Wolaita Daily News -WDN

Wolaita Daily News -WDN የበለፀገች፣ ሰላማዊ የሆነችውን እንዲሁም መልካም አስተዳደ?

 #ውሃ  #ጠማን❗ በሰዉነታችን ዉስጥ  እጅግ ጠንካራ የሆኑት አጥንት እና ጥርስ ናቸዉ ።   #ከዲምቱ  #እስከ  #ብላቴ  #ጨርቾ  #ማህበረሰብ   👇 የእነዚህ አካላት ያለ ዕድሜ በሽተኛ የ...
07/09/2025

#ውሃ #ጠማን❗

በሰዉነታችን ዉስጥ እጅግ ጠንካራ የሆኑት አጥንት እና ጥርስ ናቸዉ ። #ከዲምቱ #እስከ #ብላቴ #ጨርቾ #ማህበረሰብ

👇 የእነዚህ አካላት ያለ ዕድሜ በሽተኛ የሚሆኑባቸዉ ምክንያቶች እነሆ፦

✅ አከባቢያችን Great East Afirica rift Valley (ታላቁ የምሥራቅ አፍሪካ ሰምጥ ሸለቆ) ዉስጥ በመሆኑ

✅ለመጠጥ የሚንጠቀመዉ ዉሃ የብላቴ ወንዝ ፣ገባሪ ምንጮችና ጅረቶች ሲሆኑ እነዚህ ዉሃዎች ደግሞ

✅ከፍተኛ የፍሎራይድ መጠን ስለሚኖራቸዉ ይህ ኬሚካል ደግሞ ለአጥንት እና ለጥርስ አደገኛ ጉዳት
የሚያመጣ በመሆኑ

✔ማህበረሰቡ በሙሉ የአጥንት እና የጥርስ በሽታ ሰለባ ሆነዋል ለዘመናት።

✔ዕድሜአቸዉ ከ45 በላይ የሆኑት ያላቸዉን የሰዉነት ክብደት የሚችል ጠንካራ አጥንት ካለመኖራቸዉ
የተነሳ ያለ ዕድሜ መጎበጥ፣ Productive Age ላይ እያሉ dependant የመሆን ችግር፣

✅Spinal choard (የጀርባ አጥንት) filexibility ማጣት የተነሳ በነፃነት የመዘዋወር ችግር፣
የዕድሜ ጣሪያ አነስተኛ መሆን፣

በጣም የሚያማምሩ፣ የሚያስጎመጁ ወንዶችና ሴቶች ልጆች ጥርሰ - ብልዝ ከመሆናቸዉ የተነሳ
ኳሊቲያቸዉ መቀነስ ፣ ከ15 ዓመት ዕድሜ ጀምሮ ያለ እርጅና ጊዜ የጥርስ ህመምተኛና የተወለቄ
ጥርስ እና______ወዘተ።

✅ምን ይህ ብቻ፦
የሚንጠጣዉ ወራጅ ዉሃ ከመሆኑ የተነሳ በዝናብ ወቅት በጎርፍ ታጥቦ ወደ ወንዝ የገቡ
የበከቱና የበሰበሱ የደረቅ እና የፈሳሽ ቆሻሻዎች በአጠቃላይ አበስ ገበሱን፣ Concentrated Salts and
Chemicals ስለሚንጠቀም ተደጋጋሚ አጣዳፊ ተቅማጥና ትዉከት በሽተኛ ድንገተኛ ሞት፣የሆድ ጥገኛ ትሎች በሽተኛ፣

ከሚንጠጣዉ ዉሃ ጋር የሚገቡ ለሰዉ ጤና አደገኛ ኬሚካሎች የተነሳ በሰዉነታችን ዉስጥ toxic materials change into none toxic ( መርዛማ ነገሮችን ከሚንመገባቸዉና ከሚንጠጣቸዉ ነገሮች ጋር ከተመገብን

እንጎዱን የመከላከል ተግባር ሃላፊነት ያለዉ Liver(ጉበት) ከአቅሙ በላይ ሆኖ ስለተገኜ ራሱ በበሽታ መጠቃት
እና ሌሎችም Micros copic የሆኑ በሽታዎች ተጠቂ የሆነ ማህበረሰብ፣ አቤት ባይ አይዞህ ባይ ያጣ!!!!!

