Misganaw Darie

Misganaw Darie "በመጨረሻም ከጠላቶቻችን ንግግር የወዳጆቻችን ዝምታ አሳሰበ!!!✍️ሉተር ኪንግ
https://www.facebook.com/deramablebieza
https://t.me/biezabieza

Power (ኃይል)ከአለም አቀፍ ህጎች ይበልጣል።“ብርቱዎች የሚችሉትን ያደርጋሉ፤ ደካሞች የሚገባቸውን ይቀበላሉ።"ቱክዲዲስአለም በወታደራዊ ኃይል ፤በኢኮኖሚ ፈርጣማነት በቴክኖሎጂ እድገት የቀደ...
04/01/2026

Power (ኃይል)ከአለም አቀፍ ህጎች ይበልጣል።
“ብርቱዎች የሚችሉትን ያደርጋሉ፤ ደካሞች የሚገባቸውን ይቀበላሉ።"ቱክዲዲስ
አለም በወታደራዊ ኃይል ፤በኢኮኖሚ ፈርጣማነት በቴክኖሎጂ እድገት የቀደመ የሚመራት እንጂ አንዳንዶች እንደሚሉት idealists ሀሳብ ከሁሉ በላይ ነው የሚሉት ተዳክሞ realism theory በበላይነት የነገሰበት አለም ናት።ኩርዲስቶች የጠፉት ኃይል ስሌላቸው ሲሆን እስራኤል የገነነችውም በኃይሏ ነው።
ኃይል በሰው ልጆች ጉዳይ ውስጥ እውነተኛና መሠረታዊ ኃይል ነው።በባይወሎጅስቶች የሚነገረው food chain ትክክለኛ የኃይል ማሳያ ነው።አፅቄዎች የሚኖራቸው እጣ ፈንታ ከሌሎች ተሳቢ እንሰሳት፤ከበራሪ አእዋፍ፤ከአጠቃላይ እንሰሳት የሚበላው እንዳይበላቸው እነርሱን የማይመገብ እንዳይጨፈልቃቸው ያለውን ጫና ሁሉ መቋቋም አይችሉም።አንበሳ ደግሞ ስጋቱን ቀንሶ እያገሳ ይኖራል።

የሥነ-ምግባር እሴቶች፣ ሕጎች እና ተቋማት ብዙ ጊዜ በኃይል ይቀረጻሉ፤ ኃይል በእነርሱ አይቀረጽም

ፖለቲካን ወይም ማህበረሰብን ለመረዳት፣ ማን ኃይል እንዳለው፣ እንዴት እንዳገኘው፣ እና እንዴት እንደሚጠቀምበት መመርመር ያስፈልጋል።
ቱክዲዲስ (Thucydides) የተባለው ሰው
ከመጀመሪያዎቹ ሪያሊስቶች አንዱ ሲሆን በ Melian Dialogue ውስጥ፦
“ብርቱዎች የሚችሉትን ያደርጋሉ፤ ደካሞች የሚገባቸውን ይቀበላሉ”ይለናል። ሕይወት በአደጋ ላይ ሲሆን፣ ኃይል እንጂ ፍትህ ውጤትን አይወስንም ይላል።

ታዋቂው ፈላስፋ ማኪያቬሊ (Machiavelli) በ The Prince ስራው ውስጥ፦ፖለቲካ ከሥነ-ምግባር የተለየ የራሷ ሎጂክ አላት መሪዎች በአንዳንድ ጊዜ በተንኮል ወይም በኃይል ሆነውም ቢሆን ኃይላቸውን ማቆየት ላይ መርካታ መሆን አለባቸው።የሥነ-ምግባር ጥራት ብቻ መጠበቅ በፖለቲካ ውስጥ አደገኛ ሊሆን ይችላል በማለት ይገልፀዋል።

ሌላኛው ፀሀፊና ተመራማሪ በርናርድ ዊሊያምስ – የፖለቲካ ፍልስፍና መጀመሪያው ጥያቄ “ሥርዓትን በኃይል መጠበቅ” መሆን አለበት በማለት የኃይልን አስፈላጊነት ይገልፃል።
በአለም ያሉ መንግሥታት የሚፈልጉት ኃይልና ህልውና ነው፣ ሥነ-ምግባር አይደለም።የስነ ምግባር ሁኔታ አለምንአይገዛትም፤አገራትንም አያስከብራቸውም።በ1ኛው እና በ2ተኛው የአለም የጦርነት ሂደት ምስኪኖች ሳይፈልጉ ተወረዋል፤በኋላም በቅኝ ግዛት ተሰቃይተዋል።ኃይል ያለው ሁሉጉልበታቸውን ገንዘባቸውን ሀገራቸውን ተጠቅመውበታል።

