Gudi Ethiopia

Gudi Ethiopia Mechanical std

03/06/2026

የአማራ ፀረ-ህዝብ የሆኑ ግለሰቦች‼️

"አማራን ሰብረን ጥለነዋል" - ስብሃት ነጋ

" አማራ የሚባል ማህበረሰብ የለም"-አንዳርጋቸው ጽጌ

" ከአማራ ሱዳን ይቀርበናል" - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል

" የአማራ ህዝብ ለሆዱ የተገዛ ፍርፋሪ ልቃሚ ነው" - ቤተልሔም ዳኛቸው
ይህ የሚዲያ ንግግራቸው ለአማራ ህዝብ ያላቸውን ንቀት በግልፅ የሚያረጋግጥ ነዉ።

24/12/2025

፨፦ከቀድሞው የኢፌዲሪ ጠ/ሚኒስትር ክቡር አቶ ኃማርያም ደሳለኝ ቦሼ አንደበት......

የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ኃ /ማርያም ደሳለኝን በተለያዩ አጋጣሚዎች አግኝቻቸው አውቃለሁ። በአንድ ወቅት እንደጋሞ ህዝብ የአጋጠመንን ህዝባዊ ጥያቄ ይዘን ቤተመንግሥት ድረስ ዘልቀን የነበረ ጊዜ ስለጋሞ ህዝብና ስለጋሞነት እንዲህ ብለው ነበር።
"እኔ ለጋሞ ህዝብ ታላቅ ክብርና አክብሮት አለኝ።
ገና በወጣትነት ዕድሜዬ ለመጀመሪያ ጊዜ መሠረተ ትምህርት ለማስተማር የዘመትኩት "ጋሞ ካምባ ሶርባ" የተባለ አካባቢ ስለነበር በዚያ በወጣትነት ዕድሜዬ ከጋሞ ህዝብ ላይ መልካም ሥነ ምግባርን ፣ ፍቅርንና የክራር ጭፈራን ጨምሮ ብዙ ነገሮችን ተምሬአለሁ።
ሥራ የተቀጠርኩት በጋሞ ምድር በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነው፣ሚስት ያገባሁት እና ልጆቼን የወለድኩት በጋሞ ምድር አርባምንጭ ከተማ ነው።
በአጠቃላይ የጋሞ ምድርና ህዝብ ለእኔ እዚህ መድረስ ያስቻሉኝ የበረከቴ ምንጭ ናቸው።
የጋሞ ህዝብ ጥንታዊ ታሪክ በተመለከተም ጥንት የወላይታ ህዝብ ከአካባቢው ህዝብ ጋር በወሰን፣በግጦሽ እና በሌሎች ምክንያቶች በሚፈጠሩ የእርስ በእርስ ግጭቶችና ጦርነቶች ሁሉ የዎላይታን ህዝብ በመምራት እና በማገዝ ለዎላይታ ህዝብ ነፃ መውጣት ከፍተኛ መስዋዕትነት ይከፍል ስለነበረ ታላቁ የዎላይታ ህዝብና አባቶች ዳሞት ተራራ ከአካባቢው ሁሉ ከፍ ያለ በመሆኑ ለተደረገላቸው ድጋፍና መስዋዕትነት መታሰቢያ እንዲሆናቸው በመሸለማቸው አሁን ድረስ በዳሞት ተራራና አካባቢው የሚኖሩ ሰዎች ከጋሞ ከልዩ ልዩ ከአባቢዎች የመጡ እና በወላይታ ህዝብ ዘንድ የተከበሩ "የጋሞ ማላ"የሎንቴ ማላና ሌሎች ጎሣዎች እንደሆኑ እንዲሁም የእርሳቸውም የዘር ሀረግ ሲመዘዝ ኃይለማርያም ደሳለኝ ቦሼ ከጋሞ እንደሆኑ በከፍተኛ የቁጭት ስሜት ውስጥ ሆነው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግሥት ቤተመንግሥት ውስጥ በዎላይተኛ ቋንቋ ስለጋሞ ህዝብ ታላቅነት ፣ሃያልነት ሠላማዊነት ከልብ በመነጨ ስሜት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
(ምንጭ፦እንቆቆ ኮሶ ሻራ)
፨፦፨፦፨፦፨፦፨፦፨፦፨፦፦፨፦፨፦፨፦፨፦፨፦፨፦
የቁጫ ህዝብ የጋሞ አካል ስለመሆኑ አስቀድሜም አውቃለሁ በቁጫ ወረዳ በመሄድ በአካል ተገኝቼ ህዝብ ሰብስቤ እውነታውን ሰምቻለሁ።" አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ(የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር)
*************************************. ለጥቅም ስባል ጋሞን ማጥቃት ከባድ ጥፋት ነው!

