Wolaita Post

Wolaita Post we are in community visit our page

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ2018 የውድድር ዘመን ምድቦችEthiopian Football Federation
22/01/2026

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ2018 የውድድር ዘመን ምድቦች

Ethiopian Football Federation

የካዎ ጦና መታሰቢያ ሐውልት ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ይመረቃል።
20/01/2026

የካዎ ጦና መታሰቢያ ሐውልት ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ይመረቃል።

ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ሆነች ጥር 10 2018 በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አስተናጋጇን ሞሮኮ በማሸነፍ ሴኔጋል ዋንጫውን አንስታለች። ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ሴኔጋ...
18/01/2026

ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ሆነች

ጥር 10 2018 በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አስተናጋጇን ሞሮኮ በማሸነፍ ሴኔጋል ዋንጫውን አንስታለች።

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ሴኔጋል በተጨማሪ ሰዓት ባስቆጠረችው ብቸኛ ግብ የዋንጫ ባለቤት ሆናለች።

የሴኔጋልን የድል ግብ ፓፔ ጉዬ ከመረብ አሳርፏል።

🚨 𝗕𝗥𝗘𝗔𝗞𝗜𝗡𝗚: በአፍሪካ ዋንጫ ታምር ተከስቷል!👉በአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጫወታ ሴኔጋል ጎል አስቆጥራ ዳኛው ፋውል ነው ብሎ ሽሮ በ98ኛው ደቂቃ ዳኛው ለሞሮኮ የፍጹም ቅጣት ምት በመስጠቱ ...
18/01/2026

🚨 𝗕𝗥𝗘𝗔𝗞𝗜𝗡𝗚: በአፍሪካ ዋንጫ ታምር ተከስቷል!

👉በአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጫወታ ሴኔጋል ጎል አስቆጥራ ዳኛው ፋውል ነው ብሎ ሽሮ በ98ኛው ደቂቃ ዳኛው ለሞሮኮ የፍጹም ቅጣት ምት በመስጠቱ የሴኔጋል ተጫዋቾች የዳኛውን ውሳኔ ተቃውመው ሜዳውን ለቀው የወጡ ቢሆንም #በማኔ ጉትጎታ ተመልሶ ወደሜዳ በመግባት የሴኔጋል በረኛ የፍጹም ቅጣት ምት መልሷል። በዚህ ሰዓት ሴኔጋል ሞሮኮን 1 ለ 0 እየመራች ነው።

 #የወላይታ ንጉሥ የነበሩ የካዎ ጦና ሐውልት መጪው ማክሰኞ ዕለት ጥር 12/2018 ዓ.ም ይመረቃል።
18/01/2026

#የወላይታ ንጉሥ የነበሩ የካዎ ጦና ሐውልት መጪው ማክሰኞ ዕለት ጥር 12/2018 ዓ.ም ይመረቃል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለትውልድ የመጀመሪያውን መዳረሻ ደንቢ ኢኮ ሎጅን በይፋ መረቁ📍በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የተገነባው ይህ ሎጅ በ36.7 ሄክታር ጥብቅ ደን ላይ ያረ...
18/01/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለትውልድ የመጀመሪያውን መዳረሻ ደንቢ ኢኮ ሎጅን በይፋ መረቁ

📍በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የተገነባው ይህ ሎጅ በ36.7 ሄክታር ጥብቅ ደን ላይ ያረፈ ነው፡፡

🔊 የደንቢ ኢኮ ሎጅ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት፤ ከገበታ ለሸገር እና ገበታ ለሀገር መርኃ-ግብሮች የቀጠለ እና ሥራዎቹን ወደ አዳዲስ አካባቢዎች የወሰደ ነው ተብሏል፡፡

💬 “ሥራው ከአካባቢው በተገኙ የግንባታ ቁሳቁሶች እና በአካባቢ አቅም የተገነባ በመሆኑ ዘላቂነትን እና ባለቤትነትን ያንፀባርቃል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናግረዋል።

የተወዳጁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ የአስከሬን ሽኝት ሥነ-ሥርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እየተካሄደ ነው ***************ከትናንት በስቲያ ድንገተኛ ኅልፈቱ የተሰማው ተወዳጁ የኪነ-...
18/01/2026

የተወዳጁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ የአስከሬን ሽኝት ሥነ-ሥርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እየተካሄደ ነው
***************

ከትናንት በስቲያ ድንገተኛ ኅልፈቱ የተሰማው ተወዳጁ የኪነ-ጥበብ ባለሙያ ነጻነት ወርቅነህ የአስከሬን ሽኝት ሥነ-ሥርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እየተካሄደ ይገኛል።