ዓለም አቀፍ ሥርዓት አናርኪ/ anarchy/ ነው (ዓለም አቀፍ ባለሥልጣን የለም)አንዱ የአንዱ ጠላት ነው።ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ኃይል ዲፕሎማሲን ይመራል።ሃንስ ሞርገንታው የሀገር ጥቅም በኃይል ይተረጎማል እንዳለ ጥቅምን ለማስከበር አቅም ይጠይቃል።
♦አለም አቀፍ ህጎች፤አለም አቀፍ ስምምነቶች፤አዋጆች ሁሉ የሚሰሩት ኃይል ላላቸው ነውና ኃይል ይኑርህ።አሜሪካም የአለም አቀፍ ህግ ሣይጠይቃት የቬንዙዌላ ፕሬዜዳንትን ያሰረችው ኃይል ስላላት እንጂ በህግ አይደለም።
♦የእኛ ኃይል (አቅም) ምንድን ነው?

ነገረ ማርያም በነገረ ድኅነት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው ትምህርት ሲሆን አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ ከምልአትነቱ ሳይጎድል ...
19/10/2025

ነገረ ማርያም በነገረ ድኅነት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያለው ትምህርት ሲሆን አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ ከምልአትነቱ ሳይጎድል ሰው ሆኖ በተገለጠ ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ደንግል ማርያም በሰው ልጅ መዳን ላይ ያላትን ድርሻ (ምክንያትነት) የሚዳስስ ትምህርት ነው፡፡
እመቤታችን ድንግል ማርያም በሰው ልጅ የመዳን ጉዳይ ላይ ያላት ድርሻና ምክንያትነት ሙሴ በእስራኤላውያን፣ ቅዱስ ገብርኤል በሠለስቱ ደቂቅ፣ ኤልሳዕም በንዕማን፣ ሱራፊ ኢሳይያስን ከለምጹ በመፈወስ ውስጥ ከነበራቸው ድርሻ በላይ ትልቅ ድርሻ ነበራት፡፡(ዘፀ.፴፪፥ ፴፪፣ መዝ. ፻፭፥፳፫፣ ዳን.፫፥፳፰፣ ፪ኛነገ.፭፥፲፬፣ ዘፍ.፯፥፩-፲፪፣፩ኛጴጥ.፫፥፳.ኢሳ.፮፥፭)
ቀዳማዊ ሰው አዳም በበደሉና በኃጢአቱ ምክንያት ከነፍስ ተድላና ደስታ ከገነት ወጥቶ በግብርናተ ዲያብሎስ ሲሠቃይ የመከራ ዘመናቱ ያበቃው በእመቤታችን በድንግል ማርያም ምክንያትነት በኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አዳኝነት ነው፡፡ ምንም እንኳን ወልድ በተለየ አካሉ ከእመቤታችን ሥጋና ነፍስን ነሥቶ በተለየ አካል ቢገለጥም “በማትለይ ባሕርይ” ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ ነውና ማዳኑን ፈጽሟል፡፡ ይህም ኢየሱስ ክርስቶስን “ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነ አምላክ ነው” ብሎ ማመን እመቤታችንን “ወላዲተ አምላክ” ብለን እንድናምን ይመራናል፡፡
በአምስተኛው ክፍለ ዘመን የተነሣው መናፍቁ “ንስጥሮስ” ኢየሱስ ክርስቶስን “ሁለት ባሕርይ ነው” በማለት በክርስቶስ ላይ ተገዳድሮ እመቤታችንን “ወላዲተ ሰብእ” ብሎ ምንፍቅናን ተናግሯል፡፡ ቤተ ክርስቲያንም “ወላዲተ ሰብእ” ያይደለች “ወላዲተ አምላክ” ናት ብላ መናፍቁን አውግዛ ሃይማኖት አጽንታለች፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይህንን የአበው ውሳኔ “ኦርቶዶክሳዊ ዐለት” በማለት ይጠሩታል፡፡ (ወላዲተ አምላክ በነገረ ድኅነት)
እመቤታችን በነገረ ድኅነት ውስጥ ያላት ሚና የሚጀምረው አምላክን ከመፅነሷ አስቀድሞ በነበራት የንጽሕናና የድንግልና ሕይወት ጀምሮ ነው፡፡ አንዳንዶች “እመቤታችን ንጹሕ ሆና የተገኘችው አምላክ አስቀድሞ ስለመረጣት እንጂ የእርሷ ድርሻ አልነበረም“ ብለው ምንም ዓይነት የእርሷ ድርሻ እንዳልነበረ ምንፍቅናን የሚናገሩ አሉ፡፡ እውነታውን ግን እግዚአብሔር በእርሷ ድርሻና ተሳትፎ ለማደሪያነት እንደመረጣት መጻሕፍት ይመሰክራሉ፡፡ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ ላይ “እግዚአብሔር አብ ከሰማይ ወደ ምድር ተመለከተ፤ ሰሜንና ደቡብን ምሥራቅና ምዕራቡን አሻተተ፤ እንዳንቺ ያ ግን አላገኘምና የሚወደውን አንድ ልጁን ወዳንቺ ላከ” እንዳለ ከዓለም ትውልድ ሁሉ እርሷን የመረጣት ከሰው ልጅ ለአምላክ እናትነት ከእርሷ ውጪ በቅታ የተገኘች ስላልነበረች ነው፡፡ ቅዱስ ሔሬኔዎስ የተባለው ደገኛ ሊቅ ደግሞ ሲናገር “ጌታ ለማደሪያነት እመቤታችንን የመረጣት በዚያ ጊዜ ከነበሩ ሴቶች ጋር ተወዳድራ ሳይሆን ዓለም ከተፈጠረ እስከሚያልፍ እርሷን የሚተካከል አንድም ሰው ስለሌለ ነው” በማለት የመመረጧን ነገር አድንቆ ይናገራል፡፡እግዚአብሔር እመቤታችንን አስቀድሞ ከመርገም እና ቁራኝነት ከልሎ ጠብቋታል፤ ይህም በኋላ ላይ የሚኖራትን ጽናትና ደግነት አይቶ በአዋቂነቱ ያደረገላት እንጂ ሳትበቃና ሳትጸና ከሌላው ሰው አድልቶ ያደረገላት አልነበረም፡፡ ለምሳሌ፡- ነቢዩ ኤርምያስን “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፤ በማሕፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃሁ፤ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃሁ” ሲል ኤርምያስን ለጽድቅና ለነቢይነት ያለሱታፌው ያለ ትጋቱ የሰጠው ሆኖ ሳይሆን የበኋላ ትጋቱን በአምላክነቱ አውቆ መምረጡን ለመናገር ነው፡፡ (ኤር.፩፥፲፭)©ኢ

