28/01/2026
ወደ ኦርቶዶክስ የማልመለስበት ምክንያት ይህና ያ ነዉ ብላለች እየተባለ በስሜ እየተፃፈ ፓስት የሚደረግ ፅሁፍ ብዙዎችን ሲያከራክር አልፎ ተርፎም የኦርቶዶክስ መምህራን የኔ ፅሁፍ እንደሆነ አምነዉ ለኔ የማይገባኝን መልስ ጭምር ሰጥተዉበት አይቼ አዝኛለሁ።
የኔ ትክክለኛ ስምም ሆነ ፔጅ አፃፃፍ Sofia Shibabaw ሲሆን Sofiya Shibabaw በተሰኘ የዉሸት አካዉንት ሁልጊዜ ያላልኩትን አለች በማለት ለክርክርና ንትርክ ሲዳርጉኝ አያለሁ።
ሰሞኑን ደግሞ የግእዝ ቅዳሴዎችን ፓስት በማድረጌ ተወዛግበዉ መሆኑ ይሆናል ከኦርቶዶክሳዉያን ጋር ለማቃቃር ይሁን ለማማር
ወደ ኦርቶዶክስ የማልመለሰዉ ለዚህና ለዚህ ነዉ አለች እያሉ ደጋግመዉ ይለጥፋሉ።
የሚገርመኝ የዉሸት ሲሆን ላይኩም ሼሩም ኮሜንቱም ይበዛል።
እኔ ከኦርቶዶክ ቤተ ክርስትያን ወጥቻለሁ ብዬም ስለማላዉቅ የማልመለሰዉ ለዚህና ለዚያ ነዉ ብዬ ልፅፍ ፈፅሞ አልችልም።
እናት ቤክርስትያን ላይ ጥያቄ ሲኖረኝ በአክብሮት እንደልጅ ጥያቄዬን አቀርባለሁ እንጂ ለክርክርና ለንትርክ ድፍረቱም ፍላጎቱም የሌለኝ መሆኑ ይታወቅልኝ!!