Oda Press

Oda Press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Oda Press, Media/News Company, Mati.

በፖለቲካ ቁማር በስራቸው ውጤታማ የሆኑ ብዙ ሰዎች ከጫወታ ውጪ ሆነዋል። የዞናችን ፖለቲካ በሁሉም መዋቅር በሚባል ደረጃ ውጤት እያመጡ ያሉ አመራሮችን ከጫወታ ዉጪ አድርጓል።በፖለቲካ ቁማር ው...
28/10/2025

በፖለቲካ ቁማር በስራቸው ውጤታማ የሆኑ ብዙ ሰዎች ከጫወታ ውጪ ሆነዋል። የዞናችን ፖለቲካ በሁሉም መዋቅር በሚባል ደረጃ ውጤት እያመጡ ያሉ አመራሮችን ከጫወታ ዉጪ አድርጓል።

በፖለቲካ ቁማር ውስጥ አልፈው ጥቂት ጊዜ እንደሰሩ ባላወቁበት ምክኒያት ብቻ ህዝቡን ወግነው የፖለቲካ መስመሩን ወግነው በመቆማቸው ብቻ እጅግ ውሃ በማያነሳ ተልካሻ ምክንያት ከአመራርነት የተነሱ ሰዎች በርካታ ናቸው ።ኦዳ በተለያዩ ሰዎች በኩል በተገፉ ሰዎች ዙሪያ መረጃ አሰባስቦ የተወሰኑ ሰዎችን ለህዝቡ ያቀርባል።

እነዚህ ሰዎች በተቀመጡበት ቦታ ላይ አሁንም በታማኝነትና በትጋት ስራቸውን የሚፈፅሙ ሰዎች ናቸው። አሁን ላይ እንደሚከተለው እናቀርባለን።

1-አቶ ነብዩ ጎበና ይባላል ይህ ሰው ከዚህ ቀደም በዲላ ከተማ በክፍለ ከተማ ማዘጋጃና በዋና ማዘጋጃ ውስጥ የተሰጠውን ኃላፊነት በታማኝነት ለህዝቡ ተወጥቷል። በፖለቲካ ቁማር የመንግስትን ንብረት ያለፈቃድ አጥሮ የያዘን ሰው ህገወጥ ነው አፍርስ በሚል በህጉ መሰረት ስላፈረሰ ግለሰቡ ባለው ተሰሚነትና ገንዘብ ከስልጣን አስወግዶታል ግለሰቡ በሰራው መልካም ስራ እስከ ዛሬ ይመሰገናል።

2-አቶ ወርባ ገብረማሪያም በሴራ ከመበላቱ በፊት በወናጎ ወረዳ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በብቃት መምራት ችሎ ነበር፡፡ በተለይ 2009 ዓም በወቅቱ እየተሰራ የነበረውን አሁን ያለውን የወናጎን አዲሱን መንገድ ከወሰን ማስከበርና ከካሳ ክፍያ ጋር ያለውን ሁኔታዎችን በብቃት መርቶ ለዛሬ እንዲደርስ ያደረገ ወጣት መሪ ነው፡፡

ሴክተሮችን በብቃት መምራት ብቻም ሳይሆን ለብልሹ አሰራሮች ምቹ አለመሆኑን በወቅቱ በመደራጀት የገመገሙና እስካሁን ከሴክተር ወደሴክተር እየተሸጋሸጉ ተላላኪነታቸውን ያረጋገጡ የወናጎ ከተማም የወረዳ አመራሮች ምስኪር ናቸው፡፡

