Bilal Edris

Bilal Edris اللهم اصلح لي شآني كله ولا تكلني إلا نفسي
طرفت عيني ��
الحمد لله

11/04/2025

የእለት ተእለት ኑሯችን ውስጥ ድንገት የሚመጡብን (መቼ እንደሚመጡ የማናውቃቸው) ነገሮች አሉ። ለምሳሌ:- ረሀብ መቼ እንደሚርበን አናውቀውም ፣ መቼ እንደሚጠማን ፣ ሽንት መቼ እንደሚመጣን ፣ እንቅልፍም መቼ እንደሚይዘን ፣ በሽታም መቼ እንደሚያመን ....ብዙ ብዙ ነገሮች መቼ እንደሚመጡ አናውቅም። ህይወታችን በህይወት መስተጋብራችን በየቀኑ በምናከናውናቸው ድርጊቶች ሰርፕራይዞቻቸው የተሞላ ነው በተለይ በተለይ ደግሞ በዋናነት #ሞት መቼ ደርሶብን እንደሚይዘን የማናውቀው ትልቁ ድንገታዊ እንግዳችን ነው።

ከላይ የጠቀስናቸው ድንገት የሚይዙን ነገሮች ሁሉ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ የምንችልባቸው ናቸው። ለረሀባችንም ፣ ለጥማችንም ፣ለእንቅልፋችንም ፣ ለበሽታም ለሌሎቹም ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንችላለን። ነገር ግን እነዚህ ነገሮች ሁሉ በዱንያ ላይ ቀሪ የሆኑ የዱንያ ሀጃዎች መሆናቸው ክፋታቸው እና ዱብዳቸው ያን ያህል ነው።

ሞት ግን....ሞት ግን የኋለኛውን አለም የዘላለም ህይወትን ጉዳይ ማሰሪያ መቋጫ የተከረቸመ መዝጊያ በር ነው። ለዛም ነው ታላቁ ጌታችን አላህ ﷻ ሞት ደርሶ የዱንያ ቆይታችንን ከማገባደዳችን በፊት በቻልነው አቅም መዘጋጀት እንዳለብን የሚነግረን።

وَٱعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ ٱلْيَقِينُ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
(14 : 99)

كُلُّ نَفْسٍۢ ذَآئِقَةُ ٱلْمَوْتِ ۗ وَنَبْلُوكُم بِٱلشَّرِّ وَٱلْخَيْرِ فِتْنَةًۭ ۖ وَإِلَيْنَا تُرْجَعُونَ
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ለመፈተንም በክፉም በበጎም እንሞክራችኋለን፡፡ ወደኛም ትመለሳላችሁ፡፡
(20 : 35)

كُلُّ نَفْسٍۢ ذَآئِقَةُ ٱلْمَوْتِ ۗ وَإِنَّمَا تُوَفَّوْنَ أُجُورَكُمْ يَوْمَ ٱلْقِيَٰمَةِ ۖ فَمَن زُحْزِحَ عَنِ ٱلنَّارِ وَأُدْخِلَ ٱلْجَنَّةَ فَقَدْ فَازَ ۗ وَمَا ٱلْحَيَوٰةُ ٱلدُّنْيَآ إِلَّا مَتَٰعُ ٱلْغُرُورِ
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ምንዳዎቻችሁንም የምትሞሉት በትንሣኤ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከእሳትም የተራቀና ገነትን የተገባ ሰው በእርግጥ ምኞቱን አገኘ፡፡ ቅርቢቱም ሕይወት የመታለያ መሳሪያ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
(2 : 185)

እነዚህን እና ሌሎች ብዙ በዱንያ ህይወታችሁ ለፈጠርኳችሁ አላማ ኑሩ የሚሉ ብዙ የቁርአን አያዎችን መጥቀስ ይቻላል። በዱንያ ግርግር በተዘናጋንበት ወቅት ድንገት ሞት ከያዘን መመለሻ ወደሌለው አለም ከተገባ ፀፀት እና ለቅሶ የጉም ላይ ስዕል ብቻ ነው።

حَتَّىٰٓ إِذَا جَآءَ أَحَدَهُمُ ٱلْمَوْتُ قَالَ رَبِّ ٱرْجِعُونِ
አንዳቸውንም ሞት በመጣበት ጊዜ እንዲህ ይላል «ጌታዬ ሆይ! (ወደ ምድረ ዓለም) መልሱኝ፡፡
(22 : 99)

