13/05/2025
News | መንግሥት ቆራጥ ውሳኔ ወስኗል🚨
ምሽቱን ቀንደኛ አመፅና አድማ ቀስቃሾችን መልቀም ተጀምሯል።
ለዛሬ በቀንደኞች ተጠርቶ የነበረው አድማና አመጽ በሁሉም ክልሎች ከሽፎ መደበኛ የጤና አገልግሎቶች ቀጥለዋል። በጥቁር አንበሳና ጳውሎስ ሆስፒታሎች የተወሰኑ አክራሪዎች በዜጎች ውድ ህይወት ለማፌዝ ሞክረዋል።
ከነገ ጠዋት ጀምሮ፥
1. ገና ኢንተርን ሳለ የሚያውከው ስልጠናው ይሰረዛል፣ ከትምህርት ገበታው ይሰናበታል፣
2. እስከ ጠዋት ሁለት ሰዓት በሥራ ገበታው ተገኝቶ ሪፖርት ያላደረገ ቅጥሩ ተሰርዞ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ይለጠፋል።
3. የህክምና ሙያና አክቲቪስትነት የተምታታበት ቀጣዩና የተመኘው መንግስት እስከሚመጣ ሌላ ስራ እንዲቀይር ይደረጋል።
ህግ ይከበራል 🇪🇹