የካዎ ኮይሻ ወረዳ አከባቢ ጥበቃና ደን ልማት ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • የካዎ ኮይሻ ወረዳ አከባቢ ጥበቃና ደን ልማት ፅ/ቤት

የካዎ ኮይሻ ወረዳ አከባቢ ጥበቃና ደን ልማት ፅ/ቤት Kawo koysha woreda Environmental protection and Forest office 🇪🇹🇪🇹🎄🎄 ‼️to Controll Forest Development‼️

 #ሦሰት ቀን ብቻ ቀረ🌿🎄🎄🎄🎄🎄🎄 #"በመትከል_ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 24/2017 ዓ/ም የወረዳችን አጠቃላይ ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ ችግኝ በመትከል የበኩሉን ድርሻ በአገባቡ ሊ...
28/07/2025

#ሦሰት ቀን ብቻ ቀረ
🌿🎄🎄🎄🎄🎄🎄
#"በመትከል_ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 24/2017 ዓ/ም የወረዳችን አጠቃላይ ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ ችግኝ በመትከል የበኩሉን ድርሻ በአገባቡ ሊወጡ ይገባል፥ አቶ ደግፌ ኤርሚያስ

የወላይታ ዞን ሚልሻ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደግፌ ኤርሚያስ የዘንድሮ አንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር አስመለክቶ ያስተላለፉት መልዕክት፥

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መሪነት ላለፉት የለውጥ ዓመታት የሀገራችን አየር መዛባት ለመቆጣጠር እና በምግብ ዋስትና ረገድ ትልቅ ለውጥ ማምጣት የተቻለ እንዲሁም ከሀገር አልፎ በአፍሪካና በአለም ደረጃ ምርጥ ተሞክሮ የሚሆን ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ይህ የችግኝ ተከላ በአጠቃላይ ኢትዮጵያን ዘንድ ተቀባይነት ያገኘና የአከባቢው ገፅታ በመቀየር ለመኖር ምቹና ሳቢ እንዲሁም ከሰው ልጆች ጀምሮ ለአጠቃላይ ፍጥረታት ጤና ወሳኝ እየሆነ የመጣት ወሳኝ ተግባር ነው ብለዋል።

ይህንን ስራ በተሻለ ሁኔታ ለማስቀጠል በዘንድሮ ዓመት እንደ ሀገር "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል 700 ሚልዮን ችግኝ ለመትከል በተያዘው ዕቅድ መነሻ እንደ ወረዳችን ከ912,667 ዘጠኝ መቶ አስራ ሁለት ሽህ ስድስት መቶ ስልሳ ሰባት በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ ተይዞ ሰፊ ስራዎች እተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል።

በዚህም በወረዳችን ያሉ ከህጻናትና ከወጣቶች ጀምሮ አጠቃላይ የማህበረሰብ ክፍሎች በቀን 24/11/2017 ዓ ም ዕለተ ሐሙስ ሙሉ ቀን በዚህ ተግባር ላይ መዋል እንዳለባቸው ተጠቁመዋል።

በዕለቱ በወረዳ ደረጃ 912,667 ዘጠኝ መቶ አስራ ሁለት ስድስት መቶ ስልሳ ሰባት ችግኝ ለመትከል ሙሉ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ያለ ሲሆን በሁሉም ቀበሌ በተዘጋጀው ተከላ ቦታ ወይም በXY-ኮርድኔት በተያዘው ቦታ ላይ ጥራትን የጠበቀ ስራ ሌሊት 12 ሰዓት ጀምሮ ቀን ሙሉ መከናወን እንዳለበት ተገልጿል።

በዚህም ለንቅናቄው ስኬታማነት ከወዲሁ የተሻለ እንቅስቃሴ መደረግ ስለሚያስፈልግ የችግኝ ዝግጅትና ወደ ስፍራው የማጓጓዝ ስራ፣ የጉድጓድ ዝግጅት፣ የቅስቀሳ ስራ፣ የእርሻ መሳሪያ አቅርቦትና ሌሎች ተግባራት በዘርፉ አመራሮችና በባለድርሻ አካላት በጥብቅ ድሲፕሊን መመራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

