራዊ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሚገኝ በደብዳቤው ጠቅሷል።

"የሁለቱን ሀገራት የጋራ ብሔራዊ ጥቅምን ባስከበረ መልኩ በላቀ የመከባበር ስሜት ለመመካከር ዝግጁ ነን" ያለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ፣ አሁን በኤርትራ በኩል የተከፈተው ትንኮሳ ግን በምንም መመዘኛ ቅቡልነት የሌለው መሆኑን በማብራራት "ኤርትራ ሰራዊቷን በአስቸኳይ እንድታስወጣና ለሰላማዊ ድርድር ዝግጁ እንድትሆን በይፋ እንጠይቃለን" ሲል በአጽንኦት ይጠይቃል።

ለግማሽ ምዕተ አመት ያህል ሁለቱም አገራት በማያባራ ግጭት ላይ እንደኖሩ የሚያብራራው ደብዳቤው ይህ አይነቱ የግጭት አዙሪት በውይይትና በዲፕሎማሲያዊ ጥረት እልባት ሊያገኝ የሚችልበት እድል እንዳለ በመግለጽ በኤርትራ በኩል በጎ ምላሽ ከተገኘ የኢትዮጵያ መንግስት ልዩነቶችን በሰላማዊ ድርድር ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን ያብራራል።

በኤርትራ መንግስት በኩል እስካሁን ለዚህ ደብዳቤ የተሰጠ ይፋዊ ምላሽ የለም።

አገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ይቋቋማል !የአገው ክልል የመሆን ጥያቄ ከአማራ ክልል ጋር ግጭት ለመፍጠር ሳይሆን ሰፋ ያለ አብሮነትን ለመገንባት ያለመ ነው። ይህ ጥያቄ የአገውን ህዝብ እራሱ...
02/02/2026

አገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ይቋቋማል !

የአገው ክልል የመሆን ጥያቄ ከአማራ ክልል ጋር ግጭት ለመፍጠር ሳይሆን ሰፋ ያለ አብሮነትን ለመገንባት ያለመ ነው። ይህ ጥያቄ የአገውን ህዝብ እራሱን በራሱ እንዲያስተዳድር የራሱን እጣ ፈንታ እንዲወስን እና በአገራዊ እንዲሁም በቀጠናዊ ልማት ውስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲኖረው ያለመ ነው።

አገው የራስ ገዝ አስተዳደር እና አብሮነት

አገው የራሱን ክልል እንዲያቋቁም የሚጠየቀው ጥያቄ ከጎረቤት ክልሎች ጋር ለመጋጨት ሳይሆን ህዝቦች በጋራ እንዲለሙና በሰላም እንዲኖሩ የሚያስችል ነው። ይህ ማለት አገው እንደ አንድ ክልል ሲቋቋም ከሌሎች ክልሎች ጋር ያለውን ትስስር አቋርጦ አይደለም። ይልቁንም የራሱ የሆነ የአስተዳደር መዋቅር ሲኖረው የራሱን ሀብትና ጉልበት በብቃት በመጠቀም ለራሱ እድገት ብቻ ሳይሆን፣ ለጎረቤት ክልሎችና ለአገርም ጭምር አስተዋጽኦ ያደርጋል ማለት ነው።

በጋራ የመልማትና የመኖር ፋይዳ

* ሀብት አጠቃቀም አገው የራሱን ክልል ሲያቋቁም የተፈጥሮ ሀብቱንና የሰው ኃይሉን በብቃት በመጠቀም፣ የራሱን ኢኮኖሚ ማሳደግ ይችላል። ይህ ደግሞ በዙሪያው ያሉ ክልሎችንም ተጠቃሚ ያደርጋል።

* የህዝቦች ተሳትፎ የአገው ህዝብ በራሱ ክልል ውስጥ በመሰባሰብ የልማት ውጥኖችን በቀጥታ በማቀድና በመተግበር የአካባቢውን ችግሮች ለመፍታትና የህዝቡን ፍላጎት ለማሟላት የተሻለ አቅም ይኖረዋል።

* ሰላማዊ ትብብር ይህ ጥያቄ የግጭት ምንጭ ሳይሆን ለሰላም መረጋጋትና መከባበር መሠረት ይጥላል። እያንዳንዱ ክልል የራሱን ማንነትና አስተዳደር ሲያገኝ እርስ በርስ የሚደረገው ትብብርና መከባበር ይጠናከራል።

* አገር አቀፍ ልማት የአገው ክልል መቋቋም፣ የአጠቃላይ የአገር አቀፍ ልማት አካል ነው። እያንዳንዱ የሀገሪቱ ክፍል በራሱ አቅም ሲጠነክር አጠቃላይ የሀገሪቱ እድገትና ብልጽግና ይረጋገጣል።

በአጠቃላይ የአገው ክልል የመሆን ጥያቄ የህዝቦች የራስን በራስ የማስተዳደር መብትና ሰፋ ያለ አብሮነትን የሚያንፀባርቅ ነው። ይህ ጥያቄ እርስ በርስ በመከባበርና በጋራ በመስራት ለሁሉም ተጠቃሚነት የሚበጅ ሰላማዊና የበለፀገች ሀገር ለመገንባት አስተዋፅኦ ያደርጋል።

"አብሮነት በጭቆና ቀንበር አይገለፅም"
"የአገው ህዝብ እምቢ የሚለው ለጭቆና እንጂ አብሮ ለመኖር አይደለም"

ኢትዮጵያ ትቅደም!!
አገው ኢትዮጵያ !!

