Dicha Media

Dicha Media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dicha Media, Media/News Company, Wolaita s**o, Sodo.

ይሄ ድቻ ሚዲያ የዜና እና የወቅታዊ መረጃ ገጽ ነው። አንዳዲስ መረጃ ለማግኘት Like Page የሚለውን በመጫን Follow ያድርጉ! መረጃ ሲኖራችሁ፣ የሚዲያ ሽፋን ስትፈልጉ በውስጥ መስመር inbox ያድርጉልን ወይም በቴሌግራም በኩል ላኩልን።

👉5 እውነታዎች👈- አንዳንዴ እየወደድክ የምትርቀው አንዳንዴ ደግሞ እየጠላህ የምትቀርበው ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ አብረህ የምትኖረው ሰው አለ- አንዳንዴ ፍቅሩን ሳይገልጽልህ የሚወድህ አንዳን...
10/09/2025

👉5 እውነታዎች👈

- አንዳንዴ እየወደድክ የምትርቀው አንዳንዴ ደግሞ እየጠላህ የምትቀርበው ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ አብረህ የምትኖረው ሰው አለ

- አንዳንዴ ፍቅሩን ሳይገልጽልህ የሚወድህ አንዳንዴ ደግሞ እወድሃለው እያለ የሚጠላህ ብዙ ጊዜ ግን ስሜቱን የማታውቀው ሰው አለ

- አንዳንዴ እየራበህ የማትበላው አንዳንዴ ደግሞ ጠግበህ የምትመገበው ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ የምትውጠው ነገር አለ

- አንዳንዴ ሳትኖር የምትሞትበት አንዳንዴ ደግሞ ሞተህም የምትኖርበት ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ የምትጓዝበት ህይወት አለ

- አንዳንዴ አስደስቶህ የምታለቅስበት አንዳንዴ ደግሞ አሳዝኖህ የምታለቅስበት ብዙ ጊዜ ግን ዝም ብለህ የምታነባበት ጉዳይ አለ። በቃ ህይወት እንደዚህ ናት

ጊፋታ ዋዜማ ሲደርስ ቀናት ከሚመገቡት ምግብ እና ከሚሰሩት ክንውን ጋር ሲሆን። 1. Kosetta Shagaa - ሐሙስ ነው የሚከበረው 2. Sul"aa Bizzaa - አርብ ዕለት ይውላል 3. B...
10/09/2025

ጊፋታ ዋዜማ ሲደርስ ቀናት ከሚመገቡት ምግብ እና ከሚሰሩት ክንውን ጋር ሲሆን።

1. Kosetta Shagaa - ሐሙስ ነው የሚከበረው
2. Sul"aa Bizzaa - አርብ ዕለት ይውላል
3. Baccira Qeeraa - ቅዳሜ ይከበራል
4. Shuha Woggaa - ጊፋታ 1 ሲሆን እሁድ ይከበራል
5. Tamma Sagga - ጊፋታ 2 ሰኞ ይውላል
6. Ciishshaa galla - ዘመድ ጥየቃ ሲሆን ማክሰኞ ይውላል
7. Gaze Woliilaa - የጋዜ ጫወታ ቀን ሲሆን ረቡዕ ነው

Yoo Yoo Gifaataa🖤

የሀላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በፊፋ ምዘና ተደረገለትየሀላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም መጫወቻ ሜዳ በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ባለሙያ ምዘና ተደርጎለታልምዘናውን ያከናወነው የፊፋ ...
10/09/2025

የሀላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም በፊፋ ምዘና ተደረገለት

የሀላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም መጫወቻ ሜዳ በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ባለሙያ ምዘና ተደርጎለታል

ምዘናውን ያከናወነው የፊፋ ባለሙያ እንግሊዛዊው ኮሊን መጫወቻ ሜዳው ጨዋታ ለማከናወን ብቁ መሆኑን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገልጿል

ሜዳው ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ እንደተሰራ በመግለፅ የትኛውንም አይነት ጨዋታ የማከናወን አቅም እንዳለው በምርመራችን አረጋግጠናል ነው ያለው፡፡

የፊፋን አሰራር ጠብቆ መጫወቻ ሜዳው ፈቃድ ሲያገኝ ከድሬዳዋ ቀጥሎ በሀገራችን ሁለተኛው የፊፋ ፈቃድ ያለው የአርቴፊሻል ሜዳ ይሆናል።