በፊልም እና ቴአትር ተዋናይነት፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት እና በሌሎች የጥበብ ሥራዎቹ ስመጥር የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ሕመም ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም በድንገት ሕይወቱ ማለፉ ይታወሳል።

የተወዳጁ አርቲስት የአስከሬን ሽኝት ሥነ-ሥርዓት ቤተሰቦቹ፣ ወዳጆቹ፣ የሙያ ባልደረቦቹ፣ አድናቂዎቹ፣ የሃይማኖት አባቶች እና ካህናት፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እየተካሄደ ይገኛል።

ዜና ዕረፍትተወዳጁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ተወዳጁ የኪነ-ጥበብ ባለሙያ ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።በፊልም እና ቲያትር ተዋናይነት፣ በቴሌቪዥን ፕሮ...
16/01/2026

ዜና ዕረፍት

ተወዳጁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ተወዳጁ የኪነ-ጥበብ ባለሙያ ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

በፊልም እና ቲያትር ተዋናይነት፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት እና በሌሎች የጥበብ ስራዎች ውስጥ ስመጥር እና ተወዳጅ ከሆኑ የጥበብ ሰዎች አንዱ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ህይወቱ ማለፉ ነው የተገለፀው።

ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት እንደነበር ከኢቢስ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ቦዲቲ ካምፓስ!!በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ቦዲቲ ካምፓስ አዲስ ለተመደቡ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ደማቅ አቀባበል እየተደረገ ነ...
15/01/2026

ቦዲቲ ካምፓስ!!

በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ቦዲቲ ካምፓስ አዲስ ለተመደቡ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ደማቅ አቀባበል እየተደረገ ነው።

ውድ ተማሪዎቻችን እንኳን የሰላም እና የአብሮነት ተምሳሌት ወደሆነው ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር እና ቦዲቲ ካምፓስ እንኳን በሰላም መጣችሁ!!

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
«እውቀትን በተግባር!!»

ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2018 18ኛ እና 19ኛ ሳምንት የውድድር ቦታ ማሻሻያ!የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ10ኛ እስከ 19ኛ ሳምንት ውድድር በአዲስ አበባ፣ አዳማ እና ሀዋሳ...
08/01/2026

ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2018 18ኛ እና 19ኛ ሳምንት የውድድር ቦታ ማሻሻያ!

የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ10ኛ እስከ 19ኛ ሳምንት ውድድር በአዲስ አበባ፣ አዳማ እና ሀዋሳ ከተማ እንሚካሄድ መገለፁ ይታወቃል። 18ኛ እና 19ኛ ሳምንት በሃዋሳ ከተማ የታሰበው ውድድር በአዳማ ከተማ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም እንደሚካሄድ እያሳወቅን የውድድር ቦታ እና የሰዓት ማሻሻያ የተደረገበትን መርሐግብር አያይዘናል ።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር

ማንቼስተር ዩናይትድ ሩበን አሞሪምን አሰናበተአዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን አሰናብቷል፡፡ዩናይትድ ለ14 ወራት ክለቡን የመሩ...
05/01/2026

ማንቼስተር ዩናይትድ ሩበን አሞሪምን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪምን አሰናብቷል፡፡

ዩናይትድ ለ14 ወራት ክለቡን የመሩትን ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ማሰናበቱን አስታውቋል፡፡

ከወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር የተሰጠ የአድራሻ ለውጥ ማሳሰቢያ!!የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት፣የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት እና በከተማ አስተዳደር ግቢ ...
05/01/2026

ከወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር የተሰጠ የአድራሻ ለውጥ ማሳሰቢያ!!

የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት፣የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት እና በከተማ አስተዳደር ግቢ የሚገኙ መምሪያዎች በሙሉ በአዲሱ የከተማ አስተዳደር ህንጻ ግንባታ ምክንያት ከዚህ በፊት ለክቡራን ተገልጋዮች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየበትን የአድራሻ ከታህሳስ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ዋዱ ተብሎ በሚታወቀው ሠፈር ከእንያት ሆስፒታል ወረድ ብሎ ታፍ የነዳጅ ማደያ ፊት ለፊት በሚገኘው ህንፃ አገልግሎት እንደሚሰጥ አሳውቋል ።

በመሆኑም አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ በተጠቀሰው ቦታ ተገኝተው መስተናገድ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል ።

Address

Gununo
S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share