Misganaw Darie

Misganaw Darie "በመጨረሻም ከጠላቶቻችን ንግግር የወዳጆቻችን ዝምታ አሳሰበ!!!✍️ሉተር ኪንግ
https://www.facebook.com/deramablebieza
https://t.me/biezabieza

ሐምሌ 5ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያትየዮና ልጅ ስምዖን ጴጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው። ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው።በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር...
12/07/2025

ሐምሌ 5

ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
የዮና ልጅ ስምዖን ጴጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው። ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው።

በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሣ በማጥመድ አድጐ፣ ሚስት አግብቶ ዕድሜው ሃምሳ ስድስት ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው። በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ፣ በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል። ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል።

(ማቴ. ፲፮፥፲፯ ፣ ዮሐ. ፳፩፥፲፭)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሠራው ስሕተት ንስሐ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል። ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በኋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል። ምንም የእርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል።

በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል። አሕዛብ ግብራቸው የከፋ ነውና በኔሮን ዘመነ መንግስት በ88 አመቱ አካባቢ ሰማዕት ሁኗል።
የቅዱሳን ሐዋርያቱ በረከታቸው ትድረሰን

"ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ"   በበዓሉ የሚሰጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ሰኔ 12 የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አስመልክቶ፣ የመላእክትን አገልግሎት ከብሉይ ኪ...
18/06/2025

"ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ"
በበዓሉ የሚሰጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት

ሰኔ 12 የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አስመልክቶ፣ የመላእክትን አገልግሎት ከብሉይ ኪዳን፣ ከሐዲስ ኪዳን፣ ከዘመነ ሊቃውንት አስተምህሮ እንዲሁም የቅዱስ ሚካኤልን ልዩ ተራዳኢነት ከቅዱስ መጽሐፍና ከሊቃውንት ትምህርት በማጣመር በዝርዝር እንመለከታለን።

✍️የመላእክት አገልግሎት በብሉይ ኪዳን

በብሉይ ኪዳን መላእክት የእግዚአብሔር ፈቃድ አስፈጻሚዎች፣ መልእክተኞችና ጠባቂዎች ሆነው በተደጋጋሚ ተገልጸዋል።
✍️ መልእክተኛነት እና መገለጥ
መላእክት የእግዚአብሔርን መልእክት ለማድረስ ወደ ምድር ሲወርዱ እና ለሰዎች ሲገለጡ እናያለን። ለምሳሌ፣ አብርሃምን ልጅ እንደሚወልድ ያበሰሩት (ዘፍጥረት 18)፣ ሎጥን ከሰዶም ከመጥፋት ያዳኑት (ዘፍጥረት 19)፣ እንዲሁም ሙሴን በእሾህ ቁጥቋጦ ውስጥ የእግዚአብሔርን መገለጥ ያሳዩት መላእክት ናቸው (ዘጸአት 3÷2)።

✍️ ጠባቂነትና ረዳትነት
መላእክት የእግዚአብሔርን ሕዝብና ግለሰቦችን የሚጠብቁና የሚረዱ ናቸው። በዘፍጥረት 24÷7 ላይ አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ሚስት ለማምጣት በላከው አገልጋዩ ላይ "እግዚአብሔር መልአኩን በፊትህ ይልካል" በማለት የረዳትነት አገልግሎታቸውን ገልጿል። በነቢዩ ዳንኤል መጽሐፍ ውስጥ ደግሞ ዳንኤል ከአንበሶች ጉድጓድ የተረፈው መልአክ አፉን ስለዘጋ ነው (ዳንኤል 6÷22)።

✍️የቅጣት አስፈጻሚነት
አንዳንዴም የእግዚአብሔርን ፍርድና ቅጣት ለማስፈጸም መላእክት ተልከዋል (ዘፍጥረት 19:13፤ 2ኛ ሳሙኤል 24:16)።

✍️የመላእክት አገልግሎት በሐዲስ ኪዳን✍️
በሐዲስ ኪዳንም የመላእክት አገልግሎት ቀጥሏል፤ በተለይም ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፣ ሕይወት፣ ሞትና ትንሣኤ ጋር ተያይዞ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።

