23/08/2025
በጥገና ሥራ ምክንያት የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው የክልሉ አካባቢዎች
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቦንጋ ፣ሚዛን አማንና ቴፒ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የጥገና ስራ ለማከናወን ሲባል ከማከፋፈያ ጣቢያዎቹ የኤሌክትሪክ ኃይል በሚያገኙ አካባቢዎች ኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
በዚህ መሰረት በቀን 18/12/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ምሽት 12፡00 ሰዓት ድረስ (በቦንጋ፣ ጊንቦ፣ ጎጀብ፣ ጌሻ፣ ጢሎ፣ ጨታ፣ አዲያ፣ ጭሪ፣ ውሽውሽ፣ ሚዛን፣ ቴፒ) ኤሌክትሪክ እንደሚቋረጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገልጿል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ ክቡራን ደንበኞች የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠባበቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያስታውቃል።