Gudi Ethiopia

Gudi Ethiopia Mechanical std

02/08/2022
04/07/2022

🇞🇳 ያውቁ ኖሯል? ሳዲዮ ማኔ ጚዋታ ሲጫወት በሮኔጋል ያሉ ስራ ሚባል ዚለም፣ በቃ ለሮኔጋል ሰዎቜ እንደ በዓል ነው ፣
ለሮኔጋል ማኔ ማለት ትልቅ ስራ቞ው ነው ፣
ግድባ቞ው ነው ፣ አባት እናታ቞ው ነው ፣ ማኔ ሲጫወት ለመመልኚት በሮኔጋል ዚግድ ኳስ አፍቃሪ መሆን ዚለብህም በቃ ሮኔጋላዊ መሆን ነው ያለብህ ምክንያቱም ማኔ ለሮኔጋል አንድ አለም አቀፍ ታዋቂ እግር ኳስ ተጫዋቜ ብቻ አይደለማ እንጀራ቞ውም ዳቊዋ቞ውም ገቢያ቞ውም ነው ፣ ሳይወድ በግድ ማኔን ህዝበ ሮኔጋል ቁጭ ብሎ በሰቀቀን ያያል ፣
ታድያ እሱም አያሳፍራ቞ውም አንድ ጥሩ ወላጅ አባት ለልጁ እንደሚሆነው ነው በቻለው አቅም ህዝቡን ሚሚዳው እሱ ሚጫወተው ዚነሱ ብቻ ስለሆነ አይደለም ለነሱ ብሎ እንደሆነ በተግባር አሳይቷላ ፣
ሺኪ ነህ ቄስ ነህ ባለስልጣን ነህ ሜማግሌ አሮጊት ነው ፖስተር ነህ ቅብርጥሎ ዹለም ሮኔጋል ላይ ያልተስማማ ሁላ በአንድ ላይ ቁጭ ብሎ ተስማምቶ ሚያዚው ዹማኔን ጚዋታ ብቻ ነው ።

🗣 ማኔም ሲናገር : "ኀፍሲ ባዚርን ጚዋታ በሚጫወትበት ጊዜ ማንም አይሰራም በሮኔጋል. ሁሉም ሰው እኔን እያዚኝ በቲቪ ላይ ያተኩራል." ታድያ ለዚህ ምስኪን ህዝብ እንኳን ተጫውተህ ብታደርግለት ይቅርና ብትሞትለትስ ምን ይልሀል ለዛውም እልህ ያለበት እንባ ያቀሚሚ ፈገግታ ብልጭ እያሚገ ፣

በዚህ ዓለም ላይ ኚምንሠራው በቀር ሌላ ነገር ኹሌለ ወንድም እህቶቜ ሆይ... ለበጎ እናድርገው እስኪ ።

01/07/2022
ንቃ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ....
27/06/2022

ንቃ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ....

ለኢትዮጵያ እንቁም!

[ ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኀል ክብሚት ]

| ኢትዮጵያ ዚሕዳሎ ግድብን 3ኛ ዙር ልትሞላ ነው። ይሄንን ዙር ሞልታ ብትተወው እንኳን ዚሕዳሎው ግድብ ሥራውን ይቀጥላል። ያም ማለት ኢትዮጵያ ዹላይኛው ተፋሰስ ብቻ ሳትሆን ዹላይኛው ወሳኝ አካል ትሆናለቜ ማለት ነው።

ይሄንን ወሳኝ ዹሀገር ግብ ለማምኹን ግብጜና ሱዳን ኚአንዳንድ ዚምዕራብ ሀገሮቜ ጋር ሆነው ዹግመሉን ጀርባ ዚሚሰብሚውን ዚመጚሚሻውን ጭነት ኢትዮጵያ ላይ ለመጣል እዚተሚባሚቡ ነው።

ብዙ ጊዜ ዚአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ኹአፋቾው ዹማይጠፋው ምዕራባውያን፣ ኢትዮጵያ ለምታካሂደው አሹንጓዮ ዐሻራ ዚገንዘብ ድጋፍ ሲጠዚቁ " ግብጜ ተቃውሞ ስላላት እን቞ገራለን" ነው ያሉት። ግብጟቜ አሹንጓዮ ዐሻራን ዚኢትዮጵያን አፈር ለማስቀሚት ዹተጀመሹ ዘመቻ ነው ብለው ነው ዚሚወስዱት። ግድቡን ማስቀሚት ባይቜሉ እንኳን በደለል እድሜውን ወይም ዐቅሙን ማሳጠር አንዱ ዓላማቾው ነው። ትግሉ ብዙ መልክ ነው ያለው።

ግብጜና ሱዳን ኚአንዳንድ ዚምዕራብ ሀገሮቜ ዹመሹጃና ዚዲፕሎማሲ ድጋፍ በማግኘት ኹ4 አካላት ጋር ይሠራሉ። አሠልጥነው በሳዑዲ ተመላሜ ስም ካስገቧ቞ው አካላትፀ ኚአሞባሪ ዹውጭ ኃይሎቜ፣ ኚአሞባሪ ዹሀገር ውስጥ ተቋማት እና ኚሱዳን ታጣቂዎቜ ጋር።

በሳዑዲ በሹሃ ያሠለጠኗ቞ውን ዚኢትዮጵያ ስደተኞቜ ለማስገባት ኹፍተኛ ዚዲፕሎማሲ ጫና ፈጥሚው ነበር። በማኅበራዊ ሚዲያ በታገዘ ዘመቻ ዚኢትዮጵያውያን ኅሊና እንዲጚነቅ አድርገው ተጜዕኖ ፈጥሚዋል። እንደ አልሞባብ ያሉትን አሞባሪዎቜ በምሥራቅ ኢትዮጵያ ለማስገባት ሞክሚዋል። ዚደቡብ ሱዳን ታጣቂዎቜ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቀላ በኩል ጫና እንዲፈጥሩ ድጋፍ ተደርጎላ቞ዋል። ዚሕወሓት ሰዎቜ በጁባ በኩል ገብተው ሚብጣ ብር እያኚፋፈሉ ይሄንን ሲሠሩ ነው ዚኚሚሙት። ዚሞኔ፣ ዚጋምቀላና ዹጉሙዝ አሞባሪዎቜ ሥልጠና ወስደው በሳተላይት መሹጃ እዚተመሩ በግብጜ ድጋፍ ዚምዕራቡን ድንበር ፋታ እንዲነሡ ተልኚዋል። በአማራ ክልል ያሉ፣ ታጣቂ ነን ባዮቜም ኚውስጥ ሆነው እንዲሚብሹ ሥራ ተሰጥቷ቞ዋል።
ዚሱዳን ወታደሮቜ በኢትዮጵያ ዹሰሜን ምዕራብ ድንበር ጫና ለመፍጠር ትንኮሳ ጀምሚዋል።

በኢትዮጵያውያን ስም እዚተጻፉ ኚግብጜ ዚሚመነጩ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻዎቜ በውስጥ በሚገኙ አጋጋዮቜ እዚታገዙ ዚፕሮፓጋንዳ ሥራውን አጧጡፈውታል። በዚአካባቢው ዐመጜ ለመቀስቀስ ዚወጠኑት ሀራ አልይዝ ሲላ቞ው፣ ዚጊምቢውን ጭፍጹፋ ለማውገዝ ዹተደሹጉ እንቅስቃሎዎቜን "ዐመጜ" ብለው እስኚመጥራት ደርሰዋል።

ዹዚህ ሁሉ ዓላማ ሁለት ነው። ኢትዮጵያውያንን በሐሳብ መኹፋፈልና ዚመኚላኚያ ሠራዊቱን መወጠር። በፕሮፓጋንዳ ሥራው ኢትዮጵያውያንን በመኚፋፈል፣ በጠላቶቻ቞ው ላይ አንድ ሆነው እንዳይቆሙ ለማድሚግ ሁለት ዘዎዎቜ ታቅደዋል። በተገኘው አጋጣሚ ንጹሐንን በመግደል ዚሕዝቡን እፎይታ መንሣት ዚመጀመሪያው ነው። ኹሰሞኑ ዚታዚው ዚምዕራብ ወለጋ አሰቃቂ ዚአማራዎቜ ጭፍጹፋ ዹዚህ አካል ነው። ዹተፈለገው መግደል ብቻ ሳይሆን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል ሕዝቡን ማሾበር ነው። መጀመሪያ በሱማሌ ክልል አልሞባብ ሞክሮ ኚሞፈበትፀ በመቀጠል በጋምቀላና በደምቢዶሎ አካባቢ ተሞክሮ ኚሞፈ። በመጚሚሻ በቀቢጞ ተስፋ ዚጊምቢው ጭፍጹፋ ተፈጞመ። በሌሎቜ አካባቢዎቜ ሊፈጾሙ ዚነበሩ ክሥተቶቜም በጞጥታ አካላት በዹቀኑ እዚኚሞፉ ነው። ዚሚያመልጡ አይኖሩም ብሎ መገመት ግን አይቻልም።