✍️ የወንጌል አብሳሪነት
ገብርኤል መልአክ ለዘካርያስ የዮሐንስን መወለድ (ሉቃስ 1÷11-20)፣ ለቅድስት ድንግል ማርያም ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት አበሰረ (ሉቃስ 1:26-38)። የኢየሱስን ልደት ለእረኞች ያበሰሩትም መላእክት ናቸው (ሉቃስ 2÷9-14)።

✍️አገልጋይነትና ረዳትነት
ኢየሱስ በምድረ በዳ በሰይጣን ከተፈተነ በኋላ መላእክት መጥተው አገልግለውታል (ማቴዎስ 4:11)። በጌቴሴማኒም በጸለየበት ወቅት መልአክ ከሰማይ ተገልጦ አበረታው (ሉቃስ 22:43)።

✍️ የትንሣኤ ምስክሮች
ክርስቶስ ከሙታን ከተነሳ በኋላ መቃብሩ ባዶ እንደሆነ ለመግደላዊት ማርያምና ለሌሎቹ ሴቶች ያበሰሩት መላእክት ናቸው (ማቴዎስ 28:2-7)።

✍️ በዳግም ምፅአት
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ሲመጣ ከመላእክቱ ጋር እንደሚመጣ ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል (ማቴዎስ 25÷31)።

✍️ የመላእክት አገልግሎት በዘመነ ሊቃውንት

ከሐዋርያት ዘመን በኋላ የነበሩት የቤተክርስቲያን አባቶችና ሊቃውንት ስለ መላእክት አገልግሎት ሰፊ ትምህርት ሰጥተዋል።

✍️ ጠባቂ መላእክት
ሊቃውንቱ እያንዳንዱ ሰው ጠባቂ መልአክ እንዳለው በስፋት ያስተምራሉ። ለምሳሌ፣ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ "እያንዳንዱ ምእመን ጠባቂ መልአክ አለው" ሲል ተናግሯል።

✍️ የእግዚአብሔር ፈቃድ አስፈጻሚዎች
መላእክት የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ለመፈጸም ፈጣን እንደሆኑና በፈጣሪና በሰው መካከል ድልድይ ሆነው እንደሚያገለግሉ ተብራርቷል።

✍️የፀሎት አቅራቢዎች✍️
በራዕይ 8÷3-4 ላይ መላእክት የቅዱሳንን ጸሎት ከዕጣን ጋር በእግዚአብሔር ፊት እንደሚያቀርቡ ስለሚነገር፣ ሊቃውንት ይህንን በመጥቀስ መላእክት ለሰዎች ጸሎት ምልጃ እንደሚያደርጉ ያስረዳሉ።

👉what is lifeWhat is life?Is life livingIs it moving or talkingOr eatingOr workingOr breathingWhat is it!Is life delight...
02/06/2025

👉what is life

What is life?
Is life living
Is it moving or talking
Or eating
Or working
Or breathing
What is it!
Is life delight
Or quite bright
Does it go straight
Or right and left
Or down and up
Or curve and sharp
What is life?
Is it full or half

👉👉👉
I will want to get critical response for the above poem from philosophical and spiritual dimensions.https://t.me/biezabieza
Highlights