ግንባታውን ያከናወነው የታን ኢንጂነሪንግ ባለቤት ፎዓድ ኢብራሂም በሀገራችን ያለውን የመጫወቻ ሜዳ እጥረት ለመቅረፍ እንሰራለን ብለዋል፡፡

በቅርቡ በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ ደረጃውን የጠበቀ አርቴፊሻል መጫወቻ ሜዳ ገንብተን እናጠናቅቃለን ሲልም ጠቁሟል።

ሙሉ በሙሉ ከህዝብ በሚሰበሰብ ገንዘብ እየተሰራ ያለው የሀላባ ስታዲየም ሙሉ ግንባታውን ለማጠናቀቅ አስቀድሞ በወጣ ግምት 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ይፈጃል ተብሏል።

✍| ፋና ቲቪ

ሀሰተኛ ክስ የተቀነባበረው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተደድር ነው* የማራ ማየንስ ባለቤት አደረሰ የተባለዉ ጉዳት 1.3 ቢሊዮን ይላል* ይሄ ሁሉ ጉዳት የደረሰዉ እንዴት ነዉ ሲባል,,,...
10/09/2025

ሀሰተኛ ክስ የተቀነባበረው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተደድር ነው

* የማራ ማየንስ ባለቤት አደረሰ የተባለዉ ጉዳት 1.3 ቢሊዮን ይላል
* ይሄ ሁሉ ጉዳት የደረሰዉ እንዴት ነዉ ሲባል,,, በፍ/ቤት በማሳገዱ የተነሳ የደረሰ ጉዳት ነዉ ተብሏል።

1ኛ. ፍ/ቤት ባገደዉ ጉዳይ መጠየቅ ካለብህ ፍ/ቤቱን ነዉ መጠየቅ እንጂ ,,,ተከራካሪ ወገን ያዋጣኛል ባለዉ መንገድ ሽንጡን ገትሮ መከራከር መብት መሆኑ ቀረ እንዴ?

2ኛ. በመታገዱ ምክኒያት ፣ ማዕድኑ ምን ሆነ ተበላሸ እንዴ? ማለቴ ሌላ አካል ሊያወጣዉ አይችልም? ምን ማለት መሬቱ ውስጥ ያለዉ ማዕድን ለሁለት አመት እንዳይወጣ ፣ ለዚያዉም ህጋዊ ፍ/ቤት ዕግድ ስለጣለበት ፣ ማዕድኑ እንደ ሽንኩርት በሰበሰ ነዉ ምን ማለት ነዉ?

3ኛ. የኢፌዴሪ ሕግ መንግሥት ባለቤት ክልል ፍ/ቤት ገለልተኛ መሆን ሲገባው እንዴት ለአንድ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥብቅና ይቆማል።

ክሱ መቋረጡ ባይቀርም ቅሉ ርዕሰ መስተዳደሩ የፈፀሙት ምስበራ ይወጣብኛል የሚል ፍራቻ አላቸው። ግን እስከ መቼ አብረን እናያለን።

የህግ ሰዎች ቢያዩት interesting case ይመስለናል። ወረቀቶቹን ከWT MEDIA የተገኙ ናቸው።

ኢንጅነር ያኔ ያስረዳኸኝ ዛሬ ገብቶኛል።(በጋዜጠኛ መስከረም ጌታቸዉ)2003 ዓ.ም ለ”እንደገና” ዘጋቢ ፊልም ሥራ ስንሄድ መሠረት ድንጋይ ከተጣለ ከወራት በኋላ ነበርና ከባድ መኪኖች ሲንቀሳቀ...
10/09/2025

ኢንጅነር ያኔ ያስረዳኸኝ ዛሬ ገብቶኛል።

(በጋዜጠኛ መስከረም ጌታቸዉ)

2003 ዓ.ም ለ”እንደገና” ዘጋቢ ፊልም ሥራ ስንሄድ መሠረት ድንጋይ ከተጣለ ከወራት በኋላ ነበርና ከባድ መኪኖች ሲንቀሳቀሱ፣ ተራራ ንደው ሚደለድሉ፣ አᎆራው ሙቀቱ ብቻ የግርግር ቦታ ሁኖ ደረስን።

ሰውዬው ሲያወሩም ሲወስኑም በጣም ፈጣን ናቸው። ሁሌም ጊዜ የላቸውም።

እኛ አስር ጊዜ ላባችንን እየጠረግን እሳቸው ግን እንደወታደር ንቅንቅ ሳይሉ ቀረጽናቸው። እውነት ለመናገር የግድቡን ዲዛይን መሬት አውርደው ለማስረዳት ቢሞክሩም ሚታየው ሜዳና ተራራ ስለሆነ ብዙ ግልጽ አልሆነልኝም።

