Wolaita Daily News -WDN

Wolaita Daily News -WDN የበለፀገች፣ ሰላማዊ የሆነችውን እንዲሁም መልካም አስተዳደ?

26/03/2025

ዎላይታ ቱሣ
1989 ዓ/ም ክረምት ላይ ከእነ ሙሴ ሙንኤ፣ አብርሃም
ባልቻ፣ አብርሃም ጩርፎ ወዘተ በኃላ ተቀዛቅዞ የነበረው
የዎላይታ እግር ኳስ ምስጋና ለቄስ አባ ጂኖ ቤናንቲ
ይግባና ዳግም አንሰራራ፡፡
በዓመቱ ከዞን አሸናፊነት ቀጥሎ የደቡብ ክልል ጥሎ
ማለፍ አሸናፊ መሆኑን በማወጁ ወደ ጂማ ያቀናው ቱሣ
ለዋንጫ ለማለፍ በወቅቱ ታዋቂ ተጫዋቾችን የያዘውን
ኒያላ ገጥሞ 3:0 ከመመራት ተነስቶ በድንቅ ልጆቹ ብቃት
ታግዞ አሸናፊ የሆነበት ከባዱ ጨዋታ አይረሳም፡፡
በፍጻሜው ጨዋታ አልማ (አማራ ልማት ማህበር)
የገጠመው ዎላይታ ቱሣ 1:0 በማሸነፍ የ1989 ዓ/ም
የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ አሸናፊ መሆኑን አረጋገጠ፡፡
በዚህም 1990 ዓ/ም ኢትዮጵያን ወክሎ በአፍሪካ
confi.ዋንጫ ተሳትፎ ከኤርትራው ቀይ ባህር ቡድን ጋር
ተጫውቶ በደርሶ መልስ ጨዋታ በድምር ውጤት መሸነፉና
እንደተመለሰ ሆን ተብሎ ቡድኑ እንዲፈርስ መደረጉ
ያንገበግባል፡፡ ሀላባ ቁሊቶ ድረስ በመኪና ተንጠልጥለን
የሄድንበት የአቀባበል ሂደት ገራሚ ነበር፡፡
እልህ አስጨራሹና ተስፋ የማይቆርጠው ደፋሩ የቡድኑ
አምበል አሰፋ ሆሲሶ፣ ጌታሁን ታደሰ (ጌቼ) የተባለ አሞራ
በረኛ ብቃቱን ለመግለጽ ቃላቶች ያጥሩኛል (የቅ/
ጊዮርጊስና ብሔራዊ ቡድን አባል የነበረ፣ ዘርሁን የተባለ
ጎበዝ በረኛ ( አሮጌ አራዳ)፣ በአስተማማኝ የተከላካይ
መስመር ታከለ ቡቼ፣ አገኜው፣ ሳንቾና በኃላ ላይ ፔሌ
(በቀለ ባልቻ) ፣ጉጌ፤ ገሬ የሚባሉ የአርባምንጭ ልጆች
ወዘተ እያሉ ጎል ማስቆጠር ይናፍቃል፣ አስጨናቂ ታቦር
የተባለ በራሪ ሰው፣ የልጅ አዋቂ አሸናፊ ደበበ፣ ባቡሬ
ጊጊሩ፣ ምስጋና ባንጫ፣ የፊት ለፊት መስመሩን የሚመሩት
የጭንቅላት ኳስ በመግጨትና ጓል በማስቆጠር አደገኛ
የነበረው ሙሴ ጳውሎስ፣ ኳሷን የፈጠሩ ያህል
የሚያሰቃዯት ፤ ሙሉ በሙሉ የዘመናዊ አጥቂ ባህሪ
የተላበሱት ቃቆ ( ኢብራሂም ረሽድ) ከሶዶ እና ክሪዝ
(አለማየሁ የአባቱን ስም ረሳሁት) ከአርባምንጭ
በጥበባቸው ገዙን ፤ ማረኩን እስከ አሁንም ድረስ ሌላ
በእነሱ ደረጃ የተሰራ ኢትዮጵያዊ ጨራሽና አዝናኝ አጥቂ
አላየሁም፡፡ ስማቸውን ያላስታወስኳቸውን ይቅርታ
ተማፀንኩ፡፡
Wolaytta tuussaa እና ሶዶ ከነማ ያደርጉ የነበረው
የደርቢ ጨዋታ ወንድማማቾችን ቤት ውስጥ ለሁለት
ከፍሏል፤ የተጣላ የተኮራረፈ ስንቱ ነበር መሰላችሁ ፡፡
በቱሣ አልጋ ወራሽ ዎላይታ ድቻና በሶዶ ከነማ ቡድኖች
ዳግም የዎላይታ ደርቢ ጨዋታ ለማየት እንታደል ይሁን?
አይዞን ሶዶ ከነማ!!
የቱሣ አርማና ስያሜ ግን ከልቤ አልወጣ ብሎ
አሰቃይቶኛል፡፡ ከታጣ አርማና ስያሜ ይናፍቃል፡፡
ዎላይታ ቱሣ ከኳሱ በተጨማሪ በዘመናዊ የሙዚቃ ታሪክ
ለዎላይታ ባለውለታ ነው፡፡ ካሙዙ ካሣ የማን ውጤት
መሰላችሁ !!
ለቄስ አባ ጂኖ ቤናንቲ ክብርና አድናቆት አለኝ፡፡
ዎላይታ ቱሣ ጣይሳይ ጣዮ
ሚዞፖ ዎቶፖ ዱፎይ ዶዮ
ዎላይቶ ኔ ዎጋ ባሻይ ባዮ፡፡
Photo credit for Mesay p. Thank u
ምንጭ: Amsalu Mesene Wolaita

