Wolaita Communications

Wolaita Communications የመረጃ ምንጭ

በወላይታ ዞን "የመሐሉን ዘመን ወጥመድ መሻገር" በሚል ሀሳብ ዞናዊ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ነውወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 4/2017 በወላይታ ዞን "የመሐሉን ዘመን ወጥመድ መሻገር" በሚል ሀሳ...
12/05/2025

በወላይታ ዞን "የመሐሉን ዘመን ወጥመድ መሻገር" በሚል ሀሳብ ዞናዊ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ነው

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 4/2017 በወላይታ ዞን "የመሐሉን ዘመን ወጥመድ መሻገር" በሚል ሀሳብ ዞናዊ የአመራር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመሐሉ ዘመን የሚያጋጥሙ የሽግግር ፈተናዎችንና ተግዳሮቶችን ለመሻገር የሚያስችል የተሟላ የአመራር ብቃት ለመገንባት እና የጋራ ግንዛቤን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተገልጿል፡፡

"የመሐሉን ዘመን ወጥመድ መሻገር" በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን ሰነድ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም እያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ዙሪያ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በመድረኩ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም፣ የወላይታ ዞን የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ቶማስን ጨምሮ የዞኑ አጠቃላይ አመራር እና የወረዳና ከተማ አስተባባሪ አካላት እየተሳተፉ ናቸው።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ በከተማው በድምቀት የሚከበረውን  የስቅለትና የትንሳኤ በዓል በሠላም እንዲጠናቀቅ  የቅደመ ዝግጅት ሥራዎችን ማጠናቀቁን አሰታወቀ። ******ወላይታ ሶዶ ሚያዝያ 9/...
17/04/2025

የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ በከተማው በድምቀት የሚከበረውን የስቅለትና የትንሳኤ በዓል በሠላም እንዲጠናቀቅ የቅደመ ዝግጅት ሥራዎችን ማጠናቀቁን አሰታወቀ።

******
ወላይታ ሶዶ ሚያዝያ 9/2017ዓ.ም የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ በከተማው በድምቀት የሚከበረውን የስቅለትና የትንሳኤ በዓል በሠላም እንዲጠናቀቅ የቅደመ ዝግጅት ሥራዎችን ማጠናቀቁን አስታውቋል ።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ በከተማው የሚከበረውን የስቅለትና የትንሳኤ በዓል በማስመልከት መላው የከተማችንን የክርስትና እምነት ተከታዩች እንኳን አደረሳችሁ ያለው የከተማው ፖሊስ በዓሉን ያለምንም ስጋት በሠላም እንዲጠናቀቅ ሙሉ የቅደመ ዝግጅት ሥራዎችን በተመለከተ መልክት አስተላልፏል ።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮ/ር ሀብታሙ አሰፋ በከተማችን በድምቀት የሚከበረውን የስቅለትና የትንሳኤ በዓል ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች ወደ የቤተሰቦቻቸው የሚጡ ሰዎች ወላይታ ሶዶ እንደሚገቡ ያስታወሱት አዛዡ የንግድ፣የትራፊክ ፈሰቶች፣ በዛው ልክ የሚጠናከሩበት፣በመሆኑ እነዚህ የበዓል ሁኔታዎች ምክንያት በማድረግ ለስርቆት እና ለሌብነት እራሳቸውን የሚያዘጋጁ ግለሰቦች መኖራቸውን ያስታወሱት አዛዡ ወቅቱን በመረዳት እና በመገንዘብ ህብረተሰቡ በጥንቃቄ ግብይትና እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅረበዋል ።

ይሄ በመሆኑም የከተማ የፖሊስ በዓሉ በሠላም እንዲጠናቀቅ 24 ሰዓት የፖትሮል ቅኝት እና በሞንተርበ የታገዘ የጥንቃቄ ምልክቶችን በመሰጠት እንዲሁም በሰባቱም ቀበሊያት የፖሊስ የማህበረሰብ ቅደመ ጥንቃቄ ቅንጅታዊ ሥራዎች ተጠናክሮ የሚሰራ መሆኑን በማስረዳት የስቅለትና የትንሳኤ በሰላም እንዲከበር ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ገልጸዋል ።

