Wolaita Broadcasting Corporation - WBC

Wolaita Broadcasting Corporation - WBC NEWS

ክቡር ርዕሰ መስተዳድራችን ለክልላሉ ሰላም፣ መቻቻልና ብልፅግና ተምሳሌት የሚተጉ ናቸው።
28/08/2025

ክቡር ርዕሰ መስተዳድራችን ለክልላሉ ሰላም፣ መቻቻልና ብልፅግና ተምሳሌት የሚተጉ ናቸው።

 #ዜና ሹመት1. አቶ ዘለቀ ዛራ ፦የአረካ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ2.አቶ አብነት ጨመረ ፦የከተማው ም/ከንቲባ እና ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች...
25/08/2025

#ዜና ሹመት

1. አቶ ዘለቀ ዛራ ፦የአረካ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ

2.አቶ አብነት ጨመረ ፦የከተማው ም/ከንቲባ እና ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

3.መ/አ ተስፋዬ ኃይሌ፦የአረካ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፖለተካ ዘርፍ ኃላፊ

4.ወ/ሮ መስከረም ሙንዱሮ ፦የአረካ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

24/08/2025

በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር ከ1200 በላይ ጧሪ ላጡ፣ አረጋዊያን እና አቅመ-ደካሞች ቤቶችን ለመገንባት እንዘጋጅ፦ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር የሚከናወነው የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መርሃግብር በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በመልዕክታቸው በነገው ዕለት በነሐሴ 19/2017 በአንድ ጀምበር የብዙዎች እምባን የሚያብስ የአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ቤቶችን የመገንባትና የማደስ መርሃግብር እንደሚካሄድ ገልፀዋል።

በዚህ መርሃግብር ከ1200 በላይ ቤቶችን ጧሪ ላጡ እናቶች፤ አባቶች፣ አረጋዊያን እና አቅመ-ደካሞች ለመገንባት በሁሉም አከባቢዎች አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

ይህም በክረምት ዝናቡ፣ በበጋው ፀሀዩ ሲፈራረቅባቸው የነበሩ ወገኖቻችን የእፎይታ ህይወትን የሚሰጥ በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የአቅመ-ደካሞችን ቤት በመገንባትና በማደስ ተግባር እናቶቻችንና አባቶቻችን ስሜታቸዉን በደስታ እንባ ሲገልፁ እናያለን ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፥ ይህም ተስፋ የሚያደርግ ማህበረሰብንና ለህዝቡ የሚያስብ ትውልድንም የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ይህ መልካም ተግባር የሰዉ ልጆችን ደስ የሚያሰኝ እና በፈጣሪ ዘንድም የሚያስመሰግን እንደሆነ የተናገሩት ዋና ዋና አስተዳዳሪው፣ በዚህ መልካም ተግባር ላይ ሁሉም መሳተፍ እንዳለበትም አሳስበዋል።

በነገው ዕለት ነሓሴ 19/2017 ዓ.ም የሚከናወነው የአንድ ጀምበር የአረጋዊያንና አቅም ደካሞች ቤቶች ለመገንባት የሁሉም ሐይማኖት ተቋማት፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ዕድሮች፣ በጎ አድራጎት ማህበራት እና ሌሎች ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምረው በነቂስ በመውጣትና ተሳትፎ በማድረግ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ማበርከት እንዳለባቸውም ጥሪ አስተላልፈዋል።

24/08/2025

በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር የብዙዎችን እምባ ለማበስ በሚከናወነው በጎ ተግባር ላይ ሁሉም መሳተፍ ይገባል፦ ዶ/ር አማረ አቦታ

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ "በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በዞኑ በነገው ዕለት ነሐሴ 19/2017 ዓ.ም በአንድ ጀምበር ከ1200 ቤቶችን ለአረጋዊያንና አቅመ ደካሞች የመገንባት መርሃግብር እንደሚካሄድም ገልፀዋል።

በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር የብዙዎችን እምባ ለማበስ ለሚከናወነው መርሃግብር አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

በዞኑ ዘንድሮ በ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ16 ዋና ዋና ትኩረት መስኮች እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውሰዋል፡፡