Via:- ባዬ ጌታሁን ዘ- ብሄረሰብ አገው።

ነብስህ በሰላም ትረፍ‼️💔
16/01/2026

ነብስህ በሰላም ትረፍ‼️💔

21/11/2025

"በኢትዮጵያ የፀጥታ እና የፖለቲካ ጥያቄዎች መልስ ካላገኙ ቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ምርጫ ሊሆን አይችልም!"
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
©ዶቼ ቬለ

ዛሬም የቀጠለው የዩኒቨርስቲዎች ተቋውሞ ‼️የኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስትር ከመጭው አመት ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ  ለማድረግ ያቀደው አስገዳጅ መመሪያ ተቃውሞ እን...
18/11/2025

ዛሬም የቀጠለው የዩኒቨርስቲዎች ተቋውሞ ‼️

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስትር ከመጭው አመት ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ያቀደው አስገዳጅ መመሪያ ተቃውሞ እንደገጠመው ተገልጿል።

የትምህርት ሚንስትር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የ3ኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ፣ ለአንድ ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው መመሪያ ከመጭው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ እንዳለው አሳውቆ ነበር።

© Ras Alaya's View

የጋምቤላ ተቃውሞ‼በዛሬው ዕለት የጋምቤላ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የአደባባይ ተቃውሞ አካሂደዋል። ከፖሊስ ጋር በተፈጠረ ግጭት ሁለት ተማሪዎች በጥይት ተመተው ሆስፒታል ገብ...
14/11/2025

የጋምቤላ ተቃውሞ‼
በዛሬው ዕለት የጋምቤላ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የአደባባይ ተቃውሞ አካሂደዋል። ከፖሊስ ጋር በተፈጠረ ግጭት ሁለት ተማሪዎች በጥይት ተመተው ሆስፒታል ገብተዋል።

ወደ ውጪ አገር እልካለሁ በማለት ከ700ሺ ብር በላይ ያታለለች ክስ ተመሰረተባት‼️-----------------------------------ወደ ውጪ ሀገር እልካለሁ በማለት ሁለት ሰዎችን ከ70...
14/11/2025

ወደ ውጪ አገር እልካለሁ በማለት ከ700ሺ ብር በላይ ያታለለች ክስ ተመሰረተባት‼️
-----------------------------------
ወደ ውጪ ሀገር እልካለሁ በማለት ሁለት ሰዎችን ከ700ሺህ ብር በላይ ያታለለች ግለሰብ ላይ ክስ መመስረቱን የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ ።

ተጠርጣሪዋ እሌኒ በላይ የምትባል ሲሆን የግል ተበዳዮችን ወደ ወጪ ሀገር እልካችኋለሁ በማለት ያታለለችው በተለያየ ቀን እና ሰዓት በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 9 መተባበር ህንጻ እና ወረዳ 8 ስሪ ኤም ህንጻዎች አካባቢ በመቅጠር መሆኑን የምርመራ መዝገቡ ይገልጻል ።

ተጠርጣሪዋ አንደኛዋን የግል ተበዳይ ያታለለቻት ወደ እስራኤል ሀገር እልክሻለሁ በማለት ከክፍለ ሀገር አዲስ አበባ ካስመጣችት በኋላ ለቪዛ እና ለሂደቱ ማስጨረሻ በሚል ምክንያት 250 ሺህ ብር በካሽ እንድትሰጣት እና 2መቶ ሺህ ብር በባንክ በአካውንት እንድታስገባላት ማድረጓን በምርመራ መዝገቡ ተገልፆል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግለሰቧ ተመሳሳይ የማታለል ዘዴን ተጠቅማ ሌላኛዋን የግል ተበዳይ ወደ ኒውዚላንድ ለመላክ ተስማምታ ከኢትዮጵያ ቀጥታ መሄድ ስለማይቻል በቅድሚያ ለአረብ ኢሚሬትስ በ320 ሺህ 173 ብር C.P.O አሰርታ በመቀበል ትሰወራለች የተጠርጣሪዋ መሠወር ያስደነገጣት የግል ተበዳይ ለየካ ክ/ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጉዳዩ እንዳሳወቀችና ፖሊስ መረጃው እንደደረሰው ግለሰቧን አፈላልጎ በመያዝ ተገቢውን ምርመራ በማጣራት መዝገቡን ለዓቃቤ ህግ ልኮ ክስ የተመሰረተባት መሆኑን ፖሊስ መምሪያው አስታውቋል፡፡

ወደ ውጪ ሀገር ሄዶ የመስራት ፍላጎት ያለው ማንኛውም ሰው ህጋዊ ፈቃድ ካለው አካል ተገቢውን መስፈት በማሟላት እና በህጋዊ መንገድ ብቻ መጨረስ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን በማስተላለፍ እንደዚህ አይነት የማታለል ወንጀል የተፈጸመባቸው ግለሰቦች ካሉ ወደ የካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመቅረብ ተጠርጣሪዋን አይተው በማረጋገጥ ተጨማሪ መረጃ እንዲሆኑ ጥሪውን አስተላልፏል።

አዲስ አድማስ

Address

Lalibela

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Agew Unity Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Agew Unity Press:

Share

አገውነት!!

ዓላማችን አገውነቱን በልቡ ከትቦ፣ ለወግና ባህሉ፣ ለታሪኩና ማንነቱ ዘብ የቆመና ራሱን በራሱ የሚያስተዳድር አዲስ የአገው ትውልድ መፍጠር ነው!! ፔጁን "Like" ስላደረጉ እናመሰግናለን!!