እስቲ ፈጣሪ ያሳያችሁ፦

ከሞሮቾ እስከ ዳልቦ ድረስ ያለዉን የመንገድ ግንባታ የሠሩት Sunshine Construction ድርጅት

ለዲቾችና ለድልድያዎች በዚህ አከባቢ ዉሃ ቢንገነባ የፍሎራይድ ኮንተንት ያለዉ ስለሆነ ለመንገዱ
ዕድሜ የለዉም ቢለዉ

ከጉጂ ኦሮሚያ ከፋልቃ በብዙ ወጪ በከባድ ማሽን አስቆፍረዉ ዉሃን እያጓጓዙ ተጠቅመዋል።

ይገርማል ለአዉራ ጎዳና ለመንገድ ሥራ ፣ለድንጋይ ግንባታ ዕድመ አይሰጥም የተባለዉን ዉሃ የሚጠጣ ማህበረሰብ

Guyyee guyyiyaawu በአፄዎቹ፣በደርግ፣በኢህአዴግ የዘመናት የህዝባችንን እንቆቅልሽ በመፍታት

እንደ ስሙ የህዝባችንን ጤናን በማበልፀግ ቅቡልነት ያለዉ ፓርቲ ሀገረ መንግሥት እንዲሆን

ከህዝብ በህዝብ ለህዝብ በdirect and indirect ለተመረጣችሁ ይድረስ ይድረስ ይድረስ!!!!!!

28/08/2025

ፈጣሪ ካሳየን ብዙ እናየዋለን!!....... Kreda በወላይታ ምድር

28/08/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ር/መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ላይ በ Nuso & WT Media የተጀመረውን የኢ-ፍትሃዊነት እና የሴራ ፖለቲካ ማጋለጥ ትግል እደግፋለሁ!

አቶ ጥላሁን ከበደ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተለይ ተወላጆች፣ ተወላጆችና ተወላጆች ላይ በኢፌዲሪ ህገመንግስታችን በሰው ልጅ ስዕብና ላይ ስለሚፈፀሙ ወንጀሎች ተብሎ የተጠቀሱ ፣ ያለፍርድ የሞት ቅጣት እርምጃ የመውሰድ ወንጀሎችን በስልጣኑ አማካኝነት ከመፈፀሙም ባለፈ ከፍተኛ የሙስና ወንጀል ስፈፅም የቆዬ አሁን ላይ አንድን ብሔርን ከሌላው ብሔር ጋር በማጋጨት እልቅት ለመፈፀም ስደግስ የነበረ ለደቡብ ህዝብ ምንም ዓይነት ክብር የሌለው፣ መሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ በግምገማ ወቅት ተነስቷል፡፡ ስለዚህ አይቀርለትም፡፡ "ደግሞ ጩሁልኝ አልቅሱልኝ" ብሏችሁ ነው አይደል የሚታለቅሱለት፡፡ ግድ የለም መሪያችሁ ስመታ ትበተናላችሁ፤ በዚህ አይቀጥልም፡፡

የጥላሁን ከበደን የወንጀል ተግባርና የአሸከሮቹን አባሪ ተባባሪነት አጥብቀ እቃወማለው፡፡ ነፍሰ ገዳይና ሙሰኛ ወንጀለኞች ናቸው፡፡

Nuso & WT Media የህዝብ ድምፅ ናቸው። እውነት፣ ሀቅ፣ ፍትህ፣ ግልፅነት፣ ሰብዓዊነት፣ ቅንነትና ሚዛናዊነት የሚንፀባረቅበት መረጃዎች ዘውትር ለህብረተሰቡ ስለምታደርሱት ከልብ እናመሰግናቸዋለን!🙏

28/08/2025

በደቡብ ኢትዮጵያዊ ክልላዊ መንግሥት ር/መ በአቶ ጥላሁን ከበደ ላይ በWT-MEDIA ና NUSO የተጀመረው
የክልሉ የህዝብ ጥያቄ ነው ።
እንደግፋለን

