Organic Tigray

Organic Tigray ትግራይ የኢትዮጲያ ሀገረ መንግስት መነሻ ማዕከል ናት። የህወሓትን ቆሻሻ ታሪክ አድሰን ከኢትዮጲያዊ ወንድሞቻችን ጋር ኢትዮጲያን ከፍ እናደርጋለን።

 ❗️የትግራይ የሰላም ሀይል (TPF) የትግራይን ህዝብ ከወያኔ መንጋጋ ፈልቅቆ ለማውጣት ሌት ከቀን እየሰራ ይገኛል 💪💪💪
03/06/2026

❗️

የትግራይ የሰላም ሀይል (TPF) የትግራይን ህዝብ ከወያኔ መንጋጋ ፈልቅቆ ለማውጣት ሌት ከቀን እየሰራ ይገኛል 💪💪💪

በማያጋበው እሳት የሚለበለበው የትግራይ ወጣት ቁጥር ጨምሯል 🚫በሃገር ውስጥ ጦርነት  እየለኮሰ በሚያስፈጀው የትግራይ ወጣት ደም ያልረካው ህወሓት የተቀረውን ወጣት በሱዳን ጦርነት እንዲያልቅ ...
03/06/2026

በማያጋበው እሳት የሚለበለበው የትግራይ ወጣት ቁጥር ጨምሯል 🚫

በሃገር ውስጥ ጦርነት እየለኮሰ በሚያስፈጀው የትግራይ ወጣት ደም ያልረካው ህወሓት የተቀረውን ወጣት በሱዳን ጦርነት እንዲያልቅ የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሎበታል ።

የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ ሳይቀር ገና ህጻናት የሆኑ ለአልቡርሃን ጦር በቅጥረኚነት የሚዋጉ የህውሃት ታጣቂወችን ማርኮ ‘’ የትግራይ እናቶች ሆይ ልጆቻችሁን በማያገባቸው እንዲያልቁ አታድርጉ ‘’ በሚል የልመና ቪድዮ ሰርቶ ማሰራጨቱ የቅርብ ግዜ ትውስታ ነው ።

የፈጥኖ ደራሹን ያህል ጥቂት እንኳን ርህራሄ ለትግራይ ወጣት የማይሰማው ህወሓት ግን ህጻናትን ሳይቀር በማያገባቸው ጦርነት መማገዱን ስራየ ብሎ ተያይዞታል ።

በዚህም ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ በብሉናይል ክልል በሚገኙ በአርሚ 70 ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ በ120 ሚ.ሜ ሞርታር በፈፀመው ጥቃት 31 ቅጥረኛ የህውሃት ታጣቂወች ሲገደሉ ከ60 በላይ የሚሆኑት ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ አልጀዚራ ክልል መደኒ መላካቸው ተጠቁሟል ።

የህወሓቱ ጀነራል ጀ/ል ሙዘይ ደግሞ ግዳይ እንደጣለ ሁሉ ከሱዳን ወታደራዊ መረጃ አመራር አባዲ ጋር በመሆን ቁስለኛ ልጎብኝ በሚል ወደ መደኒ ማምራቱ ታውቋል ።

እስከመቸ ይሆን ግን የትግራይ ወጣት ህይወት የህወሓት አዛውንቶች መቀለጃ የሚሆነው ❓

  !!ጽንፈኛው ህወሓትና ጸረ ሰላሙ ፋኖ  ያደረጉት ስብሰባ ያለ ስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ በመቐለ ውጥረት ነግሷል !!የጽንፈኛው ህወሓትና የጸረ ሰላም ሃይል በትግራይ መቐለ ከተማ ያደረጉት...
03/06/2026

!!

ጽንፈኛው ህወሓትና ጸረ ሰላሙ ፋኖ ያደረጉት ስብሰባ ያለ ስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ በመቐለ ውጥረት ነግሷል !!