26/09/2025

መስቀል በቅዱስ ያሬድ እና በሌሎች አበው
ሊቃውንት ገለጣ!!!!

✍️ መስቀል መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ይለዋል።

መስቀል የቤተ ክርስቲያን መሠረት ነው። የቤተ ክርስቲያን መሠረቷ የክርስቶስ መስቀል ነው። የክርስቲያን ሰው" ሕይወቱ መስቀላዊ ፤ ተፈጥሮው መስቀላዊ ፤ ሕጉ መስቀላዊት ሕግ ናቸው። ቤተ ክርስቲያን የተወለደችው ከመስቀሉ ሥር ነው።ያለ መስቀል ቤተ ክርስቲያን የለችም።መሠረቷ መስቀል ነው። ክርስቲያናዊ ሰው መነሻው መስቀል ነው።መድረሻውም መስቀል ነው። በመስቀል ተባርኮ ክርስቲያን ይኾናል። ሕይወቱ በመስቀል ይቀጥላል። በመስቀል ተባርኮ ሕይወቱ ይፈጸማል። መስቀል የቤተ ክርስቲያኗ መሠረት ነው።በመስቀል ተባርከህ ትደቁናለህ፤ በመስቀል ተባርከህ ትቀስሳለህ፤ በመስቀል ተባርከህ ትመነኲሳለህ፤ በመስቀል ተባርከህ ትጰጵሳለህ።በመስቀል ተባርከህ ወደ መቃብር ትወርዳለህ።
✍️የቤተ ክርስቲያን እያንዳንዱ ሕይወቷ መስቀላዊ ነው።አገልግሎቷም መስቀል ያልተለየው ነው። አአትብ ወእትነሳእ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ሠለስተ አስማተ ነሢዕየ እትመረጐዝ "