20/09/2023

ጌታቸው ረዳ ካልመጣ ጊፋታ አናከብርም።
ይጠራልን

01/09/2023

ኩያሰ ኑይሳ በጦና ልጆች ተረቱ

01/09/2023

ድሮ እኔ ሳቀው የወላይታ ዞን አስተዳደር ከዞን ወቶ በፌደራል ሚኒስትር ስሆን ነው። ለአሁኑ ግን 😥😥😥

21/08/2023

አያውቁም እንጂ ይህኛውም ከልል የመጣው በወላይታ ቁርጥ ቀን ልጆች መስዋትነት ነው ።
ክቡር ለሰማዕታት!!

20/08/2023

Who's satenaw?
Satenaw is son of sate(ሳቴ).
son of sate(ሳቴ) is motolomi.
ከሞቶሎሚ ውጭ ሳቴናው አልተወለደም !!

20/08/2023

የወላይታ ዞን አስተዳደር አርባምንጭ ከመሄዱ በፊት በወላይታ ውስጥ የወረዳ ጥያቄ አለ ወይስ የለም ብሎ ፋይል ማየት ነበረበት።
ፋንጎ ህዝብ ይደመጥ!!

20/08/2023

የፋንጎ ህዝብ ወረዳነት ጥያቄ
ለምን ታፈነ?

15/08/2023

ከወላይታ ጋር እኩል ለመሆን ወላይታ ለራሱ መማሩን ትቶት እናንተን አንድ ሺህ ዓመት ማስተማር አለበት።
ታሪክ ያለው ሕይወት አለው ።

15/08/2023

ከኮመንት አለም
አንተ የምትለው ጋሞ የቱ እንደሆነ ባላውቅም ከቁጫና ከቦሮዳ ወደዛ ያለው ህዘብን እንደ ሰው ስቆጥር አይደለ አንተ ከእኔ ጋር ልታወራ የምትችለው። ስማ በወላይታ ምድር ኒውክለር ፈንድቆ እንደ ሄሮሽማ ና ናጋሳኪ ህዝብ አይምሮ ብቀጭጭ እራሱ ከእኛ ጋር ለውድድር አትቀርቡም። መጤ ባይኖ ኖሮ .......... ከውድድሩ ይቀድማል መማር፣ማወቅ ፣ ማልማት።

13/08/2023

ወላይታ ሲልጣን ፈላጊ ነው እኛን ይጮቁኑናል ሲሉት ሲልጣን ፈላጊ ብሆኑ ይህን ቤተ መንግሥት ጥሎ አይሄዱም ነበረ አላቸው

12/08/2023

ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ በፌደሬሽን ምክርቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ላይ ክስ መስርቷል

ጎጎት የጉራጌ የክልል አደረጃጀት ጥያቄ አስተጓጉለዋል ያላቸውን 2 ግለሰቦችንና 5 ተቋማትን በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከስሷቸዋል።

ትናንት ነሐሴ 5፣ 2015 ዓ.ም ከስሻቸዋለሁ ያላቸው:

