Addis mereja

Addis mereja Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis mereja, Social Media Agency, Wellega, Nek'emte.

የወባ በሽታበደቡብ የሀገሪቱ ክፍል የወባ በሽታ ወረርሽኝ በሚመስል መልኩ በጣም ብዙ ሰው እየሞተ ነው። በወላይታ ብቻ በቀን ከ40-50 ሰው እየሞተ መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች ገልፀውልኛል። ...
20/10/2024

የወባ በሽታ

በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል የወባ በሽታ ወረርሽኝ በሚመስል መልኩ በጣም ብዙ ሰው እየሞተ ነው። በወላይታ ብቻ በቀን ከ40-50 ሰው እየሞተ መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች ገልፀውልኛል። ይህ ቁጥር በቀን የሚሞተውን በትክክል ላይገልፅ ይችላል፣ምክንያቱም በሽታው ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ ስለመጣ በተለይ በገጠራማው ክፍል በርካታ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። የህክምና ቁሳቁስ እና የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት በመፈጠሩ የሞት ቁጥሩ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በስልጤ፣በከምባታ፣ በጉራጌ ዞኖች እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ እና ዙርያው ወረርሽኙ ተባብሷል ብለዋል።
የክልሉ ጤና ቢሮ በበኩሉ ከ1.2ሚሊዮን በላይ አጎበር ለማሰራጨት እየሰራሁ ነው ብሏል።

በአንድ ሳምንት ብቻ ከ51 ሺህ በላይ የወባ ህሙማን ቁጥር ተመዝግቧል " - የአማራ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ብቻ ከ51 ሺህ 650 በላይ የወባ ህሙማን ቁጥር መመዝቡን የአማራ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

በክልሉ 40 ወረዳዎች 72 በመቶ የሚሆነው የወባ ስርጭት እንደሚሸፍኑም የኢንስቲትዩቱ የወባ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዳምጤ ላንክር የገለፁ ሲሆን የበሽታው ስርጭት አሳሳቢ በመሆኑ ልዩ ትኩረት እንደሚያስፈልገው አስረድተዋል።

የወባ በሽታ ስርጭት በክልሉ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ የገለፁት አስተባባሪው የ2017 በጀት ዓመት በባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 65.8 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ጠቁመዋል።

EBS TV Vs ኮንታ ዞንከኮንታ ዞን አስተዳደር የተላለፈ መልዕክትስለ አካባቢያችን በተሳሳተና ተገቢነት በሌለ አኳሃን በተለያዩ ሚዲያ አውታሮች የሚደረጉ አሉታዊ ድርጊቶች እንዲቆሙና እንዲታረ...
15/10/2024

EBS TV Vs ኮንታ ዞን

ከኮንታ ዞን አስተዳደር የተላለፈ መልዕክት

ስለ አካባቢያችን በተሳሳተና ተገቢነት በሌለ አኳሃን በተለያዩ ሚዲያ አውታሮች የሚደረጉ አሉታዊ ድርጊቶች እንዲቆሙና እንዲታረሙ ከኮንታ ዞን አስተዳደር የተላለፈ መልዕክት

የኮንታ ዞን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውስጥ ከሚገኙ ዞኖች አንዱ ሲሆን ዞኑ ከአዲስ አበባ በጅማ በኩል 450 ኪ.ሜ ርቀት ሲኖረው በሰሜን በኩል ከኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ በምስራቅ ከዳዉሮ ዞን፣ በምዕራብ ከከፋ ዞን እና በደቡብ በኩል ደግሞ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ጋር ይዋሰናል፡፡

ኮንታ ከሀገራችን ከሁሉም አካባቢዎች በተለያየ አጋጣሚ የመጡ ብሄር ብሄረሰቦች ያለአንዳች ልዩነት ለዘመናት በሰላምና በፍቅር ተከባብረው በጋራ የሚኖሩባትና ሰርተው ያተረፉባት፣ ኖረው ወልደው የከበሩባት የብዙኃን እናት ናት፡፡

የኮንታ ማህበረሰብ እንግዳ ተቀባይ የሆነ ቸር፣ደግና የዋህ ህዝብ መሆኑን እግር ጥሏቸው ለአንድ ቀን እንኳን ደርሰው የተመለሱ አካላት የሚመሰክሩት እውነታ ነው፡፡