በአብ እና በወልድ በመንፈስ ቅዱስም ስም አማትቤ እነሳለሁ ።ብወድቅም እንኳን ሦስቱን ስሞች እንደ ምርኩዝ ተመርኩዤ እነሳለሁ እንዳለ አባ ጊዮርጊስ። ቤተ ክርስቲያን ውሃውን በመስቀል ባርካ ማየ ገቦ፤ ኅብስቱን በመስቀል ባርካ ሥጋ ወልደ እግዚአብሔር፤ ወይኑን በመስቀል ባርካ ደመ ወልደ እግዚአብሔር ወደ መኾን ትለውጠዋለች። ቤተ ክርስቲያን ውሃውን በመስቀል ባርካ ፈዋሽ ጸበል፤ አፈሩን በመስቀል ባርካ ፈዋሽ እምነት ታደርገዋለች፤ ከዓለማውያን እደ ጥበብ ተሠርቶ የመጣውን ንዋየ ቅዳሳት በሙሉ ባርካ ቅዱስ ታደርገዋለች።ክቡርም አድርጋ ታከብረዋለች። መስቀል ያልነካው ክርስቲያናዊ ሰው ክርስቲያን አይደለም። ለክርስቲያኖች ኹሉ መስቀል የሕይወታቸው ኹሉ መነሻ መድረሻ ፤ መጀመሪያ መቋጫ ነው።ስለዚህ መስቀል መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተባለ።

፪ኛ ዛኅኑ ለባሕር ወመርሶ ለአሕማር ይለዋል።
የባሕር ጸጥታዋ ፤ የመርከቦች ወደባቸው መስቀል ነው ይለዋል። መስቀል የባሕር ጸጥታ ነው።ባሕር ያለው ይህንን ዓለም ነው ። በባሕር ማዕበል ሞገድ አለ። ማዕበል ሞገድ ሲነሳ ባሕሩ ይታወካል።ማዕበል ሞገዱ ጸጥ ሲል ባሕሩ አብሮ ጸጥ ይላል። በዚህ ዓለምም ብዙ ሁከቶች አሉ። የክርስቶስን መስቀል ካሰብንበት ግን ሁከቱ ጸጥ ይላል። መስቀል የባሕረ ዓለም ጸጥታ ነው። የመርከቦችም ወደብ ነው።መርከቦች በባሕር ሲጓዙ ውለው ከወደብ ያርፋሉ።በኀጢአት በሁከተ ሥጋ በሁከተ ነፍስ የነበረ ኹሉ በመስቀል ሥር አርፎ ደስ ይሰኛልና። ጸጥ ያገኛልና ። ዳግመኛም በኦሪት በሁከተ ነፍስ የነበሩ ኹሉ በትንቢት ፥በምሳሌ፧ በራእይ መርከባቸው ሲጓዙ ኑረው በዚህ መስቀል ሥር አርፈዋልና የመርከቦች ወደብ ተባለ።

፫ኛ መስቀልን ምንጭ ብሎታል።

መስቀል አንቅዕት ለጽሙኣን እንዲል። መስቀል ለተጠሙ ምንጫቸው ነው ይለዋል። መስቀል የሕይወት ውሃ የፈለቀበት ነቅዐ ማየ ሕይወት የሕይወት ውሃ ምንጭ ነው። እመቤታችን የሕይወት ውሃ ምንጩ መነሻ የተገጠመችው ጒድጓድ ናት። ከእመቤታችን የተገኘው የሕይወት ውሃ ግን የፈሰሰው መስቀል ላይ ነው። መስቀል ጽምዐ ነፍስ የተወገደበት ጥመኞች ጥማቸውን የቆረጡበት ምንጭ ነው። ኢራቅሊስ የተባለ የቤተ ክርስቲያን ሊቅ ሃይ አበ ም ፵፱ ላይ እንዲህ ይላል። ኖኅ ከተባለ አይሁዳዊ ጋራ በኦሪት የተደረጉትን እና በሀዲስ ኪዳን የተደረጉትን ተአምራት እያነጻጸረ መጥቶ የሙሴ በትርን እና የክርስቶስ መስቀልን ያነጻጽርለታል። ከመ/ር አስተራየ

11/09/2025

ናሁ ቃለ ዐዋዲ ዘይሰብክ በገዳም
የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውኑም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ዐዘቅቱ ሁሉ ይሙላ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይበል ፤ሸካራውም መንገድ ትክክል ይሁን ፣ሥጋም የለበሰም ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ ተብሎ እንደ ተፃፈ ለኃጢአት ሥርየት የንስሀ ስብከት እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለችው አገር ሁሉ መጣ።
♦ነብይ
♦ሐዋርያ
♦ሰማዕት
♥ባሕታዊ
♥ካህን
♥ጻድቅ
♥መጥምቀ መለኮት
♥ድንግል
♥ጸያሔ ፍኖት
♥ተንከተም
♥ቃለ አዋዲ
♥መምህር ወመገሰፅ የሆነው ሴቶች ከወለዱት ሁሉ አንተን የሚያህል አይኖርም የቸባለልህ ዮሀንስ መጥምቅ ሆይ አማላጅነትህ አይለየን።