1ኛ ተከሳሽ የደቡብ ክልል ምክር ቤት የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ወስኖ ባቀረበለት መሰረት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 47/3/ ለ መሰረት በአንድ ዓመት ለጉራጌ ህዝብ ህዝበ ውሳኔ ባለማደራጀቱ፣

2ኛ ተከሳሽ የፌደሬሽን ም/ቤት የደቡብ ክልል ም/ቤት ህገ መንግስታዊ ህዝበ ውሳኔ የማደራጀት ሀላፊነቱን ባለመወጣቱ ከጉራጌ ዞን ም/ቤት የቀረበለትን አቤቱታ በ 2 ዓመት ውሳኔ የመሥጠት በማቋቋሚያ አዋጁና በፌደራል ህገ መንግስቱ 62/3/ መሰረት የተጣለበትን ሀላፊነት ባለመወጣቱ፣

3ኛ ተከሳሽ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የነባሩ የደቡብ ክልልም ሆነ የፌደራሉ ህግ መንግስት እውቅና የሌለውና ሀገሪቱ ከምትከተለው ፌደራሊዝም እውቅና ያልተሰጠው በክላስተር መደራጀት የሚል ጥናት በማጥናት በመላው ደቡብ ክልል እና በጉራጌ ህዝብ ላይ ተፈጻሚ እንዲሆን በመስራት የጉራጌ ህዝብ በህገ መንግስቱ እና በዓለማቀፋዊ የሰብዓዊ መብቶች የተከበሩለትን እና በተወካዮቹ አማካኝነት በዞኑ ም/ቤት ያጸደቀውን እራስን በእራስ የማስተዳደር መብቱን የነፈገ በመሆኑ፣

4ኛ ተከሳሽ አቶ አገኘሁ ተሻገር የፌደራሽ ም/ቤት አፈ ጉባዔ ሲሆኑ የጉራጌ ህዝብ በተወካዮቹ አማካኝነት የወሰነውና ለሚመሩት ተቋም የቀረበውን አቤቱታ ወደ ጎን በመተው ባልተሰጣቸው ስልጣን ነባሩ ደቡብ ክልል ባለበት እንዲቀጥል በማለት በፌደሬሽን ምክር ቤት አባለትም ሆነ ጉዳዩን በሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ያልተወሰነ ውሳኔ ለሚዲያ ቀርበው በመግለጻቸው፣

5ኛ ተከሳሽ የደቡብ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ከደቡብ ክልልም ሆነ ከፌደራሉ ህገ መንግስት አሰራር ውጪ በሆነ መንገድ እና አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በደቡብ ክልል ም/ቤት ሳይታወጅ የህግ እውቅና የሌለው ‹‹ኮማንድ ፖስት›› የሚባል አፋኝ አዋጅ በማወጅ በተደጋጋሚ ጊዜ የዞኑን ማህበረሰብ ሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መሰረታዊ መብቶች እንዲገደቡ በማድረጉ፣

6ኛ ተከሳሽ አቶ አለማየሁ ባውዴ ይህንኑ ‹‹ኮማንድ ፖስት›› የሚሉት ህገ ወጥ አዋጅ በደቡብ ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት በመቅረብ በመግለጽና ኮማንድ ፖስቱን በበላይነት በመምራት የዞኑን ማህበረሰብ ሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መሰረታዊ መብቶች ህገ ወጥ ገደብ እንዲደረግበት ያደረጉ በመሆኑ እና

7ኛ ተከሳሽ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በደቡብ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ የታወጀውን ህገ ወጥ ኮማንድ ፖስት ለማስፈጸም የደቡብ ክልል ልዩ ሀይል ፖሊስ አባለት በገፍ በመላው ጉራጌ ዞን በመመደብ የዞኑን ማህበረሰብ ሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መሰረታዊ መብቶች እንዲገደቡ ከማድረጉም በላይ በአንድ ሰው ላይ የሞት እና ብዙ ቁጥር ባላቸው የማህበረሰቡ ተወላጆች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም የስነ-ልቦና ጉዳት እንዲደርስባቸው ያደረገ በመሆኑ ክስ ተመስርቶባቸዋል።

ክሱን የሚከታተሉ ከ20 በላይ ጠበቆች መወከላቸውንም ፓርቲው ተናግሯል።
DDN ሐምሌ 6፣ 2015 ዓ.ም

Address

Motolomi
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Daily News -WDN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share