አቶ ወርባን አመራሩ በሙሉ እንደሚሰልሉት አንድ የቅርብ ወዳጅ አመራር ሹክ ብሎኛል፡፡ይሄ ብቻም አይደለም ወረዳውን ጥሎ እንዲወጣም በደሞዝና መደብ ሁሉ በመከልከል ለብዙ ወራት ብያስጨንቁም ጠንካራ ስለሆነ በትግስት አሸንፎ በባለሙያነት እየሰራ ያለ ወንድም ነው፡፡ለምን ሰው በብቃት መመዘን ሲገባው የሌቦች አሽከር ካልሆንክ ተብሎ የወረዳው ሙሉ አመራር በመደራጀት ድጋፍ የሚሰጥና የሚቃውም አመራር በሌለበት በጋራ ባልዋለበት ገምግመው ካነሱት በኃላ በወረዳው ያለጠያቂ የሚፈልጉትን ማድረግ ችለዋል፡፡ምክንያቱሙ ከነሱ ኔትወርክ ውጪ ያለውን ሰው ለይተው ማጥቃት ችለዋል፡፡ለዚህም ነው የወናጎ ወረዳ አስተዳደር ህንፃ ጉዳይ አሳሳብ ነው ያልኔው፡፡አሁንም በትክክል በባለሙያ አልታየም፡፡በባለሙያ ከታየ ዲላ ላይ እንዳለው የመረሳ ህንፃ ፈራሽ ነው፡፡የወናጎ ወረዳም ይሁን ከተማ መሪዎች ስለህዝብ አይጨነቁም፡፡ለህዝብ ጥቅም የቆመ አመራር በመካከላቸው ካገኙ በጋራ ያጠቃሉ፡፡

3-አቶ ይሳቅ ጂሶ ጥሩ የሚባል የሚታገል ለሌቦች አልመች ሲል ከወናጎ ከተማ አንስተው ወደ ዲላ መዝጋጃ ቤት አመጡ እዚህም ለአብነት የቤትና የመሬት ዝርፊያ አልመች ስላላቸው ምንም የሚያስገመግም ሁኔታ በሌለበት አቶ አብነት በግፍ ከቦታው አንስቶታል፡፡

አቶ ይሳቅ ጂሶ ከቦታው ከተነሳ በኃላ ሌላ ቦታ ሊሰጠው ይቅርና መደብ ለማግኝት ስንቱን ደጅ ጠና፡፡ይሄ የቅርብ ግዜ ትዝታ ነው፡፡

4-አቶ አለምብራን ተሰማ በግፍ በአቶ አብነት የአመራር ወቅት ከዲላ ከተማ የተባረረ፡፡የኔትወርኩ ተቃዋሚ ብቻ ስለሆነ ምንም ከቦታው የሚያስነሳ ምክንያት ሳይኖር የተነስ፡፡

5-ሌላኛው አቶ እርሳሱ በገቢዎችና በተለያዩ ቢሮዎች በኃላፊነት የሰራ እና ታታሪ ታማኝ ሰራተኛ ነው ይህም ሰው መዘርዘር የማልፈልገው በደል ደርሶበት ከስልጣን የተወገደ ሰው ነው፡

በዞን ውስጥ ያሉ የአሁን አመራሮች ባጠቃላይ በየአርብና ሮብ ጠንቋይ ቤት መዋያቸው እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቃለን?እነዚህ የጠንቋይ ቤት ካዳሚዎች ሰው እንዳያውቅባቸው በየእሁድ ቤተክርስቲያን ...
18/10/2025

በዞን ውስጥ ያሉ የአሁን አመራሮች ባጠቃላይ በየአርብና ሮብ ጠንቋይ ቤት መዋያቸው እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቃለን?

እነዚህ የጠንቋይ ቤት ካዳሚዎች ሰው እንዳያውቅባቸው በየእሁድ ቤተክርስቲያን እየሄዱ ህዝቤን እንቅልፍ በእንቅልፍ አድርገው አጀዝበውና አዚማቸውን ረጭተው ሰዎች አምላካቸውን እንዳያመልኩና ነገረስራቸው እንዳይገለጥ አደንዝዘው ከየቤተእምነቶች ይወጣሉ፡፡

አላማቸው ሀይማኖተኛ መምሰል ነው፡፡ነገረስራቸው ግን በስውር መገዝገዝና ሰይጣናዊ ተልኳቸውን ማስፈፀምና ወንበራቸውን ያለተቀናቃኝ ማራዘም ነው፡፡

ፖለቲካና ሀይማኖት የተለያዩ ቢሆንም ቅሉ የሆዳቸው አለመሙላት ቤተክርስቲያን ውስጥ ሁሉ ገብተው ማይክ ይይዛሉ፡፡መስበክ ያምራቸዋል፡፡ለዚህ ማሳያ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴና ተከታያቸው በየመድረኩ በተደጋጋሚ አይተናቸዋል፡፡