وَلَيْسَتِ ٱلتَّوْبَةُ لِلَّذِينَ يَعْمَلُونَ ٱلسَّيِّـَٔاتِ حَتَّىٰٓ إِذَا حَضَرَ أَحَدَهُمُ ٱلْمَوْتُ قَالَ إِنِّى تُبْتُ ٱلْـَٰٔنَ وَلَا ٱلَّذِينَ يَمُوتُونَ وَهُمْ كُفَّارٌ ۚ أُو۟لَٰٓئِكَ أَعْتَدْنَا لَهُمْ عَذَابًا أَلِيمًۭا
ጸጸትንም መቀበል ለእነዚያ ኀጢአቶችን ለሚሠሩ አንዳቸውንም ሞት በመጣበት ጊዜ «እኔ አሁን ተጸጸትኩ» ለሚልና ለነዚያም እነርሱ ከሓዲዎች ኾነው ለሚሞቱ አይደለችም፡፡ እነዚያ ለእነሱ አሳማሚን ቅጣት አዘጋጅተናል፡፡
(3 : 18)

አላህ በቀሪው የዱንያ ሀያታችን ለአኸራ ስንቅ የምንሰንቅ ታታሪ ባሮች መካከል አላህ ያድርገን።

ማሜ አላህ ይዘንልህ አላህ ቀብርህን ሰፋ አድርጎ በጀነት ኑር ያብራልህ። ከውዱ ነብይ ረሱል ﷺ በጀነተል ፊርደውስ ጎረቤት ያድርግህ።

✍️ Bilaluna

https://t.me/Xuqal

የሸዋል ዒድ (ትንሹ ዒድ)~በኢስላም አመታዊ ዒዶቻችን ሁለት ናቸው። ማስረጃውም አነስ ብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ ያስተላለፉት ሐዲሥ ነው። ነብዩ ﷺ መዲና ሲመጡ ነዋሪዎቿ የሚጫወቱባቸው ሁለት ...
04/04/2025

የሸዋል ዒድ (ትንሹ ዒድ)
~
በኢስላም አመታዊ ዒዶቻችን ሁለት ናቸው። ማስረጃውም አነስ ብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ ያስተላለፉት ሐዲሥ ነው። ነብዩ ﷺ መዲና ሲመጡ ነዋሪዎቿ የሚጫወቱባቸው ሁለት ቀናት ነበሯቸው። “ምንድን ናቸው እነዚህ ሁለት ቀናት?” ብለው ጠየቁ። “በጃሂሊያው ጊዜ እንጫወትባቸው ነበርን” አሉ። በዚህን ጊዜ የአላህ መልእክተኛ ﷺ “የላቀው አላህ ከነሱ በላጭ በሆኑ ሁለት ቀናት ተክቶላችኋል። እነሱም የአድሓ ቀንና የፊጥር ቀን ናቸው” አሉ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1039]

“ተክቶላችኋል” የሚለው አነጋገር የሙስሊሞች ዒዶች የተወሰኑና፣ በሸሪዐ የሚደነገጉ እንደሆኑ ጥቆማ ይሰጣል። የሰለፎቻችን አካሄድም ይህን ግንዛቤ ይበልጥ ያጠነክራል። ኋላ ላይ እንግድ ቢድዐዎች እስከሚመጡ ድረስ ነብዩ ﷺ ከደነገጓቸው ዒዶች ውጭ ሌላ ዒድ አልተንፀባረቀም። በተለይም ደግሞ ነብዩ ﷺ “ከሰው ሁሉ በላጩ የኔ ትውልድ ነው። ከዚያም ከእነሱ ቀጥለው የሚመጡት፤ ከዚያም ከነሱ ቀጥለው የሚመጡት” ብለው ምስክርነት የሰጡት ሶስቱ ወርቃማ ዘመን ውስጥ እንዲህ አይነት ነገር አልነበረም።

ኋላ ላይ ከመጡ እንግዳ በዓላት ውስጥ አንዱ ታዲያ የሸዋል ዒድ የሚባለው ቢድዐ ነው። ይሄ በአል በሸሪዐ ቦታ ቢኖረው ኖሮ በቁርአንና በሐዲሥ ውስጥ ይጠቀስ ነበር። ቁርአንና ሐዲሥ ውስጥ ከሌለ፣ ቀደምቶች ካላወቁት ቢድዐ ከመሆን ውጭ ሌላ ምርጫ የለም። ነብዩ ﷺ “ወደ ጀነት የሚያቀርባችሁና ከእሳት የሚያርቃችሁ ሆኖ በእርግጠኝነት የነገርኳችሁ ቢሆን እንጂ የተውኩት ነገር የለም” ብለዋል። [አሶሒሐ፡ 4/416]