ህዝቡ ሰላም ወዳድ የሆነ፣ከራሱ በላይ ለሌላው ሰላምና ደህንነት አብዝቶ የሚጨነቅ፣ ገራገር የመልካም እሴት ተምሳሌት የሆነ ህዝብ ነው፡፡

አካባቢያችን ኮንታ እንደ ሌሎቹ የሀገራችን አካባቢዎች ሁሉ የበርካታ ባህላዊ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶች የሚገኙበትና በሀገር መሪ አንደበት ጭምር "ኮንታ በምድር ላይ ከስዕል ውጭ ገነት የሚታይበት ምድር"መሆኑ ተመስክሮ ከአካባቢው ተፈጥሮ ጋር የሚሄዱ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች እየተገነባ ያለ አካባቢ ናት፡፡

ከማህበረሰባችን መልካም እሴትና ከአካባቢያችን ተፈጥሮ ሀብት ክምችት መነሻ የሀገር መሪዎች የትኩረት ማዕከል በመሆን የገበታ ለሀገር አካል የሆነው የኮይሻ ገበታ ለሀገር ፕሮጀክት፣ የጨበራ ዝሆን ዳና ሎጅ የሚገኝበት፣ የጨበራ ጩርጩራ ብሄራዊ ፓርክና በውስጡ የአፍሪካ ግዙፉ ዝሆን መገኛ፣ ከህዳሴ ግድብ ቀጥሎ ከፍተኛ የሆነና ሲጠናቀቅ 1,860 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚችል የኮይሻ ኃ/ኤ/ፓ/ ግድብ ያለበት አረንጓዴና ለምነት ከአመት አመት የማይለየው ውብ አካባቢ ነው፡፡

ኮንታ ስካይ ላይት የመሳሰሉ ትላልቅ የሆቴል ድርጅቶች የሚገኙበትና የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ዓመቱን ሙሉ የሚመላለሱበት የቱሪስት መዳረሻ የሆነ ከባቢ ነው፡፡

ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንድ የአካባቢያችን አርሶ አደር በቃላት አገላለጽ ጉድለት መነሻ የተላለፈው መልዕክት በተሳሳተ መንገድ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወጥቶ ብዙዎች ሲቀባበሉ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ይህ ግለሰብ በጫካ ውስጥ ያገኛቸውን የሀገር ውስጥ ጎብኚዎችን መንገድ እንዳይጠፋባቸውና ዝሆንና ሌሎች የዱር እንስሳትን ማግኘት የሚችሉበትን ትክክለኛ አቅጣጫ ቃላት እያጠረው በየዋህነት "በዚህ ከሄዳችሁ ኮንታ ትገባላችሁ" ያለውን ንግግር ከአውድ ውጪ በመውሰድ ተገቢነት በሌለውና በተሳሳተ መንገድ በማሰራጨት የአካባቢያችንና የህዝባችን መልካም ስም እንዲጎድፍና አካባቢው በመጥፎ እንዲቀረጽ ምክንያት እየሆነ መሆኑን ታዝበናል፡፡

የዚህ ግለሰብ የዋህነት የተሞላው ንግግርና አገላለጽ በኢትዮጵያዊ ጨዋ ባህልና አስተሳሰብ በመልካምነትና በአውንታ ተወስዶ መገለጽ ሲገባው ስለአካባቢው በቂ መረጃ በሌላቸው አካላት ዘንድ ጥርጣሬን ፈጥሯል፡፡
አሁንም በተሳሳተ ትርክት የመጥፎ ነገር ምሳሌ ሆኖ በተለያየ ማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች ሲገለጽ ይስተዋላል፡፡

ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነው በመላው ዓለም ተደራሽነት ያላቸው እንደነ ኢ.ቢ.ኤስ(ebs) የመሳሰሉ ትላልቅ ሚዲያዎችና አንዳንድ ማስታወቂያ የሚሰሩ ድርጅቶች ጭምር ይህን የግለሰቡን አገላለጽ የሚዲያ በማይገባ መንገድ ሲጠቀሙበት ይስተዋላል እሄ ስህተት ነው