ሐምሌ 5ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያትየዮና ልጅ ስምዖን ጴጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው። ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው።በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር...
12/07/2025

ሐምሌ 5

ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
የዮና ልጅ ስምዖን ጴጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው። ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው።

በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሣ በማጥመድ አድጐ፣ ሚስት አግብቶ ዕድሜው ሃምሳ ስድስት ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው። በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ፣ በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል። ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል።

(ማቴ. ፲፮፥፲፯ ፣ ዮሐ. ፳፩፥፲፭)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሠራው ስሕተት ንስሐ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል። ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በኋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል። ምንም የእርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል።

በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል። አሕዛብ ግብራቸው የከፋ ነውና በኔሮን ዘመነ መንግስት በ88 አመቱ አካባቢ ሰማዕት ሁኗል።
የቅዱሳን ሐዋርያቱ በረከታቸው ትድረሰን

"ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ"   በበዓሉ የሚሰጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ሰኔ 12 የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አስመልክቶ፣ የመላእክትን አገልግሎት ከብሉይ ኪ...
18/06/2025

"ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ"
በበዓሉ የሚሰጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት

ሰኔ 12 የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አስመልክቶ፣ የመላእክትን አገልግሎት ከብሉይ ኪዳን፣ ከሐዲስ ኪዳን፣ ከዘመነ ሊቃውንት አስተምህሮ እንዲሁም የቅዱስ ሚካኤልን ልዩ ተራዳኢነት ከቅዱስ መጽሐፍና ከሊቃውንት ትምህርት በማጣመር በዝርዝር እንመለከታለን።

✍️የመላእክት አገልግሎት በብሉይ ኪዳን

በብሉይ ኪዳን መላእክት የእግዚአብሔር ፈቃድ አስፈጻሚዎች፣ መልእክተኞችና ጠባቂዎች ሆነው በተደጋጋሚ ተገልጸዋል።
✍️ መልእክተኛነት እና መገለጥ
መላእክት የእግዚአብሔርን መልእክት ለማድረስ ወደ ምድር ሲወርዱ እና ለሰዎች ሲገለጡ እናያለን። ለምሳሌ፣ አብርሃምን ልጅ እንደሚወልድ ያበሰሩት (ዘፍጥረት 18)፣ ሎጥን ከሰዶም ከመጥፋት ያዳኑት (ዘፍጥረት 19)፣ እንዲሁም ሙሴን በእሾህ ቁጥቋጦ ውስጥ የእግዚአብሔርን መገለጥ ያሳዩት መላእክት ናቸው (ዘጸአት 3÷2)።

✍️ ጠባቂነትና ረዳትነት
መላእክት የእግዚአብሔርን ሕዝብና ግለሰቦችን የሚጠብቁና የሚረዱ ናቸው። በዘፍጥረት 24÷7 ላይ አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ሚስት ለማምጣት በላከው አገልጋዩ ላይ "እግዚአብሔር መልአኩን በፊትህ ይልካል" በማለት የረዳትነት አገልግሎታቸውን ገልጿል። በነቢዩ ዳንኤል መጽሐፍ ውስጥ ደግሞ ዳንኤል ከአንበሶች ጉድጓድ የተረፈው መልአክ አፉን ስለዘጋ ነው (ዳንኤል 6÷22)።

✍️የቅጣት አስፈጻሚነት
አንዳንዴም የእግዚአብሔርን ፍርድና ቅጣት ለማስፈጸም መላእክት ተልከዋል (ዘፍጥረት 19:13፤ 2ኛ ሳሙኤል 24:16)።

✍️የመላእክት አገልግሎት በሐዲስ ኪዳን✍️
በሐዲስ ኪዳንም የመላእክት አገልግሎት ቀጥሏል፤ በተለይም ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፣ ሕይወት፣ ሞትና ትንሣኤ ጋር ተያይዞ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።