ይሄ የሸዋል ዒድ የተወገዘ ቢድዐ እንደሆነ ዑለማኦች ይናገራሉ። አንድ ሁለቱን ልጥቀስ፦

1- ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡-

وأما اتخاذ موسم غير المواسم الشرعية كبعض ليالي شهر ربيع الأول التي يقال: إنها ليلة المولد, أو بعض ليالي رجب, أو ثامن عشر ذي الحجة, أو أول جمعة من رجب, أو ثامن من شوال الذي يسميه الجهَّال عيد الأبرار: فإنها من البدع التي لم يستحبها السلف , ولم يفعلوها.
"ሸሪዐዊ ያልሆኑ ክብረ በዓላትን ክብረ-በዓል አድርጎ መያዝ ግን ‘የመውሊድ ሌሊት’ የሚባሉትን የተወሰኑ የረቢዐል አወል ሌሊቶችን ወይም የረጀብ ሌሊቶችን ወይም ደግሞ ዙልሒጃ አስራ ስምንትን ወይም ደግሞ የረጀብ የመጀመሪያ ጁሙዐን ወይም ደግሞ መሃይማን 'የደጋጎች ዒድ' እያሉ የሚጠሩትን የመሰሉ እነዚህ ሰለፎች እንደሚወደዱ ያልገለጿቸውና ያልተገበሯቸው #ቢድዐዎች ውስጥ ናቸው።” [መጅሙዑል ፈታዋ፡ 25/298]

በተጨማሪም እንዲህ ብለዋል፦
وأما ثامن شوال : فليس عيداً لا للأبرار ولا للفجار , ولا يجوز لأحد أن يعتقده عيداً, ولا يحدث فيه شيئاً من شعائر الأعياد
"ሸዋል ስምንትን በተመለከተ ለደጋጎችም ይሁን ለባለ -ጌዎች ዒድ አይደለም። ለማንም ቢሆን ዒድ አድርጎ ሊያምንበት አይፈቀድም። በሱ ውስጥ የትኛውም የበዓላት መገለጫዎች ሊንፀባረቁበት አይገባም።" [አልኢኽቲያራቱል ፊቅሂያህ፡ 199]

2- ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲሰላም ኸዲር አሹቀይሪይ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡-

ويكون الاحتفال بهذا العيد في أحد المساجد المشهور فيختلط النساء بالرجال ويتصافحون ويتلفظون عند المصافحة بالألفاظ الجاهلية, ثم يذهبون بعد ذلك إلى صنع بعض الأطعمة الخاصة بهذه المناسبة
"ይሄ ዒድ የሚከበረው ከታዋቂ መስጂዶች ውስጥ በአንዱ ይሆናል። ከዚያ ሴቶች ከወንዶች ጋር ይቀላቀላሉ። በሰላምታ ይጨባበጣሉ። ሲጨባበጡም የጃሂሊያ ቃላትን ይናገራሉ። ከዚያም በኋላ ለዚህ ጊዜ የተለዩ የተወሰኑ የምግብ አይነቶችን ያዘጋጃሉ።" [አሱነኑ ወልሙብተደዓት፡ 166]

በመጨረሻም በአንድ ማሳሰቢያ ልዝጋ። የጉዳዩን ብይን የሚያሳዩ የሸሪዐ መሰረቶች እና የዑለማእ ንግግር እየተጠቀሰ አይኑ እያየ ልክ እኛ ከኪሳችን የተናገርን ይመስል "ሁሉን ነገር ቢድዐ አደረጋችሁብን" አይነት የአላዋቂዎች ተቃውሞ የሚያሰማ አካል ቦታ የለውም። እለቱን ዒድ አድርጎ መያዝ አይገባም ስለተባለ ዱንያ ሁሉ ቢድዐ እንደተባለ እያስመሰሉ ማቅረብም ራስን መሸወድ ነው። ሲጀመር በአንዳንድ አካባቢዎች ካልሆነ በስተቀር ይሄ ልማድ በብዙ ቦታዎች አይታወቅም። ይልቅ ከሙስሊም የሚያምረው ለማስረጃ እጅ መስጠት ነው።
=
https://t.me/Xuqal

የረመዳን 29 ኛዋ ሌሊት ምናልባትም የመጨረሻዋ ለይል ልትሆን ትችላለች የኢማም አሕመድ [ሙስነድ] የተሰኘው መጽሐፍ ላይ ከሰይዲና አቡሁረይራ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደተዘገበው የአላህ ነቢይ [...
29/03/2025

የረመዳን 29 ኛዋ ሌሊት

ምናልባትም የመጨረሻዋ ለይል ልትሆን ትችላለች
የኢማም አሕመድ [ሙስነድ] የተሰኘው መጽሐፍ ላይ ከሰይዲና አቡሁረይራ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደተዘገበው የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ አሉ: ‐«[በረመዳን] በመጨረሻው ሌሊት [ለህዝቦቼ] ሁሉ ምህረት ይደረግላቸዋል።»
ሰዎችም: ‐ «ለይለቱል‐ቀድር እርሷ ናት?» በማለት ጠየቁ።
እርሳቸውም: ‐ «በፍፁም! ነገርግን [ተቀጣሪ] ሠራተኛ ሥራውን ሲጨርስ ደመወዙ ይሰጠው የለ?!» በማለት መለሱ።»
:
አላህ ሆይ! ሥራዎቻችንን ውደድልን። በእዝነትህ ሸፍነህ ካለብን ክፍተት ጋር ረመዳናችንን ተቀበለን! 🤲

https://t.me/Xuqal

በኑ ኢስራኢሎች በግብፅ ከነበሩበት 450 ዓመታት ብዙውን በመከራና ባርነት ነበር ያሳለፉት።በተለይ ነቢይ ሙሳ ወደ ተላኩበት ዘመን የነበሩት የእስራኤል ልጆች ይደርስባቸው የነበረው እንግልትና ...
25/03/2025

