Mosa Kedir

Mosa Kedir Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mosa Kedir, Digital creator, T'ora.

 #ሰበር ዜና :-የሆርሙዝ ወሽመጥ ለዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች ክፍት ተደረገ::ሚያዚያ 9፣ 2018 :- አዲስ አበባ በመካከለኛው ምስራቅ ለወራት ዘልቆ የነበረውን ውጥረት ተከትሎ ተጥሎ የ...
17/04/2026

#ሰበር ዜና :-የሆርሙዝ ወሽመጥ ለዓለም አቀፍ የንግድ መርከቦች ክፍት ተደረገ::

ሚያዚያ 9፣ 2018 :- አዲስ አበባ በመካከለኛው ምስራቅ ለወራት ዘልቆ የነበረውን ውጥረት ተከትሎ ተጥሎ የነበረው የባህር ላይ ትራንስፖርት ገደብ መነሳቱን የኢራን መንግስት በይፋ አስታወቀ።

በእስራኤል እና በሊባኖስ መካከል የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት እንደ መልካም አጋጣሚ የተጠቀመችው ኢራን፣ በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ስታካሂድ የነበረውን የደህንነት ቁጥጥር በማላላት ለሁሉም የንግድ መርከቦች ክፍት ማድረጓን ገልጻለች።

Via Aljazeera

ስለ ቴዲ አፍሮ እቶሪከ አልበም ክቡር ዶ.ር ለማ መገርሳ ምን አሉ?የቴዲ አፍሮ አዲስ "እቶሪካ" የተሰኘ አልበም ዉስጥ "ዳስ ጣል" የምል track ላይ ትንሽ እይታዬን ላጋራችሁ እፈልጋለሁ::...
17/04/2026

ስለ ቴዲ አፍሮ እቶሪከ አልበም ክቡር ዶ.ር ለማ መገርሳ ምን አሉ?የቴዲ አፍሮ አዲስ "እቶሪካ" የተሰኘ አልበም ዉስጥ "ዳስ ጣል" የምል track ላይ ትንሽ እይታዬን ላጋራችሁ እፈልጋለሁ::
=================
ቴዲ “ሀገር የሞተበት የት ሄዶ ያለቅሳል?” ሲል የቁጭት ድምፅ አሰምቷል። እውነት ነው ሀገር ሞታለች ግን የሞተችው ሀገር እርሱ በምናቡ የሳላትና ለሚናፍቃት የጥንቷ ኢትዮጵያ ናት። ያቺ በነገሥታት መዋቅርና በፊውዳል ሥርዓት ላይ ተገንብታ የነበረችው ኢትዮጵያ በ1966 ዓ.ም. በሕዝባዊ አብዮት ላትመለስ ተቀብራለች።

​አርቲስቱ ቀጥሎም አዲስ አበባ የሁሉም አይደል ወይ?" ብሎ ሲጠይቅና "መሃል ገቡና አቆሙን ከዳር" ይላል፣ ከተማዋ የማንነት ፖለቲካ ሰለባ ሆናለች የሚል ስጋቱን ለመግለጽ ሞክሯል። ሆኖም ይህ አገላለጽ ከተጨባጭ ሁኔታው ጋር በእጅጉ ይጋጫል፦
​የምርጫ እንጂ የመገፋት ውጤት አይደለም፦ ዛሬ ላይ እንደ ለገጣፎ እና ሸገር ባሉ ራቅ ያሉ አካባቢዎች የሚገነቡ ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች (ቪላዎች) የባለሀብቶችና የከፍተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች ምርጫ እንጂ ማንም በግድ ያስወጣቸው "ዳር" አይደሉም።

ከተማ ስትሰፋ መሃል የነበረው ወደ ዳር መውጣቱ የተፈጥሮ እድገት እንጂ ፖለቲካዊ መፈናቀል ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም። አርቲስቱም ሆነ መሰሎቹ በገዛ ፍቃዳቸው በገዙት ዘመናዊ ቤት እየኖሩ "ወደ ዳር አወጡኝ" ብሎ ማልቀስ፣ በምቾት ውስጥ ሆኖ የመገለልን ካባ የመደረብ ያህል ነው።