ዚፕሮፓጋንዳው ሌላው አካል ኚግብጜ በሚመነጩና በኢትዮጵያ ተላላኪዎቜ በሚታገዙ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ባንዳዎቜ ዚሚሠራ ነው። እምነትንና ብሔርን መሠሚት ያደርጋል። በብሔሮቜ መካኚል ብጥብጥ ለመፍጠር እዚተሠራ ነው። ዚኊርቶዶክስ እና ዚእስልምና እምነቶቜን ወደ ግጭት ለመክተት ዚታቀዱ ሀራዎቜ አሉ። ዋና ዋና ዚእምነቱ አስተማሪዎቜን በመጠቀም ብጥብጥ መፍጠር። እነዚህ ሁሉ አንጀት መጎተቻ ና቞ው።

ዹዚህ ድምር ውጀት ሠራዊቱ ስትራ቎ጂካዊ ቊታ ይዞ ለኹፋው ዚሉዓላዊነት ግድጅ እንዳይሠማራ ለማድሚግ ነው። እዚህም እዚያም በመተንኮስ ሠራዊቱን ኚድንበር ወደ መንደር ለማውሚድ። ይሄንን ለማሳካት በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ተጀምሯል። በተለይም ወሳኝ ኚሚባሉ አካባቢዎቜ ሠራዊቱ ወደ ግጭት ቊታዎቜ እንዲሳብ ለማድሚግ እዚተሠራ ነው። ዚሠራዊታቜንን ዐቅምና ዚዝግጁነት ልክ ጠላቶቻቜን ጠንቅቀው ያውቁታል። ካለፈው ጊርነት በኋላ ዚኢትዮጵያ ሠራዊት ዚት ደሹጃ ላይ እንዳለ ኚወዳጆቻቜን በላይ ጠላቶቻቜን እዚመሚራ቞ውም ቢሆን ያውቁታል። ያላ቞ው አማራጭ ለተጚማሪ ዝግጁነት ፋታ እንዳያገኝ መወጠር ነው ብለው አምነዋል። በዚህ በዚያ ሞኚሩ። እምቢ አላ቞ው። አሁን ዚንዎት ሥራ቞ውን ሊሠሩ ተነሥተዋል።

ይህ ሁሉ ዚኢትዮጵያን እግር ሰብሮ ሜባ ዚማድሚግ ዕቅድ ዚሚኚሜፈው ዚጠላትን ዕቅድ ተሚድቶ፣ አንድ ሆኖ በመቆም ነው። አመራሩ እጁንና ልቡን ንጹሕ አድርጎ፣ በጎጥና በጥቅም ኚመጓተት ወጥቶ ግዳጁን ይወጣ። አካባቢውን ይጠብቅፀ ያስጠብቅፀ ኹኹፋፋይ ሐሳቊቜ ይታቀብ። ሕዝቡም ወገቡን አሥሮ፣ ሐሞቱን አኮሳትሮ ለዚአካባቢው ዘብ ይቁም። ዹወገን ሞት ያማል። ሕመሙም ዚአጥንት ሕመም ነው። በአንድ በኩል ዚተጎዱትን እዚሚዳን፣ በሌላ በኩል ዚሌሎቜን ጉዳት ለማስቀሚት አንድ ሆነን መሥራት አለብን። ዚዘመድ ቄስ እንሁን። እዚፈታን እናልቅስ። ለኢትዮጵያ እንቁም።

በዚህ ወቅት ኢትዮጵያን ለመታደግ፣ ኚጞጥታ አካላት ጋር አንድ ሆነን ኹመቆም ዚተሻለ ምንም አማራጭ ዚለም። ጥርሳቜንን ነክሰን ወሳኝ ምዕራፎቻቜንን ዚግድ እንሻገር።

25/06/2022

ዹጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ስንብት

| ኚባድ ውሳኔ ነው። በህይወት ዘመኔ እንዲህ ዓይነት ዚነፍስ ትንቅንቅ ዹሚጠይቅ ውሳኔ ላይ ዚደሚስኩበት አጋጣሚ ዚለም። ወደፊትም ይኖራል ዹሚል እምነት ዚለኝም። አሁን ግን ኚባዱን ውሳኔ ወስኛለሁ። ኚዚያ በፊት ኚራሎ ጋር ዝግ ስብሰባ በተደጋጋሚ አድርጌአለሁ። ኹነፍሮ ጋር ተሟግቌአለሁ። ዚሚቀርቡኝን ወዳጆቜ አማክሬአለሁ። በመጚሚሻም መሆን ይኖርበታል ያልኩትን አድርጌአለሁ። ምርጫ ዚለኝም።

