26/10/2025
እንጂነር አያና ብሩ The Father of Modern Ethiopia Typography ተብሎ ይጠራል! 🙏❤👏
--
እንጂነር አያና ብሩ የአማርኛ ቋንቋ የጽሕፈት መሣሪያ ፈጠራ ባለቤት ነው። ኢንጂነር ኣያና ብሩ የአማርኛ ቋንቋ የጽሕፈት መሣሪያውንና በመሣሪያው የኣከታተቡን ዘዴ የፈጠሩ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው። ትውልድና እድገቱ በ ወለጋ ሆሮ ጉድሩ ነው። እንጂነር አያና የኢትዮጵያን ስክሪፕት ለአሁኑ ትውልድ ያስተዋወቁ በመሆኑ የዘመናዊ ታይፖግራፊ አባት (the father of modern Typography) የሚል ስም ተሰጥቶታል።
በ1930ዎቹ (1932 G.C) የመጀመሪያውን የአማርኛ ታይፕራይተር የፈጠረ ምሁር ነበሩ። ኢንጅነር አያና ኦሊቬቲ ከተባለ የጣሊያን ካምፓኒ ጋር ለ 40 አመታት ያህል ሰርቶ ነው ይህንን የአማርኛ ታይፕራይተር ግኝትን እውን ማድረግ የቻለው። የኣያና መሣሪያ ባይኖር ኖሮ የቢሮ ጽሑፎችን በእጅ ጽሑፍ ተጠቅሞ መቀጠል ማዛለቁ ስለሚያጠራጥር ኢንጂነር ኣያና ለዓማርኛ እድገት ክፍተኛ ኣስተዋጽዖ ኣድርገዋል።
የአማርኛ ታይፕራይተር የፈጠረ ኢንጅነር አያና ብሩ በግንቦት 1939 ዓ/ም በጽሑፍ መኪና ለመጀመሪያ ጊዜ በስነ ጥበብ ሚኒስቴር ተፈቅዶ ጽፎ ታትሞ ያወጣው ይህ ጽሁፍ ነበር። ይህንን የመጀሪያ በጽሁፍ መኪና የታተመውን ጽሁፍ አንቡት።
ከኣድዋ ድል በኋላ ኢትዮጵያውያን የእንግሊዝኛውን የታይፕራይተር ወይም የጽሕፈት መሣሪያ ኣጠቃቀም ከተረዱ ወዲህ መሣሪያውን ለኣማርኛ ቀለሞች እንዲያገለግል ለ85 ዓመታት ግድም ቢታገሉም ሳይሳካ ቀርቷል። በመካከሉ ከተደረጉት የተለያዩ ሙከራዎች መካከል የኢንጂነር ኣያና ብሩ ሥራ ኣንዱ ነበር። ዋናውም ችግር የመሣሪያው መርገጫዎች በኣማርኛ ፊደላት መብዛት የተነሳ በቂ ስለኣልነበሩ ፊደላቱን ከተለያዩ መርገጫዎች በመሰብሰብ በመቀጣጠል የሚያስከትብ ዘዴ ወደ ፲፱፻፳፭ ዓ.ም. ግድም ኣቀረቡ። በእዚህ ዘዴ “ሀ” ከኣንድ መርገጫ ከተከተበ በኋላ “ሁ” ፊደል የሚከተበው “ሀ” ጎን የመቀነስ ምልክትን ወይም “-” በማስቀመጥ ነበር። ይኸንኑ የመቀነስ ምልክት “ለ”፣ “ሐ”፣ “መ” እና የመሳሰሉት ጎን በማስቀመጥ “ሁ”፣ “ሉ”፣ “ሑ”፣ “ሙ” ስለሚመስሉ ኣንዱኑ መቀጠያ ለተለያዩ የፈጠራ ቁርጥራጮች እንዲሆን ተደረገ። እንደነ “ሹ” የመሳስሉትን በቅጥልጥል ለመክተብ ከ“ሰ” እና የመቀነስ ምልክት የተሠራውን “ሱ” ፊደል በሌላ መርገጫ ቀደም ብሎ ወይም ወደኋላ መልሶ ሌላ ረዥም መሰመር ከሌላ መርገጫ ከ“ሰ” ኣናት ላይ በማስቀመጥ ነበር የሚሠራው።
ይህ የቅጥልጥል ፊደል ኣሠራርና መኖር ዓማርኛ ባልሆነ ነገር ቀለሞቹን በመሰሉ ነገሮች የቢሮ ሥራ መሥራት ስለተቻለ ኣያና ብሩ ለኢትዮጵያ ታላቅ ባለውለታ ናቸው። የኣያና መሣሪያ ባይኖር ኖሮ የቢሮ ጽሑፎችን በእጅ ጽሑፍ ተጠቅሞ መቀጠል ማዛለቁ ስለሚያጠራጥር ኢንጂነር ኣያና ለዓማርኛ እድገት ክፍተኛ ኣስተዋጽዖ ኣድርገዋል። እንዲህም ሆኖ ትክክለኛውን የግዕዝ ቀለሞች የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ቀደም ብለው ሲጠቀሙባቸው ስለነበርና በኋላም ሲጠቀሙበት ስለነበረ የታይፕ ፊደል ከማተሚያ ቤቶቹ ጋር ግንኙንት ኣልነበረውም። የኣያና የጽሕፈት መኪና ቀለሞችም የዓማርኛ ፊደላት ኣልነበሩም፤ ሊሆኑም ኣይችሉም። ይህ ልዩነት ያልገባቸውና ከመቶ ያነሱ መርገጫዎች ላይ የተበተኑትን የታይፕ ቁርጥራቾጭ ከ፪፻ በላይ የሆኑት የዓማርኛ ቀለሞች ኣንድ የሚመስሏቸው ዛሬም ኣሉ።
ባሻዩ ታላቁ ኢንጅነር አያና ብሩ ተመራምረው የአማርኛ ፊደል ታይፕራይተር ባይፈጥሩ ኑሮ ዛሬ ላይ አዳሜ የአማርኛ ታይፕራይተር ኪቦርድ ላይ ባልፃፍሽ ነበር። የሚያሳዝነው ይህንን በፈጠሩ ታላቅ ሰው ላይ ስንት የዘረኝነት ቅርሻት የሚያቀረሹ አሉ።
__
ስም ከመቃብር በላይ ነው ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ!...
Via :FB