እናም ከቀረጻ በኋላ በድጋሚ እኔ ምልዎት ኢንጅነር ግድቡ የት ጋ ነው ሚሆነው? ውሃው፣ ሐይቁ ፣ ማመንጫው እያልሁ ጠየቅሁ። ደከመኝ ሳይሉ በዛ በረሃ ነይ ወደዚህ አሉና ከፍ ወዳለች ቦታ ወሰዱኝ።

ኢንጅነር- ያ ይታይሻል?
እኔ- የቱ?
እሳቸው- ተራራው። ከእሱ ጀምሮ እስከዚህ ግድቡ ነው። ነይ ወደዚህ ያ ማዶስ ይታይሻል?

እኔ- ከፀሐይ ቃጠሎ የተነሳ መተንፈስ እያቃተኝ በውስጤ ምነው ባልጀምርሁ ባይገባኝስ እያልሁ የቱ? አልሁ

ኢንጅነር- የእጄን አቅጣጫ ተመልከቺ እሱ ደግሞ ትልቁ ሐይቅ ነው። ነይ ደግሞ ወደዛ እንሂድ ያ ደግሞ እያሉ ሲያልቅ የሚኖረውን ገጽታ አስረዱኝ።

ኢንጅነር ስመኘው እንዲህ ናቸው። ለመጣ ለሄደው ሁሉ ያስረዳሉ። አይሰለቹም። “አትሳቀቁ ጠይቁ የእናንተ እኮ ነው”ይላሉ።

2004 ዓ.ም “የጉባ ተጋድሎ” ን ልንሠራ ደወልሁ።

ኢንጅነር ልንመጣ ነበር።

መስከረም እያስፈቀድሽ ነው? ልጅሽ እኮ ነው። ያኔ የነበረውን አረሳም አሉኝ። ደስ አለኝ። ሄድን አገኘናቸው።

በዚያው ጉልበት ነበሩ። ይመራሉም ይሠራሉም። ለእኛ የተቆፈረ መሬት ብቻ ቢታየንም እሳቸው ለእኛ እንዲገባን በቀላል ለማስረዳት ብዙ ደከሙ።

ስንመለስ ከእኔ ጋ ነው ምትመለሱት ብለው ራሳቸው መኪናቸውን እየነዱ በየከተማው እየጋበዙን ጥሩ የማይረሳ የቤተሰብ ጊዜ አሳልፈን አዲስ አበባ ገባን። 

በእነዛ ሁሉ ኪሎ ሜትሮች ስለግድቡና ግድቡ ብቻ ነበር ወሬያቸው። ስለጠቀሜታው አብዝተው ደግሞ ስለዲፕሎማሲ ጫናው። ደክሞን ተኝተን ስንነቃ እሳቸው ቀጥለዋል። መሀል ላይ ቢገርመኝ ሳላስበው “ኢንጅር ቤተሰብ ደህና ናቸው?” አልሁ። ዞረው አይተው “አላቆም አልሁ” አሉና ፈገግ ብለው “ ደህና ናቸው። ግን ብዙ እያገኘኋቸው አይደለም” አሉኝ።

2011 ዓ.ም “መንታ መንገድ” ዘጋቢ ፊልምን ለመሥራት በድጋሚ ደወልሁ “ እናንተ ስታስፈቅዱ እኮ ይከብደኛል” አሉ። ያው ትህትናቸው እንጂ ካለፍቃድ መሄድ እንደማይቻል ያውቁታል።

ተፈቀደ ሄድን። ከስር ያያዝሁት ፎቶ ከባዱን መርዶ ከመስማታችን ከወራት በፊት ለዚሁ ሥራ ሂደን ባገኘናቸው ወቅት ነበር።

ያኔ ቅርጽ ይዞ መሬት ወርዶ ነበርና ስናየው ደስ አለን።
ሁሌም አልቆ ማየት ምኞታቸው ነበር። እኛ በሳቸው ልክ ምንሮጥ አይመስላቸው። ደጋግመው “ የያዝነው ኃላፊነት ከባድ ነው” ይላሉ። አልቆ ማየትን ሲያወሩ እየተመረቀ ቦታው ያለን ያህል እንዲሰማን ያደርጋሉ። ጉጉታቸው ይጋባል።

ኢንጅነር እንዳላርቅህ አንተ ልበልህ።

ዛሬ ከ14 ዓመታት በኋላ ግድባችን ተመረቀ እኮ። እግዚአብሔር ለምን ባይባልም አንዲት ሰከንድ ቢፈቅድና ብታይ ብዬ ተመኘሁ።

ዛሬ ያኔ በባዶ መሬት ያስረዳኸኝ ገብቶኛል። እንዴት ያምራል መሰለህ?