በአንድ በኩል ፋጭኤ ይላሉ በሌላ በኩል ባህል የማይገዛቸውን ሰዎች በሃይማኖት ስም ለመገዝገዝ ይኳትናሉ፡፡ይሄ ሁሉ የወንበር ፍቅራቸውን ለማስጠበቅና ለሺያጭ ያወጡትን ዞን ያለተቀናቃኝ ለመሸጥ እንዲያመቻቸው ነው፡፡

በርግጥ ጌዴኦ እግዚአብሔር ስላለው አንደነዝዝም አንፈዝም፡፡በአባገዳ ቢፎሚ ለእርግማን ብንጠራም አንፈራም አንኮራም በድል ተመልሰን ስራቸውንና ሴራቸውን ማፈራርሱን ቀጥለናል፡፡

በሴት ጭን ሥር እያደሩና ለሰይጣን እየገበሩ አይመሯተም እግዚአብሔር ቀድሟቸዋል፡፡ወንበራቸውም እሾክ ይሆንባቸዋል፡፡አይቀመጡም ሴረኛች፣ካዳሚዎች፣ገዝጋዦች አትቀጥሉም፡፡የትላንት በኔትወርክ የሰራችሁት ሴራቹ ተበጣጥሷል፡፡ተስፋ ቁረጡ፡፡ምሁር ጠልነታችሁ በዞኑ ከጫፍ እስከጫፍ ታውቋል፡፡

ምንድነው ከወናጎ ከተማ የምሰማው?ባለፊው የባሌ-ቡቂሳ ትምርት ቤት ያለበትን ችግር በርሰ መምሩ ድረ-ገፅ ለህዝብና ለመንግስት ያሰማውን ትንሽዬ ጩኼት ተከትለው ከዞን አስተዳደር ዶ/ር ዝናቡ ወ...
17/10/2025

ምንድነው ከወናጎ ከተማ የምሰማው?

ባለፊው የባሌ-ቡቂሳ ትምርት ቤት ያለበትን ችግር በርሰ መምሩ ድረ-ገፅ ለህዝብና ለመንግስት ያሰማውን ትንሽዬ ጩኼት ተከትለው ከዞን አስተዳደር ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ አማካኝነት ባለፈው ለኮሪደር ምርቃ በማስመሰል 800.000 ሺህ ብሩን በተቀራመቱበት ዕለት በርሳነ መምርና በጉዳዩ ላይ አሉ የሚባሉ አካላት ላይ ዕርምጃ ውሰዱ ብሎ መመሪያ አስተላልፎ ከሄደ ብኃላ በስልክም ጭምር በየዕለቱ አሽከር ለሆነውና ለሴት አባራሪው አስራት በየነ እየደወለ በምን አደረሳቹ ብሎ ሲጠይቅ ሁለተናው ርሰመምር አስረናል፡አንደናው ከሥራው ስለታገዴ ጠፍታል ሲለው በፍጥነት ካለበት እንድመጣ አድርጉት ብሎ በድጋም መመራ ሰቷል፡፡

ይሄንን የዞኑን አስተዳደር ትዛዝ ለማስከበር የወናጎ ከተማ ከንቲባ ትምርት ጠል የሆነው አቶ አስራት ርሰመምሩን ለማስመጣት ፈልጎ ሲያጣው በርሰመምሩ ቤት ውስጥ ያለችውን የ4 ወር አራስ የርሰ መምሩን ባሌቤት ከአጥብ ህፃኗ ጋር ፖሊስ ጣባ አስሮ ይገኛል፡፡

አሁንም ምንለው የትምህርት ስብራት የሚጠገነው ትጉ በሆኑ በተማሩ ወጣቶች መሪነት እንጂ ወንበር ለማስጠበቅ ብሎ በሚኖሩ በማይምና በደካማ አመራር ሰጪዎች አይደለም፡፡

የትምርት ቤቱን መምራንንና ባለድርሻ አካላትን ሰብስቦ በውሸት መደሰኮር ለውጥ አያመጣም፡፡ለውጥ እንዲመጣ መጀመሪያ አመራሩ መለወጥ አለበት፡፡የመደመር እሳቤ ያልገባው ደንቆሮ ብቻ በጎጥ ተሰባስበው እንዴት የትምርት ስብራት ሊጠገን?