26/08/2025

እኛ እንደ ህዝብ ያጣናው ነገር ብኖር:...
- የለለውን የለም ያለውን አለ
- ያልተሰራውን አልተሰራም የተሰራውን ተሰርቷል
- እውነትን እውነት ሀሰትን ሀሰት
ጥፋትን ጥፋት ልማትን ልማት
እድገትን እድገት ውድቀትን ውድቀት
ጥንካሬን ጥንካሬ ድክመትን ድክመት... ወዘተ የሚልና ያሉበትን እንድያዩ አቅጣጫ የሚጠቁም ጠፍቶ ተቸገርን!¡!...የቆመ የሚመስል እንዳይውድቅ ይጠንቀቅ ይላል ቅዱስ ቃሉ!!! በንፁህ ህልና መተራረምና መወቃቀስ ቢኖር እላለሁ!!! "Michchikko mooqiyan dochchikko kushiyan" gees nu asay!
Credit - Almaz Anjulo

25/08/2025

(ዘ-ሐበሻ ዜና) አሜሪካ ትላንት ውስጥ የአየር ድብደባ ፈፀመች፡፡ የአሜሪካ አየር ሀይል ትላንት ቅዳሜ (ዜናው እየተዘገበ እያለ እዚህ እሁድ ነው) በሱማሊያ ፑንትላንድ ግዛት በድሮን የታገዘ ድብደባ መፈፀሙ ተዘገበ፡፡

ይህ ድብደባ የተፈፀመው የአይኤስ ጠንካራ ይዞታ በሆነው ባላድ ተራራ አካባቢ ነው፡፡ ከስፍራው የተሰራጩ ዘገባዎች እንደገለፁት ድብደባው በርካታ ሰአታትን የፈጀ ነበር፡፡ ከቦሳሶ ወደብ እንብዛም የማይርቀው ይህ ስፍራ የአሸባሪው ሀይል ጠንካራ ምሽግ የሚገኝበት ሲሆን አርብ እለት የፑንትላንድ ሀይሎች በዚህ ቦታ ላይ ባደረጉት ውጊያ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ነበር፡፡

የፑንትላንድ ፕሬዝደንት ሰኢድ አብዱላሂ ዴኒ በጦር ሀይላቸው ላይ የደረሰው ጥቃት ተጨማሪ ጉዳት እንዳያስከትል በመስጋት ወታደሮቻቸው ወደኋላ እንዲያፈገፍጉ ትእዛዝ መስጠታቸውም ተዘግቦ ነበር፡፡ ይህ በሆነ በነጋታው ማለትም ትላንት ለሊት የአሜሪካ አየር ሀይል የአይኤስ ጠንካራ ምሽግ በሆነው በዚህ ስፍራ ላይ የድሮን ጥቃት መፈፀሙ የተገለፀ ሲሆን የጥቃቱ ያደረሰው ጉዳት ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ አልታወቀም፡፡

25/08/2025

!

ሰሞኑን ወጣቱ ባለሀብት ኢ/ር ብርሃነ መስቀል ክንፈ በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ የተለያዩ ሀሳቦች እየተዘዋወሩ መሆኑን በማስተዋል ስለእሥራቱ ጉዳይ የሚከተሉትን የህግ ጥያቄዎች የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መግለጫ እንዲሰጥ ማንሳት ወደድኩ :- ባልተጣራ መረጃ ማንኛውንም አካል ላለመውቀስና ላለመዝለፍ ትክክለኛው መረጃ እሻለሁ።

"የአንዳንድ ግለሰቦች እሥር ከግለሰብ እሥር በላይ በመሆኑ ህዝቡ ትክክለኛ መረጃ የማወቅ መብት አለው!"

1. የታሰረው በፍርድ ቤት ትፅዛዝ ነው ወይ በወንጀል ድርጊት ተጠርጥሮ ነው?

2. የተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት ምንድነው ?

3. የት ? መች ነው የተከሰተው ? የወንጀል ምርመራው የተጀመረው የት ነው?

4. ምርመራውን የጀመረው አካል ማን ነው [ የደቡብ ኢት/ያ ክልል ፖሊስ / ፌዴራል ፖሊስ / ጋሞ ዞን ፖሊስ ]

5. የተጠረጠረበት ወንጀል ድርጊት የዋስትና መብት የሚነፍግ ነው/አይደለም ?

6. እሥር ቤት ቤተሰቡ ባሉበት አከባቢ ሊታሰር አይችልም ወይ?

