SHEKA MEDIA HUB

SHEKA MEDIA HUB "የታማኝ መረጃዎች ማዕከል!"

የሂፕ ሆፕ ሙዚቃ አቀንቃኙ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ) “ከምን ልጀምር” የተሰኘ አዲስ አልበም ይፋ አደረገ******************በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በተለይም በሂፕ ሆፕ (Hip Hop...
06/02/2026

የሂፕ ሆፕ ሙዚቃ አቀንቃኙ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ) “ከምን ልጀምር” የተሰኘ አዲስ አልበም ይፋ አደረገ
******************

በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ በተለይም በሂፕ ሆፕ (Hip Hop) ዘውግ ውስጥ የራሱን ደማቅ አሻራ እያሳረፈ የሚገኘው እና በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ዝነኛው ድምፃዊ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ 4ኛ የስቱዲዮ አልበሙን ለአድማጮች ለማቅረብ መዘጋጀቱን በይፋ አስታወቀ።

“ከምን ልጀምር” የሚል መጠሪያ የተሰጠውን ይህን አዲስ አልበም ለማዘጋጀት ስድስት ወራት የፈጀ ሲሆን፣ በውስጡ 15 አዳዲስ ሙዚቃዎችን አካቷል። አልበሙ በመጪው ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ለገበያ እንደሚውልም ተገልጿል።

ልጅ ሚካኤል አልበሙን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፥ “ይህን የሙዚቃ ስልት እኔ አልጀመርኩትም፤ ከታላላቆቼ በክብር የተቀበልኩትን በክብር ለህዝቡ አደርሳለሁ” በማለት በኢትዮጵያ በሂፕ ሆፕ የሙዚቃ ዘውግ መሠረት ለጣሉ ሙዚቀኞች በክብር እውቅና ሰጥቷል።

በተጨማሪም ስልቱን ከኢትዮጵያ ባህል፣ ታሪክ እና ዜማ ጋር በማዋሃድ ለዘመኑ ትውልድ በሚመጥን መልኩ ለማቅረብ መሞከሩን ገልጾ፤ በዚህ መንገድ ለኢትዮጵያዊ ሂፕ ሆፕ ዘውግ የራሱን ልዩ አሻራ ማሳረፍ መቻሉን አስታውቋል።

“ከምን ልጀምር” የተሰኘው አልበም የልጅ ሚካኤል የሙዚቃ ጉዞን፣ የሕይወት ትምህርቶችን፣ ማህበራዊ ጉዳዮችን እና የትውልድ ሀሳቦችን በሂፕ ሆፕ ቅርፅ ውስጥ በጥልቅ የሚያቀርብ እንደሆነም ተገልጿል።

04/12/2025

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏!

13/10/2025
PHOTO JOURNAL.  for  -Masha-Teppi road project!!!!!!.     .
13/10/2025

PHOTO JOURNAL.
for -Masha-Teppi road project!!!!!!.
.

04/10/2025

ዜና ሹመት!

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል።

በብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሠረት ከክልል እስከ ታችኛው መዋቅር ያሉት አመራሮች የግምገማና የምዘና መድረክ በጥብቅ ዲስፕሊን በመምራት በክልል ደረጃ አመራሩን መልሶ የማደራጀት ሥራ ተከናዉኗል።

የአመራር ስምሪቱ የአመራርን ውጤታማነት፣ ስነ ምግባርን እና ዝግጁነትን መሠረት በማድረግ በጥልቀት የተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።

አዲስ የተሾሙና የተሸጋሸጉ አመራሮች መንግስትና ህዝብ የጣለባቸውን ኃላፊነት ተነሳሽነት በላቀ ብቃትና ተልዕኮዎችን በብቃት እንዲወጡ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

በዚህም መሠረት

1.አቶ ተመስገን ከበደ:-የፋይናንስ ቢሮ ቢሮ ኃላፊ

2.ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ:-ፕላንና ልማት ቢሮ ቢሮ ኃላፊ

3.ወ/ሮ ቤቴልሔም ዳንኤል ልዑል:-ፍትሕ ቢሮ ቢሮ ኃላፊ

4.አቶ መቱ አኮ:-አርብቶ አደርና ቆላማ አካ/ ቢሮ ቢሮ ኃላፊ

5.አቶ ንጉሤ ወ/ጊዮርጊስ:-ፐቢሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ል/ቢሮ ቢሮ ኃላፊ

6.አቶ ታሪኩ አካሉ:- ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ

7.አቶ ዘመድኩን ሰለሞን:-ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ ኃላፊ

8.አቶ ሰብስቤ ሻወኖ :-ልዩ አማካሪና አማ/ጽ/ቤት ኃላፊ ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