ሁሌም ያን ድካምህን አንረሳም!

በድጋሚ እንኳን ደስ አለን።

ላሰቡ፣ ለጀመሩ፣ ለጨረሱ ሁሉ ምስጋና ይሁን!

ቫን ዳይክ ስታዲየም በስሙ ተሰየመለት 🔠➺ ኔዘርላንዳዊው የሊቨርፑሉ ተከላካይ ቨርጅል ቫን ዳይክ የልጅነት ክለብ የሆነው ዊሊም በቨርጅል ቫን ዳይክ ስም ስታዲየም ሰይመዋል ➺ የኔዘርላንዱ ክለ...
09/09/2025

ቫን ዳይክ ስታዲየም በስሙ ተሰየመለት 🔠

➺ ኔዘርላንዳዊው የሊቨርፑሉ ተከላካይ ቨርጅል ቫን ዳይክ የልጅነት ክለብ የሆነው ዊሊም በቨርጅል ቫን ዳይክ ስም ስታዲየም ሰይመዋል

➺ የኔዘርላንዱ ክለብ ዊሌም የሰየመው የታዳጊውን ቡድን ስታዲየም ሲሆን ቫን ዳይክም በቦታው በመገኘት ስታዲየሙን መርቆታል

ምንጭ ፡ SKY SPORT 🏅

09/09/2025

እንኳን ለታላቁ የህዳሴው ግድብ ምረቃ አደረሳችሁ! 🇪🇹

🏅 🇪🇹 በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ጉልህ ሚና የነበራቸው አመራሮች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ታላቁን የሀገሪቱን የክብር ኒሻን ተሸለሙ።የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ...
09/09/2025

🏅 🇪🇹

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ጉልህ ሚና የነበራቸው አመራሮች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ታላቁን የሀገሪቱን የክብር ኒሻን ተሸለሙ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ፣ ለግድቡ ግንባታ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አመራሮች የክብር ኒሻን ተበርክቶላቸዋል። እነዚህም፦

* ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን አማካለኝ፦ ከህዳር 2004 ዓ.ም እስከ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም የፕሮጀክቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ በመሆን ያገለገሉ ናቸው።

* ኢንጂነር ከማል አህመድ ሱሌይማን፦ ከሚያዝያ 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን ስራ አስኪያጅ ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ።

* አቶ በላቸው ካሳ ወልዴ፦ በምክትል ስራ አስኪያጅ ማዕረግ የፕሮጀክቱ ሳይት አስተባባሪ ነበሩ።

* ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፦ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ በመሆን ግድቡን በስኬት እንዲጠናቀቅ መርተዋል።
እነዚህ አመራሮች የክብር ሽልማቱን የተረከቡት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እጅ ነው።

Via ከጉባ ከተማ በቀጥታ

የህዳሴው ግድብ እውን እንዲሆን ቦንድ የገዛችሁ የመንግስት ሰራተኞች፣ ባለሀብቶች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባሎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች፣ የዲያስፖራ ወገኖች፣ ግድቡ እንዲሳካ ከግብፆች ጋር የተ...
09/09/2025

የህዳሴው ግድብ እውን እንዲሆን ቦንድ የገዛችሁ የመንግስት ሰራተኞች፣ ባለሀብቶች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባሎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች፣ የዲያስፖራ ወገኖች፣ ግድቡ እንዲሳካ ከግብፆች ጋር የተፋለማችሁ የዲጂታል ሰራዊቶች፣ ይህ ግድብ እንዲያልቅ አመራር የሰጣችሁ አጠቃላይ የፌደራልና የክልል አመራሮች፣ ግድቡን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ አመራርና ክትትል ላደረጉት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር አብይ አህመድ እና በምክርና ድጋፍ አጠገባቸው ያሉ ባለሞያዎችን ጨምሮ እንኳን ደስ አላችሁ🙏 እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ🙏 ከግድቡ የሚመነጨው ሀይል ኢትዮጵያን ያብራ፣ ኢትዮጵያ ትድመቅበት🌻 እንኳን ደስ አለን♥