7. ባለፈው የፋና ቴሌቪዥን በምርመራ ዘገባው "የማዕድን ሥር ቁማር" በሚል ርዕስ በዘረፉ ያለውን ብልሹ አሠራር ሥርጭት ከማድረጉ ጋር ተገናኝተው ይኄ ሃቅ በመውጣቱ መነሻ በሴራ ታስሮ ሊሆን ይችላል ተብሎ እየተዘዋወረ የሚገኘው መረጃ ትክክል ነው ወይ?

የግርጌ ማስታወሻ:-
1. ወጣቱ ባለሀብት በክልላችንና በሀገራችን በኢንሸስትመንት ዘርፍ ተሰማርቶ ለኢኮኖሚ ዕድገት የድርሻው ከማበርከቱ በተጨማሪ በወላይታ ዞን የተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ሲያጋጥሙ እና የልማት እንቅስቃሴዎች ከማንኛውም ሰው ቀድሞ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያበረክት መቆየቱ ይታወሳል ።

2. ወጣቱ ባለሀብት እንደማንኛውም ግለሰብ በወንጀል ሊጠረጠርና በህግ ቁጥጥር ሥር ሊውል የሚችል መሆኑ የሚታመን ቢሆንም አያያዙና የወንጀል ምርመራው ሂደት በህግ የበላይነት የተመሠረተ የተያዙ ሰዎች ሰብዓዊ መብቶች ባከበረ መልክ መሆን ይገባል።

3. ወጣቱ ባለሀብት አሁን ያለበት ሁኔታና የተያዘበት አግባብ በሚመለከተው አካል በግልፅ ለህዝቡ መግለጫ ሊሰጥ ይገባል።

4. መግለጫ ለመስጠት መዘገየቱ በህዝቡ ዘንድ የእሥሩ ሁኔታ ከህግ አግባብ ውጭ "የማዕድን ሥር ቁማር ዶክሜንታሪ" ጋር በተያያዘ እንደሆነ በስፋት እየተተናፈሰ የሚገኘውን መረጃ እንድናምን ያስገድዳል :: ይህ ደግሞ የህግ የበላይነት መርህን የተከተለ አሠራር አይደለም።

ጠበቃና መምህር ተከተል ላቤና ጤራ

ነሐሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

25/08/2025

በዎላይታ በበርካታ በጎ ተግባራት እና በልማት ስራዎች ተሳትፎ የሚታወቀውን ወጣት ባለሀብትን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አስሮ ወደ አርባምንጭ እያመጣ እንደሆነ ተገለፀ።

የማራ ማይነርስ ባለቤት የሆኑትን አቶ ብርሃነመስቀል ክንፈን (ቤቢ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተለያዩ ወንጀሎች እንፈልጋለን የሚል የፍርድቤት መጥሪያ ይዘው እንደመጡና ጉዳዩን በአርባምንጭ ለማየት ይዘን እንሄዳለን" በሚል ከአዲስአበባ በአሁኑ ሰዓት እያመጡ እንደሆነ ለWT ሚዲያ የአይን እማኝ አስረድተዋል።

የአይን እማኝ እንደገለፀው የማራ ማይነርስ ባለቤት የሆኑትን አቶ ብርሃነመስቀልን ከ20 በላይ የሚሆኑ የታጠቁና ያልታጠቁ ኃይሎች በፖሊስ መኪና ጭኖ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6:00 አከባቢ መውሰዳቸውን አስረድተዋል።

ከ32 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች ያቀፈዉን ክልል ይመሩ ዘንድ ቢሾሙም ከትዉልድ አከባቢያቸዉ ዉጪ ሌላዉን አካባቢ ማየት ተስኗቸዋል ተብለዉ እና ስልጣናቸዉን ተገን በማድረግ ሌብነት ዉስጥ በመዘፈቃቸዉ የሚተቹት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ ከከሰል ድንጋይ ማዕድን ጋር በተገናኘ የተፈፀመበትን በደል በፍርድ ቤት እየሞገተ የሚገኘዉን ወጣቱን የማራ ማይነርስ ባለቤትን አቶ ብርሃነ መስቀል እና ሌሎች የዎላይታ ባለሃብቶችን በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ስማቸዉን በማጠልሸት ሊከሷቸዉ ማቀዳቸውን ከዉስጥ ምጮች ያገኘነዉ መረጃ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በተለይ የማራ ማይነርስ ባለቤት አቶ ብርሃነ መስቀል በደሉን ወደ ፍርድ ቤት ከመዉሰዱ ባሻገር የፓርቲ ሚዲያ የሆነዉ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን መጥቶ በክልሉ ዉሃና ማዕድን ቢሮ ዉስጥ የሚፈፀመዉን ብልሽትና ሌብነት እንዲያጋልጥ አድርጓል በሚል ርዕሰ መስተዳድሩን ትልቅ ነጥብ ማስጣሉን ተከትሎ መፈላለግ እየሰፋ መምጣቱ ተነግሯል።