ማንኛውም ጥቆማ ሲኖር የከተማ ፖሊስ የኢንተለጀንስ እና የመረጃ ስልኮች 0465510146 ይደውሉ

በወላይታ ሶዶ ከተማ  በወቅታዊ ከተማዋ ዞናዊ አጠቃላይ ነባራዊ  ሁኔታዎች ዙሪያ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል ***ወላይታ ሶዶ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በወቅታዊ ከተማዋ ዞ...
11/03/2025

በወላይታ ሶዶ ከተማ በወቅታዊ ከተማዋ ዞናዊ አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል

***
ወላይታ ሶዶ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በወቅታዊ ከተማዋ ዞናዊ አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ውይይት መካሄድ ጀምሯል ።

በውይይቱ የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አማካሪ አቶ ተመሰገን ታደሰ ፣የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ፍሬው ሞገስ ዶ/ር ፣የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልፅግና ፖርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፀጋ ተ/ሀይማኖት፣የወላይታ ዞን ሰነምግባርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ አበራ የከተማው አስተባባሪዎች እና የከተማው አጠቃላይ አመራር በተገኙበት ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የተዘጋጀ የዕውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ከተማ ጋሞ ባህል ማዕከል እየተካሄደ ...
15/12/2024

19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የተዘጋጀ የዕውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ከተማ ጋሞ ባህል ማዕከል እየተካሄደ ነው።

ጽዱ፣ አረንጓዴዋ፣ ህብረብሔራዊቷ፣ ባለ 7 በር የንግድና ኢንቨስትመንት ማዕከል፣ የ50 ነገስታት ምድር፣ የሠላምና የመቻቻል ተምሳሌት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካና አስተዳደር መቀመጫ  #...
06/12/2024

ጽዱ፣ አረንጓዴዋ፣ ህብረብሔራዊቷ፣ ባለ 7 በር የንግድና ኢንቨስትመንት ማዕከል፣ የ50 ነገስታት ምድር፣ የሠላምና የመቻቻል ተምሳሌት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካና አስተዳደር መቀመጫ #ወላይታ ሶዶ ከተማ ውብ ገጽታ፤

በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ሀንጋዳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በመስኖ እየለማ የሚገኝ የጥቅል ጎመን ምርት በምስል፤
04/12/2024

በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ሀንጋዳ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በመስኖ እየለማ የሚገኝ የጥቅል ጎመን ምርት በምስል፤

በወላይታ ሶዶ ከተማ በመኖሪያ ቤት ግንባታ ለተደራጁ 70 ማህበራት ቤት መስሪያ ቦታ እርክብክብ ተደረገላቸውወላይታ ሶዶ: ህዳር 25/2017 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በመኖሪያ ቤት ግንባታ ለ...
04/12/2024

በወላይታ ሶዶ ከተማ በመኖሪያ ቤት ግንባታ ለተደራጁ 70 ማህበራት ቤት መስሪያ ቦታ እርክብክብ ተደረገላቸው

ወላይታ ሶዶ: ህዳር 25/2017 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በመኖሪያ ቤት ግንባታ ለተደራጁ 70 ማህበራት ቤት መስሪያ ቦታ እርክብክብ ተደርጎላቸዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ፍሬው ሞገስ እንደገለፁት በከተማዋ በተለያዩ ጊዜያት በማህበር ተደራጅተው ቦታ ሳያገኙ የቆዩ ማህበራትን መልካም አስተዳደር ችግር መፍታትና ተገቢ ምላሽ መስጠት ቀዳሚ እንደሆነ ገልጸዋል።

አክለውም መንግስት ባመቻቸው ዕድል ተጠቅመው በህጋዊ መንገድ የተደራጁ ማህበራትን በተገቢው በማጣራት በዘርፉ የሚስተዋለውን ማጭበርበርና ሌብነት በማጋለጥ የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ ከምን ጊዜውም በላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