እንኳን ደስ አለሽ ኢትዮጵያ ሀገሬ! 🇪🇹🇪🇹‎ምስጋና  🙏‎* ለጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር ዶክተር አብይ አህመድ ‎* ለቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር አቶ መለስ ዜናዊ ‎* ለቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር...
09/09/2025

እንኳን ደስ አለሽ ኢትዮጵያ ሀገሬ! 🇪🇹🇪🇹

‎ምስጋና 🙏
‎* ለጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር ዶክተር አብይ አህመድ
‎* ለቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር አቶ መለስ ዜናዊ
‎* ለቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር ክቡር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ
‎* ለክቡር ለአጼ ኃይሌስላሴ
‎* ለክቡር ኢ/ር ስመኘው በቀለ
‎* ለክቡር ኢ/ር ክፍሌ ሆሮ
‎* ለክቡር ኢ/ር ስለሺ በቀለ
‎* ቦንድ ለገዙ ኢትዮጵያውያን
‎* ለደጉ የኢትዮጵያ ህዝብ
‎* ስለ አባይ ቀን ለሊት የሚጮሁት የሚዲያ አካላቶች
‎ትልቅ ክብር ይገባቸዋል::

‎ፀሀይና ብርድ ችለዉ ላባቸውን ጠብ አድርገው እዚህ ላደረሱ:
‎* ኢንጀነሮች
‎* ኤሌክትሪሻን
‎* የጉልበት ሰራተኞች
‎ * ለሀገር መከላከያ ሠራዊት

‎ሁላችሁንም እናመሰግናለን። 🙏

‎አባይ አባይ
‎የሀገር ሲሳይ

‎ኢትዮጵያ ትበለፅጋለች ታድጋለች ታብባለች

ኢንጂነር ስመኘው በቀለ፡ የህዳሴ ግድብ የማይረሳው ጀግና!የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲነሳ፣ ግዙፉ የኮንክሪት አካል ብቻ ሳይሆን፣ ለዚህ ብሔራዊ ፕሮጀክት ህይወቱን የሰጠው፣ በእውቀቱና በ...
09/09/2025

ኢንጂነር ስመኘው በቀለ፡ የህዳሴ ግድብ የማይረሳው ጀግና!

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲነሳ፣ ግዙፉ የኮንክሪት አካል ብቻ ሳይሆን፣ ለዚህ ብሔራዊ ፕሮጀክት ህይወቱን የሰጠው፣ በእውቀቱና በጽናቱ ምሰሶ የነበረው አንድ ሰው በደማቁ ይታወሳል – ኢንጂነር ስመኘው በቀለ። ስማቸው በህዝብ ልብ ውስጥ ለዘላለም ታትሞ ይኖራል። ኢንጂነር ስመኘው ከባዶ የተጀመረውን የህልም ፕሮጀክት ወደ እውነታ ለመቀየር ያሳዩት ቁርጠኝነት፣ እውቀትና መስዋዕትነት የብዙ ትውልዶችን አድናቆት ያተረፈ ነው።

ኢንጂነር ስመኘው በቀለ፣ የተማሩና ብሩህ አዕምሮ የነበራቸው ኢትዮጵያዊ ነበሩ። በሀገራቸው ወንዞች ላይ ታላቅ ነገር የመስራት ራዕይ ከልጅነታቸው ጀምሮ በውስጣቸው ያደገ ይመስላል። የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ምህንድስና ትምህርታቸውን ሲከታተሉ፣ እውቀታቸውን ለሀገራቸው ልማት ለማዋል ቆርጠው ተነሱ።

የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሲጀመር፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን አይኖች በተስፋ ወደ ስራው አቀኑ። ነገር ግን ፕሮጀክቱ ትልቅ ፈተናዎች ነበሩበት። ገንዘብ የለም፣ የውጭ ድጋፍ የለም፣ ዓለም አቀፍ ጫናም ነበር። በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ነበር ኢንጂነር ስመኘው የቀለሙን ብሩሽ አንስተው፣ ከባዶ ሸራ ላይ የህልም ምህንድስናቸውን መሳል የጀመሩት። ዋና ስራ አስኪያጅና የፕሮጀክቱ ኢንጂነር በመሆን፣ ራዕዩን ወደ ተጨባጭ እቅድ፣ እቅዱን ደግሞ ወደ ግዙፍ ግንባታ የመለወጡን ታላቅ ሃላፊነት ተሸከሙ።