አዎን! ማይክና ብዕር ሰቅዬአለሁ። ኚእንግዲህ በዚትኛውም ዚሚዲያ መድሚክ ላይ አልገኝም። ኚምሰራበት EMS መልቀቄን ዚማሳውቀው በኚባድ ሀዘን ነው። ብዙ ምክንያቶቜ ቢኖሩኝም ዚቀተሰቀ ጉዳይ ግን ዋንኛው መሆኑን መግለጜ እፈልጋለሁ። ኚአራቱ ዚስንብት ምክንያቶቜ ሶስቱ ኚእኔና ኚቀተሰቀ ጋር ዚተያያዙ ና቞ው። ባለፉት 16ዓመታት፣ ኹሀገር ቀት አንስቶ በኢትዮጵያ ዚፖለቲካ ትግል ውስጥ አብራቜሁኝ ዚነበራቜሁ፣ በዚህም በዚያም ጩኞት ስንጋራ በጋራ ዹነበርን ሁሉ ኚልብ አመሰግናቜኋለሁ።

ባልደሚቊቌ በርቱ። በEMS በጋራ ዹጀመርነውን ራዕይ ኚዳር እንደምታደርሱት ቅንጣት ታክል አልጠራጠርም። አብሬአቜሁ እስኚ ደሎቲቱ ባለመዝለቄ አዝናለሁ። ዹተጀመሹው መንገድ አባጣ ጎርባጣ ቢበዛውም በኢትዮጵያዊ ጜናት እንደምትሻገሩት እተማመንባቜኋለሁ። አንድ ቀን ዳግም እቀላቀላቜሁ ይሆናል። ለጊዜው እኔ ሩጫዬን አቁሜአለሁ። እናንተ ግን ጠንክሩ። ግፉበት። ኢትዮጵያ ኚእናንተ ብዙ ትጠብቃለቜና።

ለሁሉም ኢትዮጵያን ፈጣሪ ይጠብቅልን። ኚመጣባት ክፉ አደጋ ይታደጋት ዘንድ ጾሎቮን እቀጥላለሁ። በጥሞና ጊዜዬም ስለኢትዮጵያ ማሰቀን አላቋርጥም። ሀገሬ ልቀ ውስጥ ናትና ሁሌም፣ ዚትም አስባታለሁ። በተሹፈ ሁላቜሁንም አመሰግናለሁ።

በመጚሚሻም ኢትዮጵያ ታሞንፋለቜ። ቾር ሰንብቱ!

18/06/2022
08/06/2022
08/06/2022

#እኛም ነገ ምን እንደሚገጥመን አናውቅምና መርዳት እንኳን ባንቜል ፈጣሪ ይማርህ እያልን መልዕክቱን ሌር እናድርግለት አደራራ !!

#ዚወጣቱ ወንድማቜን ዚድሚሱልኝ ጥሪ😭😭

#ኚታቜ በፎቶ ላይ ዚምትመለኚቱት ወንድማቜን ዹፍኖተ ሰላም ኹተማ ነዋሪ ዹሆነው ወጣት አንተነህ ይባላል ባለ ብዙ ተስፋ ፣ ብዙ ህልም ዹነበሹው ወንድማቜን ነበር😭😭

#ዛሬ ግን በጉበት በሜታ ምክኒያት እንደዚህ ስብር ብዬ ዹአልጋ ቁራኛ ኹሆነ ወራቶቜ ተቆጠሩ ቀተሰቊቹ ያላ቞ውን ጥሪት ጹርሰው ሊያሳክሙት ቢሞክሩም ሁሉም ነገር ኹአቅማቾው በላይ ሆኖባ቞ዋል😭

#ህይወት ለአንዱ ደስታ ለሌላው ደግሞ ሀዘን ትሆናለቜ ዛሬ ዹቆምን ቢመስለንም እኛም ነገ ምን እንደሚገጥመን አናውቅምና ፈጣሪ ይማርህ ርያላቜሁ መልዕክቱን ሌር አድርጉለት

#ንግድ ባንክ ፊ 1000201515808 ( አንተነህ አበበ ጎበዜ )

#ስልክ ቁጥር ፊ 09 23 53 57 82

#ሰውን ለመርዳት ትክክለኛው ግዜ አሁን ነው !!