✍️ የወንጌል አብሳሪነት
ገብርኤል መልአክ ለዘካርያስ የዮሐንስን መወለድ (ሉቃስ 1÷11-20)፣ ለቅድስት ድንግል ማርያም ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት አበሰረ (ሉቃስ 1:26-38)። የኢየሱስን ልደት ለእረኞች ያበሰሩትም መላእክት ናቸው (ሉቃስ 2÷9-14)።

✍️አገልጋይነትና ረዳትነት
ኢየሱስ በምድረ በዳ በሰይጣን ከተፈተነ በኋላ መላእክት መጥተው አገልግለውታል (ማቴዎስ 4:11)። በጌቴሴማኒም በጸለየበት ወቅት መልአክ ከሰማይ ተገልጦ አበረታው (ሉቃስ 22:43)።

✍️ የትንሣኤ ምስክሮች
ክርስቶስ ከሙታን ከተነሳ በኋላ መቃብሩ ባዶ እንደሆነ ለመግደላዊት ማርያምና ለሌሎቹ ሴቶች ያበሰሩት መላእክት ናቸው (ማቴዎስ 28:2-7)።

✍️ በዳግም ምፅአት
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ሲመጣ ከመላእክቱ ጋር እንደሚመጣ ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል (ማቴዎስ 25÷31)።

✍️ የመላእክት አገልግሎት በዘመነ ሊቃውንት

ከሐዋርያት ዘመን በኋላ የነበሩት የቤተክርስቲያን አባቶችና ሊቃውንት ስለ መላእክት አገልግሎት ሰፊ ትምህርት ሰጥተዋል።

✍️ ጠባቂ መላእክት
ሊቃውንቱ እያንዳንዱ ሰው ጠባቂ መልአክ እንዳለው በስፋት ያስተምራሉ። ለምሳሌ፣ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ "እያንዳንዱ ምእመን ጠባቂ መልአክ አለው" ሲል ተናግሯል።

✍️ የእግዚአብሔር ፈቃድ አስፈጻሚዎች
መላእክት የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ለመፈጸም ፈጣን እንደሆኑና በፈጣሪና በሰው መካከል ድልድይ ሆነው እንደሚያገለግሉ ተብራርቷል።

✍️የፀሎት አቅራቢዎች✍️
በራዕይ 8÷3-4 ላይ መላእክት የቅዱሳንን ጸሎት ከዕጣን ጋር በእግዚአብሔር ፊት እንደሚያቀርቡ ስለሚነገር፣ ሊቃውንት ይህንን በመጥቀስ መላእክት ለሰዎች ጸሎት ምልጃ እንደሚያደርጉ ያስረዳሉ።

👉what is lifeWhat is life?Is life livingIs it moving or talkingOr eatingOr workingOr breathingWhat is it!Is life delight...
02/06/2025

👉what is life

What is life?
Is life living
Is it moving or talking
Or eating
Or working
Or breathing
What is it!
Is life delight
Or quite bright
Does it go straight
Or right and left
Or down and up
Or curve and sharp
What is life?
Is it full or half

👉👉👉
I will want to get critical response for the above poem from philosophical and spiritual dimensions.https://t.me/biezabieza
Highlights