በኑ ኢስራኢሎች በግብፅ ከነበሩበት 450 ዓመታት ብዙውን በመከራና ባርነት ነበር ያሳለፉት።በተለይ ነቢይ ሙሳ ወደ ተላኩበት ዘመን የነበሩት የእስራኤል ልጆች ይደርስባቸው የነበረው እንግልትና ግፍ የከፋ ነበር።የነቢ ሙሳን ተዓምራት ካዩ በኃላ ማመን ያልፈለጉ ጭፍን የፊርዓውን ተከታዮች ለፊርዓውን ለምን ዝም ትለዋለህ ነበር ያሉት:-

وَقَالَ الْمَلَأُ مِن قَوْمِ فِرْعَوْنَ أَتَذَرُ مُوسَىٰ وَقَوْمَهُ لِيُفْسِدُوا فِي الْأَرْضِ وَيَذَرَكَ وَآلِهَتَكَ ۚ قَالَ سَنُقَتِّلُ أَبْنَاءَهُمْ وَنَسْتَحْيِي نِسَاءَهُمْ وَإِنَّا فَوْقَهُمْ قَاهِرُونَ

ከፈርዖንም ሰዎች ታላላቆቹ (ለፈርዖን) «ሙሳንና ሰዎቹን በምድር ላይ እንዲያበላሹና (ሙሳም) አንተንና አማልክቶችህን እንዲተው ትተዋቸዋለህን» አሉ፡፡"

የፊርዓውንም ምላሽ ይህ ነበር:-
«ወንዶች ልጆቻቸውን እንገድላለን፡፡ ሴቶቻቸውንም እናስቀራለን፡፡ እኛም ከበላያቸው ነን፡፡ አሸናፊዎች (ነን)» አለ፡፡"

በኑ እስራኢሎች ከሙሳ በፊትም መከራ ውስጥ ነበሩ።ከአሏህ ዘንድ የተላከ ነፃ አውጪ ነቢያቸው መጥቶም ያ መከራ አልቀነሰም።እንደውም እጅጉኑ ነበር የበረታው።ይህን ያዩት ነቢይ ሙሳም ይህ የአሏህ ምድራዊ ሱነን(ህግጋት) እንደሆነ በመግለፅ ህዝባቸው እንዲታገስ ነበር የመከሩት።

قَالَ مُوسَىٰ لِقَوْمِهِ اسْتَعِينُوا بِاللَّهِ وَاصْبِرُوا ۖ إِنَّ الْأَرْضَ لِلَّهِ يُورِثُهَا مَن يَشَاءُ مِنْ عِبَادِهِ ۖ وَالْعَاقِبَةُ لِلْمُتَّقِينَ

"ሙሳ ለሰዎቹ፡- «ለአላህ ተገዙ ታገሱም፡፡ ምድር ለአላህ ናትና፡፡ ከባሮቹ ለሚሻው ያወርሳታል፡፡ ምሰጉንዋም ፍጻሜ ለጥንቁቆቹ ናት» አላቸው፡፡"

ህዝባቸው ግን ከአሏህ ዘንድ ይመጣል ብለው የጠበቁት ነፃ አውጪ ከነሱ ጋር ኖሮ ይህን ያክል መከራ ይበረታብናል ብለው ስላልጠበቁ ተማረው ነበር።ይህን ምሬታቸውን ትዕግስት ባጣ ስሜት ውስጥ ሆነው ከመግለፅም ወደኃላ አላሉም:-

قَالُوا أُوذِينَا مِن قَبْلِ أَن تَأْتِيَنَا وَمِن بَعْدِ مَا جِئْتَنَا ۚ
"«ከመምጣትህም በፊት ከመጣኽልንም በኋላ ተሰቃየን» አሉት፡፡"