በዚህም አቶ ብርሃነመስቀልን በህገወጥ መንገድ ለማሳሰር በህግ አግባብ ለመሄድ ምንም ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻላቸዉ በተደጋጋሚ ለካቢኔያቸዉ ቢያቀርቡም የካቢኔ አባላቱ በክልሉ የፍትህ ስርዓት ላይ ጣልቃ እንደማይገቡ፤ እንዲሁም የህግ ማስከበሩ ስራ ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ተጠብቆ በማስረጃ ላይ ተመስርቶ ብቻ እንዲሆን አቋም በመያዝ ሀሳባቸዉን ዉድቅ እንዳደረጉባቸዉ ነዉ ከዉስጥ ሾልከዉ የሚወጡ መረጃዎች የሚጠቁሙት፡፡

በካቢኔያቸዉ ተደጋጋሚ ዉሳኔ የተበሳጩት አቶ ጥላሁን ከበደ አሁን ላይ የክልሉ ካብኔ ሳያውቅ በጥቅምና በተለያዩ ትስስር የሚገኙ ሰዎችን በመጠቀም ከፍትህ ቢሮ ጋር በመተባበር መጥሪያ በማውጣት እንዲታሰር አድርገዋል።

ክልሉ በተለይ በከሰል ማዕድን ማዉጣት ላይ ከህግ አግባብ ዉጪ በአከባቢያዊነት እና በግል ጥቅም ትስስር የሚደረግን ዝርፊያ ዘጋቢ ፊልሙ ፍንትዉ አድርጎ ያሳየ ሲሆን በርካታ የርዕሰ መስተዳደር ስር ያሉ ባለስልጣናት የከሰል ማዕድን ቦታ በተለያዩ ማህበራት ስም መያዛቸዉን ነዉ መረጃዎች የሚጠቁሙት፡፡

በአከባቢው በበርካታ በጎ እና ልማት ስራዎች ተሳትፎ የሚታወቀው ወጣት ባለሀብት ብርሃነመስቀል ክንፈ በዎላይታ ዞን አበላ አባያ ወረዳ ላይ ግዙፍ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የስራ ዕድል ይፈጥራል የተባለ የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ለማስጀመር ህጋዊ መስፈርቶችን በሙሉ በማሟላት 40 ሄክታር መሬት የጠየቀው ከብዙ ውጣውረድ በኋላ በቀን 9/2/2017 ዓ.ም የክልሉ ካቢኔ ባደረገው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ መወሰኑ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ በግልጽና በተጨባጭ በዎላይታ ላይ ኢንቨስትመንት እንዳይስፋፋ ቀጥተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ የሚገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ በቀን 28/2/2017 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ የርዕሰ መስተዳድሩ ምክር ቤት የወሰነው የኢንቨስትመንት መሬት

22/08/2025

ድንበራችን ብርብር ተሻግሮ ነው ያለው ፣ሙሉ ም/አባያ ፣ቁጫ፣ቦሮዳ መሬቱም ህዝቦችን ወላይታ ናቸው። የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደ እሥራኤል ህዝባችንን ና መሬታችን እንመልሳለን
💪💪

12/08/2025

የዛሬን ብቻ በማሰብ የድምቱ ከተማ አስተዳደር ወሰን በCSA በተወሰነዉ ዉሳኔ መሰረት ያለማካለል ችግር መልካም ጅማርዎቻችን ላይ እንቅፋት ልያመጣ ይችላል!

