Akiya Media

Akiya Media Akiya Media አኪያ ሚዲያ welcome to our YouTube Channel Subscribe now and gat more benefits.

09/08/2025
  የትግራይ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ በትግራይና አፋር ክልሎች አዋሳኝ የሚንቀሳቀሰው የትግራይ አፈንጋጭ ታጣቂ ቡድን ዛሬ በክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት አድርሷል በማለት ማምሻውን...
09/08/2025


የትግራይ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ በትግራይና አፋር ክልሎች አዋሳኝ የሚንቀሳቀሰው የትግራይ አፈንጋጭ ታጣቂ ቡድን ዛሬ በክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት አድርሷል በማለት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ከሷል።

ቢሮው፣ ታጣቂ ቡድኑ "ጠብጣብ" በተባለ ቦታ ላይ አደረሰው ባለው ጥቃት የአንድ የክልሉ ጸጥታ ኃይል አባል ሕይወት መጥፋቱን ገልጧል። ይህ አጥፊ ተግባር ከቀጠለ ቡድኑን በሚመሩና በሚያስተባብሩ አካላት ላይ ርምጃ እወስዳለሁ በማለት ያስጠነቀቀው ቢሮው፣ ደም መፋሰሱ ባስቸኳይ ይቁም በማለት ጥሪ አድርጓል።

Akiya Media Meta Newsroom @

08/08/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ ከምሽቱ 7:19 ላይ አርብ ምሽት ላይ !
ከደብረብርሃን ትንሽ ረቀት ላይ 4.6 የተመዘገበ

የቅድስት ድንግል ማርያም ምስልቪዲዩ https://t.me/AkiyaMediaB  ያገኙታልሰሞኑን በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የታየው ሁኔታ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። በሰማይ ላይ በድንገት ብቅ ያለው ደ...
08/08/2025

የቅድስት ድንግል ማርያም ምስል

ቪዲዩ https://t.me/AkiyaMediaB ያገኙታል

ሰሞኑን በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የታየው ሁኔታ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። በሰማይ ላይ በድንገት ብቅ ያለው ደመና የቅድስት ድንግል ማርያም ምስል ብዙዎች ተመልክተዋል።

ይህ አስደናቂ ትዕይንት ሲነገር በቪዲዮም ተቀርጿል። በተለይም አንድ ወጣት ከልቡ "ወላሂ ማርያም" ነች እያለ ሲደመጥ፣ ክስተቱ ምን ያህል አስገራሚ እንደነበር ያሳያል።

ብዙዎች እንደሚሉት፣ በደመናው መካከል የድንግል ማርያም ምስል መታየቱ እጅግ መንፈሳዊ ስሜት ቀስቅሷል።

ይህ ያልተለመደ የሰማይ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ብዙዎችን እያነጋገረ ሲሆን፣

ተአምር ነው የሚሉ አስተያየቶች
እየተሰጡበት ይገኛል።

Facebook 🗳

https://www.facebook.com/share/1AwjSPfv8T/

Telegram 📱

https://t.me/AkiyaMediaB

ምን ጉድ ናት .........
07/08/2025

ምን ጉድ ናት .........

Check out Lyric Craft’s video.

07/08/2025

በቲክቶክ ሲዘዋወር ያገኘነው ነው በዚህ ጉዳይ ሞን ትላላችሁ ?

በኢትዮጵያና በሱማሊያ መካከል አዲስ ውጥረት መስፈኑ ተገለፀ፡፡ ከስፍራው የተሰራጩ መረጃዎች እንዳስረዱት በትላንትናው እለት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ከኢትዮጵያ ጋር ድንበር በሚዋ...
07/08/2025

በኢትዮጵያና በሱማሊያ መካከል አዲስ ውጥረት መስፈኑ ተገለፀ፡፡ ከስፍራው የተሰራጩ መረጃዎች እንዳስረዱት በትላንትናው እለት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ከኢትዮጵያ ጋር ድንበር በሚዋሰነው ጌዶ ክልል ዶሎ ከተማ ተገኝተው ነበር፡፡

በከተማው ውስጥ ከሚገኙ የአገር ሽማግሌዎችና የጁባላንድ አስተዳደር ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረጉት መኮንኖቹ ‹‹አሁን ያለው ሁኔታ ለኢትዮጵያ የድንበር ጥበቃ አስተማማኝ አይደለም›› የሚል መልእክት ማስተላለፋቸው ተዘግቧል፡፡ በዚህ መሰረት አካባቢውን በተለይም ባለድ ሀዎ የተሰኘውን ስፍራ የሱማሊያ መከላከያ ሰራዊት ለቆ እንዲወጣ ጥያቄ እንዳቀረቡ ተገልጿል፡፡