01/06/2025

ዕርገት
ይህ ሳምንት ከብዙ በጥቂቱ የሚከተሉትን ሳምንት ይባላል
፩.የማረግ የመውጣት ሳምንት
፪.የተስፋ ሳምንት
፫.የደጅ ጽናት ሳምንት
፬.የትእዛዝ ሳምንት
፭.የቡራኬ ሳምንት
፮.የመሰናበት ሳምንት
፯.የመለየት ሳምንት ጌታ በሥጋ
፰.የመምረጥ ሳምንት ማትያስን
፱.የመሾም ሳምንት ሉቃ ፳፬.፵፭-ፍ ፩.፩-ፍ
ዕርገትን በተመለከተ ዮሐንስ አፈወርቅ አርባ ስድስተኛውን የዳዊትን መዝሙር በተረጎመበት የምርመራ መጽሐፋ እንግዲህ ድል መንሣት በአ ለበት የነጋሪት ድምፅ እግዚአብሔር ዐረገ አለ እርሱ ዐረገ አለ እንጂ መላእክት አሳረጉት አላለም በፊቱ መንገድ የሚመ ራ አልፈለገም በዚያው ጎዳና እርሱ ዐረገ እንጂ ኤልያስ በዚያ መንገድ እንደክርስቶስ እንዲህ ሊያ ደርግ አልቻለምና የኤ ልያስ ባሕርይ በዚህ መንገድ ሊያርግ አልቻለም መላእክት ወደታዘዙበት ቦታ ወሰዱት እንጂ አንድ አካል አንድ ባሕርይ የሚሆን የእግዚአብሔር ቃል ግን መላእክትን የፈጠረ ነው ና በሥልጣኑ ዐረገ ስለዚህም ወንጌላዊው ሉቃስ የሐዋርያትን ሥራ በሚናገር መጽሐፉ ወደ ሰማይ ሲያርግ ደቀመዛ ሙርቱ ወደርእሱ አቅንተው ያዩ እንደነበረ ተናገረ አሳረጉት አላለም ወይም ተሸከ ሙት አላለም ያረገ በት ቦታ ገንዘቡ ነውና ሕማም የሚስማመው ግዙ ፍ ሥጋን ተዋሕዶ ሳለ ከስቅ ለቱ አስቀድሞ በባ ሕር ላይ ከሔደ ነፋስን ከፍሎ ሲያርግ ቢታይ ማን ም ማን አይጠራጠር ሥጋውአልተለወጠምና።
ሃይ አበ ዮሐ አፈ 67.12-16 በዚህ የዕርገት ሰን በት ወንጌል መንፈስቅዱስን እስኪያገዩ በኢየሩ ሳሌም(በጽርሐ ጽዮን)ደጅ እንዲ ጸኑ በተስፋ እንዲ ጠብቁ በኢየሩሳሌም እንዲጸኑ እንዲቀመጡ እንዳ ይወጡ ታዝዘዋል።
ጌታ የካህናት የመምህራን
ኢየሩሳሌም የቤተክርስቲያን
ሐዋርያት የ70 አርዲእት 36 ቅዱሳት አንስት የመላው ምእመናን ምሳሌ
በሥርዓተቤተክርስቲያን እንድንጸና አምላክ ይርዳን
ግንቦት ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
ከDima Giyorgisገፅ

29/05/2025

በታደሰ ቴሌ ሰልባኖ የታፀፈው "ቅስም የሰበረው እርምጃ"በ1985 ዓ.ም የተፃፈ ታሪክን፤ፖለቲካና ወታደራዊ አሰላለፍ በደንብ የሚያሳይ መጽሐፍ ነው።ፀሀፊው"ሞት የተፈረደበት 17 ወታደር(አይ ምፅዋ የሚል መፅሐፍም አላቸው......
ለምን ትዝ እንዳለኝ እኔጃ