"በመትከል ማንሰራራት" የዘንድሮ አንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ሰው እርስ በርስ ተቀናጅቶ ተናብቦ መስራት የየራሱን ድርሻ በአገባቡ መወጣት እንደሚገባ ተጠቁመዋል።

የዘንድሮ የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ 🌹🌲👉 በሀገር አቀፍ   #700  ሚሊዮን 🌹🌲👉በደቡብ ኢት/ያ  #60ሚሊዮን 🌹🌲👉በወላይታ ዞን  #17 ሚሊዮን  በላይ🌹🌲👉በካዎ ኮይሻ ወ...
28/07/2025

የዘንድሮ የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ
🌹🌲👉 በሀገር አቀፍ #700 ሚሊዮን
🌹🌲👉በደቡብ ኢት/ያ #60ሚሊዮን
🌹🌲👉በወላይታ ዞን #17 ሚሊዮን በላይ
🌹🌲👉በካዎ ኮይሻ ወረዳ 912,667 ችግኖች በላይ በአንድ ጀንበር ይተከላል።
🌲🌲🌲🌲🌲🌲🎄🎄🎄🎄🌿🌱🌱
በወረዳችን በዘንድሮው ክረምት #ሐምሌ 👉24/2017 ለሚከናወነው የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸዘው 912,667 ችግኞች ተዘጋጅተዋል።
🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄
ዘንድሮ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በወረዳችን 912,667 ችግኞች XY-ኮርዲኔት በተዘጋጀላቸው 12 የተከላ ቦታዎች ይተከላሉ።
🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳
የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም እንደሀገር ከተመራበት ጊዜ ጀምሮ የደን ሽፋናችን ዕድገት እያሳየ ይገኛል። በዚህም አገራችን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት እያደረገች ላለው ጥረት ሚናው የጎላ ነው።
🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀
በወረዳችንም በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ሥራ በርካታ ለውጦች ተመዝግበዋል። በሚደረጉ የተከላ ሥራዎች ተራሮች በደን እንዲሸፈኑ በማድረግ በተራራው ግርጌ በሚኖሩት ላይ የጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት አደጋ እንዳይደርስ በመከላከል ረገድ ችግኝ መትከል አይተኬ ሚናውን ይጫወታል።
🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲
በዚህ መሰረት በሐምሌ 24/2017 መላው የወረዳችን ህዝቦች፣ ሴቶችና ወጣቶች በአደረጃጀት በነቂስ በመውጣት በተከላ ፕሮግራሙ ላይ እንድትሳተፉ መልዕክቱን አቀርባለሁ።

ፔጁን , Like

 #ማሳሰቢያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀምሌ 24/2017 ዓ/ም ለሚካሄድ የአንድ ጀምበር ተከላ ትኩረት የሚሹ ጉዳዯች ተብሎ የተለዩ ነጥቦች•  በቂ የተከላ ጉድጓድ በሁሉም የተከላ ሳይቶች በተገቢ ...
25/07/2025

#ማሳሰቢያ

በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀምሌ 24/2017 ዓ/ም ለሚካሄድ የአንድ ጀምበር ተከላ ትኩረት የሚሹ ጉዳዯች ተብሎ የተለዩ ነጥቦች

• በቂ የተከላ ጉድጓድ በሁሉም የተከላ ሳይቶች በተገቢ መልኩ መዘጋጀቱን መረጋገጥ

• ለተከላ የደረሱ ችግⶉችን ቆጥሮ መለየትና ወደ ተከላ ቦታዎች በጥንቃቄ ማጓጓዝ

• በተከላ ላይ የሚሳተፍ ህዝብ በየማህበራዊ መሰረት በአደረጃጀት መለየትና ለተከላ ፕሮግራም መቀስቀስ

• ለተከላ አግልግሎት የሚውል የእጅ መሳሪያ ህዝቡ ይዞ እንድወጣ ማሳሰብ

• የሪፖርተሮችን ስልክ እንደሚሰራ እስከ ተከላ ቀን ድረስ ደጋግሞ መረጋገጥ

• ርፖርተሮች ዝግጁ ሆነው በተከላ ዕለት ማልደው ወደ ተመደቡበት የተከላ ቦታ በመሄድ ሪፖርት በSMS message እንድልኩ ማድረግ