የጽንፈኛው ህወሓትና የጸረ ሰላም ሃይል በትግራይ መቐለ ከተማ ያደረጉት ስብስባ ያለ ምንም ስምምነት መለያያታቸው ታውቋል ።

እንደ እያሪኮ ህዝብ ቋንቋቸው የተደበላለቀባቸው እነዚህ ቡድኖች ዘይትና ውሃ መሆናቸውን በተግባር እያየን ይገኛል።

በሁለቱ ቡድኖች መካከል መቼም የማያስማመቸው ነገር እንዳለ የታወቀ ሲሆን በሁለቱ ቡድኖች መካከል በመግባት ለማስማማት የሞከረው የሻዕቢያ ቡድን ምንም መፍትሄ ማምጣት እንዳልቻለ ከቦታው የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ።

ህወሓትም የጸረ ሰላም ቡድን አዛዦች ካልተስማማችሁ ከዚህ በሰላም አትወጡም በማለት በተሰበሰቡት አክሱም ሆቴል ዙሪያ ሁለት ክፍለ ጦር ወታደሮችን አሰማርቶ በጸረ ሰላም አዛዦች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ተዘጋጅቷል።

ቅዱስነታቸው  ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን  መልእክት፦በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች...
03/06/2026

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት፦

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።

የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።

በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

ህገ ወጥ ምክር ቤቱን አንቀበልም ☑️ ታሪካዊ ስህተት መስራት የማይደክመው የህወሃት አመራር የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በይፋ ጥሶ በትግራይ ክልል የሚገኘው ህገ-ወጥ ምክር ቤት አካሂዷ አ...
02/06/2026

ህገ ወጥ ምክር ቤቱን አንቀበልም ☑️

ታሪካዊ ስህተት መስራት የማይደክመው የህወሃት አመራር የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በይፋ ጥሶ በትግራይ ክልል የሚገኘው ህገ-ወጥ ምክር ቤት አካሂዷ አዲስ ሹመት ሰጥቷል።

ይህን የቡድኑን ተግባር በትግራይ ክልል የሚገኙ ተፎካካሪ ፓርቲወች ወቅሷል፤ በህገወጡ ምክር ቤት የተሰጣቸውን የመቀመጫ ኮታ እንደማይቀበሉት ይፋ በማድረግ የጥፋት ተግባሩ ተባባሪ እንደማይሆኑ አስመስክሯል።

አክለውም በክልሉ ሹመት የተሰጣቸው አካላት ምንም አይነት በቂ የሆነ እውቀትና ልምድ የሌላቸው፣ ክልሉን ወደ ባሰ አዘቅት የሚከቱ ናቸው ሲሉ ተችተዋል።

 ‼️ህወሓት የሥራ አስፈጻሚና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን አባረረ❗️የፅንፈኛው ህውሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ከግንቦት 16 እስከ 23/2018 ዓ.ም ያደረገውን ስብሰባ ውሳኔወችን በማስተላለፍር ቋጭቷ...
02/06/2026

‼️

ህወሓት የሥራ አስፈጻሚና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን አባረረ❗️

የፅንፈኛው ህውሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ከግንቦት 16 እስከ 23/2018 ዓ.ም ያደረገውን ስብሰባ ውሳኔወችን በማስተላለፍር ቋጭቷል፡፡

በዚህም የቡድኑ ስራ አስፈፃሚ እና የማዕከላይ ኮሚቴ አባላት የነበሩ ግለሰቦችን በይፋ በማባረር በሌላ ታማኝ በሚላቸዉ ሰዎች በይፋ መተካቱ ታውቋል ፤ ያባረራቸውን አባላትም ወደተቀናቃኝ ሃይሎች እንዳይቀየጡ በሚል በአስቸኳይ ዕርምጃ ሊወስድባቸው መሆኑም ተሰምቷል ፡፡

በትግራይ ወላጆች፣ ነጋዴዎችና ተፈናቃዮች ላይ የፖለቲካ ቁማር የሚጫወተው ህውሓት ከገዛ ኣባለቱ ጋር እራሱ መስማማት አልቻለም

 !!የምልስ ታጣቂው ዕርምጃ እየመረረ መምጣቱ የህወሓት አመራሮችን ጭንቅ ውስጥ ከቷቸዋል! ከሰሞኑ በሽሬ አካባቢ በሚገኝ አንድ የወርቅ መቆፈሪያ ስፍራ ላይ የተሰማሩ ምልስ ታጣቂወች ልክ በሌሎ...
02/06/2026

!!