ኢንጂነር ስመኘው በቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው ብቻ የሚሰሩ አልነበሩም። በፀሐይ ሲቃ የምትፋጀው በረሃማው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ፣ ከሰራተኞች ጎን ቆመው፣ ጭቃ እየለወሱ፣ ድንጋይ እየገፉ፣ እያንዳንዱን የግድቡ ክፍል ከወረቀት ወደ ምድር ሲያመጡ ይታዩ ነበር።

* ተግዳሮቶችን በቆራጥነት መጋፈጥ: የገንዘብ እጥረት፣ የቴክኒክ ችግሮች፣ ዓለም አቀፍ ጫናዎች ሲያጋጥሙ፣ እሳቸው ምላሽ የሚሰጡት በእውቀት፣ በፅናትና በፈጠራ ነበር። ውስብስብ የምህንድስና ስሌቶችን ከሀገር በቀል እውቀት ጋር በማዋሃድ በርካታ ችግሮችን ፈትተዋል።

* የሰራተኞች አባትና መሪ: ለሰራተኞቻቸው አባት፣ አስተማሪና ወዳጅ ነበሩ። ለራሳቸው የሚፈልጉትን ሳይሆን፣ ለፕሮጀክቱ የሚጠቅመውን ብቻ የሚመርጡ፣ ራስ ወዳድነት የሌለባቸው መሪ ነበሩ። በሳቸው መሪነት ብዙ ወጣት ኢንጂነሮችና የቴክኒክ ባለሙያዎች አድገዋል።

* የቁርጠኝነት ምሳሌ: እስከ መጨረሻው እስትንፋሳቸው ድረስ ለፕሮጀክቱ ታማኝ ነበሩ። ሌት ተቀን ይሰሩ ነበር፤ ህዳሴ ግድብ ለእሳቸው ስራ ብቻ ሳይሆን የህይወት ትርጉም ነበር።

የማይሞተው ቅርስ የኢንጂነር ስመኘው ጉልህ አስተዋፅኦ የሚታየው በግድቡ ግዙፍ መጠን ብቻ አይደለም። ዋናው አስተዋፅኦቸው የኢትዮጵያን የራሷን የመስራት አቅም ለአለም ያሳዩበት መንገድ ነው። ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ታላቅ ፕሮጀክት፣ በራሳቸው እውቀትና ገንዘብ መገንባት እንደሚችሉ ያሳዩበት ህያው ማስረጃ ናቸው።

ኢንጂነር ስመኘው ባይኖሩም፣ የሰሩት ስራ ግን ህያው ነው። የህዳሴ ግድብ ውሃ ማመንጨት ሲጀምር፣ መብራት ሲሰጥ፣ ለሚሊዮኖች ህይወት ሲሆን፣ የኢንጂነር ስመኘው ስም በደማቁ መፃፉ ብቻ ሳይሆን፣ ስራቸው ህያው ሆኖ ለዘላለም ይኖራል። ለትውልድ የሚተላለፍ፣ በትጋትና በራስ መተማመን የተገነባ የድል ምልክት ናቸው።

የኢንጂነር ስመኘው በቀለ ታሪክ፣ የኢትዮጵያን የቁርጠኝነት መንፈስ የሚያሳይ፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ ልማት ምን ያህል አስተዋፅኦ ማድረግ እንደሚችል የሚያሳይ ተምሳሌት ነው። ስማቸውም ሆነ ተግባራቸው በወርቃማ ቀለም በታሪክ መዝገብ ላይ ተቀርጾ ይኖራል።

ለወላይታ ድቻ የቁርጥ ቀን የሆነው አባታችን አብዲ ራዋ በታላቁ የወላይታ ጊፋታ ስጦታ የቤት መኪና ገዝተን እንሰጠዋለን !ለዚህ ደግሞ ህፃን ሽማግሌ ሳይል ሁሉም ይሳተፋል ።በሱ ምክንያት ያገኘ...
08/09/2025

ለወላይታ ድቻ የቁርጥ ቀን የሆነው አባታችን አብዲ ራዋ በታላቁ የወላይታ ጊፋታ ስጦታ የቤት መኪና ገዝተን እንሰጠዋለን !

ለዚህ ደግሞ ህፃን ሽማግሌ ሳይል ሁሉም ይሳተፋል ።

በሱ ምክንያት ያገኘነው ዋንጫ ለኛ በመኪና የሚለካ አይደለምና እስኪ ሁላችንም ከታቻ በተቀመጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ የበኩላችሁን እንዲትወጡ በአክብሮት እንጠይቃለን። 🙏

CBE: 1000716207599
Alemayehu & Abdi & Amsalu

Address

Wolaita S**o
S**o
4620

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dicha Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share