Ethio Daily

Ethio Daily We strive to reach Trustworthy NEWS .

01/10/2024

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የቀድሞውን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አንዷለም አድማሴን የውጭ ጉዳዮች ኃላፊ አድርጎ መሾሙ ታውቋል።

ዶ/ር አንዷለም ከዚህ በፊት በግዙፉ ኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚነት እንዲሁም በደቡብ ሱዳን ውስጥ ከሌሎች ግለሰቦች ጋር ባቋቋሙት አዲስ የቴሌኮም ኩባንያ በኃፊነት በመሥራት ላይ ነበሩ ተብሏል።

ሳፋሪኮም ኩባንያ አዲሱ የሾማቸው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ በቴሌኮምኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያካበቱትን ልምድ በመጠቀም የኩባንያውን ስኬታማነት ያስቀጥላሉ መባሉን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቦታል።

01/10/2024

መስከረም 21፣ 2017 ኢራን ወደ እስራኤል ሚሳኤል ማስወንጨፍ መጀመሯን የእስራኤል መከላከያ ሃይል አስታወቀ፡፡ የሚሳኤል ጥቃቶቹ ወደ እስራኤል ዋና ከተማ ቴላቪቭ ያነጣጠሩ መሆናቸው ተነግሯል፡፡ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎም የቴላቪቭ ነዋሪዎች የአደጋ ማስጠንቀቂያ ሲሰሙ ደህንነታቸው ወደ ሚጠበቅ ቦታ በፍጥነት እንዲሄዱ የሀገሪቱ መከላከያ ሀይል ማሳሰቡን ቢቢሲ ዘግቧል::

10/08/2024

🥇ታምራት ቶላ የኦሎምፒክ ማራቶን ክብረ ወሰን ሰበረ

የፓሪስ ኦሎምፒክ የወንዶች ማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊው ታምራት ቶላ ባለድል ሆኗል ። የ32 ዓመቱ ታምራት ውድድሩን ያጠናቀቀው 2 ሰዓት ከ6 ሴኮንድ ከ26 ማይክሮ ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ነው ። ይህ ሰዓት አዲስ የኦሎምፒክ ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል ። ቤልጄማዊው በሽር አብዲ ነጋየ 21 ሰከንዶች ዘግይቶ በመግባት የብር ሜዳሊያ አሸናፊነቱን ሲያስጠብቅ ፣ ኬንያዊው ቤንሰን ኪፕሮቶ ደሞ የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊ ሆኗል ። የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊው እና አዲሱ የኦሎምፒክ ክብረ ወሰን ባለቤት ታምራት ቶላ በጉዳት ምክንያት ለመሳተፍ ያልቻለውን የሀገሩን ልጅ ሲሳይ ለማን ተክቶ በቅርብ ቀናት ውስጥ ከኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ጋር የተቀላቀለ መሆኑ ይታወሳል።(Photo: AP)

05/08/2024

በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል አልቀናቸውም

ሐምሌ 29፣ 2016 በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል አልቀናቸውም፡፡

ኢትዮጵያ የተጠበቀችበት የ5 ሺህ ሜትር የሴቶች የፍጻሜ ውድድር ምሽት 4 ሰዓት ከ15 ላይ ተካሂዷል፡፡

በዚህም እጅጋየሁ ታዬ 5ኛ፣ መዲና ኢሳ 6ኛ እንዲሁም ጉዳፍ ፀጋይ 8ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።

የአፄ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት እድሳት ተጀመረበጎንደር ከተማ የፋሲል ቤተ መንግሥት እድሳት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡ ‹‹በአጭር ግዜ ውስጥ ፋሲልን ወደ...
01/08/2024