**ከመሬት ተነስቶ ነባር የጋሞ ህዝብን ለመበተን የሚደረግ ሩጫ የጥገኞች ሰራ ነው! መቼም አይሳካም።

*** በጋሞ ዞን የማንነት ጥያቄ የሚያነሱት ጋሞዎች ሳይሆኑ በሴራ ፖለቲካ የተካኑ ሌቦች ናቸው!

**በታሪክ የማውቀው ቁጫ እና ዶርዜ ጋሞ ስለመሆናቸው ማስረጃ አያስፈልግም! ጋሞ ናቸው።

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ በአንድ መድረክ ካዎራው ተወስዶ በማህበራዊ ገጽ ከተለቀቀው የተወሰደ።
(ምንጭ ፦ መዓዛ አሸናፊ እና ሸዋ ኮሶ ሻራ)

03/08/2025

ወረቀት ያለዉ እንጅ የተማረ ሰዉ በኢትዮጵያ የለም::ምን ትላለህ??

02/08/2022
04/07/2022

🇸🇳 ያውቁ ኖሯል? ሳዲዮ ማኔ ጨዋታ ሲጫወት በሴኔጋል ያሉ ስራ ሚባል የለም፣ በቃ ለሴኔጋል ሰዎች እንደ በዓል ነው ፣
ለሴኔጋል ማኔ ማለት ትልቅ ስራቸው ነው ፣
ግድባቸው ነው ፣ አባት እናታቸው ነው ፣ ማኔ ሲጫወት ለመመልከት በሴኔጋል የግድ ኳስ አፍቃሪ መሆን የለብህም በቃ ሴኔጋላዊ መሆን ነው ያለብህ ምክንያቱም ማኔ ለሴኔጋል አንድ አለም አቀፍ ታዋቂ እግር ኳስ ተጫዋች ብቻ አይደለማ እንጀራቸውም ዳቦዋቸውም ገቢያቸውም ነው ፣ ሳይወድ በግድ ማኔን ህዝበ ሴኔጋል ቁጭ ብሎ በሰቀቀን ያያል ፣
ታድያ እሱም አያሳፍራቸውም አንድ ጥሩ ወላጅ አባት ለልጁ እንደሚሆነው ነው በቻለው አቅም ህዝቡን ሚረዳው እሱ ሚጫወተው የነሱ ብቻ ስለሆነ አይደለም ለነሱ ብሎ እንደሆነ በተግባር አሳይቷላ ፣
ሺኪ ነህ ቄስ ነህ ባለስልጣን ነህ ሽማግሌ አሮጊት ነው ፖስተር ነህ ቅብርጥሴ የለም ሴኔጋል ላይ ያልተስማማ ሁላ በአንድ ላይ ቁጭ ብሎ ተስማምቶ ሚያየው የማኔን ጨዋታ ብቻ ነው ።

🗣 ማኔም ሲናገር : "ኤፍሲ ባየርን ጨዋታ በሚጫወትበት ጊዜ ማንም አይሰራም በሴኔጋል. ሁሉም ሰው እኔን እያየኝ በቲቪ ላይ ያተኩራል." ታድያ ለዚህ ምስኪን ህዝብ እንኳን ተጫውተህ ብታደርግለት ይቅርና ብትሞትለትስ ምን ይልሀል ለዛውም እልህ ያለበት እንባ ያቀረረ ፈገግታ ብልጭ እያረገ ፣

በዚህ ዓለም ላይ ከምንሠራው በቀር ሌላ ነገር ከሌለ ወንድም እህቶች ሆይ... ለበጎ እናድርገው እስኪ ።

01/07/2022
ንቃ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ....
27/06/2022

ንቃ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ....