የመንግስት ዕቅድና የድምቱ ከተማ አስተዳደር ዕድገት ነገን ታሳቢ ከማድረግ ይልቅ የዛሬን ጥቅም ብቻ የማሰብ ችግር በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ኢየጨመሬ ይገኛል፡፡

የድምቱ ከተማ አስተዳደር ዕድገት መነሻ በማድረግ ነገን መስራት ካልተቻለ መከራው በሚመጣውም ትውልድና ለከተማዉ ሕዝብ ይቀጥላል ፡፡

መጀመሪያ 8 ቀበሌያት በCSA ተወስኖ ከክልል ጀምሮ እስከ ዞን ዕዉቅና ተሰጥቶ የተላከዉን ወደጎን በመተዉ በአሁኑ ሰዓት 4 ቀበሌያትን ብቻ በመምረጥ ወደ ከተማ አስተዳደሩ ያካተቱ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ከተሞች የፈርጅ ለውጥ በከተሞች መካከል ጤናማ የሆነ የዕድገት ፉክክር እንዲኖር፣ የአገልግሎት አሰጣጣቸው እንዲሻሻል ከማድረጉ ባሻገር በራሳቸው የመወሰን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ የመንግስት ዕቀድና ዓለማ ሆኖ ኢያለ ከድምቱ ከተማ አስተዳደር ጋር የተወሰኑ ቦምቤ ከተማ አስተዳር፣ሻንቶ ከተማ አስተዳደርና በዴሳ ከተማ አስተዳር መጀመሪያ የተወሰነዉን ሙሉ በሙሉና ጨምሮ ያካለሉ ስሆን ድምቱ ከተማ አስተዳደር ከተወሰነዉ ቀንሶ በማስተዳደራቸዉ ከፍተኛ ቅሬታ ኢየፈጠረ ይገኛል።

ስለዚህ የሚመለክተዉ አካል መጀመሪያ ድምቱ ከተማ አስተዳደር ከፈርጅ 4 ወደ ፈርጅ 3 በተቀመጠዉ criteria መሰረት ለዉጥ መደረጉ እየታወቀ እያለ እስከአሁን የከተማ ወሰን ለሕዝብ ግልጽ ሳያደርግና የከተማ ኘላን ሥራ ሳይጀመር ቆይቷል፡፡

የከተማ ፕላን ለከተሞች የወደፊት እድገት ዋና ምሶሶ ከመሆኑም ባለፈ ለከተማው ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት በማምጣት ጤናማና ደስተኛ ማህበረሰብ ለመፍጠርና ለዜጎቻቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ለመሰጠት ወሳኝ ስለሆነ የወደፊት የከተማዉ ዕድገት ታሳቢ በማድረግና ለሕዝብ ግልጽ በማድረግ እንድሰራ እንጠይቃለን፡፡

ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ እያደረጉ ያሉ የዞኑ አስተባባሪ አካላቶች ልብ ማለት የሚገባው ጉዳይ ነው።