9.አቶ አንተነህ አየለ:-ስትራቴጂክ ሥራ አመራር
ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

10.ረ/ኮሚሽነር ዶክተር ካሣ:-ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

11.አቶ ታምሩ ዋጫሎ:-የክልሉ ም/ቤት ጽ/ቤት ኃላፊቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

12.አቶ አማኑኤል አሰፋ:-ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
ዋና ዳይሬከተር

13.ዶ/ር ጌታቸው ወልያብ:-ማዕድንና ኢነርጂ ኤጄንሲ ዋ/ዋና ዳይሬከተር

14.አቶ ግዛው ጋግያብ:-ማዕድን ኮርፖሬሽን ዋ/ዳይሬከተር ዋና ዳይሬከተር

15.ኢንጂነር ፈልታሞ ዲቢሎ:-መስኖ ተቋ/አስ/ ኤጄንሲ
ዋና ዳይሬክተር

16.አቶ ሰለሞን አየለ:-የልማት መረጃ ሥ/ሥነሕዝብ ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ

17.አቶ ሚሊዮን አደሞ:-የልማት ዕቅድና ኢኮኖሚ አስ/ ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ

18.አቶ ዓለሙ ኬስኩ:-ሚሊሻ ጽ/ቤት ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

19.አቶ እሸቱ ጎዴቶ :-ሰው ሃብት ል/ሥራ አመ/ ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

20.አቶ ዓለሙ ገብሬ:-ሠራተኛ አሠሪ ዘርፍም/ቢሮ ኃላፊ

21.ዶ/ር ተክለዓብ ቡሎ:-ቴ/ሙያ ትም/ሥልጠና ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

22.አቶ ዳዊት ወንድሙ ወጁ:-ሥራ እድል ፈጠራ ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

23.አቶ ዳዊት ደስታ ዳልቡ:-ስፖርት ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

24.ወ/ሮ ራሄል ሌዊ :-ሴቶች ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ

25.አቶ አያሌው ካይሳ:-ወጣቶች ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

26.አቶ ፍቅሬ ኃይሌ:-ውሃ ሃብት አስተዳደር ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

27.ወ/ሮ አስገደች ወልደየስ:-ገበያ ልማት ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

28.አቶ ማሙሸት አምበቻ:-የአከባቢ ጥበቃና አየር ን/ ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ

29.ወ/ሮ ለምለም አምሳሉ:-የጋራ ግዥና ን/ማስወገድ ዘርፍም/ቢሮ ኃላፊ

30.ወ/ሮ ብዙነሽ ዜብዲዮስ:-የት/መንገድ ል/ ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊም/ቢሮ ኃላፊ

31.አቶ ዘመዴ አንዳርጌ:-ትራንስፖርት ዘርፍም/ቢሮ ኃላፊ

32.አቶ አሸብር ኤካሎ:-የቤቶች ልማትና አስተዳደር ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ

33.አቶ አክሊሉ ተገኝ:-የከተሞች የማስፈጸም አቅም ግንባታና አረንጓዴ ላማት ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ

34.አቶ አሥራት አዳሮ:-የመሶብ አንድ ማዕከል ሥራ አስፈጻሚ ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

35.አቶ አህመድን አወል:-የመሶብ አንድ ማዕከል ም/ሥራ አስ/ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

36.አቶ ገሰሰ ገበየሁ:-የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ
ም/ቢሮ ኃላፊ

37.አቶ ሳምሶን አድማሱ:-በዴሞ/ሥ/ማስ/ማዕ/ አቅም ግንባታ ዳይሬከተር ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

38.ወ/ሮ ጽዮን ታዬ:-በዴሞ/ሥ/ማስ/ማዕ/ ኢንስፔ/ ሥ/ም ም/ኮሚሽነር ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

39.ወ/ሮ ሐሲያ ዓሊ:-በዴሞ/ሥ/ማስ/ማዕ/ ሕዝብ ግን/ ሚዲያ ዳይሬከተር
ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

40.አቶ ዮናስ ቦኒ:-በዴሞ/ሥ/ማስ/ማዕ/ አደረጃጃት ዘርፍ ዳይሬከተር ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

41.ወ/ሮ ላምሮት ረታ:-በዴሞ/ሥ/ማስ/ማዕ/ የዴሞ/ባህል ግ/ የምርጫ ጉ/ዳይሬከተር
ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

42.አቶ ዘላለም ለገሰ:-በዴሞ/ሥ/ማስ/ማዕ/ የት/ተቋማት ክትትል ዳይሬከተር ም/ቢሮ ኃላፊ ማዕረግ

43.ም/ኮማንደር ታከለ ታደሰ:-የወንጀልና ትራፊክ ምርመራ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር

44.ረ/ኮሚሽነር ፈቀደ በቀለ:-የአስተዳደር ልማት ዘርፍ ም/ኮሚሽነር

45.ም/ኮማንደር አስናቀ ሐብቴ:-ወንጀል መከላከል ዘርፍ ም/ኮሚሽነር

ለአንድ ሳምንት የሚቆየው አስገራሚው የቻይናውያን ብሔራዊ ቀን አከባበር********************ቻይናውያን የፈረንጆቹን ጥቅምት 1 ብሔራዊ ቀናቸው አድርገው ያከብሩታል፡፡ እ.ኤ.አ በ19...
02/10/2025

ለአንድ ሳምንት የሚቆየው አስገራሚው የቻይናውያን ብሔራዊ ቀን አከባበር
********************

ቻይናውያን የፈረንጆቹን ጥቅምት 1 ብሔራዊ ቀናቸው አድርገው ያከብሩታል፡፡

እ.ኤ.አ በ1949 የቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ሲቋቋም ሊቀመንበሩ ማኦ ዜዱንግ በቤጂንግ ቲያመን አደባባይ ብሄራዊ ቀናችን ዛሬ ነው ባሉት መሰረት በዓሉ ዛሬም ድረስ በድምቀት እንደሚከበር ሲጂቲኤን ዘግቧል።

በዓሉ በመቶ ሚሊዮን ቻይናውያን በጉጉት የሚጠበቅ በዓል ነው የሚዘልቀውም ደግሞ ለ 1 ሳምንት ሲሆን የንግድ፣ የትራንስፖርት እና የቱሪዝም ዘርፎች ከምን ግዜውም በላይ የሚነቃቁበትም ወቅት ነው።

በዚህ የአከባበር ሳምንት ላይ ስራ ዝግ ሲሆን፤ ለዚህ ቀን አስቀድመው የሚያስቡት ቻይናውያን ሰራተኞች ይህን ጊዜ ለማካካስ ቀደም ብለው ከመደበኛ የስራ ሰዓታቸው ውጪ ተጨማሪ ጊዜያትን በስራ ላይ ያሳልፋሉ።

ቻይናውያኑ በዚሁ ወቅት በአለም ላይ ትልቅ የሚባለውን የሀገር ውስጥ ጉዞ የሚያደርጉ ሲሆን፤ ውብ ተፈጥሮ ወደ አለባቸው መስኮች፣ ተራራዎችና የውሀ አካላት ላይ በመሄድም ይዝናናሉ፡፡

በዚሁ ጊዜ የትራንስፖርቱ አንቅስቃሴ በባቡር ብቻ በ7 ቀናት ውስጥ 219 ሚሊዮን መንገደኞች እንደሚጓጓዙ ይገለጻል።

በዚህ ሳምንት የገጠር ነዋሪዎች ወደ ከተሞች የሚተሙ ሲሆን፤ በብሔራዊ ቀን ላይ የርችት ስነ-ስርዓት፣ የወታደራዊ ሰልፍ እና ታሪካዊ ቦታዎች ይጎበኛሉ፤ ይህ ወቅት በቻይና የቱሪዝም ማዕበል ተብሎም ይታወቃል።

በርካታ ጎብኚዎችም ይህን ትርዒት ለመጎብኘት ከተለያዩ የአለማችን ክፍሎች ወደ ቻይና ይመጣሉ፡፡

ብሔራዊ ቀኗን ለቱሪዝም እና ለሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንደመነቃቂያ ጊዜ የምትቆጥረው ቻይና በርካቶችን በማስደመም ላይም ትገኛለች።

የጃፓን ባህላዊ የሪክሾ ጉዞ፡ የቱሪስቶችን ትኩረት የሳበው የመጓጓዣ ዘዴመስከረም 22 ቀን 2018(SMH) በጃፓን የባህል ማዕከል በሆነችው ቶኪዮ እና በአካባቢዋ የሚገኙት የሪክሾ (ሰው የሚጎ...
02/10/2025

የጃፓን ባህላዊ የሪክሾ ጉዞ፡ የቱሪስቶችን ትኩረት የሳበው የመጓጓዣ ዘዴ

መስከረም 22 ቀን 2018(SMH) በጃፓን የባህል ማዕከል በሆነችው ቶኪዮ እና በአካባቢዋ የሚገኙት የሪክሾ (ሰው የሚጎትተው ጋሪ) ጉብኝቶች ለቱሪስቶች ልዩ መስህብ ሆነዋል። ዋናው የሪክሾ ማዕከል በቶኪዮ የሚገኘው ታሪካዊው አሳኩሳ ሰፈር ሲሆን፣ ሾፌሮች በባህላዊው ካሚናሪሞን በር እና በሴንሶጂ ቤተመቅደስ ዙሪያ በብዛት ይገኛሉ።

