21/03/2026
የኢሠራ ወረዳ መንግስትና ብልፅግና ፓርቲ በወላድ እናት ላይ እየቀለዱ እንደሆነ ሕዝብ ይወቅ !
በቀን 11/07/2018 በዳሊ ጤና ጣቢያ አንድት ወላድ እናት በምጥ ተያይዛ ወደ 5:00 ሰዓት አከባቢ ገብታለች, ይህች እናት በምጥ ሥርዓት ወይም ሂደት ላይ ችግር ስለነበረባት እስከ ምሽቱ 4: 00 ድረስ ክትትል ተደርጎላት መውለድ ባለመቻሏ ጤና ባለሙያዎች ወደ ሆስፕታል ሪፌር አድርጓታል, ለአምቡላንስ ስደወል የወረዳ አመራሮች ነዳጅ የለንም በማለት ጉዳዩን ከሰሙ በኋላ ለችግሩ መፍትሔ ከማመቻት ይልቅ ስልክ ዘግቶ ተኝቷል /የወረዳ አስተዳዳሪ,የጤና ኃላፊ, የአስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ,የፓርቲ አመራሮች ናቸው/ እጅግ ያሳዝናል በእናት እንድህ አይጨከንም, ነዳጅ ልጠፋ ይችላል ግን መፍትሔ ማበጀት ስገባቸው ስልክ መዝጋት የመንግስትና የሕዝብን ሐላፍነት መዘንጋት ነው ,ግን እንደነሱ ያልጨከነ ፈጣሪ ቤተሰብ ተስፋ ቆርጦ እያለቀሰ እያለ ከብዙ ስቃይ በኋላ በቀን 12/07/2018 ጧት 2:00 ሰዓት ገደማ ህይወቷ ተርፎ በሠላም ተገላግላለች, ለስልጠና ለስብሰባ ስሆን የማይጠፋ ነዳጅ ለእናት ስሆን ይጠፋል ወይ? ሕዝብን እየመራው ነው የሚል መንግስት እንደት መጠባበቂያ አንድ በርሜል ነዳጅ ያጣል? ይህን ካጣ ደግሞ ሕዝብን እየመራን ነው ማለት ይቻላል ወይ? ይህንን ሕዝብ ይፍረድ !!!