ባለፉት ዓመታት በበጎ ተግባር ለኑሮ የማይመቹ የተጎሳቀሉ ደሳሳ ጎጆዎች ተቃንተው ታድሰዋል ያሉት ኃላፊው በክረምት ዝናቡ፣ በበጋው ፀሀዩ ሲፈራረቅባቸው የነበሩ ወገኖቻችንም የእፎይታ ህይወትን ጀምረዋልም ብለዋል።

ፓርቲያችን ብልፅግና አብሮነትን፣ መተሳሰብን፣ እርስ በርስ መረዳዳትን ማዕከል በማድረግ ባለፉት በለውጥ ዓመታት ሰው ተኮር ተግባራትን በማስቀደም በርካታ ሰውኛ ተግባራትን መከናወኑንም ጠቅሰዋል።

ፓርቲው ለዜጎች ክብር ቅድሚያ የሚሰጥ ሰው ተኮር ፓርቲ እንደሆነ በመጠቀስ፤ እርስ በርስ የመረዳዳት፣ የመደጋገፍ፣ አብሮ የማደግና የመበልጸግ መልካም እሴቶችን ማጎልበት የብልጽግና ፓርቲ ልዩ መገለጫዎች መሆናቸውንም ገልፀዋል።

በነገው ዕለት በአንድ ጀምበር በየአከባቢያችን የሚገኙ አቅም ላጠራቸዉ፣ ጧሪና ቀባሪ ያጡ እናቶችንና አባቶችን ቤት ለመገንባት የሁላችን ተሳትፎን ይሻል ያሉት ኃላፊው፥ ፍቅርንና መልካምነትን የሚገልጽ ተግባር ላይ ህብረተሰብ ክፍሎች በነቂስ ወጥቶ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተዋፆኦ ማበርከት እንዳለባቸውም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

#በጎነት

በወላይታ ዞን በሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የመንገድ ዳር መብራት ሙሉ በሙሉ ግንባታው ተጠናቅቆ አገልግሎት መሰጠት ጀምሯል። !! !!
22/08/2025

በወላይታ ዞን በሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የመንገድ ዳር መብራት ሙሉ በሙሉ ግንባታው ተጠናቅቆ አገልግሎት መሰጠት ጀምሯል።

!!
!!

*ከመደመር ሐሳብ እስከ አንድነት ጉዞ!*የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "መደመር" ፍልስፍና ጉዞውን የጀመረው ከአንድ መሠረታዊ ጥያቄ ነው፦ እያንዳንዳችን እንደ ግለሰብ ቂምንና ጥላ...
20/08/2025

*ከመደመር ሐሳብ እስከ አንድነት ጉዞ!*

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "መደመር" ፍልስፍና ጉዞውን የጀመረው ከአንድ መሠረታዊ ጥያቄ ነው፦ እያንዳንዳችን እንደ ግለሰብ ቂምንና ጥላቻን አስወግደን፣ ይቅርታንና ፍቅርን ስንመርጥ ምን አይነት ማኅበረሰብ መፍጠር እንችላለን?

"*መደመር*" የተሰኘው የመጀመሪያው መጽሐፋቸው፣ ይህንን የውስጥ ለውጥ አስፈላጊነት በማስገንዘብ፣ ግለሰቦች ከአሉታዊ አስተሳሰቦች ራሳቸውን አላቀው አዎንታዊ እይታን እንዲያዳብሩ ያበረታታል።

በ**"የመደመር መንገድ"**፣ ይህ የግለሰብ ለውጥ ወደ ማኅበረሰባዊ መስተጋብር እንዴት እንደሚሸጋገር ያሳያል። የተለያዩ ባህሎች፣ ቋንቋዎች እና ታሪኮች ያሏቸው ሕዝቦች ልዩነቶቻቸውን እንደ ጌጥ በመቁጠር፣ ለጋራ ብልጽግና እንዴት በጋራ ሊቆሙ እንደሚችሉ ያስረዳል።

"*የመደመር ትውልድ*" ደግሞ ይህንን የአንድነት መንፈስ ለቀጣዩ ትውልድ ማሻገር ላይ ያተኩራል። ታሪክን በአግባቡ በመረዳት፣ ከስህተቶች በመማር እና የጋራ እሴቶችን በማዳበር ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና እድገት መሠረት የሚጥል ትውልድን የመፍጠር ራዕይን ያንጸባርቃል።