የቀሩ ማህበራትን አስፈላጊውን የማጣራት ሥራ በመስራት በአጭር ጊዜ ምላሽ ለመስጠት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገ/ት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተመስገን ቡቃቶ ማህበራት የተሰጣቸውን ቦታ በተያዘለት ጊዜና የከተማውን ፕላን በጠበቀ መንገድ በመስራት ለሌሎች ማህበራትም ሞዴል ልሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ የ"ጊፋታ" በዓል በድምቀት ለማክበር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
18/09/2024

በወላይታ ሶዶ ከተማ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ የ"ጊፋታ" በዓል በድምቀት ለማክበር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የ100 ቀን ዕቅድ ዙሪያ የወላይታ ዞን አስተዳደር ከሁሉም ዞን፣ወረዳና ከተማ አስተዳደር  አመራር አካላት ጋር ዉይይት እያካሄደ ይገኛል።በውይይቱም ከሐምሌ 1 ጀምሮ የመንግስትና የፓርቲ ተግባ...
30/09/2023

የ100 ቀን ዕቅድ ዙሪያ የወላይታ ዞን አስተዳደር ከሁሉም ዞን፣ወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራር አካላት ጋር ዉይይት እያካሄደ ይገኛል።

በውይይቱም ከሐምሌ 1 ጀምሮ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት እንዴት እንደተመራ የወላይታ ዞን አስተዳደር ገመገመ።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ በንግግራቸው ገበያን ለማረጋጋት በገጠሪቱ ክፍል የተሰማሩ የግሉ ባለሀብቶች የህብረተሰቡን የኑሮ ዉድነትን ለማረጋጋት ከመንግስት አመራር ጋር በጋራ በከተማም በገጠር ለህብረተሰቡ ገበያን ሊያረጋጋ በሚችል ሁኔታ ምርት ማቅረብ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

ክቡር አስተዳዳሪው አክለውም በተለይ የሰላሙን ጉዳይ ህዝቡ ባለቤት በመሆን ህገወጦችን አድኖ በመያዝ ለህግ ማቅረብ እንዳለባቸውና ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው ገልፀዋል።

አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለህዝብ በአግባቡ እንዲሰጡ በተለይ የፋይናንስ፣የማዘጋጃ ቤት፣የጤና ተቋማት እንዲሁም የትምህርት ተቋማት የተሻለ መስራትና በራቸውን ክፍት በማድረግ ተገልጋይ እርካታ እንዲያገኝ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በግምገማው የወላይታ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አሳምነው አይዛ በበኩላቸው ባሳለፍነው ጊዜያት የታዩብንን ችግሮች ምን ነበሩ ይህን ችግርስ እንዴት አለፍነው የሚለውን በጥልቀት በማየት በቀጣይ 100 ቀን የተሻለ ስራ በመስራት ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ኃላፊው አክለውም በጊዜ የለኝም መንፈስ አመራሩ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ በመስራት የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዳለበትም አሳስበዋል።

ለአደጋ አጋላጭ የሆኑ የባለሁለት እግር ሞተር ተሽከርካሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፓሊስ አስታወቀ።በሶዶ ከተማ የመርካቶ ዩሿ ቀበሌ የትራፊክ ፓሊስ እና የፀጥታ ሀይሎች ባደረጉት የተቀናጀ ኦ...
21/07/2023

ለአደጋ አጋላጭ የሆኑ የባለሁለት እግር ሞተር ተሽከርካሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፓሊስ አስታወቀ።

በሶዶ ከተማ የመርካቶ ዩሿ ቀበሌ የትራፊክ ፓሊስ እና የፀጥታ ሀይሎች ባደረጉት የተቀናጀ ኦፕሬሽን በቁጥር በርካታ የባለሁለት እግር ሞተር ተሽከርካሪዎች ተይዘዋል።

ከተፈቀደላቸው መስመሮች እና የፍጥነት ገደብ ሲያሽከረክሩ የነበሩ ግለሰቦችን ምርመራ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል።

የመርካቶ ዩሿ የትራፊክ ፓሊስ አሰተባባሪ ዋና ሣጅን ዝናቡ ገዛኸኝ እንደገለፁት የባለሁለት እግር ሞተር ተሽከርካሪ የአደጋ መንስኤ ከመሆናቸውም በላይ የወንጀል ድርጊት መፈፀሚያ ስለሚሆኑ ጥብቅ ክትትል ይደረግባቸዋል።