23/05/2025

ስለ ሊቁ አራት አይና ጎሹ እነ አለቃ ለማ ከከተቡት፤የሞጣ ጊወርጊስ ሰ/ት/ቤት የ25ኛ አመት ምስረታ ካዘጋጀው መፅሔት በተጨማሪ እጓለ ወልደ ዮሀንስ የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ መፅሐፋቸው ላይ በዘመኑ ከነበሩ አሉ ከሚባሉ ሊቃውንት ብቻ ሳይሆን ስማቸውን አለም አቀፋዊ ከሆኑት ታላላቅ ሊቆች ከእነ አባ ጊወርጊስ ከእነ ቅ/ያሬድ ጋር ያነሷቹዋል።እንደ አለቃ ለማ ደግሞ ከመ/ር ኤስድሮስ ቀጥሎ ለመጽሐፍት ትርጓሜ ዋና መሠረቱ እርሳቸው እንደሆኑ ይናገራሉ።በአንድ ቀን 74 የመፅሐፍት ትርጓሜ መ/ር ማስመረቅ ዕፁብ ከማስባል ውጭ በምን ይገለጣል።ሊቁ ከታላቁ ዲማ ጊወርጊስ ገዳም ጋር በነገረ ሃይማኖት አለመግባባት እንደነበር ቢገለፅም ፤በቅኔ መጎሻሸም ቢኖርም እንደ አለቃ ለማ ተማሪዎቻቸው በገዳሙ አዘርግተው በደቀ መዝሙራቸው ፩.በእነ መ/ር ተጠምቀ መድኅን ጉባኤአስተምረዋል።፪.በመፍቀሬ ተዋሕዶው ዓፄ ቴዎድሮስ ዘመን በደብረ ታቦር ጉባኤ እንዴት በንጉሱ እንዴት ቅኔ ተሰጣቸው?
፫.ለምን እንደ ሌሎች መፍቀሬ ቅባት ተግሳፅ አልደረሰባቸውም?
፬.መ/ራቸውም ሆኑ ተማሪዎቻቸው የነገረ ተዋሕዶ አስተምሕሮት በሰፊው የሰበኩ ናቸው።እውነት ሊቁ የነገረ ቅባት ተከታይ ቢሆኑ ኑሮ ከደቀ መዝሙሮቻቸው ጉባኤ ዘርግቶ የእርሳቸውን አስተምሕሮ የሚከተል ባልጠፋም ነበር።እነ አቡነ አብርሀም የተባሉ አባቶች በዜና ጳጳሳት እንደ ተጠቀሰው ጎጃም ዙረው አስተምረው ቅባቶችን አጥምቀዋል ሊቁ የነገረ ተዋሕዶ እምነት ደጋፊ ናቸው ወደ ሚለው ይወስደናል።አንድ ዲማ አንድ አባት ጠይቄ ነበር ያለኝ ወንድም "የጉባኤ ቤት ፍክክር ስለነበር የእኛ ይበልጣል አይነት ለማሳየት በጥያቄ ለመፈተን የተደረገ ክርክር ይመስላል እንጂ በመጨረሻም በሕይወታቸው ፍፃሜ በተዋሕዶ ከበረ ብለው የሚያምኑ እንደሆነ መስክረው ነው ያረፉት"ብሎኛል።Dima የተባለው ገፅ እንዲ፦አራት ዓይና ጎሹትውልድ ሀገራቸው ደብረማርቆስ አካባቢ የውሽ ሚካኤል ተወለዱ።ነፍጠኛ ሥላሴ እንደሆነም ይነገራል።የተማሩት ሞጣ ጊዮርጊስ ከአቶ አደራነህ ነው።ከአቶ አደራነህ ቀጥለው በሞጣ ጊዮርጊስ ለብዙ ዘመናት ያስተማሩ ከ80 በላይ ታዋቂ ሊቃውንትን በትምህርት ወልደው ለቤተክርስቲያን ተተኪ ትው ልድን ማፍራት የቻሉ ሊቅ ነበሩ፣ከተማሪዎቻቸውም መካከል
፩.አለቃ ገብረ ኤልያስ ዘግራራም ደብረማርቆስ አካባቢ
፪.መምህር ሰው አገኘሁ ዘደብረ ወርቅ
፫.መምህር ጸበሉ ዘደብረ ዘይት፬.አለቃ እንግዳ ዘጽላሎ ፭.አለቃ እንግዳ ራብዓይ ዘጎንጅ ፮.አለቃ የተመኙ ዘሞጣ
፯.መምህር ሰው አገኘሁ ዘየትኖራ ዳግማዊ ፰.አለቃ ለምለም ወልደማርያም
፱.አለቃ ቀጨኔ ወልደማርያም ዘሸዋ
፲.አለቃ ሥነጊዮርጊስ ዘአንኮበር
፲፩.አለቃ ተክለ ጽዮን ፲፪.አለቃ ገብረየስ ዘደብረብርሃን
፲፫.አቡነ አብርሐም ይገኙበታል ከአራት ዓይና ጎሹ ከተማሩት ከእነዚህ ሊቃውንት የቤተክርስቲያንን ትምህርት ያልቀመሱ የሀገራችን ሊቃውንት ባለ መኖራቸውየነበረው አራት ዓይና ጎሹ የዕውቀት ማዕከል ሆነው ሊቃውንትን ይሰበስቡ እንደነበር ይታመናል።በዘመናቸው የጎጃሙ መስፍን ደጃዝማች ተድላ ጓሉ በግብር ጊዜ እርሳቸው በድንክ አልጋ ተቀምጠው ሊቁ አራት ዓይና ጎሹን በዙፋን አልጋ ያስቀምጧቸው ነበር።በመጨረሻ ጥር 29 ቀን በ1861 ዓ.ም አርፈው የውሽ ሚካኤል ተቀብረ ዋል የውሽ ሚካኤል ሂደው የተቀበሩበት ምክንያት በሥጋ የተወለዱበት ቦታ ስለሆነ ነው።
ሃይማኖትን በተመለከተ ቅብዓት ያለተዋሕዶ ተዋሕዶ አያከብርም በማለት ሁለቱንም ያምኑ እንደነበር ይነገራል ኋላ ግን በአጼ ቴዋድሮስ ደብረ ላይ።ገባኤ ተደርጎ ሃይማኖታቸው ተዋሕዶ እንደሆነ ወደተዋሕዶ እንደተመለሱ በቅኔያቸው አረጋግጠዋል ይሉናል።https://t