01/06/2025

ዕርገት
ይህ ሳምንት ከብዙ በጥቂቱ የሚከተሉትን ሳምንት ይባላል
፩.የማረግ የመውጣት ሳምንት
፪.የተስፋ ሳምንት
፫.የደጅ ጽናት ሳምንት
፬.የትእዛዝ ሳምንት
፭.የቡራኬ ሳምንት
፮.የመሰናበት ሳምንት
፯.የመለየት ሳምንት ጌታ በሥጋ
፰.የመምረጥ ሳምንት ማትያስን
፱.የመሾም ሳምንት ሉቃ ፳፬.፵፭-ፍ ፩.፩-ፍ
ዕርገትን በተመለከተ ዮሐንስ አፈወርቅ አርባ ስድስተኛውን የዳዊትን መዝሙር በተረጎመበት የምርመራ መጽሐፋ እንግዲህ ድል መንሣት በአ ለበት የነጋሪት ድምፅ እግዚአብሔር ዐረገ አለ እርሱ ዐረገ አለ እንጂ መላእክት አሳረጉት አላለም በፊቱ መንገድ የሚመ ራ አልፈለገም በዚያው ጎዳና እርሱ ዐረገ እንጂ ኤልያስ በዚያ መንገድ እንደክርስቶስ እንዲህ ሊያ ደርግ አልቻለምና የኤ ልያስ ባሕርይ በዚህ መንገድ ሊያርግ አልቻለም መላእክት ወደታዘዙበት ቦታ ወሰዱት እንጂ አንድ አካል አንድ ባሕርይ የሚሆን የእግዚአብሔር ቃል ግን መላእክትን የፈጠረ ነው ና በሥልጣኑ ዐረገ ስለዚህም ወንጌላዊው ሉቃስ የሐዋርያትን ሥራ በሚናገር መጽሐፉ ወደ ሰማይ ሲያርግ ደቀመዛ ሙርቱ ወደርእሱ አቅንተው ያዩ እንደነበረ ተናገረ አሳረጉት አላለም ወይም ተሸከ ሙት አላለም ያረገ በት ቦታ ገንዘቡ ነውና ሕማም የሚስማመው ግዙ ፍ ሥጋን ተዋሕዶ ሳለ ከስቅ ለቱ አስቀድሞ በባ ሕር ላይ ከሔደ ነፋስን ከፍሎ ሲያርግ ቢታይ ማን ም ማን አይጠራጠር ሥጋውአልተለወጠምና።
ሃይ አበ ዮሐ አፈ 67.12-16 በዚህ የዕርገት ሰን በት ወንጌል መንፈስቅዱስን እስኪያገዩ በኢየሩ ሳሌም(በጽርሐ ጽዮን)ደጅ እንዲ ጸኑ በተስፋ እንዲ ጠብቁ በኢየሩሳሌም እንዲጸኑ እንዲቀመጡ እንዳ ይወጡ ታዝዘዋል።
ጌታ የካህናት የመምህራን
ኢየሩሳሌም የቤተክርስቲያን
ሐዋርያት የ70 አርዲእት 36 ቅዱሳት አንስት የመላው ምእመናን ምሳሌ
በሥርዓተቤተክርስቲያን እንድንጸና አምላክ ይርዳን
ግንቦት ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
ከDima Giyorgisገፅ

29/05/2025

በታደሰ ቴሌ ሰልባኖ የታፀፈው "ቅስም የሰበረው እርምጃ"በ1985 ዓ.ም የተፃፈ ታሪክን፤ፖለቲካና ወታደራዊ አሰላለፍ በደንብ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው።ፀሀፊው"ሞት የተፈረደበት 17 ወታደር(አይ ምፅዋ የሚል መፅሐፍም አላቸው......
ለምን ትዝ እንዳለኝ እኔጃ