የምልስ ታጣቂው ዕርምጃ እየመረረ መምጣቱ የህወሓት አመራሮችን ጭንቅ ውስጥ ከቷቸዋል!

ከሰሞኑ በሽሬ አካባቢ በሚገኝ አንድ የወርቅ መቆፈሪያ ስፍራ ላይ የተሰማሩ ምልስ ታጣቂወች ልክ በሌሎች አካባቢወች እንዳደረጉት ሁሉ ሊያፍሷቸው የመጡትን የህወሓት ታጣቂወች ዶግ አመድ አድርገው መሳሪያቸውን መታጠቃቸው ታውቋል!!

ይህ የምልስ ታጣቂው ዕርምጃ እየመረረ መምጣት ታድያ የህወሓት አመራሮችን ጭንቅ ውስጥ ከትቶ ለግዜው በወርቅ ስፍራወች ላይ አፈሳው እንዳይደረግ ትዕዛዝ እንዲያስተላልፉ ማስገደዱ ተረጋግጧል።

ትግራይ ሓይሊ ሰላም   ናብ ትግራይ ናብ ዓድና ምስ ዕጥቅና ክንኣቱ ዝኽልኽለና ዝኾነ ይኹን ሓይሊ የለን። መሬት ትግራይ ይትረፍ ንዓና ሻዕብያ ዝተብሃለ ኣረመንያዊ ሓይሊ'ኳ ከም ድላዩ ኣብ መ...
01/06/2026

ትግራይ ሓይሊ ሰላም ናብ ትግራይ

ናብ ዓድና ምስ ዕጥቅና ክንኣቱ ዝኽልኽለና ዝኾነ ይኹን ሓይሊ የለን። መሬት ትግራይ ይትረፍ ንዓና ሻዕብያ ዝተብሃለ ኣረመንያዊ ሓይሊ'ኳ ከም ድላዩ ኣብ መላእ ትግራይ ይዛወን እዩ ዘሎ።

ሎሚ ይኹን ፅባሕ ናብ ትግራይ ክንኣቲ መሰልናን ግቡእናን እዩ። ብትእዛዝ ዕጡቅ ጉጅለ ህወሓትን ልዕሊ ኮርን ተገዲዱን ትግራዋይነትና ክሒዱን ደው ከብለና ዝፍትን ዕጡቅ እንተሃልዩ ሓላፍነት ክወስድ ይግባእ።

ንሕና ተጋሩ ኢና። ንሕና ፅሩያት ተጋሩን መቦቀልና ኣብ ትግራይ ዝኾንና ጀጋኑ ነበር ተጋደልቲ TDF ኢና። ንትግራይ ክንብል ብፆትና ዝሰዋእና ዓርስና ዝቆሰልናን ዝሰንከልናን ኢና። ነገር ግን ንሕና "ዓጀብቲ ሓደ ኣምባገነን ውድብ ኣይንኾንን" ኢልና ምእንተ ትግራይን ህዝቢ ትግራይን ኣብ ምቅላስ ኖርከብ ደቂ ህዝቢ እምበር ሸፋቱ ስለዘይኾንና ናብ ናይ ባዓልና ምድሪ ትግራይ ክንኣቲ ግድን እዩ።

ዕላማና ግልፂ እዩ!
ኣብ ትግራይ ስርዓታዊ ለውጢ ኣምፂእና ፤ ተሳትፎ ኩለን ፖለቲካዊ ውድባት ዘለዎን ዕጥቂ ዘይብሉን ክልላዊ መንግስቲ ክምስረት ምግባር እዩ።

Tigrai Peace Force
ትግራይ ሓይሊ ሰላም
24 ጉምበት 2018ዓ/ም
ሓራ መሬት

 !!ህወሓት ማይ ዓይኒ እና አዲ አርጌ ስደተኞች ካምፕ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ያለ ፈቃዳቸው ለፖለቲካ ጥቅሙ ሲል  ለኢሳያስ አሳልፎ ሊሰጣቸው ነው!!አምባገነኑ የኤርትራ መንግስት ኢሳ...
01/06/2026

!!