✏መረጃ የዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ ዉሎ 👉የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ጉዳይ♣.ሊቀ ጳጳሱ ተነስተው ሌላ ሊቀ ጳጳስ ይመደብ የሊቀ ጳጳሱ ምደባ ከሌሎቹ የምደባ ጥያቄ ጋር እንዲታይ፦ ♣ ያለ ቅዱስ ፓ...
21/05/2025

✏መረጃ
የዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ ዉሎ

👉የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ጉዳይ

♣.ሊቀ ጳጳሱ ተነስተው ሌላ ሊቀ ጳጳስ ይመደብ የሊቀ ጳጳሱ ምደባ ከሌሎቹ የምደባ ጥያቄ ጋር እንዲታይ፦

♣ ያለ ቅዱስ ፓትርያርኩ ፈቃድ የሔዱት መነኮሳትና መነኮሳይያት ቀኖናና ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው እዛው እንዲያገለግሉ እንዲደረግ ፦

♣. አምስቱ መነኮሳት እስከ አሁን በእግድ የቆዩበት እንደቀኖና ተቆጥሮላቸው በማስጠንቀቂያ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ ፦

♣. በቀጣይ ወደ ገዳማቱ የሚላኩ አባቶች በሕግና በመመሪያ እንዲሆን ተወስኗል።

👉ሀገረ ስብከት እንሁን በሚል ጥያቄ ያቀረቡት:-

♣. የራያ ስድስቱ ወረዳዎች

♣. የየም ዞን ልዩ ወረዳዎች

♣ የካማሿ ዞን ወረዳዎች ሀገረ ስብከት አንዲሆኑ ተወስኗል ፣ በእነዚህ እና የኢየሩሳሌምን እና የሚጠበቀው የጠቅላይ ሥራአስኪያጅ ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እንዲሁም የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ምደባ ጉዳይ በቀጣይ እንደሚታይ የመረጃ ምንጮቻችን ለኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ አድርሰውናል ።

♣የመሪ እቅድና የአዳዲስ ኮሌጆች ይቋቋምልን ጥያቄ ለነገ ተዛውሯል። ከሰዓት በኋላ የምዕራብ ካናዳ ጉዳይ ይታያል ተብሎ ይጠበቃል።

ታሪክ የትናንት ብቻ ሣይሆን የዛሬም የነገም ነው♥♥♥

"ዮሐንስ አፈ ወርቅ ፤ ዮሐንስ ዕንቆ ጳዝዮን ፤ ዮሐንስ ልሳነ ወርቅ"👉🏽 ትምህርቱ ያማረ ፣ አንደበቱ በወንጌል ትርጓሜ የታሸ ፣ የክርስቶስን አምላክነት ለአለም ሁሉ ያስተማረ የቤተ ክርስቲያ...
20/05/2025

"ዮሐንስ አፈ ወርቅ ፤ ዮሐንስ ዕንቆ ጳዝዮን ፤ ዮሐንስ ልሳነ ወርቅ"

👉🏽 ትምህርቱ ያማረ ፣ አንደበቱ በወንጌል ትርጓሜ የታሸ ፣ የክርስቶስን አምላክነት ለአለም ሁሉ ያስተማረ የቤተ ክርስቲያን ሊቅ ነው። የእመቤታችንን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለነገስታቱ ያስረዳ ፣ የሐዲስ ኪዳንን ጠንካራ ሀሳቦች አምላክ በገለጸለት የጥበብ መንገድና ለሰው በሚረዳ መልኩ የተረጎመ የቤተ ክርስቲያን ማኅቶት ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ።

👉🏽 ኢትዮጵያን በብርሃኑ ያበራ ፣ ሐዲስ ሐዋርያ ተብሎ የተጠራ ፣ የተክለ ሐይማኖት ፍልሰተ ዓጽሙ በዚሁ ቀን ይከበራል። ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳንን በህይወተ ስጋ ሳሉ ብቻ ሳይሆን ካረፉም በኋላ መልካም ስራቸውን ትዘክራለች። ቅዱሳንም በምድር ላይ እያሉ ብቻ ሳይሆን በክርስቶስ እቅፍ ሆነውም ሰውን እንድሚረዱ አማናዊቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለምዕመናን ታስተምራለች። የቅድስት ክርስቶስ ሰምራንም ዜና ተጋድሎ ሁልጊዜ ትዘክራለች።