• የSMS message ቁጥር ብቻ የሚቀበል ለሪፖርተሮች ማሳሰብ (በSMS message ላይ በማንኛውም ቋንቋ ቃላት መጻፍ፥ ኮማ መጠቀም፥ ሌላም ሌላም ነገር መጻፍ አያስፈልግም)።

• በዞን እና በወረዳ ደረጃ ከሁለቱ ተቋማት (ከግብርና እና ከደንና አከባቢ ጥበቃ) ኮማንድ ፖስት መሰየሙን አረጋግⶏ ለክልሉ ኮማንድ ፖስት ከእነ ስልልካቸው እስከ 19/11/2017 ጧት 4፡00 ድረስ ማሳወቅ

• በዞኖች የተሰየሙ ኮማንድ ፖስት ወደ ወረዳ እና ከወረዳ የተመደቡ ወደ ቀበሌ መውረዳቸውን ማረጋገጥ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአንድ ጀምበር  #60 ሚሊዮን ችግኝ ይተከላል። #ሐምሌ 24/2017እንዘጋጅ!
25/07/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአንድ ጀምበር #60 ሚሊዮን ችግኝ ይተከላል።
#ሐምሌ 24/2017
እንዘጋጅ!

 #በአንድ ጀምበር  #700ሚሊዮን  ችግኝ እንትከል ።
24/07/2025

#በአንድ ጀምበር #700ሚሊዮን ችግኝ እንትከል ።

ሐምሌ 24 ቀን 2017ዓ.ም 700 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀንበር።

እንዘጋጅ!

#አረንጓዴዐሻራ



🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲የካዎ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አበባየሁ ዮሐንስ የተለያዩ የግብርና ልማት ስራዎችን ያሉበት ደረጃ ለማየት መስክ ምልከታ አደረጉ 🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🥀🥀🥀🥀🎋🎋 ፣...
10/04/2025

🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲የካዎ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አበባየሁ ዮሐንስ የተለያዩ የግብርና ልማት ስራዎችን ያሉበት ደረጃ ለማየት መስክ ምልከታ አደረጉ 🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳🥀🥀🥀🥀🎋🎋

፣ ሚያዝያ 2/2017 ዓ.ም
የካዎ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አበባየሁ ዮሐንስ የ2017 በጀት ዓመት የተለያዩ የአሬንጓዴ አሻራ ቅድሜ ዝግጅት ስራዎችን ያሉበት ደረጃ ለማየት መስክ ምልከታ አደረጉ።

🌲🌲በምልከተው ለአሬንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ዘርፈ ብዙ ጠቀመታ ያላቸውን የተለያዪ የደን ችግኝ ስራዎች ያሉበት ደረጃ እና ለበልግ ተከላ የደረሱ ችግኞችንና ለበልግ ወቅት ችግኝ ተከላ እየተዘጋጀ ያለው ጓድጓድ ቁፋሮ ሰራም ጭምር ታቅዶ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆኑን እና ትልቅ ለአረንጓዴ አሻራ ለትውልድ ቅርስ መሆኑን ተመላክቷል።

🌲🌲በግብርና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እና ሌሎችም የግብርና ልማት ስራዎችን ያሉበት ደረጃ ተዘዋውረው ጎበኝተዋል።

በመስክ ምልከታው የካዎ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አበባየሁ ዮሐንስ፣ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላቸው በቀለ፣ የወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ቤት ምሁራን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ላምበቦ ቡልአሞ ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በጉብኝት ቦታ ተገኝተዋል።

በዞኑ ለነባር ደኖች የሕጋዊ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት በመስጠት የመንከባከብና የመጠበቅ ሥራ መሰራት አለበት፦ዶ/ሮ ዳንኤል ዳሌቦምቤ፤የካቲት 26/2017 የወላይታ ዞን አከባቢ ጥበቃና ደን ል...
05/03/2025

በዞኑ ለነባር ደኖች የሕጋዊ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት በመስጠት የመንከባከብና የመጠበቅ ሥራ መሰራት አለበት፦ዶ/ሮ ዳንኤል ዳሌ