ለኢትዮጵያ እንቁም!

[ ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ]

| ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን 3ኛ ዙር ልትሞላ ነው። ይሄንን ዙር ሞልታ ብትተወው እንኳን የሕዳሴው ግድብ ሥራውን ይቀጥላል። ያም ማለት ኢትዮጵያ የላይኛው ተፋሰስ ብቻ ሳትሆን የላይኛው ወሳኝ አካል ትሆናለች ማለት ነው።

ይሄንን ወሳኝ የሀገር ግብ ለማምከን ግብጽና ሱዳን ከአንዳንድ የምዕራብ ሀገሮች ጋር ሆነው የግመሉን ጀርባ የሚሰብረውን የመጨረሻውን ጭነት ኢትዮጵያ ላይ ለመጣል እየተረባረቡ ነው።

ብዙ ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ከአፋቸው የማይጠፋው ምዕራባውያን፣ ኢትዮጵያ ለምታካሂደው አረንጓዴ ዐሻራ የገንዘብ ድጋፍ ሲጠየቁ " ግብጽ ተቃውሞ ስላላት እንቸገራለን" ነው ያሉት። ግብጾች አረንጓዴ ዐሻራን የኢትዮጵያን አፈር ለማስቀረት የተጀመረ ዘመቻ ነው ብለው ነው የሚወስዱት። ግድቡን ማስቀረት ባይችሉ እንኳን በደለል እድሜውን ወይም ዐቅሙን ማሳጠር አንዱ ዓላማቸው ነው። ትግሉ ብዙ መልክ ነው ያለው።

ግብጽና ሱዳን ከአንዳንድ የምዕራብ ሀገሮች የመረጃና የዲፕሎማሲ ድጋፍ በማግኘት ከ4 አካላት ጋር ይሠራሉ። አሠልጥነው በሳዑዲ ተመላሽ ስም ካስገቧቸው አካላት፤ ከአሸባሪ የውጭ ኃይሎች፣ ከአሸባሪ የሀገር ውስጥ ተቋማት እና ከሱዳን ታጣቂዎች ጋር።

በሳዑዲ በረሃ ያሠለጠኗቸውን የኢትዮጵያ ስደተኞች ለማስገባት ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ጫና ፈጥረው ነበር። በማኅበራዊ ሚዲያ በታገዘ ዘመቻ የኢትዮጵያውያን ኅሊና እንዲጨነቅ አድርገው ተጽዕኖ ፈጥረዋል። እንደ አልሸባብ ያሉትን አሸባሪዎች በምሥራቅ ኢትዮጵያ ለማስገባት ሞክረዋል። የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ በኩል ጫና እንዲፈጥሩ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል። የሕወሓት ሰዎች በጁባ በኩል ገብተው ረብጣ ብር እያከፋፈሉ ይሄንን ሲሠሩ ነው የከረሙት። የሸኔ፣ የጋምቤላና የጉሙዝ አሸባሪዎች ሥልጠና ወስደው በሳተላይት መረጃ እየተመሩ በግብጽ ድጋፍ የምዕራቡን ድንበር ፋታ እንዲነሡ ተልከዋል። በአማራ ክልል ያሉ፣ ታጣቂ ነን ባዮችም ከውስጥ ሆነው እንዲረብሹ ሥራ ተሰጥቷቸዋል።
የሱዳን ወታደሮች በኢትዮጵያ የሰሜን ምዕራብ ድንበር ጫና ለመፍጠር ትንኮሳ ጀምረዋል።

በኢትዮጵያውያን ስም እየተጻፉ ከግብጽ የሚመነጩ የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻዎች በውስጥ በሚገኙ አጋጋዮች እየታገዙ የፕሮፓጋንዳ ሥራውን አጧጡፈውታል። በየአካባቢው ዐመጽ ለመቀስቀስ የወጠኑት ሤራ አልይዝ ሲላቸው፣ የጊምቢውን ጭፍጨፋ ለማውገዝ የተደረጉ እንቅስቃሴዎችን "ዐመጽ" ብለው እስከመጥራት ደርሰዋል።