👉🏽 አፈ ወርቅ ዮሐንስ ለንጉሱ ለአርቃድዮስ "ኢያእመራ ዮሴፍ እስከአመወለደት ወልደ ዘበኩራ" ያለውን የሐዋርያውን ቃል እንዲህ አስረድቶት ነበር።

👉🏽 በዘመኑ ንጉሱ አርቃድዮስ ሊቀጳጳሱ ዮሐንስ አፈወርቅ ነበሩ። እጠይቀዋለሁ ሲል ይዘነጋዋል ከእለታት በአንዳቸው ንጉሱ ከነሰራዊቱ ሊቀጳጳሱ ከነማህበሩ በተሰበሰበት ንጉሱ ሊቀጳጳሱን ኢያእመራ ዮሴፍ እስከአመወለደት ወልደ ዘበኩራ ያለው የሐዋርያው ቃል ወንዶች ሴቶችን ከወለዱ በኋላ በግብር እንዲያውቋቸው ከወለደች በኋላ በግብር አወቃት ማለት ነውን ብሎ ጠየቀው። ዮሐንስም መልሶ ይህ እስከ ፍጻሜ የሌለው እስከ ነው ኢወለደት ሜልኮል እስከ አመ ሞተት ይላል ከሞተች በኋላ ወለደች ማለት ነውን ፤ ኢተመይጠ ቋዕ እስከአመነትገ ማየአይኅ ይላል ከጎደለ በኋላ ተመለሰ ማለት ነውን ፤ ወአነ እሄሉ ምስሌክሙ እስከኅልቀተአለም ይላል ከዚያ በኋላ ከኛ ጋር አይኖርም ማለት ነውን? ይህም እስከ እንዲህ ያለ ፍጻሜ የሌለው እስከ ነው ብሎ አስረድቶታል።

👉🏽 አንድም ፍጻሜ ያለው ነው ለነቢያት በብዙ ኅብረመልክዕ የሚታይ ጌታ በማህጸኗ ባደረ ጊዜ ቦ አመ ታቅየሀይህ ከመ ፅጌ ሮማን ወቦ አመ ትጸዓዱ ከመ ጽጌረዳ ወቦ አመ ታህመለምል ከመ ሀመልማለ ገነት ወቦ አመ ታጽደለድል ከመ ጽጌ ናርዶስ ብርሌ ጠጅ ቢቀዱበት ጠጅ ፤ ጠላ ቢቀዱበት ጠላ ፤ ውሃ ቢቀዱበት ውሃ መስሎ እንዲታይ እመቤታችንም ጸንሳ ሳለች በብዙ ኅብረመልክዕ እየተለዋወጠች ትታየው ነበር ጌታን ከወለደች በኋላ ግን በአንድ ኅብረመልክዕ አውቋታል ብሎ ተርጉሞለታል።

👉🏽 ይህን ሲተረጉምለት ከሰገነት የነበረች የእመቤታችን ስዕል ከቦታዋ ላይ አፈፍ ብላ ተነስታ ሠናየ ተናገርከ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ሠናየ ተናገርከ ዮሐንስ ዕንቆ ጳዝዮን ሠናየ ተናገርከ ዮሐንስ ልሳነ ወርቅ ብላ ስማው ዞራ ከሰገነቷ ላይ ሄዳ ተቀምጣለች። ስታመሰግንም ከፊት በር እስከ ኋላ በር ድረስ ተሰምታለች በዚህ ጊዜ ንጉሱ ከወርቁ የጠራውን ፤ ከጃን ሸላሚ ብልሁን አስመጥቶ ሁለት ልሳናተ ወርቅ አሰርቶ አንዱን ከቤተ እግዚአብሔር አንዱን ከቤተመዛግብት አኑሮታል። ንጉሱ እንዲህ ብሎ ጠየቀ ሊቀጳጳሱ እንዲህ ብሎ መለሰ ለመባል ለዝክረ ነገር።

የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል በረከትና ረድኤት እንዲሁም ጥበቃ አይለየን።
tiktok.com/
Misganaw Darie
https://t.me/biezabieza
ከዮሐንስ እሸቱ ገፅ
𝑭𝒐𝒍𝒍𝒐𝒘𝒆𝒓𝒔.Christ Followers የክርስቶስ ተከታዮች
Highlights for Children

19/05/2025

ከዋኖች አለቆች መካከል ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ ፤ት/ዳን፲፥፲፫
ሠላም ለአፅፋረ እዴከ ሚካኤል ሆይ.. .........ከወራሪ ጠላት ታድናት ዘንድ ሰውነቴን እደ ኅሊናዋን ወደ አንተ ዘርግታ ትማልዳለችና፣ነፍሴን የረዳሁሽ መልአክ እኔ ነኝ አይዞሽ ደረስሁልሽ በላት።
በግንቦት ፲፪ ሊቀ መላዕክት ቅ/ሚካኤል የመታሰቢያ በዓሉን በድርሳነ ሚካኤል ያስቀምጠዋል።በዚህ ዕለት ነብዩ ዳንኤል በባቢሎን በጉርጓድ ተጥሎ ባለበት ሠዓት ቅ/ሚካኤል ዕንባቆም ለአጫጆች ሊወስድ የነበረውን ምግብ ወደ ነብዩ ዳንኤል ባቢሎን እንዲወስደው አንዲት የራስ ፀጉሩን አንጠልጥሎ ወስዶ መግቦታል።ከመገበው በኋላም ምግቡ ምንም ሣይጎድል እንደ ገና ዕንባቆምን ይሁዳ ለአጫጆች አድርሶታል።ይህ ታሪክ የሆነው ከ605 ባቢሎን ከወረዱ በኋላ ቅድመ ከልደተ ክርስቶስ እንደሆነ ይገለፃል።
#ዳንኤል ማለትም እግዚአብሔር ፈራጅ ነው ማለት ነው።ከመሳፍንት ቤተሰብ የተወለደ ትልቅ መተርጉም ነው።እግዚአብሔርን በማመኑ እግዚአብሔርም ሁሌ ከእርሱ ጋር ነው።ባቢሎንና ይሁዳን በሠከንድ ያገናኝና ይመግበዋል።ምግቡን በበረከት ይሞላለታል።
# # #የኦርቶዶክስ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ተዓምር፣ድርሳንም ሆነ ገድልን ስትዘክር አይናቸው የሚቀላ ሠዎች አስተምህሮታችን መፅሀፋዊ እንጂ አፋዊ አይደለም።ዛሬም ለዳንኤል የደረሰ መላዕክት ለእኛም ድረስልን እንለዋለን።
♦አቤቱ በኢትዮጵያ ሁነን ኑሯችን ባቢሎን ለሆን ልጆችህ የሚጠት ቀን ደርሷልና ተነሱ በለን!!!!
Telegram.. https://t.me/biezabieza
የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን, Followers
Daily Highlight

17/05/2025

የታሪክ ፤የፍልስፍና፤የህግ፣የልብ ወለድና ሃይማኖታዊ መፅሐፍትን ያገኙበታል።

02/08/2023

ከፀሐይ አጠገብ የነበረው ኮከብ

የአምላክ ሰው መሆንና ተወልዶ የማደጉ ዜና ሲነገር ሁልጊዜም የሚዘነጋ ክብሩ ግን ከብዙ ቅዱሳን ክብር የሚበልጥ አንድ ታላቅ ሰው ዛሬ በልቡናዬ ውል አለ፡፡ መቼም ከፀሐይ አጠገብ ያለ ኮከብ በፀሐይ ብርሃን ምክንያት መሸፈኑ አይቀርምና በተወለደው የጽድቅ ፀሐይ ፣ የሰላም ንጉሥ በልደቱ ደስታ ተውጠን ፣ በገብርኤል ብሥራት ፣ በድንግል ምስጋና ፣ በመላእክት ዝማሬ ተስበን የዘነጋነውን ፣ ድምቀት ሳያንሰው የተሸፈነውን ኮከብ የቅዱስ ዮሴፍን ነገር ባሰብኩኝ ጊዜ ክብሩን ለመናገር ልቡናዬ ተጨነቀ፡፡