"*የመደመር መንግሥት*" ይህንን ሀገር በቀል አስተሳሰብ ወደ መንግሥታዊ መዋቅር ከፍልስፍና ወደ ተቋማዊ ትግበራ መምጣቱን የሚያሳይ ነው።

ይህ አካሄድ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ሕዝብ ጥበብና እምቅ አቅም ላይ ያላቸውን እምነት እና ጥገኛ ካልሆነ አስተሳሰብ የመነጨ ራዕይ እንዳላቸው ያሳያል።

19/08/2025

የመደመር ትውልድ

ሀገር ገንቢ ትርክትን ለማጠናከር ከተፈለገ፤ ዘርፈ ብዙ ጥላቻ ጠንሳሽና አፍራሽ ትርክቶችን መቆጣጠር ያስፈልጋል። ይኽን ለማድረግም፡ በረዥም ጊዜ፡ ሀገር በቀል የማኅበራዊ ሚዲያን ማበልጸግ ዋናው ትኩረታችን መሆን አለበት። በአጭር ጊዜ ደግሞ፤ ማኅበራዊ ሚዲያውን ለመግራት እንዲያስችል፤ ማኅበራዊ ሚዲያውን የሚገዛ የሕግና የአስተዳደር ሥርዓት መንደፍ ያስፈልጋል።

በማኅበራዊ ሚዲያ መረጃን ማሠራጨት መብት እንደሆነው ሁሉ፤ የጥላቻ መልዕክትንና የተሳሳተ መረጃን ማስተላለፍ ወንጀል ሆኖ ተጠያቂነትን ማስከተል አለበት።

በዚህ ረገድ ፀድቀው ወደ ሥራ የገቡ የሕግ ማዕቀፎች ቢኖሩም፤ ከይዘትና ከአፈጻጸም አንጻር የሚኖሩ ክፍተቶችን በመሙላት፤ ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል።

የቴክኖሎጂው ባለቤትነት ከኛ ቁጥጥር ውጭ እንደ መሆኑ፤ የሚፈለገውን ተጠያቂነት ለማምጣትና ማኅበራዊ ሚዲያውን ለመግዛት፤ ከባለቤት ተቋማቱ ጋር መሥራትና የቴክኖሎጂ ዐቅምን ማሳደግ ወሳኝ ይሆናሉ፡፡
ከመደመር ትውልድ ገጽ 214 የተወሰደ

16/07/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mesay Wana, Tegegn Tantu Tegegn, Torres Naule Shalom, Wonde Mano, Arega Loha, Feleke Bololo, Abebayehu Aske, Elias Eta, Singer Aschalew Ayide, Chekole Taye, Habtamu Hanjalo, Asrat Bonga, Aman Yishak, Lij Jemal Zemito Abeyo, Abraham Della, Abel Ayele, Abraham Ayele, የማይቻለው የለም, Zerihun Ayza, Muse Basha Baramo, Mahmmad Hame, የትግል ውጤት, Afework Ye Gebrel Lij, John John, Jeeli Chamo tnx

“ወላይታ ድቻ በCAF Confederation ለመሳተፍ የሚያስችለዉን ፎርማሊቲ በማሟላት በትናትናው እለት በCAF ምዝገባ ጨርሷል” አቶ አሰፋ ሆሲሳ (የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ)በWogeta ...
16/07/2025

“ወላይታ ድቻ በCAF Confederation ለመሳተፍ የሚያስችለዉን ፎርማሊቲ በማሟላት በትናትናው እለት በCAF ምዝገባ ጨርሷል”

አቶ አሰፋ ሆሲሳ (የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ)
በWogeta FM 96.6 ከደቂቃዎች በፊት! ከተናገረው የተወሰደ

ጠንካሮችንና ለወላይታ እግር ኳስ ባለውለታ የሆኑ አካላትን አለማመስገን በውስጤ ግርታ እየፈጠረብኝ ነውብዙ ጊዜ በብዙ ነገር ተወጥረን ህዝባችን በማይጠቅሙና ሙያዊ ተግባራትንና በሙያ የተካኑ አ...
06/07/2025

ጠንካሮችንና ለወላይታ እግር ኳስ ባለውለታ የሆኑ አካላትን አለማመስገን በውስጤ ግርታ እየፈጠረብኝ ነው

ብዙ ጊዜ በብዙ ነገር ተወጥረን ህዝባችን በማይጠቅሙና ሙያዊ ተግባራትንና በሙያ የተካኑ አካላትን ከማመስገንና ከማበረታታት ተቆጥበን ቆይተናል። ይህ አካሄድ ንፉግነትን ያሳያል!