የአፄ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት እድሳት ተጀመረ

በጎንደር ከተማ የፋሲል ቤተ መንግሥት እድሳት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡ ‹‹በአጭር ግዜ ውስጥ ፋሲልን ወደ ቀደመ ግርማ ሞገሡ እንመልሰዋለን›› ሲሉም በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡ በ16ኛው ክፍለ ዘመን በአፄ ፋሲለደስ በተቆረቆረችው ጎንደር ከተማ የሚገኘው የአፄ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት፣ በዓለም ቅርሶች መዝገብ በ1979 ዓ.ም. መስፈሩ ይታወቃል፡፡ የአፄ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት ፋሲል ግቢ ወይም ነገሥታት ግቢ በ1628 ዓ.ም. የተሠራ ሲሆን፣ ቤተ መዛግብት፣ የአፄ ፋሲል መዋኛ፣ ቁስቋም ማርያም ቤተ ክርስቲያን፣ ራስ ግምብና ደረስጌ ማርያምን ይዟል፡፡ አፄ ፋሲለደስ የመጀመሪያውንና ታላቁን ግንብ ሲያሰሩ፣ ከእሳቸው በኋላ የነበሩት ነገሥታትም ለ220 ዓመታት የየራሳቸውን ሕንፃ በመሥራት ቦታው በቅርስ እንዲዳብር አስችለዋል፡፡

በጎንደር ከተማ የፋሲል ቤተ መንግሥት እድሳት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡ ‹‹በአጭር ግዜ ውስጥ ፋሲልን ወደ ቀደመ ግርማ ሞገሡ እንመልሰዋለን›› .....

  2024 Olompic Schedule
31/07/2024

2024 Olompic Schedule

31/07/2024

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ11.5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች፡፡

ሐምሌ ፳፭/፳፻፲፮ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የስብክተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ብጹእ አቡነ ማርቆስ ጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በመገኘት ድጋፉን አስረክበዋል፡፡

በደረሰው አደጋ ቤተ-ክርስቲያኗ ማዘኗን የገለጹት አቡነ ማርቆስ፤ ለተጎጂ ወገኖችም መጽናናትን እንደሚመኙ ተናግረዋል፡፡

አሁን እንደተቋም ቤተ-ክርስቲያኗ ካደረገችው ድጋፍ በተጓዳኝ ምዕመኑን በማስተባበርም በቀጣይ ድጋፍ እንደሚደረግም ገልጸዋል፡፡

ድጋፊን የተቀበሉት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳደሪ ዳግማዊ አየለ፤ ቤተ-ክርስቲያኗ አደጋው ከደረሰ ጀምሮ ተጎጂዎችን ከማጽናናት ጀምሮ ባደረገችው ያልተቋረጠ ድጋፍ ምስጋናቸውን በማመስገን በቀጣይ ሌሎች ሀይማኖታዊ ይሁኑ ሀይማኖታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተጎጂ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

31/07/2024

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ስርአት ማሻሻያን አስመልክቶ የሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፦

ኢትዮጵያ በትናንትናው ዕለት መንግሥት አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራምን አስመልክቶ የሰጠውን መግለጫ ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻሉን ያስታውቃል፡፡

ከዛሬ ጀምሮ ሥራ ላይ የሚውለው ይህ ማሻሻያ ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ወደሆነና በገበያ ላይ ወደተመሠረተ የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት እንደሚያሸጋግራትና በኢኮኖሚ ውስጥ ለረጅም ጊዜ ተንሰራፍቶ የቆየውን የማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋትና መዛባት እንደሚያሻሽል ይታመናል፡፡

የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ማሻሻያው በአዲሱ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መሠረት የሚተገበር ይሆናል፡፡

ይህ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሀ ግብር ላይ የተመሠረተና በቀጣይ ሥራ ላይ ከሚውሉ ሰፊ ማክሮ ኢኮኖሚአዊ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ዋና ግቡ ቀጣይነት ያለው፣ መሠረተ ሰፊና ሁሉን አሳታፊ የኢኮኖሚ ዕድገት መኖሩን ለማረጋገጥ ነው፡፡

የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ማሻሻያው ቁልፍ ይዘት ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ የሚከተሉትን ዐበይት አዳዲስ የፖሊሲ ለውጦችን ያካትታል፡-

1. የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል ወደሚወስንበት የገበያ ሥርዓት ይሸጋገራል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሚና፣ ገበያውን በማረጋጋት ላይ ያተኮረ ይሆናል፡፡

2. የውጭ ምንዛሪን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የማስተላለፍ ግዴታ ቀሪ ሆኗል፡፡ በመሆኑም፣ ላኪዎችና ንግድ ባንኮች ያፈሩትን የውጭ ምንዛሪ ለራሳቸው ማስቀረት ይችላሉይህም ለግሉ ዘርፍ የሚሰጠውን የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በእጅጉ ያሻሽላል፡፡

