05/07/2026
"ውሾች ይጮኻሉ፣ ግመሎች ይራመዳሉ" እያሉ የሚሳለቁብንን ሰዎች ስመለከት... እነዚህ "ውሾች" የሚሏቸው የዋሁንና ታጋሹን ህዝባችንን ይሆን?የሚል ጥያቄ አነሳብኝ✍️
አንድ እውነት አለ... ዛሬ ህዝብ ዝም ያለው ስለተመቸው ወይም ስለማያውቅ አይደለም። በፍርሃት፣ በቁጭት እና "ከዛሬ ነገ ይሻላል" በሚል ተስፋ ውስጥ ሆኖ ነገሮችን በትዕግስት እያየ ነው። ዝምታ ሰላም ማለት አይደለም፤ የንቀትና የበደል ጽዋ ሲሞላ ግን የዝምታው ፍንዳታ ያስፈራል። ዝምታውን ፍሩት!
ለወላይታ መብት መታገል ዛሬ ሳይሆን ትላንት ነበረበት! ካልታገለን፣ የራሳችንን መብትና ክብር ካላስከበርንማ የሌሎች ባሪያ መሆናችን እኮ የሩቅ አይሆንም። የባርነት ስሜት ምን ያህል ተስፋ አስቆራጭና አንገት አስደፊ እንደሆነ ያየውና የቀመሰው ብቻ ያውቀዋል። መብትና ግዴታ ምን እንደሆነ... በሰው ስር "ጆሮ ጠብ" ሆኖ ሶስት ድግሪ ለተሸከመ አሽቃባጭና ሆድ አደር መቼም አይገባውም!
የወላይታ ችግር የሁላችንም፣ የሁላችንም ቤት ያንኳኳ ህመም ነው። ወላይታ የሌለባት፣ ክብሯ የተናቀባት ኢትዮጵያ ለእኔ ምን ትጠቅመኛለች? ይህ የሚገባህ ግን ከቤት ወጥተህ በሰው ሀገር ስትኖር፣ ማንነትህ ሲናቅ ብቻ ነው። ከቤት ያልወጣ፣ ችግር ያላየ ሰው ስለ ወላይታ ክብርና ጥቅም አይገባውም። ለዚህ እኮ ነው የማንም ተላላኪ መጥቶ የነገረውን የሀሰት ተረት እንደ እውነት ተቀብሎ ወላይታንና ወገኑን አሳልፎ የሚሸጠው! የሌላ ሀገር ሰው በወላይታ መሬትና ላብ በልጽጎ፣ በገዛ ሀገሩ ላይ ይሰራል የእኛዎቹ የገዛ አባቱን እናቱን ሃገሩን ይሰርቃል።
ይህ ቁጭት የሁላችንም ነው። ዝምታችንን ፍሩት! የህዝብ እምባ በመሬት አይቀርም!