ቤቱን ያልመራ በመጠጥና በሴት ዳሌ የሰከረ የጎበጠ ከንትባ እራሱን ከማኮፈስና በትንሹ ከመርካት ወጪ ዘላቂ መፍትሔ የማምንጨት ጉልበት የለውም!!

የዞኑ አመራር የጥቅም ተጋሪ ስለሆነና ችግር ፈቺ ሐሳብ ስለሌላቸው ችግሮችን ሁሉ በእስራት ለመፍታት ይሞክራሉ፡፡

እስራት መፍትሔ ግን አይሆንም!!!!

ለተጠየቀው ጥያቄ ጀንበራችው ሳትጠልቅ ቀጥተኛ መልስ ስጡበት!!!!!!!

ጆሮ ያለው ይስማ!!!!!!ትውልድ የሚቀረፀው በትምህርት ነው፡፡የጌዴኦ ህፃናት እንዳይማሩ በየቦታው በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንዲማሩ በዶ/ር ዝናቡ ወልዴና በካቢኔያቸው ተፈርዶባቸዋል፡፡"እኔ ...
14/10/2025

ጆሮ ያለው ይስማ!!!!!!

ትውልድ የሚቀረፀው በትምህርት ነው፡፡የጌዴኦ ህፃናት እንዳይማሩ በየቦታው በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንዲማሩ በዶ/ር ዝናቡ ወልዴና በካቢኔያቸው ተፈርዶባቸዋል፡፡

"እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" ብሎ ትውልዱን አቀንጭሮ ሊያጠፋ የተነሳውን የዶ/ር ዝናቡ ወልዴን አስተዳደር ሁሉም ሰው የችግሩ ሰለባ ስለሆነ ህፃን አዋቂ ሳይባል መቃወም አለበት፡፡ሁሌም ስንጮህ የነበርነው ችግር አሁን አግጦ መቷል ወገን ተዘጋጅ፡፡

የህፃናት የመማር መብታቸው መጠበቅ አለበት፡፡በአንድ ቀን ጎርፍ ተጥለቅልቆ ለሚጠፋው ኮሪደር ለካቢኔ 800.000 ብር ወጪ የቀን አበል ከማድረግ ልብ ያለው አመራር ቢሆን ለትውልድ ያስብ ነበር፡፡ይህ ወናጎ ከተማ ላይ የተደረገ ነው፡፡ሌላ አከባብ ያሌውን ቤቱ ይቁጠረው፡፡

እንደዚ አይነት ችግሮችን በሚዲያ በድፍረት አውጥቶ የሚናገር ደፋር አመራርም ባለሙያ በሌለበት የበሌ-ቡቂሳ ርዕሳነ መምህራን፣መምህራንና ወሜህ አባላት ችግሩ አሳሳብ ስለሆነ ሰሚ አጣን ብለው ለበርካታ አመታት ጆሮ የሚሰጥ አመራር በማጣታቸው ወደሚዲያ አውጥተዋል፡፡

ግን ግን ማን ሚላሽ ሊሰጥ የዞን አስተዳደር ጨምሮ ለከተማው ከንቲባ አስተዳደራዊ እርምጃ ውሰድ በማለት "እንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ" እንዲሉ እስከ ዛሬ ያልተፈጠረ ውንጀል በትምርት ቤቱ አካላት ላይ መስርተው ግማሹ ታስሮው ግማሹን እየተፈለገው ነው፡፡

የትምርት ስብራትን ለመጠገን ስለትምርት የሚጮሂ ሰው ያስፈልገዋል ስትጮህ ግን በህብ የተመረጠ ጩኸት የሚሰማ አመራር ያስፈልጋል፡፡እነዚህ የብልፅግና የመደመር ዕሳቤ አልገባቸውምና ብልፅግናን አልተረዱም፡፡ይሄን ጥያቄ የሚመልስ ከዞንም ከወናጎ ከተማም የለም፡፡ህዝብ ይወቅ፡፡ እንግዲህ እኔዚ አመራሮች ናቸው ብልፅግናዎች፡፡ ለታሪክ ይቀመጥ፡፡

አሁን መምራን ተረጋግተው መስራት አልተቻሉም፡፡ርሰመምራን ታስረዋል፡፡ መምራንም እየተዋከቡ ነው like shere የምታደርጉ ተጠንቀቁ እያንዳንድህ እየተባለ ዛቻው በርትቷል፡፡ማን ይስማ፡፡አሁን ጉዳዩ የዞን ሆኗል፡፡

የሁሉም ትግል ይጠይቃል ለውጥ የጋራ ነው፡፡ለልጆቻችን ስንል እናፋፍማለን፡፡የፈራ ይመለስ ለስጋና ለዳሌ የተጋደመ አመራር ጌዴኦን አይወክልም፡፡

በሌ-ቡቂሳ የሎኮሰው የትምርት እሳት በሆድ አደር አመራር ምክንያት አይቆምም!!!!!!