በዚህም ታርጋ ፣ ስፖኪዬ እና ሌሎች አስፈላጊውን ደረጃ የማያሟሉትን ከመንገድ ፍሰት በማውጣት ለህጋዊ አሰራር መስፍን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ዋና ሣጅን ዝናቡ ገልፀዋል።

የመርካቶ ዪሿ ቀበሌ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ እና ማህበረሰብ አቀፋ ወንጀል መከላከል ሀላፊ ምክትል ሳጅን ክፋሌ ይሳሀቅ ወቅቱ ክረምት በመሆኑ የጎማ ፣ የፌሬቻ እና ሌሎችም በቀላሉ ከአደጋ መታደግ የሚያስችሉ ግብአቶች ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ምክትል ሳጅን ክፋሌ አክለውም አሽከርካሪዎች እራሳቸውን እና ሌሎችንም ከአደጋ የመጠበቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

ከህብረተሰቡ ከሚደርሱ ጥቆማዎች ውስጥ ታርጋ የሌላቸው እና ለመለየት የሚያስቸግሩ እንዲሁም በከፍተኛ ፍጥነት የሚያሽከረክሩ ሞተረኞች የስጋት ምንጭ በመሆናቸው በተቀናጀ መልኩ እርምጃው መወሰዱን የቀበሌው ሰላም እና ፀጥታ ሀላፊ ገልፀዋል።

ወንጀልን ለመከላከል ህብረተሰብ አጠራጣሪ ነገሮችን በከተማው ፓሊስ የመረጃ ስልክ ቁጥር 046 551 0146 በመደወል ጥቆማ መስጠት እንደሚቻል ጥሪ ቀርቧል።

የዎላይታ ሶዶ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት።

የበጎ አድራጎት ስራዎች በዎላይታ ሶዶ ከተማ ተጠናክሮ እንደቀጠለ  ተገለፀ።የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት በወጣቶች ንቁ ተሳትፎ  እና የመንግስት ድጋፍ የበርካቶችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛ...
10/07/2023

የበጎ አድራጎት ስራዎች በዎላይታ ሶዶ ከተማ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ተገለፀ።

የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት በወጣቶች ንቁ ተሳትፎ እና የመንግስት ድጋፍ የበርካቶችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል ።

በአረጋውያን ቤት ጥገና ፣ የደም ልገሳ እና የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የከተማ ማፅዳት እና አደባባይ ማስዋብ ስራ በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እየተከናወነ ነው።

የጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ ጥሪ በመቀበል የከተማው ወጣቶች በአረንጓዴ አሻራ በነቂስ እየተሳተፉ እንደሚገኙም ተገልጿል።

በተለይም ከቀናት በኋላ የሚደረገው የ500 ቢሊዮን በአንድ ጀምበር ዝግጅት እየተጠናቀቀ ሲሆን በጎ ፈቃደኛ ወጣት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በአንድነት አሻራቸውን ያሳርፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በተያዘው ክረምት ከ19 ሺ በላይ ወጣቶችን በበጎ ፈቃደኝነት በማነቃነቅ 57 ሺ ገደማ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ እየተሰራ ይገኛል ነው የተባለው።

የዎላይታ ሶዶ ከተማ ወጣቶች እና ስፓርት
ፅህፈት ተግባሩን በዋናነት እያስተባበረ የሚገኝ ሲሆን ወጣቶች በፅህፈት ቤቱ በመገኘት በተዘጋጁ 11 የበጎ አገልግሎት አማራጮች በመሳተፍ ህብረተሰቡ እንዲያገለግሉ ጥሪ ቀርቧል። ስል የሶዶ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል

አጆራ መንትያ ፏፏቴ በዞናችን ወላይታ አገልግሎት እየሰጡ ካሉ ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች መካከል አንደኛ ሲሆን በወላይታ ዞን በቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ አጆራ ቀበሌ የሚገኝ ተፈጥሯዊ መስህብ ነው፡...
02/07/2023