የዚህ ሁሉ ዓላማ ሁለት ነው። ኢትዮጵያውያንን በሐሳብ መከፋፈልና የመከላከያ ሠራዊቱን መወጠር። በፕሮፓጋንዳ ሥራው ኢትዮጵያውያንን በመከፋፈል፣ በጠላቶቻቸው ላይ አንድ ሆነው እንዳይቆሙ ለማድረግ ሁለት ዘዴዎች ታቅደዋል። በተገኘው አጋጣሚ ንጹሐንን በመግደል የሕዝቡን እፎይታ መንሣት የመጀመሪያው ነው። ከሰሞኑ የታየው የምዕራብ ወለጋ አሰቃቂ የአማራዎች ጭፍጨፋ የዚህ አካል ነው። የተፈለገው መግደል ብቻ ሳይሆን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል ሕዝቡን ማሸበር ነው። መጀመሪያ በሱማሌ ክልል አልሸባብ ሞክሮ ከሸፈበት፤ በመቀጠል በጋምቤላና በደምቢዶሎ አካባቢ ተሞክሮ ከሸፈ። በመጨረሻ በቀቢጸ ተስፋ የጊምቢው ጭፍጨፋ ተፈጸመ። በሌሎች አካባቢዎች ሊፈጸሙ የነበሩ ክሥተቶችም በጸጥታ አካላት በየቀኑ እየከሸፉ ነው። የሚያመልጡ አይኖሩም ብሎ መገመት ግን አይቻልም።

የፕሮፓጋንዳው ሌላው አካል ከግብጽ በሚመነጩና በኢትዮጵያ ተላላኪዎች በሚታገዙ የማኅበራዊ ሚዲያ ባንዳዎች የሚሠራ ነው። እምነትንና ብሔርን መሠረት ያደርጋል። በብሔሮች መካከል ብጥብጥ ለመፍጠር እየተሠራ ነው። የኦርቶዶክስ እና የእስልምና እምነቶችን ወደ ግጭት ለመክተት የታቀዱ ሤራዎች አሉ። ዋና ዋና የእምነቱ አስተማሪዎችን በመጠቀም ብጥብጥ መፍጠር። እነዚህ ሁሉ አንጀት መጎተቻ ናቸው።

የዚህ ድምር ውጤት ሠራዊቱ ስትራቴጂካዊ ቦታ ይዞ ለከፋው የሉዓላዊነት ግድጅ እንዳይሠማራ ለማድረግ ነው። እዚህም እዚያም በመተንኮስ ሠራዊቱን ከድንበር ወደ መንደር ለማውረድ። ይሄንን ለማሳካት በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ተጀምሯል። በተለይም ወሳኝ ከሚባሉ አካባቢዎች ሠራዊቱ ወደ ግጭት ቦታዎች እንዲሳብ ለማድረግ እየተሠራ ነው። የሠራዊታችንን ዐቅምና የዝግጁነት ልክ ጠላቶቻችን ጠንቅቀው ያውቁታል። ካለፈው ጦርነት በኋላ የኢትዮጵያ ሠራዊት የት ደረጃ ላይ እንዳለ ከወዳጆቻችን በላይ ጠላቶቻችን እየመረራቸውም ቢሆን ያውቁታል። ያላቸው አማራጭ ለተጨማሪ ዝግጁነት ፋታ እንዳያገኝ መወጠር ነው ብለው አምነዋል። በዚህ በዚያ ሞከሩ። እምቢ አላቸው። አሁን የንዴት ሥራቸውን ሊሠሩ ተነሥተዋል።