ጥራት ያለው ትምርት ለጌዴኦ ተማሪዎች!!!!

የፌዴራሉ መንግስት አዲሱን የደመወዝ ጭማሪ በጀቱን ለቂቃለው ብሏል፡፡የኛ ክልልና ዞን ምን አሉ?  ግርምሽ ከበጀቷ ለመቆንደድ ነው መሰለኝ ዝም ነው!! ጪጭ ነው!!!
11/10/2025

የፌዴራሉ መንግስት አዲሱን የደመወዝ ጭማሪ በጀቱን ለቂቃለው ብሏል፡፡የኛ ክልልና ዞን ምን አሉ? ግርምሽ ከበጀቷ ለመቆንደድ ነው መሰለኝ ዝም ነው!! ጪጭ ነው!!!

አትበል ቀደም ቀደም ትሆናለህ ደም በደም፡፡ገዝጋዡ የጌዴኦ ዞን ፖለቲካ ዛሬም በጥቂቱ እንመልከትየጌዴኦ ዞን የወቅቱ ዋና አስተዳደር የሆኑት ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ አሁን ያለውን የphoto ፖለቲካ...
10/10/2025

አትበል ቀደም ቀደም ትሆናለህ ደም በደም፡፡

ገዝጋዡ የጌዴኦ ዞን ፖለቲካ ዛሬም በጥቂቱ እንመልከት

የጌዴኦ ዞን የወቅቱ ዋና አስተዳደር የሆኑት ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ አሁን ያለውን የphoto ፖለቲካ በደንብ ይረዳዋል፡፡እኛም የphoto ፖለቲካውን በደንብ እናውቃለን፡፡

አንድ ከፍተኛ የክልሉ አመራር ወደ ዞናችን ሲመጡ እንዴት አጠቃላይ አመራር እንደሚስገበገብ በፎቶ ፖለቲካው በየድረገፁ ሲለጠፍ አይተናል፡፡የሚገርመው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ ወደ ዞናችን ሲመጡ በሚዲያም ይሁን በመድረክ ክብሩን ለማሳነስ መሯሯጣችው የክልሉን ስልጣን ለመሻማት ፊትፊት ለመውጣት የምታደርጉት እሩጫ የዚህ ፎቶ አነሳስ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡

ገዝግዛችሁ ለመጣል የምትሔዱት ርቀት ከባድ አንደሆነ እናውቃለን፡፡ነገር ግን የቻይና ምርት እርባናቢስ መሆኑን አስጠንቅቀን ነግረናል፡፡ቻይና የምትሰራቸው ነገሮች በሙሉ ፌክ ናቸው፡፡እንደዛውም ዝናቡ ወልዴ በፌክ የቻይና ዶ/ሬት የማትችለውን ግዝገዛ አቁም ባይሆን፡፡ከቦታህ ብትነሳም ለድጋፍ ብትተጋ መልካም ነው፡፡

የእነዛ ጓዶችህ ክፍ ምክር ብዙ ሙሁራንን ከዞን እንዳሸሸ የሚቀርና እንደዚ የሚቀጥል መስሏችው የማይገፋ ተራራ ለመግፋት መንጠራራት ዋጋውን አሁን ካለበት ከፍ ያደርገዋል፡፡

በትናንት ቦታ ላይ ያለው ድንጋይ ብቻ ነው፡፡ሴራችሁ ሳይታወቅ ቀርቶ አይደለም፡፡የአቶ ጥላሁን ከበደን አጀንዳ ተሸካሚና አስፈፃሚ በመሆን በክልልም፣በዞን እና በወረዳና ከተማ ያሉት ካቢኔ አባላት ሪፎርም ስላልተደረገ በድፍረት በየደረጃው ተቀናጅታችሁ ብትንቀሳቀሱም ምንም ለውጥ አለመምጣቱ ምስክር ነው፡፡oda press የምትለው አንገታችሁ ላይ ገመዱን አታጥብቁ ተረጋጉ፡፡