በቅድስናው እያመንን ፣ ውለታውንም እያወቅን የምንዘነጋውን ምናልባትም አንዳንድ ሰዎች የድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለማቃለል ስሙን በክፉ ማስረጃነት ሲያነሱብን ከእነርሱ ሸሸን ብለን ሳናውቅ ከበረከቱ የሸሸነውን ጻድቅ ዛሬ ልዘክረው ብል ልቤ በጥፋተኝነት ስሜት ተጨነቀብኝ፡፡

ስለ እርሱ ብዙ ያልዘመርንበትን ፣ ብዙ ያልተቀኘንበትን ዘመን ሳስብ ‘ላዕከ ማርያም ቅዱስ ዮሴፍ ሆይ ስለረሳንህ ቀኛችን ትርሳን ፣ ስላላሰብንህም ምላሳችን ከትናጋችን ይጣበቅ’ ብዬ ይቅርታውን ለመለመን ተመኘሁ፡፡

ቅዱስ ዮሴፍን ማን ብለን እንጥራው? እርሱ እንደሆን እንደ አብርሃም ዘመዶቹን የተወ አማኝ ፣ እንደ ይስሐቅ የታዘዘውን ብቻ ያደረገ ትሑት ፣ እንደ ያዕቆብ በእምነት ግብጽ የወረደ ስደተኛ ነውና እርሱን ለመግለፅ እንደምን ያለ ቋንቋ እንጠቀም ይሆን?

እስቲ ንገሩኝ? ‘መልካሙን እረኛ’ ክርስቶስን የጠበቀውን እረኛ ቅዱስ ዮሴፍን ከቶ በምን ቃል እንገልጸዋለን? የአብን ልጅ ያሳደገውን (ሐፃኔ ወልደ አብ) ቅዱስ ዮሴፍን በምን ቅኔ እናወድሰው?

ሕዝቅኤል ያያትን የእስራኤል አምላክ ገብቶባት ለዘላለም የተዘጋችውን ደጅ የጠበቀውን ታማኝ ዘብ ፤ ‘ከበሩ ደጀ ሰላም መንገድ በዚያ ይገባል በዚያም ይወጣል’ ተብሎ የተነገረለትን የተዘጋችው በር ደጀ ጠኚ ፣ ከታላቅዋ ተራራ ከድንግል ማርያም ያለ ሰው እጅ ድንጋይ ተፈንቅሎ ሲወርድ ቆሞ የተመለከተውን የሐዲስ ኪዳኑን ዳንኤል ከቶ እንዴት ባለ ቃል እንገልጸዋለን?

በቤተ ልሔም ግርግም ውስጥ በላምና አህያ መካከል የተኛውን ሕፃን የተመለከተውንና እንደ ነቢዩ ዕንባቆም
‘በማዕከለ ክልዔ እንስሳ ርኢኩከ’ /በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ/ ሊል የሚቻለውን የቅዱስ ዮሴፍን ክብር በምን አቅማችን እንግለጸው?

ወደ ግብጽ ወርዶ ለወገኖቹና ለዓለም ሁሉ ምግብን እንዳቆየው የብሉይ ኪዳኑ ዮሴፍ ወደ ግብጽ በመከራ ተሰድዶ የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን ለሁላችን ላቆየልን ጻድቅ እንዴት ያለ የምስጋና ቃል እናዋጣ?
ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌገፅ የተወሰደ

ለቅዱስ ዮሴፍ ዝክር ሐምሌ 26
ከብርሃን እናት ገፆች የተቆረሰ
(ወተዘከረኒ ለኃጥእ ገብርከ ተክለ ማርያም )

አለቃ ገብረ ሐና ታላላቅ የሚባሉ ፈላስፎችን የሚያስንቁ እነ ሆፕስና አኩያንስ፣እነ አርስቶትልና ሶቅራጥስ፣እነ ኦገስቲንና ማኬቬሌን የሚወዳደሩ ሊቅ የናበጋ ጊወርጊስ ተወላጅ ነበሩ።
01/08/2023

አለቃ ገብረ ሐና ታላላቅ የሚባሉ ፈላስፎችን የሚያስንቁ እነ ሆፕስና አኩያንስ፣እነ አርስቶትልና ሶቅራጥስ፣እነ ኦገስቲንና ማኬቬሌን የሚወዳደሩ ሊቅ የናበጋ ጊወርጊስ ተወላጅ ነበሩ።

Address

Bieza
Motta
MOTTA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Misganaw Darie posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Misganaw Darie:

Share