ሰው ፍጠረቱ ነውን ችኩል ነው።ለፍርድ ይቸኩላል።የቆየበት መከራ እንዲነሳለት ካለው ፅኑ ፍላጎት የተነሳ ፤የጊዜያት መርዘም በፍጥነት ተስፋን ያስቆርጠዋል።በዚህ ጊዜ ከአሏህ የተላከለትና በመለኮታዊ ራዕይ የሚመራ ነፃ አውጪውን ሳይቀር ይጠራጠራል።ይተቻል።ይህን መቀየር እንደማይችሉም በመግለፅ የአሏህ ትዕዛዝ እንደሚመጣና ነፃ እንደሚሆኑ በመግለፅ ያፅናኑ ገቡ:-

قَالَ عَسَىٰ رَبُّكُمْ أَن يُهْلِكَ عَدُوَّكُمْ وَيَسْتَخْلِفَكُمْ فِي الْأَرْضِ فَيَنظُرَ كَيْفَ تَعْمَلُونَ

«ጌታችሁ ጠላቶቻችሁን ሊያጠፋ እንዴት እንደምትሠሩም ይመለከት ዘንድ በምድር ላይ ሊተካችሁ ይሻል» አላቸው፡፡

ታዲያ ነቢይ ሙሳ እንዳሉት የአሏህ ትዕዛዝ የመጣ ጊዜ፤ሲያማርሩ የነበሩት ሰዎች ናቸው ፊርዓውንና ሰራዊቱ ሲሰምጥ የተመለከቱት።ይህ የአሏህ ሱና ነው።ዛሬም ይኸው ሱናው በመተግበር ላይ ይገኛል።

https://t.me/Xuqal

21/03/2025

ኩንታ ኪንቴ የሶሐባ ዘር መሆኑን ታውቃላችሁ ጋይስ? ኩንታ ኪንቴ በ90ዎቹ የተሠራ የአሜሪካን የባርነት ሰቆቃ የሚያሳይ ፊልም ነው። በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ መሆኑ ይታወቃል። በፊልሙ የተወከለው ገጸባህሪ ኩንታ ደግሞ የሶሐባ ዘር መሆኑን አሌክስ ሄይሊ አጣርቷል። በጉዳዩ ላይ ከሸይኽ ዑመር ሱለይማን ጋር ቆይታ ያደረገው ሸይኽ ሙስጠፋ ብሪግስ የሚከተለውን ብሏል…

https://t.me/Xuqal

゚viralシfypシ゚viralシalシ

*ረመዷን ²⁰*ፈትሁል መካ የተደረገበት (መካ የተከፈተበት) ...ቀን ነው።ውዱ ነብይ ረሱሉል አሚን عليه افضل صلوات الله وسلامه عليه ወደ አላህ መንገድ በመጣራታቸው ምክኒያ...
19/03/2025

*ረመዷን ²⁰*

ፈትሁል መካ የተደረገበት (መካ የተከፈተበት) ...ቀን ነው።ውዱ ነብይ ረሱሉል አሚን عليه افضل صلوات الله وسلامه عليه ወደ አላህ መንገድ በመጣራታቸው ምክኒያት በግፍ ከተባረሩባት የትውልድ መንደራቸው መካ ከአመታት ቆይታ በሏላ ዳግም ድል አድርገው በድል ወደ መካ የተመለሱበት ቀን።

በተጨማሪም ኢንሻአላህ ነገ ሌሊት የተሀጁድ ሰላትን እነጀምራለን። ረሱል عليه افضل صلوات الله وسلامه عليه በረመዳን የመጨረሻው 10 ቀናቶች ውስጥ ለይለተል ቀድርን ጠብቁባቸው ካሏቸው ጎዶሎ ቀናቶች ውስጥ የመጀመሪያዋ ጎዶሎ ቀን የነገዋ ሌሊት ናት ያውም በ ለይለተል ጁሙአ። አላህ ለይለተል ቀድርን ይወፍቀን ረመዷን 20

ኢላሂ! መጠጊያችን፣ መሸሻችን፣ ብርሃናችን፣ መሪያችን፣ ደጋፊያችን…
ወንጀላችንን ማረን፤ ከውድቀታችን አንሳን፤ ከህመማችን ፈውሰን፤ ቃልኪዳንህን አድስልን፤ መንገዳችንን አቃናልን።
:
ኢላሃና!
በዲን፣ በዱንያ እና በአኸራ ጉዳያችን ላይ የሚያስጨንቀንን ሁሉ ገላግለን።
የሚጎዳንን፣ የሚያሰቃየንን፣ የሚያንገላታንን፣ የሚያስፈራንን፣ የሚያስቆጨንን፣ የሚያስተክዘንን ነገር ሁሉ አንተው ጠብቀን አንተው ፈርጀን።
ኢላሃና!
በሐላልህ ከሐራምህ ጠብቀን። በችሮታህም ካንተ ውጪ ከማንም ከመከጀል ሰውረን።
ኢላሂ! ከበዳዮች በደል ጠብቀን!