​​በቴሌቪዥን መስኮት (እንደ ሰይፉ ፋንታሁን ፕሮግራም) በምናየው ምስል፣ አርቲስቱ እጅግ በደላውና ዘመናዊ በሆነ የኑሮ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ግልጽ ነው። በዚህ የቅንጦት ኑሮ ውስጥ ሆኖ "ተገፋን፣ ተገለልን" የሚል የለቅሶ ቃና ማሰማት፣ ከእውነተኛው የሕዝብ ችግር ጋር የማይገናኝ የቃላት ጨዋታ ነው። ይህ አይነቱ አቀራረብ በወቅታዊው የፖለቲካ ስሜት ተጠቃሚ ለመሆን የሚደረግ ጥረት እንጂ፣ በተግባር የሚታየውን የራሱን የተደላደለ ኑሮ አይወክልም።

ባጭሩ፣ የቴዲ አፍሮ የግጥም ስራዎች ካለፈው የፊውዳል ናፍቆት ያልተላቀቁ እና ከራሱ የኑሮ ደረጃ ጋር የማይጣጣሙ ናቸው። ዛሬ ላይ የሚያስፈልገው የሞተን ሥርዓት እየናፈቁ ማልቀስ ሳይሆን፣ አዲሷንና የሁሉንም እኩልነት የምታከብረውን ኢትዮጵያ በእውነታው ዓለም መገንባት ነው።

በመጨረሻ የ 8 ቁጠር አባዜ ታዉቃላችሁ ወይ? ተቃርኖ ወይስ ድጋፍ ይወክላል?

8 ዓመት ጠብቆ ለሕዝብ ድምፅ ለመሆን ነው የመጣው? ወይስ ለሽቀለ ነው?

እንሰማለን..........እንፈርዳለን!

በምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት በዋና አፈጉባኤ  በወ/ሮ መዲና ኤርጎሻ የተመራ ልዑካን ቡድን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ በስልጤ ዞን ላንፉሮ ወረዳ  ምክር ቤት ገብተዋል። ➖➖➖➖➖➖➖ሚያዝያ...
16/04/2026

በምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት በዋና አፈጉባኤ በወ/ሮ መዲና ኤርጎሻ የተመራ ልዑካን ቡድን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ በስልጤ ዞን ላንፉሮ ወረዳ ምክር ቤት ገብተዋል።
➖➖➖➖➖➖➖
ሚያዝያ 8/2018ዓ.ም (ላንፉሮ ኮሙዩኒኬሽን) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት በዋና አፈጉባኤ በወ/ሮ መዲና ኤርጎሻ የተመራ ልዑካን ቡድን የልምድ ልውውጥ ለማድረግ በስልጤ ዞን ላንፉሮ ወረዳ ምክር ቤት ተገኝቷል ።

በዚህም በወረዳው ዋና አስተዳደሪ በአቶ ሸምሴ ጉንዳ እና በላንፉሮ ወረዳ በዋና አፈጉባኤ በክብርት በወይዘሮ ተሚማ ልግብቾ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

በልምድ ልውውጡም በወረዳው በምክር ቤት በተከናወኑ በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ትክረት ያደረገ መሆኑም ተጠቅሷል

እንኳን ደስ ያለንሀላባ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አደገ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2018 የውድድር ዘመን ምድብ ለ 20ኛ ሳምንት ጨዋታ ዛሬ በሀላባ ከተማ እና ደሴ ከተማ መካከል ሀዋ...
15/04/2026

እንኳን ደስ ያለን
ሀላባ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አደገ

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2018 የውድድር ዘመን ምድብ ለ 20ኛ ሳምንት ጨዋታ ዛሬ በሀላባ ከተማ እና ደሴ ከተማ መካከል ሀዋሳ ላይ ተደርጓል።

በዚህም ጨዋታ ሀላባ ከተማ ደሴ ከተማን 1 ለ 0 በማሸነፍ ነጥቡን 38 አድርሶ አንድ ጨዋታ እየቀረው በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል።

07/04/2026

የአላህ አንተ ሰላም አርገው !!

30/09/2025
04/06/2025

❤ “የአረፋ ቀን ፆም ያለፈውንና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል!!”
ረሱል (ﷺ)
ነገ መፆም እንዳንረሳ‼

Address

T'ora

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mosa Kedir posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share