28/10/2025
በፖለቲካ ቁማር በስራቸው ውጤታማ የሆኑ ብዙ ሰዎች ከጫወታ ውጪ ሆነዋል። የዞናችን ፖለቲካ በሁሉም መዋቅር በሚባል ደረጃ ውጤት እያመጡ ያሉ አመራሮችን ከጫወታ ዉጪ አድርጓል።
በፖለቲካ ቁማር ውስጥ አልፈው ጥቂት ጊዜ እንደሰሩ ባላወቁበት ምክኒያት ብቻ ህዝቡን ወግነው የፖለቲካ መስመሩን ወግነው በመቆማቸው ብቻ እጅግ ውሃ በማያነሳ ተልካሻ ምክንያት ከአመራርነት የተነሱ ሰዎች በርካታ ናቸው ።ኦዳ በተለያዩ ሰዎች በኩል በተገፉ ሰዎች ዙሪያ መረጃ አሰባስቦ የተወሰኑ ሰዎችን ለህዝቡ ያቀርባል።
እነዚህ ሰዎች በተቀመጡበት ቦታ ላይ አሁንም በታማኝነትና በትጋት ስራቸውን የሚፈፅሙ ሰዎች ናቸው። አሁን ላይ እንደሚከተለው እናቀርባለን።
1-አቶ ነብዩ ጎበና ይባላል ይህ ሰው ከዚህ ቀደም በዲላ ከተማ በክፍለ ከተማ ማዘጋጃና በዋና ማዘጋጃ ውስጥ የተሰጠውን ኃላፊነት በታማኝነት ለህዝቡ ተወጥቷል። በፖለቲካ ቁማር የመንግስትን ንብረት ያለፈቃድ አጥሮ የያዘን ሰው ህገወጥ ነው አፍርስ በሚል በህጉ መሰረት ስላፈረሰ ግለሰቡ ባለው ተሰሚነትና ገንዘብ ከስልጣን አስወግዶታል ግለሰቡ በሰራው መልካም ስራ እስከ ዛሬ ይመሰገናል።
2-አቶ ወርባ ገብረማሪያም በሴራ ከመበላቱ በፊት በወናጎ ወረዳ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በብቃት መምራት ችሎ ነበር፡፡ በተለይ 2009 ዓም በወቅቱ እየተሰራ የነበረውን አሁን ያለውን የወናጎን አዲሱን መንገድ ከወሰን ማስከበርና ከካሳ ክፍያ ጋር ያለውን ሁኔታዎችን በብቃት መርቶ ለዛሬ እንዲደርስ ያደረገ ወጣት መሪ ነው፡፡
ሴክተሮችን በብቃት መምራት ብቻም ሳይሆን ለብልሹ አሰራሮች ምቹ አለመሆኑን በወቅቱ በመደራጀት የገመገሙና እስካሁን ከሴክተር ወደሴክተር እየተሸጋሸጉ ተላላኪነታቸውን ያረጋገጡ የወናጎ ከተማም የወረዳ አመራሮች ምስኪር ናቸው፡፡
አቶ ወርባን አመራሩ በሙሉ እንደሚሰልሉት አንድ የቅርብ ወዳጅ አመራር ሹክ ብሎኛል፡፡ይሄ ብቻም አይደለም ወረዳውን ጥሎ እንዲወጣም በደሞዝና መደብ ሁሉ በመከልከል ለብዙ ወራት ብያስጨንቁም ጠንካራ ስለሆነ በትግስት አሸንፎ በባለሙያነት እየሰራ ያለ ወንድም ነው፡፡ለምን ሰው በብቃት መመዘን ሲገባው የሌቦች አሽከር ካልሆንክ ተብሎ የወረዳው ሙሉ አመራር በመደራጀት ድጋፍ የሚሰጥና የሚቃውም አመራር በሌለበት በጋራ ባልዋለበት ገምግመው ካነሱት በኃላ በወረዳው ያለጠያቂ የሚፈልጉትን ማድረግ ችለዋል፡፡ምክንያቱሙ ከነሱ ኔትወርክ ውጪ ያለውን ሰው ለይተው ማጥቃት ችለዋል፡፡ለዚህም ነው የወናጎ ወረዳ አስተዳደር ህንፃ ጉዳይ አሳሳብ ነው ያልኔው፡፡አሁንም በትክክል በባለሙያ አልታየም፡፡በባለሙያ ከታየ ዲላ ላይ እንዳለው የመረሳ ህንፃ ፈራሽ ነው፡፡የወናጎ ወረዳም ይሁን ከተማ መሪዎች ስለህዝብ አይጨነቁም፡፡ለህዝብ ጥቅም የቆመ አመራር በመካከላቸው ካገኙ በጋራ ያጠቃሉ፡፡
3-አቶ ይሳቅ ጂሶ ጥሩ የሚባል የሚታገል ለሌቦች አልመች ሲል ከወናጎ ከተማ አንስተው ወደ ዲላ መዝጋጃ ቤት አመጡ እዚህም ለአብነት የቤትና የመሬት ዝርፊያ አልመች ስላላቸው ምንም የሚያስገመግም ሁኔታ በሌለበት አቶ አብነት በግፍ ከቦታው አንስቶታል፡፡
አቶ ይሳቅ ጂሶ ከቦታው ከተነሳ በኃላ ሌላ ቦታ ሊሰጠው ይቅርና መደብ ለማግኝት ስንቱን ደጅ ጠና፡፡ይሄ የቅርብ ግዜ ትዝታ ነው፡፡
4-አቶ አለምብራን ተሰማ በግፍ በአቶ አብነት የአመራር ወቅት ከዲላ ከተማ የተባረረ፡፡የኔትወርኩ ተቃዋሚ ብቻ ስለሆነ ምንም ከቦታው የሚያስነሳ ምክንያት ሳይኖር የተነስ፡፡
5-ሌላኛው አቶ እርሳሱ በገቢዎችና በተለያዩ ቢሮዎች በኃላፊነት የሰራ እና ታታሪ ታማኝ ሰራተኛ ነው ይህም ሰው መዘርዘር የማልፈልገው በደል ደርሶበት ከስልጣን የተወገደ ሰው ነው፡