bilaluna

ረመዷን ¹⁸ረመዷን ሙባረክ ተባብለን ሳንጨርስ፣ ትናንት ከፊላችን ከፊሉን በመምጣቱ ተደስቶ እንዳላበሰረ ይኸው ከግማሽ አለፈ። አልፎም የመጨረሻዎቹ 10 ቀናት ውስጥ ልንገባ 2 ቀን ብቻ ቀረው።...
18/03/2025

ረመዷን ¹⁸

ረመዷን ሙባረክ ተባብለን ሳንጨርስ፣ ትናንት ከፊላችን ከፊሉን በመምጣቱ ተደስቶ እንዳላበሰረ ይኸው ከግማሽ አለፈ። አልፎም የመጨረሻዎቹ 10 ቀናት ውስጥ ልንገባ 2 ቀን ብቻ ቀረው።

ከኛ ውስጥ ቀዳሚው ስራው ላይ የጠነከረና በሚገባ የሰነቀው ነው። ተቅዋው ወደ መሸሻው አላህ ገፍቶ የወሰደው ነው።😭 አሁንም እንፍጠን አሕባብ፣ ይህ ወር የተቆጠሩ የእስትንፋሶች ጥርቅም ነውና በፍጥነት ያበቃል። ያለፈው ላይመለስ፣ የቀረውም ካለፈው የበለጠ ፈንታ የለውም። እንቻኮል አሕባብ ትትንፋሾቻችንን እንጠቀም።

ዙበይር ኢብነል ዐዋም (ረዐ) እንዲህ ይላሉ " ከናንተ ውስጥ የቻለ ድብቅ መልካም ስራ ይኑረው።"

"ድብቅ ሰናይ ተግባር" በሚስጥር የሚደረግ ማንኛውም መልካም ስራ ሲሆን፣ አላህ እንጂ ማንም የማያየው ነው።

- በጨለማ ውስጥ የምትሰግዳት ሰላት
- ቁርአንን እየቀሩ በብዛት ማኽተም
- ደብቀህ የምትሰጣት ሰደቃ
- ለቸገረው የምትደርሳት መፍትሄ
- ባል የሞተባትንና የቲሞችን መንከባከብህ
- ለወላጆች የምትውለው መልካምነት
- በሱሑር ሰዐት የምታደርገው ኢስቲግፋር
- ጀሊሉን አላህን በማውሳትና መፍራት የምታፈሰው ጠብታ እምባ
- በሁሉም ሁኔታ መልካም ኒያ ማድረግ

ከላይ ያየናቸው ሁሉ ሰው የማይደርስባቸው በልብ ጓዳ ውስጥ ተጠንስሰው የሚተገበሩ ናቸው። ድብቅ ሰናይ ስራ የእውነተና እምነትና ኢኽላስ መረጃዎች ናቸው። አንድ ባሪያ ወደ ጌታው አላህ ይቃረብባቸዋል፣ ለነፍሱም ለረዥም ጊዜ አስፈልጎቱ ይቆጥብበታል። የአላህ ጥላ እንጂ የማንም ጥላ በሌለበት ቀን ጥላ ይሆኑለታል።

የኻቲማ ማማር መልካም ስራን ደብቆ ከመስራት ፍሬዎች ነው። ድብቅ መልካም ስራዎች ለሸይጧን እጅግ ይከብዱታል። የርሱ ስራ ደግሞ የአንድን ባሪያ ስራ ከድብቅነት ወደ አውላላ ማውጣት አንዱ ወጥመዱ ነው። ከኢኽላስ መስመር ወደ ይዩልኝ፣ ሽርክ፣በራስ ወደ መገረም እና እውቅና ማጋለጥ ነው።

ሰለፎች አንድ ሰው ሚስትና ልጆች የማያውቁት ድብቅ መልካም ስራ ይኖረው ዘንድ ይመክራሉ። በድብቅ የምትሰራው መልካም ስራ በዚህ ረመዷን እንልመድ።

የረመዳን ወር በአግባቡ ለተጠቀመበት ሰው በአላህ ፍቃድ ያለፈ ወንጀሉ ሲታበስለት። በአግባቡ ያልተጠቀመበት፣ እራሱን ወደ አላህ እናወደ ኸይር ስራ ያልመለስ ሰው ደግሞ ከአላህ ራህመት የሚወጣበት ወር ነው።

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንደተናገሩት

"ከልብ በመነጨ እምነት እና ከአላህ ዘንድ ምንዳን ተስፋ በማድረግ የረመዳን ወር ጾምን ፤ የሚጾም የቀደሙት ትናንሽ ኃጢአቶቹ ሁሉ ይሰረዙለታል፡፡" [ሰሂህ አል ቡኻሪ 38]