ይህ ሁሉ የኢትዮጵያን እግር ሰብሮ ሽባ የማድረግ ዕቅድ የሚከሽፈው የጠላትን ዕቅድ ተረድቶ፣ አንድ ሆኖ በመቆም ነው። አመራሩ እጁንና ልቡን ንጹሕ አድርጎ፣ በጎጥና በጥቅም ከመጓተት ወጥቶ ግዳጁን ይወጣ። አካባቢውን ይጠብቅ፤ ያስጠብቅ፤ ከከፋፋይ ሐሳቦች ይታቀብ። ሕዝቡም ወገቡን አሥሮ፣ ሐሞቱን አኮሳትሮ ለየአካባቢው ዘብ ይቁም። የወገን ሞት ያማል። ሕመሙም የአጥንት ሕመም ነው። በአንድ በኩል የተጎዱትን እየረዳን፣ በሌላ በኩል የሌሎችን ጉዳት ለማስቀረት አንድ ሆነን መሥራት አለብን። የዘመድ ቄስ እንሁን። እየፈታን እናልቅስ። ለኢትዮጵያ እንቁም።

በዚህ ወቅት ኢትዮጵያን ለመታደግ፣ ከጸጥታ አካላት ጋር አንድ ሆነን ከመቆም የተሻለ ምንም አማራጭ የለም። ጥርሳችንን ነክሰን ወሳኝ ምዕራፎቻችንን የግድ እንሻገር።

25/06/2022

የጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ስንብት

| ከባድ ውሳኔ ነው። በህይወት ዘመኔ እንዲህ ዓይነት የነፍስ ትንቅንቅ የሚጠይቅ ውሳኔ ላይ የደረስኩበት አጋጣሚ የለም። ወደፊትም ይኖራል የሚል እምነት የለኝም። አሁን ግን ከባዱን ውሳኔ ወስኛለሁ። ከዚያ በፊት ከራሴ ጋር ዝግ ስብሰባ በተደጋጋሚ አድርጌአለሁ። ከነፍሴ ጋር ተሟግቼአለሁ። የሚቀርቡኝን ወዳጆች አማክሬአለሁ። በመጨረሻም መሆን ይኖርበታል ያልኩትን አድርጌአለሁ። ምርጫ የለኝም።

አዎን! ማይክና ብዕር ሰቅዬአለሁ። ከእንግዲህ በየትኛውም የሚዲያ መድረክ ላይ አልገኝም። ከምሰራበት EMS መልቀቄን የማሳውቀው በከባድ ሀዘን ነው። ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩኝም የቤተሰቤ ጉዳይ ግን ዋንኛው መሆኑን መግለጽ እፈልጋለሁ። ከአራቱ የስንብት ምክንያቶች ሶስቱ ከእኔና ከቤተሰቤ ጋር የተያያዙ ናቸው። ባለፉት 16ዓመታት፣ ከሀገር ቤት አንስቶ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግል ውስጥ አብራችሁኝ የነበራችሁ፣ በዚህም በዚያም ጩኸት ስንጋራ በጋራ የነበርን ሁሉ ከልብ አመሰግናችኋለሁ።

ባልደረቦቼ በርቱ። በEMS በጋራ የጀመርነውን ራዕይ ከዳር እንደምታደርሱት ቅንጣት ታክል አልጠራጠርም። አብሬአችሁ እስከ ደሴቲቱ ባለመዝለቄ አዝናለሁ። የተጀመረው መንገድ አባጣ ጎርባጣ ቢበዛውም በኢትዮጵያዊ ጽናት እንደምትሻገሩት እተማመንባችኋለሁ። አንድ ቀን ዳግም እቀላቀላችሁ ይሆናል። ለጊዜው እኔ ሩጫዬን አቁሜአለሁ። እናንተ ግን ጠንክሩ። ግፉበት። ኢትዮጵያ ከእናንተ ብዙ ትጠብቃለችና።

ለሁሉም ኢትዮጵያን ፈጣሪ ይጠብቅልን። ከመጣባት ክፉ አደጋ ይታደጋት ዘንድ ጸሎቴን እቀጥላለሁ። በጥሞና ጊዜዬም ስለኢትዮጵያ ማሰቤን አላቋርጥም። ሀገሬ ልቤ ውስጥ ናትና ሁሌም፣ የትም አስባታለሁ። በተረፈ ሁላችሁንም አመሰግናለሁ።

በመጨረሻም ኢትዮጵያ ታሸንፋለች። ቸር ሰንብቱ!

Address

S**o

Telephone

+251955325483

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gudi Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category