ህወሓት ማይ ዓይኒ እና አዲ አርጌ ስደተኞች ካምፕ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ያለ ፈቃዳቸው ለፖለቲካ ጥቅሙ ሲል ለኢሳያስ አሳልፎ ሊሰጣቸው ነው!!

አምባገነኑ የኤርትራ መንግስት ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራን የወላድ መካን ካደረጋት ቆይቷል።

ይህ ዲሞክራሲ ያማያውቀው፣ ለወጣቱ የማይመቸው፣ ከራሱ ስልጣን ውጭ ለህዝቡ ደንታ የለለው ኢሳያስ የኤርትራን ወጣት ትውልድ ሀገር አልቦ በማድረግ በየ ሀገሩ ስደተኛ አድርጎታል።

ኢሳያስ በዚህም አላበቃም ፤ ከጽንፈኛው ህወሓት ጋር ጽምዶ የሚል የጥቅም ጋብቻ በመመስረት ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ለማወክ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

ከዚህ ጎን ለጎንም ኢሳያስን እና አንባገነናዊ አስተዳደሩን በመሸሽ ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የገቡ ስደተኞች በአስገዳጅ ለማስመለስ ከህወሓት ጋር እየተዋዋለ ይገኛል።

ለአብነትም በትግራይ በማይ ዓይኒ እና አዲ አርጌ ስደተኞች ካምፕ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን ያለፈቃዳቸው ህወሓት ከሻዕቢያ በሚያገኘው ጥቅም የተነሳ አሳልፎ ሊሰጣቸው በማሰብ ባድሜ አካባቢ በካምፕ እያጎራቸው ይገኛሉ።

ህወሓት በነዚህ ኤርትራዊያን ስደተኞች ላይ በነፍሳቸው እየቆመረ ያለው ከሻዕቢያ ጋር ከዚህ ቀደም በመሰረተው የፅምዶ ጋብቻ ሲሆን አሁን ላይም ኤርትራዊያን ስደተኞችን ለአረመኔው ኢሳያስ አሳልፎ በመስጠት ሳዋ ወታደራዊ ካምፕ ሊያስገባቸው ጫፍ ላይ ይገኛል።

በትግራይ ወላጆች ላይ የሚደርሰው ግፍ በከፋ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል‼️ በማዕከላዊ ዝን ዓብይ ዓዲ ከተማ 01 ቀበሌ በግንቦት 17 እና 18 ‘’ ልጆቻችሁን ደብቃችኋል አምጡ ‘’ በሚል 19 እ...
31/05/2026

በትግራይ ወላጆች ላይ የሚደርሰው ግፍ በከፋ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል‼️

በማዕከላዊ ዝን ዓብይ ዓዲ ከተማ 01 ቀበሌ በግንቦት 17 እና 18 ‘’ ልጆቻችሁን ደብቃችኋል አምጡ ‘’ በሚል 19 እናቶችን እና 13 አባቶችን በድምሩ 32 ወላጆችን ጽንፈኛ ቡድኑ አፍኖ በመውሰድ ምግብ እና ውሃ ጭምር እንዳይቀርብላቸው በመከልከል እያሰቃያቸው እንደሚገኝ ተረጋግጧል፡፡

የህውሓት ስብስብ፣ አሁን ላይ እየገጠመው ያለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተከትሎ በንጹሐን ወላጆች ላይ የሚፈጽመው ግፍና አረመኔነት በከፋ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ወጣቱ ይህን የወላጆቹን ስቃይ ለመጨረሻ ግዛ ለመቋጨት ግፈኛውን ቡድን ለመገርሰስ ከሚታገሉት ጋር ሊሰለፍ ይገባዋል

Address

Mekelle

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Organic Tigray posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Organic Tigray:

Share