በሌላ ዘገባ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦

"ከልብ በመነጨ እምነት እና ከአላህ ዘንድ ምንዳን ተስፋ በማድረግ በእሱ ውስጥ (በረመዳን ወር) በሌሊት የሚቆም ከዚያ በፊት የነበሩ ኃጢአቶቹ ሁሉ ይቅር ይባልለታል፡፡" [ቡኻሪ ዘግበውታል]

ኢብኑል ጀውዚ ረሂመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦

12ቱ ወሮች ፤ እንደ 12ቱ የያዕቁብ (ዐ.ሰ) ልጆች ናቸው፡፡ ዩሱፍ (ዐ.ሰ) ለያዕቆብ (ዐ.ሰ) በጣም የተወደደ ልጅ እንደነበረ ሁሉ። ረመዳንም በአላህ ዘንድ በጣም የተወደደ ወር ነው። ልክ አላህ በአንድ የዩሱፍ ዱአ አማካኝነት ፤ 11 ወንድሞችን ይቅር እንዳላቸው ሁሉ በአንድ የረመዳን ዱዓ ለ 11 ወሮች ይቅር ይላል፡፡

የረመዳን ወር መቶለት እራሱን ወደ አላህ እና ወደ ኸይር ስራ ሳይመልስ በአግባቡ ያልተጠቀመበት፣ ሰው ከአላህ ራህመት የወጣ ሰው ነው።

ረሱል (ሰ•ዐ•ወ) በሶስት ነገሮች ያልተጠቀመ ሰው ፤ ከአላህ ራህመት የወጣ ሰው ነው አሉ። እነሱም፦

1. ረመዳን መቶ ራሱን ወደ ከይር ስራ ያልመለሰ ሰው ነው፣
2. የኔ ስም ሲነሳ ሰለዋት የማያወርድ ሰው፣
3. እናትና አባቱ በህይወት እያሉ ያልተጠቀመባቸው ሰው ነው

የቀረችንን ጊዜ በአግባቡ እንጠቀማት
Bilaluna Edris Ah
https://t.me/Xuqal

ረመዷን - 17***በየዓመቱ ረመዷን 17ኛው ቀን ላይ ስንደርስ ታላቁ የበድር ጦርነት ይታወሰናል፡፡ ታላቁ ነቢይ ሶ.ዐ.ወ. በወጉ እንኳን  ያልታጠቁ በእግረኛ የተሞላ ሁለት ፈረሠኛ እና ሰባ ...
16/03/2025

ረመዷን - 17
***

በየዓመቱ ረመዷን 17ኛው ቀን ላይ ስንደርስ ታላቁ የበድር ጦርነት ይታወሰናል፡፡ ታላቁ ነቢይ ሶ.ዐ.ወ. በወጉ እንኳን ያልታጠቁ በእግረኛ የተሞላ ሁለት ፈረሠኛ እና ሰባ ግመል የያዘ በቁጥር 314 የሚሆን ሠራዊት በመያዝ በሶስት ዕጥፍ ከሚበልጣቸው በደንብ ከተደራጀና ከታጠቀ የጠላት ጦር ጋር ገጠሙ፡፡

በዚህ ቀን ነቢዩ ሶ.ዐ.ወ. አምላካቸዉን በዱዓ ለመኑ፣ ወተወቱ፣ ተማፀኑ፡፡ ይህችን ጥቂት ጭፍራ በሽንፈት እንድትጠፋ የፈረድክካት እንደሆነ አማኝ ስለማይኖር በምድር ላይ አትመለክም እስከማለት ደረሱ፡፡ ያች ኃይል የማይናወት ፅኑ ኢማን ነበራት ፡፡ በሚገርም መልኩ ጦርነቱ በሙስሊሞች አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡

በድር የቁርጥ ቀን ነበር፡፡ የመለያ ቀን ነበር፡፡ እውነት ከሐሰት፣ ጥመት ከቅናቻ፣ ክህደት ከእምነት፣ ብርሃን ከጨለማ የተለየበት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በሞራል ከፍ ያሉት ሙስሊሞች እየጠነከሩ ሄዱ፡፡ ወደኋላ አልተመለሱም፡፡

ሀቅ እና ባጢል የተለየበት ቀን ተውሒድ በሽርክ ላይ የነገሰበት እለት አለም በታላቁ ነብይ ብርሀን ሀ ብላ መድመቅ የጀመረችበት እለት

«ﻳَﻮْﻡَ ﺍﻟْﻔُﺮْﻗَﺎﻥِ ﻳَﻮْﻡَ ﺍﻟْﺘَﻘَﻰ ﺍﻟْﺠَﻤْﻌَﺎﻥ»

እኛንስ ለምን በድር ራቀን? ለዛ ኡማ የስኬት ሚስጥር የሆነው ቁርአን በእጃችን እያለ በነሱ ግዜ የነበረው ኢስላም አሁንም እያለ እነሱን የረዳቸው አላህ አሁንም እያለ? እና በድር ለምን የራቀን ይመስላቹሀል? ለምንስ በመካከላችን ሙናፊق"ች የበዙ ይመስላቹሀል?!