ገዝጋዥ ፖለቲካ እራስ ወዳድ ነው፡፡የማህበረሰብ ለውጥ አይፈልግም፡፡የግል ጥቅም ላይ ብቻ የተመሰረተ ነው፡፡ስልጣን ከተነጠቀ በራሱ ህይወት ላይ እስከመፍረድ የሚያደርስ ራስወዳድ ነው፡፡
በቀጣይ በክልል ያሉትን ስም እየጠቀስን ሥራቸውን እያጋለጥን እናዋርዳለን፡፡
አሁን በለጠፍኩት ፎቶ ላይ ማን ከፊት መሆን ነበረበት?

ኢሄ ሁሉ አመራር ዛሬ ለማስመረቅ ወናጎ ውሏል አንድም ስለበሌቂሳ ት/ቤት ያሰበም የተመለከተም የለም፡፡አሁን እቺን የበሬ ግንባር ምታክል ነገር ኮሪደር ብለው ለፖለትካ ፍጆታቸው ሲሉ ተኮልኩለው...
09/10/2025

ኢሄ ሁሉ አመራር ዛሬ ለማስመረቅ ወናጎ ውሏል አንድም ስለበሌቂሳ ት/ቤት ያሰበም የተመለከተም የለም፡፡

አሁን እቺን የበሬ ግንባር ምታክል ነገር ኮሪደር ብለው ለፖለትካ ፍጆታቸው ሲሉ ተኮልኩለው መጡ፡፡ለሳምንታት ለማይቆይ ተራ ነገር ለመመረቅ፡፡

በትውልድ ላይ ስሩ ነው እያልን ያለነው፡፡የህዝቡ ጩሔት የማይገዳቸው መሆናቸው ግልፅ ማሳያ ነው፡፡ኮሪደር ትምህርት ቤት አይገነባም፡፡በጀቱ ለትምህርት አዊላችው ብትሆኑ ትደነቁ ነበር፡፡የደሃ ልጂ ምንም የተመቻቸ መማሪያ ክፍልና ቁሳቁስ ስለሌለው ጎዳና እያደረ ቤንዚን ያሸታል እናንተ ደግሞ አበላችሁን አስልታችው አካውንታችሁን አቀባብላችው ለዚ ተራ ግንባታ ከፀሐፊ እስከ አስተዳደር ተሰባስባችው መጣችው ግዜ ዳኛ ነው ከመጠየቅ አትድኑም፡፡

ይባስ ብላችው የት/ቤቱ ርዕሳነ መምህራንን ለማሳሰር ከዶ/ር ዝናቡ ወልዴ መልዕክት ተቀብለው እንደመጡ የሚናገሩ ሶስት የፖሊስ አባላት ት/ቤቱን እያሸበሩ ውለዋል፡፡

የትምህርት ጉዳይ የርዕሳነ መምህራን፣የመምህራንና የተማሪዎች ጉዳይ አድርጎ የሚመለከት ሰው በ21ኛው ክ/ዘመን ያለ አይመስለኝም፡፡ምናልባት ካድሬ ካልሆነ በቀር፡፡

ስለዚህ የትምህርት ጉዳይ የኔም ያንተም የሁሉም ማህበረሰብ ጉዳይ ነው፡፡ስለዚ ትግል የጋራ ነው፡፡የጥቂቶች ስላልሆነ ሁላችሁም ለመታሰር እየተፈለጉ ባሉት ርዕሳነ መምህራንና መምህራን ጎን እንድት ቆሙ Oda press ጥሪ ታቀርባለች፡፡

በጌዴኦ ዞን ህዝብ ይመራኛል ብሎ በምርጫ ወደፊት የመጡ አመራሮች ለጌዴኦ ህዝብ ከመታገል ይልቅ ለግል ጥቅማቸው መጨነቃቸው በህዝብ ውስጥ ግርምትን ፈጥሯል፡፡በዞን የተሾሙት ህዝብን ያሻግራሉ ተ...
01/10/2025