26/03/2025

ዎላይታ ቱሣ
1989 ዓ/ም ክረምት ላይ ከእነ ሙሴ ሙንኤ፣ አብርሃም
ባልቻ፣ አብርሃም ጩርፎ ወዘተ በኃላ ተቀዛቅዞ የነበረው
የዎላይታ እግር ኳስ ምስጋና ለቄስ አባ ጂኖ ቤናንቲ
ይግባና ዳግም አንሰራራ፡፡
በዓመቱ ከዞን አሸናፊነት ቀጥሎ የደቡብ ክልል ጥሎ
ማለፍ አሸናፊ መሆኑን በማወጁ ወደ ጂማ ያቀናው ቱሣ
ለዋንጫ ለማለፍ በወቅቱ ታዋቂ ተጫዋቾችን የያዘውን
ኒያላ ገጥሞ 3:0 ከመመራት ተነስቶ በድንቅ ልጆቹ ብቃት
ታግዞ አሸናፊ የሆነበት ከባዱ ጨዋታ አይረሳም፡፡
በፍጻሜው ጨዋታ አልማ (አማራ ልማት ማህበር)
የገጠመው ዎላይታ ቱሣ 1:0 በማሸነፍ የ1989 ዓ/ም
የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ አሸናፊ መሆኑን አረጋገጠ፡፡
በዚህም 1990 ዓ/ም ኢትዮጵያን ወክሎ በአፍሪካ
confi.ዋንጫ ተሳትፎ ከኤርትራው ቀይ ባህር ቡድን ጋር
ተጫውቶ በደርሶ መልስ ጨዋታ በድምር ውጤት መሸነፉና
እንደተመለሰ ሆን ተብሎ ቡድኑ እንዲፈርስ መደረጉ
ያንገበግባል፡፡ ሀላባ ቁሊቶ ድረስ በመኪና ተንጠልጥለን
የሄድንበት የአቀባበል ሂደት ገራሚ ነበር፡፡
እልህ አስጨራሹና ተስፋ የማይቆርጠው ደፋሩ የቡድኑ
አምበል አሰፋ ሆሲሶ፣ ጌታሁን ታደሰ (ጌቼ) የተባለ አሞራ
በረኛ ብቃቱን ለመግለጽ ቃላቶች ያጥሩኛል (የቅ/
ጊዮርጊስና ብሔራዊ ቡድን አባል የነበረ፣ ዘርሁን የተባለ
ጎበዝ በረኛ ( አሮጌ አራዳ)፣ በአስተማማኝ የተከላካይ
መስመር ታከለ ቡቼ፣ አገኜው፣ ሳንቾና በኃላ ላይ ፔሌ
(በቀለ ባልቻ) ፣ጉጌ፤ ገሬ የሚባሉ የአርባምንጭ ልጆች
ወዘተ እያሉ ጎል ማስቆጠር ይናፍቃል፣ አስጨናቂ ታቦር
የተባለ በራሪ ሰው፣ የልጅ አዋቂ አሸናፊ ደበበ፣ ባቡሬ
ጊጊሩ፣ ምስጋና ባንጫ፣ የፊት ለፊት መስመሩን የሚመሩት
የጭንቅላት ኳስ በመግጨትና ጓል በማስቆጠር አደገኛ
የነበረው ሙሴ ጳውሎስ፣ ኳሷን የፈጠሩ ያህል
የሚያሰቃዯት ፤ ሙሉ በሙሉ የዘመናዊ አጥቂ ባህሪ
የተላበሱት ቃቆ ( ኢብራሂም ረሽድ) ከሶዶ እና ክሪዝ
(አለማየሁ የአባቱን ስም ረሳሁት) ከአርባምንጭ
በጥበባቸው ገዙን ፤ ማረኩን እስከ አሁንም ድረስ ሌላ
በእነሱ ደረጃ የተሰራ ኢትዮጵያዊ ጨራሽና አዝናኝ አጥቂ
አላየሁም፡፡ ስማቸውን ያላስታወስኳቸውን ይቅርታ
ተማፀንኩ፡፡
Wolaytta tuussaa እና ሶዶ ከነማ ያደርጉ የነበረው
የደርቢ ጨዋታ ወንድማማቾችን ቤት ውስጥ ለሁለት
ከፍሏል፤ የተጣላ የተኮራረፈ ስንቱ ነበር መሰላችሁ ፡፡
በቱሣ አልጋ ወራሽ ዎላይታ ድቻና በሶዶ ከነማ ቡድኖች
ዳግም የዎላይታ ደርቢ ጨዋታ ለማየት እንታደል ይሁን?
አይዞን ሶዶ ከነማ!!
የቱሣ አርማና ስያሜ ግን ከልቤ አልወጣ ብሎ
አሰቃይቶኛል፡፡ ከታጣ አርማና ስያሜ ይናፍቃል፡፡
ዎላይታ ቱሣ ከኳሱ በተጨማሪ በዘመናዊ የሙዚቃ ታሪክ
ለዎላይታ ባለውለታ ነው፡፡ ካሙዙ ካሣ የማን ውጤት
መሰላችሁ !!
ለቄስ አባ ጂኖ ቤናንቲ ክብርና አድናቆት አለኝ፡፡
ዎላይታ ቱሣ ጣይሳይ ጣዮ
ሚዞፖ ዎቶፖ ዱፎይ ዶዮ
ዎላይቶ ኔ ዎጋ ባሻይ ባዮ፡፡
Photo credit for Mesay p. Thank u
ምንጭ: Amsalu Mesene Wolaita

20/09/2023

ጌታቸው ረዳ ካልመጣ ጊፋታ አናከብርም።
ይጠራልን

Address

Motolomi
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Daily News -WDN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share