23/05/2025

ስለ ሊቁ አራት አይና ጎሹ እነ አለቃ ለማ ከከተቡት፤የሞጣ ጊወርጊስ ሰ/ት/ቤት የ25ኛ አመት ምስረታ ካዘጋጀው መፅሔት በተጨማሪ እጓለ ወልደ ዮሀንስ የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ መፅሐፋቸው ላይ በዘመኑ ከነበሩ አሉ ከሚባሉ ሊቃውንት ብቻ ሳይሆን ስማቸውን አለም አቀፋዊ ከሆኑት ታላላቅ ሊቆች ከእነ አባ ጊወርጊስ ከእነ ቅ/ያሬድ ጋር ያነሷቹዋል።እንደ አለቃ ለማ ደግሞ ከመ/ር ኤስድሮስ ቀጥሎ ለመጽሐፍት ትርጓሜ ዋና መሠረቱ እርሳቸው እንደሆኑ ይናገራሉ።በአንድ ቀን 74 የመፅሐፍት ትርጓሜ መ/ር ማስመረቅ ዕፁብ ከማስባል ውጭ በምን ይገለጣል።ሊቁ ከታላቁ ዲማ ጊወርጊስ ገዳም ጋር በነገረ ሃይማኖት አለመግባባት እንደነበር ቢገለፅም ፤በቅኔ መጎሻሸም ቢኖርም እንደ አለቃ ለማ ተማሪዎቻቸው በገዳሙ አዘርግተው በደቀ መዝሙራቸው ፩.በእነ መ/ር ተጠምቀ መድኅን ጉባኤአስተምረዋል።፪.በመፍቀሬ ተዋሕዶው ዓፄ ቴዎድሮስ ዘመን በደብረ ታቦር ጉባኤ እንዴት በንጉሱ እንዴት ቅኔ ተሰጣቸው?
፫.ለምን እንደ ሌሎች መፍቀሬ ቅባት ተግሳፅ አልደረሰባቸውም?
፬.መ/ራቸውም ሆኑ ተማሪዎቻቸው የነገረ ተዋሕዶ አስተምሕሮት በሰፊው የሰበኩ ናቸው።እውነት ሊቁ የነገረ ቅባት ተከታይ ቢሆኑ ኑሮ ከደቀ መዝሙሮቻቸው ጉባኤ ዘርግቶ የእርሳቸውን አስተምሕሮ የሚከተል ባልጠፋም ነበር።እነ አቡነ አብርሀም የተባሉ አባቶች በዜና ጳጳሳት እንደ ተጠቀሰው ጎጃም ዙረው አስተምረው ቅባቶችን አጥምቀዋል ሊቁ የነገረ ተዋሕዶ እምነት ደጋፊ ናቸው ወደ ሚለው ይወስደናል።አንድ ዲማ አንድ አባት ጠይቄ ነበር ያለኝ ወንድም "የጉባኤ ቤት ፍክክር ስለነበር የእኛ ይበልጣል አይነት ለማሳየት በጥያቄ ለመፈተን የተደረገ ክርክር ይመስላል እንጂ በመጨረሻም በሕይወታቸው ፍፃሜ በተዋሕዶ ከበረ ብለው የሚያምኑ እንደሆነ መስክረው ነው ያረፉት"ብሎኛል።Dima የተባለው ገፅ እንዲ፦አራት ዓይና ጎሹትውልድ ሀገራቸው ደብረማርቆስ አካባቢ የውሽ ሚካኤል ተወለዱ።ነፍጠኛ ሥላሴ እንደሆነም ይነገራል።የተማሩት ሞጣ ጊዮርጊስ ከአቶ አደራነህ ነው።ከአቶ አደራነህ ቀጥለው በሞጣ ጊዮርጊስ ለብዙ ዘመናት ያስተማሩ ከ80 በላይ ታዋቂ ሊቃውንትን በትምህርት ወልደው ለቤተክርስቲያን ተተኪ ትው ልድን ማፍራት የቻሉ ሊቅ ነበሩ፣ከተማሪዎቻቸውም መካከል
፩.አለቃ ገብረ ኤልያስ ዘግራራም ደብረማርቆስ አካባቢ
፪.መምህር ሰው አገኘሁ ዘደብረ ወርቅ
፫.መምህር ጸበሉ ዘደብረ ዘይት፬.አለቃ እንግዳ ዘጽላሎ ፭.አለቃ እንግዳ ራብዓይ ዘጎንጅ ፮.አለቃ የተመኙ ዘሞጣ
፯.መምህር ሰው አገኘሁ ዘየትኖራ ዳግማዊ ፰.አለቃ ለምለም ወልደማርያም
፱.አለቃ ቀጨኔ ወልደማርያም ዘሸዋ
፲.አለቃ ሥነጊዮርጊስ ዘአንኮበር
፲፩.አለቃ ተክለ ጽዮን ፲፪.አለቃ ገብረየስ ዘደብረብርሃን
፲፫.አቡነ አብርሐም ይገኙበታል ከአራት ዓይና ጎሹ ከተማሩት ከእነዚህ ሊቃውንት የቤተክርስቲያንን ትምህርት ያልቀመሱ የሀገራችን ሊቃውንት ባለ መኖራቸውየነበረው አራት ዓይና ጎሹ የዕውቀት ማዕከል ሆነው ሊቃውንትን ይሰበስቡ እንደነበር ይታመናል።በዘመናቸው የጎጃሙ መስፍን ደጃዝማች ተድላ ጓሉ በግብር ጊዜ እርሳቸው በድንክ አልጋ ተቀምጠው ሊቁ አራት ዓይና ጎሹን በዙፋን አልጋ ያስቀምጧቸው ነበር።በመጨረሻ ጥር 29 ቀን በ1861 ዓ.ም አርፈው የውሽ ሚካኤል ተቀብረ ዋል የውሽ ሚካኤል ሂደው የተቀበሩበት ምክንያት በሥጋ የተወለዱበት ቦታ ስለሆነ ነው።
ሃይማኖትን በተመለከተ ቅብዓት ያለተዋሕዶ ተዋሕዶ አያከብርም በማለት ሁለቱንም ያምኑ እንደነበር ይነገራል ኋላ ግን በአጼ ቴዋድሮስ ደብረ ላይ።ገባኤ ተደርጎ ሃይማኖታቸው ተዋሕዶ እንደሆነ ወደተዋሕዶ እንደተመለሱ በቅኔያቸው አረጋግጠዋል ይሉናል።https://t

Address

Bieza
Motta
MOTTA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Misganaw Darie posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Misganaw Darie:

Share