በጌዴኦ ዞን ህዝብ ይመራኛል ብሎ በምርጫ ወደፊት የመጡ አመራሮች ለጌዴኦ ህዝብ ከመታገል ይልቅ ለግል ጥቅማቸው መጨነቃቸው በህዝብ ውስጥ ግርምትን ፈጥሯል፡፡
በዞን የተሾሙት ህዝብን ያሻግራሉ ተብለው የዞኑን ስልጣን በበላይነት የተቆናጠጡ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ ከየወረዳና ከተማ አስተዳደሮች በውል የማይታወቅ ሚሊየን ብሮችን በጌልማ በኩል ገቢ በማስደረግ የቀጣይ የግል ህይወታቸውን ለማደላደል የተለያዩ የንግድና የመኖሪያ ቤት ግንባታ ላይ የዘረፉትን ገንዘቡ ለመደበቅ እሩጫ ላይ ናቸው፡፡ለህዝብ ጥቅም ቢውል በርካታ መሰረተ ልማት ማከናውን የሚችል የህዝብን ሀብት ዶ/ር ዝናቡና ካቢኔያቸው በመዝረፍ ገንዘቡን በባንክ ቢያስቀምጡ መንግስ የሀብት ምንጭ አጣርቶ ይይዛል በሚል ስጋት መኪና በመግዛት ለኪራይ በመስጠትና በየቦታው አዳዲስ ቤት ግንባታ ላይ ተወጥረዋል፡፡ይህን ተሞክሮ ደግሞ የወሰዱት ከአቶ ጥላሁን ከበደ እንደሆነ በየ ቢራ ቤቱ የሚናገሩ የካቢኔ አባላት ምስክር ናቸው፡፡አቶ ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሆኑት የክልሉን ሀብት 75 በመቶውን ወደ ጋሞ ልማት ማህበር በማዘዋወር እንደሆነ ይነገርላቸዋል፡፡

ዶ/ር ዝናቡ ወልዴም በተመሳሳ አካሄድ መንግስት ሰራተኛው በየወሩ ከደሞዝ ተቆራጭ በማድረግና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከገቢያቸውና አርሶ አደሩ ከምርቱና ከልጆቹ ጉሮሮ እየቀነሰ የደገፈውን ጌልማ በአቶ ብዙነህ አጋፋሪነት ጅርጂቱ ለግለስብ ተጠቃሚነት ወሏል፡፡

እነዚህን የሙስናና የሌብነት ቅሌት በውስጥ ሆኖ የሚታገል አንድም አመራር አለመኖሩ እጅግ በጣም ይገርማል፡፡ምክንያቱም ሁሉም አመራር በኔትወርክ የተሰባሰበ ስለሆነ ገበናቸውን ተሸፋፍነው በመሸላለም ለመለያየት በቅተዋል፡፡

ለዚህም ነው የጌዴኦ ህዝብ ሰሚ ጆሮ በማጣቱ ብልፅግና ላይ ተስፋ የቆረጠው፡፡

ብዙ አከባቢዎች እሮሮ ብቻ እስኪሆን አመራሩ ለራሱ ብልፅግና እየተጋ ይገኛል፡፡ለህዝብ ደንታ የላቸውም፡፡

ምክንያቱም ከዚህ ቀደም በርካታ ምሁራንን በተለያዩ ስልቶች ከአከባቢው በማራቅና በውሸት ግምገማ በውስጥ በመደራጀት ብቁና ምሁራንን ያገለለ የካቢኔ መዋቅር ዞኑ ላይ በመዘርጋት ጌዴኦን እንደ አሜሪካን የወተት ላም በቀን 3ስቴ እያለቡ አቀጨጩት፡፡

በግልፅና በስውር የሚታገል ብቁ አመራር ካለመኖሩ የተነሳ ተላላኪና አጎብዳጅ ለሆዱ የተገዛ አመራር ተፈጥሯል፡፡አመራርነት በግዢ የተሰጠው ደግሞ ከመሸላለምና ግምገማውን በከፍተኛ ውጤት ከማለፍ ውጪ ምን አዲስ ነገር ለማህበረሰቡ ይፈጥራል፡፡