15/10/2024

በባህር ዳር ከተማ ሙሉዓለም አዳራሽ ፊት ለፊት አምሳል ምትኬ የባህል ምሽት ላይ ቃጠሎ መነሳቱ ተነግሯል።

በጋዛው ጦርነት ላይ የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ ኢራን በእስራኤል ላይ ጥቃት ከመፈጸም እንደምትታቀብ አስታወቀችበነገው እለት በኳታር ወይም ግብጽ በሀማስ አና እስራኤል መካከል የተኩስ አ...
14/08/2024

በጋዛው ጦርነት ላይ የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ ኢራን በእስራኤል ላይ ጥቃት ከመፈጸም እንደምትታቀብ አስታወቀች

በነገው እለት በኳታር ወይም ግብጽ በሀማስ አና እስራኤል መካከል የተኩስ አቁም ድርድር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል

ኢራን ምን ያህል ጊዜ እንደምትታገስ ይፋ ባታደርግም የተኩስ አቁም ስምምነት የሚፈጸም ከሆነ በእስራኤል ላይ ጥቃት እንደማትሰነዝር አ
ኢራን የአስታውቃለች በጋዛው ጦርነት ላይ የተኩስ አቁም ስምምነት የሚፈጸም ከሆነ በእስራኤል ላይ እሰነዝረዋለሁ ያለችውን የአጸፋ ምላሽ እንደምታጤነው አስታወቀች፡፡

የሀገሪቱ የደህንነት ተቋም ከፍተኛ ባለስልጣን ለሮይተርስ እንደተናገሩት ቴልአቪቭ በኢራን ሉአላዊ ክልል ውስጥ በመግባት ለፈጸመችው ወንጀል ማካካሻው የተኩስ አቁም ስምምነት ብቻ ነው ብለዋል፡፡

የሀማስ የፖለቲካ ቢሮ ሀላፊ እስማኤል ሀኒየህ ግድያን ተከትሎ ቴሄራን በአይነቱ ከፍተኛ የተባለ ቀጥተኛ ጥቃት በእስራኤል ላይ እንደምትፈጽም ለሳምንታት ስትዝት ቆይታለች፡፡

የደህንነት ባለስልጣኑ ኢራን ከቀጠናው አጋሮቿ ጋር በመሆን ለተፈጸመው ጥፋት ተመጣጣኝ እርምጃ ለመውሰድ በቂ ዝግጅት አድርጋ ማጠናቀቋን አስታውቀዋል፡፡

በነገው እለት በኳታር ወይም በግብጽ በሀማስ እና እስራኤል መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ድርድር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፤ ይሁንና ኢራን የአጸፋ ምላሽ ከመስጠቷ በፊት ለድርድሩ ሂደት ምን ያህል ጊዜ እንደምትታገስ በይፋ አላሳወቀችም፡፡

የነጩ ቤተ መንግስት ቃል አቀባይ ጆን ኪርባይ በዚህ ሳምንት ኢራን የዛተችውን ጥቃት ልትፈጽም እንደምትችል የደህንነት መረጃዎች ማመላከታቸውን በትላንትናው እለት በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል፡፡

አክለውም የአጸፋ ምላሹ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ከመካሄዱ ወይም ውጤቱ ከመታወቁ በፊት የሚደረግ ከሆነ የድርድር ሂደቱ ላይ ጥላ እንደሚያጠላ ነው ቃል አቀባዩ የተናገሩት፡፡

የእስራኤል የመከላከያ ሚንስትር ዮቭ ጋለንት በበኩላቸው በቴሄራን እና በቤሩት የሚገኙ ሁኔታዎችን በቅርበት እየተከታተልን ነው፤ ጥቃት ሊሰነዘር የሚችለበትን ሁኔታ እና ኢላማ ላይ ቅድም ዝግጅት አድርገናል ብለዋል፡፡

በቅርብ ሳምንታት በቀጠናው እያየለ የመጣውን ውጥረት ለማርገብ አሜሪካ የተለያዩ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን በማድረግ ላይ ስትሆን ቱርክን ጨምሮ ሶስት የአካባቢው ሀገራት ቴሄራን ውጥረቱን ከሚያባበስ የአጸፋ ምላሽ እንድትታቀብ እንዲያግባቡ ሀላፊነት ሰጥታለች፡፡

ሮይተርስ እንደዘገበው ኢራን በዚህ የአጸፋ ምላሽ ማስፈራርያ የጋዛውን ጦርነት ማስቆም የምትችል ከሆነ ከፍተኛ ድል የሚጎናጽፋት ነው። ሆኖም ይህ የማይሳካ ከሆነ ቀጠናዊ ግጭት እንዲቀሰቀስ ባትፈልግም በቴልአቪቭ ላይ ጥቃት ከመሰንዘር ወደ ኋላ አትልም፡፡