08/06/2022

ቀተሰብ ተስፋ ቆርጩ በቃ አበቃ ሲል በእናንተ ደጋግ ወገኖቜ ልጆቜ ታክመው ተስፋ቞ው ለምልሞ ብዙ ግዜ አይተናል ስለዚህ እንዲህ ያለ ነገር ስናይ አይተን እንዳላዚ አናልፍም እናንተም እንደማታልፉ እናውቃለን እግዜር ውስጣቜሁን እንዳሳሰባቜሁ ይሁን ዚምትሰጡ ሌር ዚምታደርጉ እግዚያብሔር ብድራታቜሁን ይክፈል
እግዚያብሔር ለዚህ ቀተሰብ ዘንበል ይበል
***
ይህ ዹ9 ዓመት ልጅ እዮኀል ዳንኀል ይባላልፀ በ 8 ዓመቱ በኚባድ አፕላስቲክ አኒሚያ (Severe Aplastic Anemia) ተይዞ 1ዓመት ሙሉ እዚተሰቃዚ ነው።

ዚጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እዮኀል ዹመቅኒ ንቅለ ተኹላ (bonemarrow transplant) ህክምና እንደሚያስፈልገው ወስኗል።

ወደ ውጪ ሄዶ ለመታኚም ብዙ ወጪ ይጠይቃል ይህንን ቀተሰቊቹ መሾፈን ስለማይቜሉ ተሚባርበን ሕይወቱን እንታደግ ስል ጥሪያቜንን እናቀርባለን!
👇
https://gofund.me/cba652e0
ዚኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000007608482
ብርሃን ባንክ
1012244241632
***
ዚእዮኀል ቀተሰቊቜ ስልክ
09 75 76 06 35 ፣
09 13 85 25 80

07/06/2022

"በመኪና እዚለመንኩ 😭😭 ነበርፀ ለ4 ልጆቌ ህይወቮን ለማቆዚት..."
***
ሰላም ጀና ይስጥልኝ ወንድሜ ፀጋነሜ ጥላሁን እባላለሁ። አዲስ አበባ ውስጥ አብነት አካባቢ ነዋሪ ነኝ። እባክህ እርዳታህን እሻለሁ ዕድሜ 36ሲሆን ዚአራት ልጆቜ እናት አና ባለትዳር ነኝ። በደሚሰብኝ ዚኩላሊት ህመም ያለፉትን 2 አመታት በዲያለስስ ህክምና ላይ እገኛለሁ። እስኚ አሁን ያቅሜን ጥራለሁ ፈጣሪም እሚድቶኝ ደጋግ ሰዎቜም ተጹምሹው እዚህ ደርሻለው አሁን ደሞ ያለፈውን 3ወር ጀና ቢሮ ወሚቀት(ፍቃድ)ሰቶኝ በመኪና እዚለመንኩ 😭😭😭 ነበር ለልጆቌ ህይወቮን ለማቆዚት ነገር ግን ለምኜም 3ጊዜ በሳምንት እንኳን ማድሚግ አልተቻለም ምክንያቱም ኹተለመነው ላይ ያው ለመኪና ለስፒኚር ለሹፌሩ ለነዳጅ እዚተባለ ገንዘቡ አይጠራቀምም ይህ ብቻ አይደለም መኪና ውስጥ መቀመጥ በራሱ ሙቀቱ እንዳለ ሁኑ ተጚማሪም ዚወገብ ህመም ያዘኝ እባክህ ወንድሜ ለልጆቌ ብለህ ለኔም ጌታ ብድራቱን ይኹፍልሃል እባክህ እርዳኝ ተስፋ ሁነኝ።

እኔ ዚምቜለውን አድርጌያለሁፀ እባካቜሁ ደጋጎቜ ሆይ ያለንን በማካፈል ዚእነዚህን ውብ ህፃናት እናት እንታደጋትፀ እንፀልይላት ለልጆቿ ትኑርላ቞ው😭

1000291506619
(ዚኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
ፀጋነሜ ጥላሁን ባይሳ
/0923026185/

ሌር ሳታደርጉ እንዳታልፉ በእግዚአብሔር ስም እንማፀናለን። #ዚፍቅርመንገድ

Address

S**o

Telephone

+251955325483

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gudi Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category