ስለዚህ እነዚህ አቅመ-ቢስ አመራሮች በክልል ደረጃ ተገኝተውም ትግል ለማድረግ ብቁ አይደሉም ከማጎብደድ ውጪ ለዞኑ ጠብ የሚል የሚታይ ነገር መስራት አልቻሉም ለራሳቸው ከመበልፀግ ውጪ፡፡

ሀሰተኛ ማህበራዊ ሚዲያ እኛን ተፅኖ ለማድረግ በመክፈት "እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል"አይነት አመለካከት በማራመድና እስከምርጫ ማንም አይነካንም በሚል ክፉ ምኞት በመወጠር ሌብነትን እንደ ስራ የቆጠረ የዞንና የወረዳ ካብኔ በግዜ ካልተወገደ አሁን ያለው እሮሮ ከጌዴኦ አልፎ እንደ 2009ዓም ወደ አገሪቱ እንደሚዛመት ጥርጥር የለውም፡፡
የጌዴኦ አምላክ ሳይውል ሳያድር ይፈርዳል፡፡

በጀት ለውድመት ውጤት ያስመዘገበው የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ የዲላ ከተማ ትምህርት መምሪያ ይፍረሱ።።።ተቋሙ ለግል ይሰጥ።።።የጌዴኦ ዞን 2017 የትምህርት ዘመን ካስፈተናቸው ውስጥ 574...
18/09/2025

በጀት ለውድመት ውጤት ያስመዘገበው የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ የዲላ ከተማ ትምህርት መምሪያ ይፍረሱ።።።ተቋሙ ለግል ይሰጥ።።።

የጌዴኦ ዞን 2017 የትምህርት ዘመን ካስፈተናቸው ውስጥ 5745 ተማሪዎች መካከል 280 ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ማግኘታቸውን በወጣው መረጃ መነሻ ተመልክተናል።

ይሁን እንጂ ያለፉት አብዛኛውን ተማሪዎች የዲላ ዶንቦስኮና ይርጋጨፌ ዩኒየን አካዳሚ ተማሪዎች ናቸው።

ዞኑ አጠቃላይ ካሉ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ካሳለፋቸው 280 ተማሪዎች ውስጥ 112 ተማሪዎች የይርጋጨፌ ዩኒየንና የዶንቦስኮ ተማሪዎች ናቸው ።

አጠቃላይ ከዲላ ውጪ የጌዴኦ ዞን ቢሊየን ብር በጀት አውጥቶ የትምህርት ስራ ሰርቻለሁ ብሎ አጠቃላይ ለመምህራንና ለትምህርት ጽ/ቤት ሰራተኞች በአበልና በደሞዝ የከፈለው ገንዘብ 150 ሚሊየን ብር ያልፋል ነገር ግን አጠቃላይ በዘንድሮ ከዲላ ውጪ ያሳለፋቸው ተማሪዎች ቁጥር 68 ብቻ ነው 112 ተማሪዎች በግል ትምህርት ቤት ይርጋጨፌና ዶንቦስኮ ተማሪዎች ናቸው።

ይህ ሁሉ በጀት ከመንግስት ቋት ወጥቶ ለእነዚህ ለግል ተቋም ቢሰጥ ኖሮ በሺዎች ማሳለፍ እንችል ነበረ። ትምህርቱን በጀት ለመቀራመት በሚል ብቻ ፖለቲካ አድርገው በዘር በጎሣ ሰንሰለት ያለ ብቃት አመራር የትምህርት ቤት ባለሙያ ይመደብና ትውልድ ይሞታል ነጌ ለማኝ ትውልድ ማፍሪያ ተቋም አድርገዋል ብቻ ትግሌ ትምህርት ከፖለቲካ ነፃ ይሁን በእውቀትና በባለሙያ ይመራ በዘር በጎሣ በዘመድ አዝማድ በጀት ያለበትን ቦታ ተቆናጥጠው ስራ እንዳይሰራ መምህራኑ በነፃነት እንዳይሰራ ሀሉንም ነገር ፖለተካ አድርገው ትውልድ የሚገድሉ ይነሱ ዘማች ክፍሌ ቀድሞ ይነሳ

31/08/2025

ላልተወሰነ ጊዜ ሀዘን ላይ ስላለን ስራ አቋርጠናል ተመልሰን ስንመጣ የምናሳወቅ ይሆናል

Address

Mati

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Oda Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share