በተጨማሪም፣ ከዋና ከተማው ውጭ የምትገኘውና "ትንሿ ኤዶ" በመባል የምትታወቀው ካዋጎኤ ከተማም፣ በጥንታዊ መጋዘኖች በተሰለፉ ጎዳናዎች ላይ የሪክሾ አገልግሎት ትሰጣለች።

የጉዞ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የሪክሾ ጉብኝት ለመጀመር አስቀድሞ ቦታ ማስያዝ (Booking) ሁልጊዜም ግዴታ አይደለም።

ቱሪስቶች በቀጥታ ወደ ሾፌር በመቅረብና ዋጋ በመዋዋል የአጭር ጊዜ ጉዞዎችን ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል። ይህ ድንገተኛ የጉዞ ፍላጎትን ያሟላል።

ይሁንና፣ ለተሟላ እና ለታቀደ ጉዞ አስቀድሞ መመዝገብ ይመከራል፤ ምክንያቱም እንግሊዝኛ ወይም ሌላ የውጭ ቋንቋ አቀላጥፎ የሚናገር ሾፌር እንዲያገለግልዎ ከፈለጉ፣ አስቀድሞ በመመዝገብ የቋንቋ ችሎታ ያለው ሹፌር እንዲመደብልዎ ማረጋገጥ ይቻላል።

ከአንድ ሰዓት በላይ የሚወስዱ ረጅም ጉዞዎች ወይም በአንድ ጊዜ ከአንድ በላይ ሪክሾ የሚጠይቅ የቡድን ጉዞ ሲኖርም፣ አገልግሎቱ ያለ መቆራረጥ በአንድ ጊዜ እንዲጀመር ቅድመ-ቦኪንግ አስፈላጊ ነው።

ከዚህም በተጨማሪ፣ በዓላት፣ ቅዳሜና እሁድ እና ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት በሚኖርበት ጊዜ ወረፋን ለማስቀረት እና አገልግሎቱ እንዳያመልጥ አስቀድሞ መመዝገብ ብልህነት ነው ተብሏል።

በመሆኑም፣ የጃፓንን ባህላዊ የሪክሾ ጉብኝት ለመጀመር ተለዋዋጭነት ቢኖርም፣ የጉዞውን ምቾት፣ የቋንቋ ድጋፍ እና ጥራት ለማረጋገጥ በቅድሚያ ቦታ ማስያዝ አስተማማኝ ምርጫ ነው ተብሏል።

💔💔💔💔😭RIP.
02/10/2025

💔💔💔💔😭RIP.

02/10/2025

ሙሽራው በሰርጉ ስነ-ስርዓት ላይ ሕይወቱ አለፈ******አሽራፍ አቡ ሃኪም በሀገሬው ባህልና ወግ መሰረት ልቡ የወደዳትን ኮረዳ መርጦ ለቤተሰቡም አሳውቆ ለሰርጉ ቀን ቀጠሮ ይዟል።አቅም በፈቀደ...
28/09/2025

ሙሽራው በሰርጉ ስነ-ስርዓት ላይ ሕይወቱ አለፈ
******

አሽራፍ አቡ ሃኪም በሀገሬው ባህልና ወግ መሰረት ልቡ የወደዳትን ኮረዳ መርጦ ለቤተሰቡም አሳውቆ ለሰርጉ ቀን ቀጠሮ ይዟል።

አቅም በፈቀደ መጠን ለሰርጉ አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል።

ሙሽራውም ሙሽሪትም፣ ቤተዘመድ እና ወዳጅ ጓደኛ ልጆች ሁሉ ተሰብስበው ሰርጉ ላይ እየታደሙ ነበር።

ሙሽሮች እጅ ለእጅ ተያይዘው እየጨፈሩ በቤተዘመዱ ታጅበው በደስታ እያሳለፉ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ።

ሙሽራው በግብፅ ባህል ጥንዶች ሲጋቡ የሚይዙትን ዱላ እንደያዘ ድንገት ተዝለፍልፎ ወደ መሬት ወደቀ።

የሰርጉ ታዳሚዎች የሙሽራውን ሕይወት ለማትረፍ ጥረት ቢያደርጉም ግን አልቻሉም።

ሙሽራው በደስታው ቀን ሕይወቱ አለፈ፤ ደስታው እና ጭፈራው ወደ ሀዘን ተቀየረ።

የሙሽራው ሞት መንስኤ የልብ በሽታ መሆኑን በሀገሪቱ ሀኪሞች መረጋገጡን ዘ ሰን ዘግቧል።

Address

Masha

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SHEKA MEDIA HUB posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share