3. ቀደም ሲል በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ ተነሥቷል፡፡ ወደ ውጭ የሚደረግ የካፒታል ሂሳብ ፍሰት እንደ በፊቱ የተገደበ ቢሆንም፣ የውጭ ምንዛሪ ገበያው ለገቢ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነጻ ሆኗል፡፡

4. ምርቶችን ወደ ውጭ የሚልኩ ነጋዴዎች ካፈሩት የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለራሳቸው ያስቀሩት የነበረው 40 በመቶ ወደ 50 በመቶ ከፍ ብሏል፡፡

5. ቀደም ሲል ባንኮች ለተለያዩ ገቢ ሸቀጦች የሚጠቀሙበት የውጭ ምንዛሪ አሠራርና አደላደል ደንቦች ቀሪ ሆነዋል፡፡

6. አሁን በሥራ ካሉና በባንኮች ከተቋቋሙ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች (Forex Bureaus) በተጨማሪ ባንክ ያልሆኑ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ይቋቋማሉ፡፡ለእነዚህ ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎችም በገበያ ዋጋ የውጭ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ እንዲገዙና እንዲሸጡ የሥራ ፈቃድ ይሰጣቸዋል፡፡

7. ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ረገድ የተጣሉ ክልከላዎች ለማንሳት በቅርብ ጊዜ የማሻሻያ ደንብ ይወጣል፡፡

8. በውጭ ተቋማት፣ በውጭ ኢንቨስተሮች እና በትውልደ ኢትዮጵያውያን (በዳያስፖራዎች) የተከፈቱ የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦችን አስተዳደር የሚመለከቱ በርካታ ሕጎች እንዲላሉ ተደርጓል፡፡

9. በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ የሆኑ ሰዎች ከውጭ የሚላክላቸውን ሐዋላ፣ በውጭ ምንዛሪ የሚከፈል ደሞዝን/የኪራይ ገቢን እና ሌሎች ገቢዎችን የሚያስቀምጡባቸውን የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦች እንዲከፍቱ፣ እንዲሁም እነዚህን የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦች ተጠቅመው የውጭ አገልግሎት ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ተፈቅዷል፡፡

10.ቀደም ሲል የግል ኩባንያዎች ወይም ባንኮች በሚወስዷቸው የውጭ ብድሮች ላይ ይከፍሉት የነበረው የወለድ ተመን ጣሪያ ተነሥቷል፡፡

11. መመዘኛውን የሚያሟሉ የውጭ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ስነደ

31/07/2024

ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ያካተታቸው 13 ዐበይት አዳዲስ የፖሊሲ ለውጦች፡-

1. የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል ወደሚወስንበት የገበያ ሥርዓት ይሸጋገራል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሚና፣ ገበያውን በማረጋጋት ላይ ያተኮረ ይሆናል፡፡

2. የውጭ ምንዛሪን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የማስተላለፍ ግዴታ ቀሪ ሆኗል፡፡ በመሆኑም፣ ላኪዎችና ንግድ ባንኮች ያፈሩትን የውጭ ምንዛሪ ለራሳቸው ማስቀረት ይችላሉይህም ለግሉ ዘርፍ የሚሰጠውን የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በእጅጉ ያሻሽላል፡፡

3. ቀደም ሲል በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ ተነሥቷል፡፡ ወደ ውጭ የሚደረግ የካፒታል ሂሳብ ፍሰት እንደ በፊቱ የተገደበ ቢሆንም፣ የውጭ ምንዛሪ ገበያው ለገቢ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነጻ ሆኗል፡፡

4. ምርቶችን ወደ ውጭ የሚልኩ ነጋዴዎች ካፈሩት የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለራሳቸው ያስቀሩት የነበረው 40 በመቶ ወደ 50 በመቶ ብሏል፡፡

5. ቀደም ሲል ባንኮች ለተለያዩ ገቢ ሸቀጦች የሚጠቀሙበት የውጭ ምንዛሪ አሠራርና አደላደል ደንቦች ቀሪ ሆነዋል፡፡

6. አሁን በሥራ ካሉና በባንኮች ከተቋቋሙ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች (Forex Bureaus) በተጨማሪ ባንክ ያልሆኑ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ይቋቋማሉ፡፡ ለእነዚህ ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎችም በገበያ ዋጋ የውጭ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ እንዲገዙና እንዲሸጡ የሥራ ፈቃድ ይሰጣቸዋል፡፡

7. ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ረገድ የተጣሉ ክልከላዎች ለማንሳት በቅርብ ጊዜ የማሻሻያ ደንብ ይወጣል፡፡

8. በውጭ ተቋማት፣ በውጭ ኢንቨስተሮች እና በትውልደ ኢትዮጵያውያን (በዳያስፖራዎች) የተከፈቱ የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦችን አስተዳደር የሚመለከቱ በርካታ ሕጎች እንዲላሉ ተደርጓል፡፡

9. በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ የሆኑ ሰዎች ከውጭ የሚላክላቸውን ሐዋላ፣ በውጭ ምንዛሪ የሚከፈል ደሞዝን/የኪራይ ገቢን እና ሌሎች ገቢዎችን የሚያስቀምጡባቸውን የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦች እንዲከፍቱ፣ እንዲሁም እነዚህን የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦች ተጠቅመው የውጭ አገልግሎት ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ተፈቅዷል፡፡

10.ቀደም ሲል የግል ኩባንያዎች ወይም ባንኮች በሚወስዷቸው የውጭ ብድሮች ላይ ይከፍሉት የነበረው የወለድ ተመን ጣሪያ ተነሥቷል፡፡

11. መመዘኛውን የሚያሟሉ የውጭ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ስነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ (Ethiopian Securities Exchange) እንዲሳተፉ ተፈቅዷል፡፡

12. በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ የሚሠሩ ኩባንያዎች የውጭ ምንዛሪ ገቢያቸውን ሙሉ በሙሉ ለራሳቸው መያዝን ጨምሮ ልዩ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም መብት ተሰጥቷቸዋል፡፡

13. ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ወይም ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መንገደኞች ሊይዙ በሚገባ የውጭ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ መጠን ላይ ተጥለው የነበሩ የተለያዩ ጥብቅ ደንቦች እንዲላሉ ተደርጓል፡፡

  2024 Olompic
21/07/2024

2024 Olompic

21/04/2024

አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በ1 ሺህ 500 ሜትር በታሪክ ሶስተኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸነፈች
አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በ1 ሺህ 500 ሜትር ርቀት በታሪክ ሶስተኛውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸነፈች።

በቻይና ዢያሜን እየተካሄደ ባለው ዲያመንድ ሊግ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ 3:50.30 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀች ሲሆን፤ የገባችበት ሰዓት በርቀቱ በታሪክ ሶስተኛው ፈጣን ሰዓት መሆኑን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ ያመላክታል።

በውድድሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል።

በዚህም ጉዳፍ ጸጋይን ተከትለው ብርቄ ሃይሎም፣ ወርቅነሽ ምስለ፣ ድርቤ ወልተጂ እና ፍሬወይኒ ሃይሉ ተከታትለው ገብተዋል።

ፔሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።በእግር ኳሱ ዓለም ትልቅ ስም ያለው ብራዚላዊው ታሪካዊ የእግር ኳስ ተጫዋች ፔሌ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።የቀድሞ እግር ኳስ ተጫዋቹ ባጋጠመው ህመም ...
29/12/2022

ፔሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

በእግር ኳሱ ዓለም ትልቅ ስም ያለው ብራዚላዊው ታሪካዊ የእግር ኳስ ተጫዋች ፔሌ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።

የቀድሞ እግር ኳስ ተጫዋቹ ባጋጠመው ህመም ሆስፒታል ገብቶ ህክምና ሲከታተል የቆየ ቢሆንም ህይወቱን ማዳን አልተቻለም።

ከብራዚል ብሔራዊ ቡድን ጋር ሶስት / 3 የዓለም ዋንጫዎችን ማሸናፍ የቻለው ፔሌ በሰማንያ ሁለት ዓመቱ ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው

Address

Mizan Teferi

Opening Hours

Monday 00:00 - 18:00
Tuesday 00:00 - 18:00
Wednesday 00:00 - 18:00
Thursday 00:00 - 18:00
Friday 00:00 - 18:00
Saturday 00:00 - 18:00
Sunday 00:00 - 18:00

Telephone

+251-0471350192

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Daily posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Daily:

Share