ከዚህ ባለፈም ኢራን በድርድር ሂደት ላይ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ የጎንዮሽ ስብሰባዎች እና የዲፕሎማሲ ጥረቶች ላይ ተሳትፎ እንዲኖራት ትፈልጋለች ተብሏል፡፡

በትላንትናው እለት አሜሪካ ፣ ብሪታንያ ፣ ፈረንሳይ እና ጣሊያን ጥቃት ከመሰንዘር እንድትታቀብ ጥሪ ቢያቀርቡም ተሄራን ጥሪውን ሳትቀበለው ቀርታለች፡፡

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በታጣቂዎች ጥቃት 13 ሰዎች ህይወት አለፈ!በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ ውስጥ በትናንትናው ዕለት ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 13 ሰዎች ህይወት ማለፉ...
14/12/2023

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ በታጣቂዎች ጥቃት 13 ሰዎች ህይወት አለፈ!

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ ውስጥ በትናንትናው ዕለት ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 13 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ጆጅ በተባለ በአንድ ገጠራማ ቀበሌ ውስጥ ወደ ቡሬ ወረዳ በቆ ጣቦ በተባለ ስፍራ እህል ለመጫን በመኪና እየተንቀሳቀሱ ባሉበት ወቅት ጠዋት12፡00 ገደማ ላይ ጥቃቱ መፈጸሙን ነዋሪዎች አመልክተዋል፡፡

ጥቃቱ የደረሰበት የጆጅ ቀበሌ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሲሳይ አበዋ በጥቃቱ 13 ሰዎች ህይወት ማለፉን አረጋግጠዋል፡፡ ጽንፈኛ ያሏቸው ሐይሎች ጥቃቱን ማድረሳቸውን ገልጸዋል፡፡በተደጋጋሚ የታጣቂዎች ጥቃት ሰለባ በሆነችው የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ 10 ከሚደርሱ ቀበሌዎች 49ሺ የሚደርሱ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው እንደሚገኙ ተገልጿል። ዘገባው የዶይቸ ቬለ ነው።

የአቶ ታዬ ደንደአ ባለቤት ይኖሩበት የነበረውን ቤት ለቀው እንዲወጡ ታዘዙ!መንግሥትን ለመጣል ከሚንቀሳቀስ አማጺ ቡድን ጋር በማሴር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር...
14/12/2023

የአቶ ታዬ ደንደአ ባለቤት ይኖሩበት የነበረውን ቤት ለቀው እንዲወጡ ታዘዙ!

መንግሥትን ለመጣል ከሚንቀሳቀስ አማጺ ቡድን ጋር በማሴር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ቤተሰቦች ከሚኖሩበት የመንግሥት ቤት እንዲለቁ ተነገራቸው።

የአቶ ታዬን ሰኞ ምሽት በፀጥታ ኃይሎች ከቤታቸው ተይዘው መወሰዳቸውን ለቢቢሲ የተናገሩት ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ አለማየሁ፣ ማክሰኞ ጠዋት የመንግሥት ቤቶችን ከሚያስተዳድረው ተቋም አስከ ሐሙስ ድረስ ቤቱን ለቀው እንዲወጡ መታዘዛቸውን ገልጸዋል።

የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አባል እና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት እንደራሴው አቶ ታዬ ደንደአ ባለፉት ጥቂት ወራት በግል የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው እና በመገናኛ ብዙኃን ላይ በሚያንጸባርቁት ከመንግሥት አቋም በሚቃረን አስተያየታቸው መነጋገሪያ ሆነው ነበር።

ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ጋር ስለተካሄደው ድርድር መክሸፍ፣ ስለሙስና፣ በኦሮሚያ ክልል ስላለው ግጭት እና አዲስ አበባ ውስጥ ሊካሄድ ታቅዶ በተከለከለው ሰላማዊ ሰልፍ ዙሪያ መንግሥትን የሚተች ጠንካራ አቋም ማንጸባረቃቸውን ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በተጻፈ ደብዳቤ ከኃላፊነታቸው መባረራቸው ይታወ

14/06/2023

Address

Wellega
Nek'emte

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis mereja posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share