ቦምቤ፤የካቲት 26/2017 የወላይታ ዞን አከባቢ ጥበቃና ደን ልማት ጽ/ቤት ከባለድርሻ አካላት በመሆን በዞኑ ለሚገኙት ነባር ደኖች የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ምዝገባ ማስጀመሪያ ንቅናቄ መድረክን አካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የወላይታ ዞን ም/አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ዳንኤል ዳሌ ንቅናቄውን ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር መቀናጀት ያስፈልጋል ብለዋል።

ደን ህይወት ነው ህይወትን ይሰጣል፣ ደን ሀብትም ጭምር እንደሆነ የተናገሩት ም/አስተዳዳሪው ህብረተሰቡ ለደኖች ትኩረት እንዲሰጥ ያለውን ፋይዳና ጠቀሜታውን ማስገንዘብ ያስፈልጋልም ብለዋል።

ደኖችን የሚጠበቁበትና የሚንከባከቡበት ህጋዊ ስርዓትን መበጀት ይገባል ያሉት ም/አስተዳዳሪው የደን መብትንም ማረጋገጥ እንደሚገባም አመላክተዋል።

ደንን በመጨፍጨፍ ማጥፋት ቀላል እንደሆነ የተናገሩት ም/አስተዳዳሪው ደንን ተክሎ ማሳደግ ግን እጅግ ከባድ እንደሆነም አስገንዝበዋል።

የዘርፉ ባለሙያዎች ለደኖች ይዞታን ማስጠበቅ ይኖርባቸዋል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የይዞታ ማረጋገጫ እንዲኖረው ማድረግ እንደሚያስፈልግም ጠቅሰዋል።

በዞኑ የሚገኙ ለነባር ደኖች የሕጋዊ ይዞታ ማረጋገጫ በመስጠት የመንከባከብና የመጠበቅ ሥራ መሰራት እንዳለበትም ተናግረዋል።

የመሬት አጠቃቀምና ስርጭት በትክክለኛ በሆነ አገባብ መሆን እንደሚገባ ያሳሰቡት ም/አስተዳዳሪው የመሬት አጠቃቀም ስርዓቱ በትኩረት መምራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

በማሳ እና በመስኖ አውታሮች አከባቢ የሚገኙ ባህር ዛፍን በመንቀል በሰብል የመተካት ስራ በሁሉም አከባቢዎች መጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል።

የወላይታ ዞን አከባቢ ጥበቃና ደን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መርክነህ ማለዳ በዞኑ በግል፣ በማኅበረሰብና በመንግስት የሚገኙ የደን ዓይነቶችን በመለየት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር በመስጠት በተፈጥሮ ደን ሀብቶች ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስ ያለመ መድረክ መሆኑንም ገልፀዋል።

ይህም ጽ/ቤቱ ከገጠር መሬት አስተዳደር ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀትና በመተባበር የሚተገበር መሆኑን አስታውቀዋል።

በየአካባቢው በደን የተሸፈኑ መሬቶችን ህጋዊ ማረጋገጫ መስጠት ያስፈልጋል ያሉት አቶ መርክነህ ማረጋገጫ መስጠቱ ያሉ ደኖችን በዝርዝር ለመያዝ እጅግ ወሳኝ እንደሆነም ገልጸዋል።

የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ም/ኃላፊና የገጠር መሬት አስተዳደር ዘርፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስፋው ሴታ የደን መሬቶችን ባለቤትነት ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን ማበርከት ይጠብቅባቸዋል ብለዋል።

ደንን ለማስተዳደርና በዘርፉ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ከገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጋር የተሟላና የተረጋገጠ መረጃ መያዝ ወሳኝ እንደሆነም አስገንዝበዋል።

የመሬት ሀብት በዘላቂነት ለመጠቀም የሚያችል ስርዓት በመዘርጋት ለልማት ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ያስፈልጋልም ብለዋል።

በንቅናቄው መድረክ የጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አባላትና የወረዳና ከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

26/02/2025
26/02/2025
24/02/2025
24/02/2025

Address

Kawo Koysha
Sodo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የካዎ ኮይሻ ወረዳ አከባቢ ጥበቃና ደን ልማት ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share