አጆራ መንትያ ፏፏቴ

በዞናችን ወላይታ አገልግሎት እየሰጡ ካሉ ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች መካከል አንደኛ ሲሆን በወላይታ ዞን በቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ አጆራ ቀበሌ የሚገኝ ተፈጥሯዊ መስህብ ነው፡፡

ይህ ተፈጥሮ መስህብ ውብና ማራኪ የሆነ የሰውን ልጅ ከሚያማልል ከተፈጥሮ ፀጋዎች ተርታ የሚጠሩ ለአገር ውስጥም ሆነ ለውጪ አገር ቱሪስቶች ቀልብ የሚስብ ለጎብኚዎች በሚመች መልኩ ከአዲስ አበባ በሆሳዕና መንገድ 320 ኪ.ሜ ከአዲስ አበባ በሻሸመኔ መንገድ 435 ኪ.ሜ ከሀዋሳ በ212 ኪ.ሜ፣ ከዞናችን ርዕሰ ከተማ ሶዶ በ56 ኪ.ሜ ፣ ከወረዳው ከተማ ቦምቤ በ5 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡

አጆራ ፏፏቴ ሶኬ እና አጃንቾ ከሚባሉ ትላልቅ ወንዞች የሚፈጠሩ መንትያ ፏፏቴዎች ናቸው፡፡

ሁለቱ ፏፏቴዎች 400 ሜትር ተራርቀው ገደል እየተምዘገዘጉ የሚወርዱ አጃንቾ 210 ሜትር ወደ ትልቁ ገደል ጢሰ መስሎ ሲወርድ በተመሳሳይ ሶከ 170 ሜትር ቀልቁል የሚወረወር ድንቅ የተፈጥሮ ስጦታዎች ናቸው፡፡

ከፏፏቴዎቹ በተጨማሪ ሌሎች በርካታ የዱር እንስሳትም መኖርያ ነው፡፡

በተለይም ጉሬዛ ፣ ድኩላ ፣ ከርከሮ፣ ዝንጆሮ፣ ነብር ፣ አጋዘን ፣ ጦጣ እና የተፈጥሮ የዕፅዋት ዝሪያዎች በአከባቢው የተለያየ ስያሜ የሚሰጣቸው ከመኖራቸውም አልፎ ለምግብነት የሚጠቁሙ ቦይና/ጎዳሬ እና ሌሎችም ሥራ ሥር ተክሎች በብዛት ይገኛሉ፡፡

ይህንን ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህብ ልዩ የሚያደርገው

➣ፏፏቴው በሚገርም ሁኔታ የተለያዩ ወንዞች መንትያ ሆነው መውረድ

➣ፏፏቴዎች በ400 ሜትር ተራሪቀው ጎን ለጎን መፈሰሳቸው

➣ፏፏቴው ብቻ አይደለም አከባቢው በተለያዩ የዱር እንስሳትና የዕፅዋት ዝሪያዎች በመኖሩ የቱሪስቶችን ቀልብ መሳብ የሚችል መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

ዎጌታ ኤፍ ኤም በመስክ ምልከታ ይህንን ቦታ የተመለከተ ስሆን ይህንን ቦታ ለመጎብኘት ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ ለሚመጡ ቱሪስቶች የቆይታ ጊዜ ለማራዘም የተሰሩ ስራዎች በጅምር የቀሩ መሆናቸውን ተመልክቷል።

የቱሪስቶችን ቀልብ በመሳብ የቆይታ ጊዜያቸውን ለማብዛት ወሳኝ የሆኑ መንገድ ፣ መብራት ፣ ውሃ ፣ ኢንተርኔት እና ሌሎች መሠረተ ልማቶች አለመሟላት ከመስህቡ ማግኘት የሚገባውን ገቢ ማግኘት አለመቻሉንና ይህንን ቦታ ለማልማት የተለያዩ አካላት ቃል የገቡ ቢሆኑም ግን ምንም አይነት ስራ እስከአሁን መሰራት አለመቻላቸውን ከአካባቢው ነዋሪዎች መረዳት ችለናል።

ይህን ተፈጥሯአዊ መስህብ ሄደው እንዲያዩ እንጋብዛለን።

ምንጭ :- የወላይታ ዞን አሰተዳደር እና ሌሎች መፅሐፍት።

Address

Wolaita
S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share