ከታላቁ ነብያችን ﷺ አስተምሮት መራቃችን ከቁርአን ይልቅ ሰው ሰራሽ ህጎችን ለሂወታችን መመሪያ ማድረጋችን ቁርአንን ስናነብ ያለ ተደቡር (ማስተንተን፣መረዳት) ማንበባችን፣ ታሪኮቻችንን ከፍታዎቻችን መለስ ብለን አለመቃኘታችን እና የመጣንበትን ምንገድ ለኢስላም የተከፈለውን ዋጋ አለማወቃችን ሌላም ብዙ ብዙ ምክንያቶች........ያ ቀን ለዛሬያችን መነሻ ነው፡፡ መለስ ብለን ታሪኮቻችንን እናንብብ፣ እንወቅ፣ ለልጆቻችን እናስተምር፡፡ ከታሪክም ትምህርት እንውሰድ፡፡ እነርሱ በደም ያፀኑትን ኢስላም እኛ ይዘነው መጽናት አይክበደን፡፡

ﺇﻗﺮﺃ ﺍﻟﺘﺎﺭﻳﺦ ﺇﺫ ﻓﻴﻪ ﺍﻟﻌﺒﺮ .. ﺿﺎﻉ ﻗﻮﻡ ﻟﻴﺲ ﻳﺪﺭﻭﻥ ﺍﻟﺨﺒﺮ!
bilaluna
https://t.me/Xuqal

15/03/2025
ረመዳን መጣላችሁ!!ወንጀሎችን በመልካም ስራዎች አቃጥሎ አመድ የሚያደርገው ወር ከበራፋችሁ ቆመላችሁ። ውበቷ ቀልብን ይገዛል። መንፈስን ይቆጣጠራል። በወሯ አጋማሽ ትደምቃለች። ብርሀኗ አይሞቅም...
28/02/2025

ረመዳን መጣላችሁ!!
ወንጀሎችን በመልካም ስራዎች አቃጥሎ አመድ የሚያደርገው ወር ከበራፋችሁ ቆመላችሁ።

ውበቷ ቀልብን ይገዛል። መንፈስን ይቆጣጠራል። በወሯ አጋማሽ ትደምቃለች። ብርሀኗ አይሞቅም። በሷ መታየት አዲሱ ወር ይታወጃል። የአላህ ፍቃድ ከሆነ ዛሬ ብቅ ብላ የራህመቱ ወር መግባቱን ታበስረናለች።

ለዚህ የላቀ ወር በሰላምና በጤና የምትደርሱ! ወደ መልካም ተግባር ተጣደፉ! ነፍሳችሁን ከእንቅልፏ ቀስቅሳችሁ የሁለቱንም ዓለም ስኬት እንድታጣጥም አድርጉ።

@ https://t.me/Xuqal

ልናስታውሳችሁ ወደድን«ሰደቃ የሚሰጥ የሆነ ሰው የሚሰጠው ሰደቃ በምስኪኑ እጅ ከማረፉ በፊት በአሏህ እጅ ላይ እንደሚያርፍለት ቢያውቅ ኖሮ ተቀባዩ ከሚያገኘው የደስታ ስሜት የበለጠ ሰጪው ይደሰ...
10/02/2025

ልናስታውሳችሁ ወደድን

«ሰደቃ የሚሰጥ የሆነ ሰው የሚሰጠው ሰደቃ በምስኪኑ እጅ ከማረፉ በፊት በአሏህ እጅ ላይ እንደሚያርፍለት ቢያውቅ ኖሮ ተቀባዩ ከሚያገኘው የደስታ ስሜት የበለጠ ሰጪው ይደሰት ነበር።»
ኢብኑል ቀይም {ራህመቱላሂ ዐለይሂ}

በቻልንው አቅም ወገኖችን እንርዳ!
ሠላም እድርና መረዳጃ ማህበር በምንሰራቸው ስራዎች ድጋፍ እና እገዛ ማድረግ ለምትፈልጉ
የአካውንት ሰም ፦ ሠላም እድርና መረዳጃ ማህበር
 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ :_ 1000175714417
 ዘምዘም ባንክ:- 0023617110301
 ሂጅራ ባንክ፡-1005388310001
 አባይ ባንክ :- 2432011491462019
 አቢሲኒያ ባንክ:-1496969614
አድራሻ፡ ሎግያ አቡዘር መስጂድ ቅጥር ግቢ ውስጥ
📞 0913298062/0912679757

#ሼር እናድርግ

@ https://t.me/Xuqal

22/01/2025

#القران #حكمةالله #الفرقان #الله ゚viralシfypシ゚viralシalシ

Address

Logya

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bilal Edris posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share