BALEE TIME

BALEE TIME Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from BALEE TIME, Music Award, Robe.

የነሐሴ 19 ቀን 2016 የዓለም ዜናበየመን የባሕር ዳርቻ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አሳፍራ ትጓዝ የነበረች  ጀልባ በመስቸሟ ቢያንስ 13 ሰዎች ሲሞቱ 14ቱ እስከአሁን ደብዛቸው አልተገኘም።ጀ...
25/08/2024

የነሐሴ 19 ቀን 2016 የዓለም ዜና
በየመን የባሕር ዳርቻ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አሳፍራ ትጓዝ የነበረች ጀልባ በመስቸሟ ቢያንስ 13 ሰዎች ሲሞቱ 14ቱ እስከአሁን ደብዛቸው አልተገኘም።
ጀልባዋ 25 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችና 2 የመናውያን የጀልባዋ ቀዛፊዎች አሳፍራ ከጅቡቲ የተነሳች ሲሆን በየመን የባሕር ዳርቻ እስከአሁን ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ መስጠሟ አለምአቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት በእንግሊዝኛ ምህጻሩ IMO አስታውቋል።

ሂዝቦላህ ከ320 ሚሳይሎችን በእስራኤል ላይ ማዝነቡን አስታወቀ። እስራኤል በበኩሏ የሂዝቦላህ ይዞታዎች ናቸው ባለቻቸው በደቡብ ሊባኖስ በሚገኙ ኢላማዎች ላይ መጠነሰፊ የአየር ጥቃት መፈጸሟን የሐገሪቱ መከላከያ ሰራዊት አስታውቋል። በጥቃቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የሂዝቦላህ ሮኬት ማስወንጨፊያዎች መውደማቸውንም አክሏል።

በፓኪስታን በደረሱ 2 የተለያዩ የአውቶብስ መገልበጥ አደጋዎች 44 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ። ከሞቱት 12ቱ ለሐይማኖታዊ ሥነ-ስርዓት ሲጓዙ የነበሩ ናቸው ተብሏል።

ሩስያ ለዛሬ አጥቢያ ሌሊት በሰሜንና ምዕራብ ዩክሬይን በፈጸመችው የድሮንና የሚሳይል በርካታ ጥቃቶች ቢያንስ 1 ሰው ሲሞት 29 ሰዎች መጎዳታቸውን የዩክሬይን ባለስልጣናት አስታወቁ።

ፖለቲካኢትዮጵያየነሐሴ 19 ቀን 2016 የዓለም ዜናTo play this audio please enable JavaScript, and consider upgrading to a web browser that supports HTML5 videoፖለቲካኢትዮጵያYohannes Gebreegziabher19 ነሐሴ 2016እሑድ፣ ነሐሴ 19 2016https://p.dw.com/p/...

06/12/2023

በአዲስ አበባ የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ በቅርቡ ይጀመራል ተባለ!

በአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ የማረጋገጥ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር የከተማዋ የመሬት፣ ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታወቀ። እስከ 2016 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ330 ሺህ በላይ ቁራሽ መሬቶችና የጋራ መኖሪያ ቤቶች በካዳስተር ሥርዓት እንደተመዘገቡም ተገልጿል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ግፋወሰን ዴሲሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በከተማዋ በ80 ሺህ የመሬት ይዞታዎችን እና 80 ሺህ ባለመብቶችን የማረጋገጥ ሥራ በቅርቡ ይጀመራል።

የመሬት ይዞታ የማረጋገጥ ሥራው ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በስተቀር በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተግባራዊ ይደረጋል ያሉት አቶ ግፋወሰን፤ ይህ የይዞታ ማረጋገጥ እወጃ ከተላለፈ ከአሥራ አምሥት ቀን በኋላ የይዞታ ይረጋገጥልኝ ጥያቄዎች ማቅረብ ይቻላል ብለዋል። የማረጋገጥ ሥራውም በ80 ቀታናዎችና በ320 ሰፈሮች እንደሚከናወን ጠቁመዋል።

በከተማዋ 444 ሺህ ቁራሽ መሬት እና 750 ሺህ ባለመብቶች አሉ ያሉት አቶ ግፋወሰን፤ ከዚህ ውስጥ በዘመናዊ የመሬት ይዞታ ምዝገባ ሥርዓት የተከናወነባቸው ቁራሽ መሬቶች 172 ሺህ ሲሆኑ 335 ሺህ የሚሆኑት ደግሞ የግል ይዞታዎች በሊዝ እና በኪራይ የሕዝብ መጠቀሚያ ቦታ ያላቸው ባለመብቶች ናቸው ብለዋል።

እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ፤ ይዞታዎቹ የግል ይዞታዎች በነባርና በሊዝ ስሪት፤ አረንጓዴ መሠረተ ልማት፣ መንገድ፣ ክፍት ቦታ፣ የአስተዳደር ቦታዎች እና ሌሎችን ይጨምራል። በዘመናዊ የመሬት ይዞታ ምዝገባ ሥርዓት በዋናነት ሁለት ዓይነት ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን አንደኛው የሪል እስቴት ካዳስተር ነው። ሁለተኛው ደግሞ መብት ክልከላና ኃላፊነትን የሚመዘግብ ሥርዓት ነው።

በዘንድሮ በጀት ዓመት ሥር ነቀል የሆነ የይዞታ ማረጋገጥ ሥራ ይሠራል ያሉት አቶ ግፋወሰን፤ በጀት ዓመቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ በአምሥት ክፍለ ከተሞች የካዳስተር ሥርዓት ሙሉ ለሙሉ እውን ይሆናል። እነዚህም አራዳ፣ ቂርቆስ፣ ልደታ፣ ጉለሌና አዲስ ከተማ ናቸው ብለዋል።

በከተማዋ ካሉት 424 ሺህ በላይ የመሬት ይዞታዎች መካከል በዘመናዊ የመሬት ይዞታ ምዝገባ ሥርዓት የተከናወነባቸው ከ330 ሺህ በላይ ቁራሽ መሬቶችና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ናቸው። በዘንድሮ ሩብ ዓመት 53 ሺህ የመሬት ይዞታዎች ወደ ካዳስተር ሥርዓት መግባቱን ገልጸዋል።

በ2015 በጀት ዓመት ወደ ካዳስተር ሥርዓት የገባው 120 ሺህ የመሬት ይዞታዎች ሲሆኑ የ2016 በጀት ዓመት እቅዱ ደግሞ 120 ሺህ የመሬት ይዞታዎችን ወደ ዘመናዊ የካዳስተር ሥርዓት ለማስገባት እየተሠራ እንደሆነም ተናግረዋል።

በይዞታ ማረጋገጥ ሂደት ከሚያጋጥሙት ተግዳሮቶች ውስጥ የባለይዞታዎች ማመልከቻ አለመያዝ፣ አጎራባች አለመፈራረም፣ የባለይዞታዎች ግንዛቤ ማነስ ተጠቃሽ ናቸው ያሉት አቶ ግፋወሰን፤ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ሁሉም ክፍለ ከተማ የመረጃ ማሰባሰብና ማደራጀቱን ሥራ አጠናቀው ለይዞታ ማረጋገጥ እወጃ ዝግጁ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

ኤጀንሲው በ7ኛው ዙር የይዞታ ማረጋገጥ እወጃ ከ160ሺ በላይ ቁራሽ መሬቶችንና የጋራ መኖሪያ ቤቶችን አረጋግጦ በካዳስተር ሥርዓት ለመመዝገብ የዝግጅት ምዕራፍ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

06/08/2022

◈ የእስራኤል የአዬር ጥቃት በፍልስጢን ጋዛ የብዙዎችን ሕይዎት ቀጥፏል‼
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

በጋዛ ሰርጥ እና በእስራዔል መካከል የተከፈተው የከባድ መሳሪያ ተኩስ ልውውጥ አዲስ ውጥረት በቀጣናው አንግሷል፡፡

ምሽቱን ከባድ መሳሪያዎች ሲተኮሱ አድረዋል፤በርካታ ቁጥር ያላቸው ሮኬቶችም ወደ እስራኤል ምድር ተወንጭፈዋል፡፡

በእስራዔል የአየር ጥቃት ቢያንስ አስር ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውን ተከትሎ ነው ከጋዛ በኩል እንዲህ ዓይነቱ ጥቃት የተሰነዘረው፡፡

የጋዛ ሰርጥ ሰማይም ደም ለበሰ፤የታጣቂዎቹ መሪ ታይሲር ጃባሪም ተገደሉ ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

እስራኤል ከፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ (ፒ አይ ጄ) ቡድን የተጋረጠ ስጋት አለብኝ የሚል ክስ ታቀርባለች ፡፡

እስራኤል በ1941 ዓ.ም በዴቪድ ቤንጎሪያን አማካኝነት ከ1ሺሕ 994 ዓመታት በኋላ ዳግም አገር ሆና ከተመሰረተችበት ጊዜ አንስቶ ፍልስጤማውያን በእስራዔል ኃይሎች ጫና በርትቶባቸዋል ፡፡

የፍልስጤም ጉዳይ በአረቡ ዓለም ያለውን ፖለቲካዊ አካሄድ የለወጠ ነው፡፡ዓረቦች ከእስራኤል ጋር ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቢያቋርጡም ግብጽ ከእስራኤል ጋር ወዳጅ በመሆን አረብ ነን ከሚሉ አገራት የቀደማት አልነበረም፡፡

በ1970ዓ.ም በግብጹ ፕሬዚዳንት አንዋር ሳዳት እና በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜናሒም ቤገን መካከል የተደረገው የካምፕ ዴቪድ ስምምነት መሆኑ ነው።

በወቅቱ ዩናይትድ ስቴትስ በፕሬዚዳንቷ ጂሚ ካርተር በኩል የካይሮ እና የቴል-አቪቭ አደራዳሪ እንደነበረች የሚዘንጋ አይደለም።
አሁንም የእስራኤል እና የራስ ገዟ ፍልስጤም
ፖለቲካዊ ሁኔታ መቋጫ አልተገኘለትም ፡፡

በአዲሱ የእስራኤል አየር ጥቃት የአምስት ዓመት ታዳጊ ህይወት አልፏል፡፡በርካታ ቁጥር ያላቸው ዜጎችም ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

ፒ ኤ ጄ ከ1መቶ በላይ ሮኬቶችን በማስወንጨፍ አጸፋዊ ምላሽ ሰጥቻለለሁ ብሏል፡፡ እስራኤል ንፁሐንን በገፍ እየጨፈጨፈች የሐገር ግንባታዋን፤ የግዛት ማስፋፋት እኩይ ተግባሯን ያለምንም ስጋት ስትፈፅም ዓለማቀፉ ማሕበረሰብ በዝምታ ማዬቱን ገፍቶበታል።

E/r Mohammed Jemal-ማሜ 🇪🇹🇪🇹

Address

Robe

Telephone

+97470973262

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when BALEE TIME posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category