ስሞኑ የወላይታ ዲቻ አሸናፊነት ጋር በተገናኘ ተገቢውን ግልጋሎት እና በስፖርታዊ ሙያው ከክለቡም አልፎ የዞኑ ስፖርት ዕድገት ሁነኛ ሚና እየተወጣ ያለ አካልና ከወላይታ አልፎ በሀገራችን እግርኳስ በሙያዊ እውቀት እያገለገለ የሚገኝ ግለሰብ ላስተዋውቃችሁ።

ክቡር አቶ አሰፋ ኦስሶ ይባላል። አቶ አሰፋ የወላይታ ቱሳ እግር ኳስ ጀምሮ ወላይታ በእግር ኳስ ታሪክ ገናና እንድሆን ያደረገ እና በሙያው የተካነ መሆኑን ስንቶች እናውቃለን?

አቶ አሰፋ ከሰፊው ህዝብ ይሁንታ በማገኘት ክለቡ ከጊዜ ወደጊዜ የተሻለ ቁመና ላይ እንድገኝ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል እየለፉ ከሚገኙ ግለሰቦች ቀዳሚው ስፍራ ይይዛል።

አቶ አሰፋ ከወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ ሥራአስኪያጅነት አልፎ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሊግ ካምፓኒ ቦርድ አባል ሆኖ እያገለገለ ያለ ጠንካራ ባለሙያ ነው።

ይሁን እንጅ አንዳንድ ፅንፈኛ አስተሳሰብ ያጎናጸፉ አካላት እንደየፍላጎታቸው ለወርቃማው ክለባችን የሚለፉ እንደእነ አስፋ አስሶ አይነት ጠንካራ አካላትን ለማጠላሸት ሲሞክሩ እንመለከታለን።

ይሁን እንጂ ጀግናው አቶ አሰፋ ለማንኛውም ወሬ ጆሮ ሳይሰጥ ክለቡና የክለቡ ቤተሰብ መላው ወላይታ ህዝብ ቀና ብሎ እንድራመዱ ስም የሚያስጠራ ወላይታ ዲቻን ያፈራ ጀግና የህዝብ ልጅ ነው።

የክለቡ አቋም ስቀንስ ኤኬለ ነው ተጠያቂ: የክለቡ አቋም የሚያስደንቅ ስሆን እኔ ነኝ የሚሉ አካላት ባሉበት ለአንድ ትልቅ ዓላማ እየለፋ ቆይቷል አቶ አሰፋ

ወንድማችን አሰፋ ክለቡ በአፊሪካ መድረክ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ያበረከተው አስተዋጽኦ በወላይታ ታሪክ እየተዘከረ ይኖራል።


አቶ አሰፋ ለወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ብዙ ውለታ የዋለለትና በሙያው የተካነ እንቁ የወላይታ ህዝብ ልጅ ነውና ሰፊው የወላይታ ህዝብ እውቅና እንድሰጥ እፈልጋለሁ።

እስቲ ሁላችንም ከትችት ወጥተን ወርቃማው ክለባችን የድል ጉዞ አጠናክሮ እንዲቀጥል በተባበረ ክንድ እንሰራ እያልኩ የዛሬውን መልዕክት በዚህ አበቃለሁ።

እናመሰግናለን አሰፋ ኦስሶ👏👏👏👏

ጀግኒት እንወድሻለን!!
02/07/2025

ጀግኒት እንወድሻለን!!

የወላይታ አምላክ አይተኛም !!!! እንኳን ደስአላችሁ! እንኳን ደስ አለን!!!
01/07/2025

የወላይታ አምላክ አይተኛም !!!! እንኳን ደስአላችሁ! እንኳን ደስ አለን!!!

Address

S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Broadcasting Corporation - WBC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wolaita Broadcasting Corporation - WBC:

Share