ይህንን አካባቢ በቅርቡ የሱማሊያ መከላከያ ሰራዊት ከጁባላንድ ታጣቂዎች ላይ ነጥቆ መቆጣጠሩ የሚታወስ ነው፡፡

የጌዶ ክልል ዋና አስተዳዳሪ አብዱላሂ ሺምብር በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያ የጦር መኮንኖች ይህንን ጥያቄ ማቅረባቸውን አረጋግጠዋል፡፡ አስተዳዳሪ ሲናገሩ ‹‹የኢትዮጵያ የጦር መኮንኖች በ72 ሰአታት ውስጥ የሱማሊያ ወታደሮች ለቀው እንዲወጡ ትዝዛዝ ሰጥተዋል፡፡ ይህን ትእዛዝ የሰጡት ግን በሱማሊያ ድንበር ውስጥ ነው፡፡›› ካሉ በኋላ ትእዛዙን እንደሚቃወሙ ገልፀዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ እስካሁን ከሱማሊያ ፌዴራል መንግስትና ከኢትዮጵያ በኩል የተባለ ነገር የለም፡፡

በኢትዮጵያ ወታደራዊ መኮንኖችና በጌዶ ክልል አስተዳደር መካከል የተፈጠረው ይህ ክስተት፣ በቀላሉ የሚታይ የድንበር ውዝግብ ሳይሆን፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ አደገኛ ምዕራፍ ሊያስገባ የሚችል፣ በከፍተኛ ጥንቃቄ መያዝ ያለበት ጉዳይ ነው።

ይህንን ዜና ተከትሎ በቀጣዮቹ ቀናት ሊፈጠሩ የሚችሉ ሶስት ዋና ዋና ክስተቶች አሉ፦

1. ከባድ የዲፕሎማሲያዊ ቀውስ

ይህ በጣም ፈጣኑና ተጠባቂው ውጤት ነው።

⚫️ የሶማሊያ መንግስት ምላሽ፦ ምንም እንኳን የሶማሊያ ፌደራላዊ መንግስት ለጊዜው ዝምታን ቢመርጥም፣ ይህ ዝምታ ሊቀጥል አይችልም። የኢትዮጵያ ጦር በግዛቴ ውስጥ ገብቶ ለሀገሬ ጦር የ72-ሰዓት ኡልቲማተም ሰጠ መባሉ፣ የሉዓላዊነት ጥያቄን በቀጥታ የሚነካ በመሆኑ፣ የሞቃዲሾ መንግስት ድርጊቱን በይፋ እንዲያወግዝ ይገደዳል።

⚫️ ዓለም አቀፍ ጫና፦ ሶማሊያ፣ ጉዳዩን ወደ ቀጠናዊ ድርጅቶች (እንደ ኢጋድ እና የአፍሪካ ህብረት) እንዲሁም ወደ ተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት በመውሰድ በኢትዮጵያ ላይ የዲፕሎማሲ ጫና ለመፍጠር ትሞክራለች።

2. ወታደራዊ ፍጥጫ

ይህ በጣም አደገኛውና አስፈሪው አማራጭ ነው።

⚫️የኢትዮጵያ ጦር የሰጠው የ72-ሰዓት የጊዜ ገደብ ሲያበቃ፣ የሶማሊያ ጦር ከቦታው የማይወጣ ከሆነ፣ የኢትዮጵያ ጦር ኃይል ለመጠቀም ይገደድ ይሆን? የሚለው ወሳኝ ጥያቄ ይሆናል።

⚫️ የኢትዮጵያ ጦር ኃይል ለመጠቀም ከወሰነ፣ በሁለቱ ሀገራት ብሔራዊ ጦሮች መካከል ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭት ሊቀሰቀስ ይችላል። ይህ ደግሞ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ስስ የሰላም ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ሊያናጋ የሚችል አዲስ ጦርነት ይሆናል።

3. የሶማሊያ የውስጥ ፖለቲካ መባባስ

የኢትዮጵያ እርምጃ፣ የሶማሊያን የውስጥ ፖለቲካ የበለጠ ሊያወሳስበው ይችላል።

⚫️ የሶማሊያ ጦር ከቦታው እንዲወጣ መጠየቁ፣ በቅርቡ አካባቢውን ተነጥቆ የነበረውን የጁባላንድን አስተዳደር በቀጥታ የሚጠቅም ነው። ይህም፣ ኢትዮጵያ በሞቃዲሾ ማዕከላዊ መንግስት እና በጁባላንድ ክልላዊ አስተዳደር መካከል ባለው የሥልጣን ሽኩቻ ውስጥ የአንድ ወገን ደጋፊ ሆና እየገባች እንደሆነ ሊያስቆጥራት ይችላል።

በቀጣዮቹ 72 ሰዓታት የሚሆነው ነገር ወሳኝ ነው። የሁለቱም ሀገራት መንግስታት ጦርነትን ለማስቀረት አስቸኳይ የዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን ካላደረጉ፣ እና የሶማሊያ ጦር ከቦታው ለመውጣት ካልተስማማ፣ በአፍሪካ ቀንድ አዲስና አደገኛ የሆነ ግጭት ልናይ እንችላለን።

Akiya Media Meta Newsroom

06/08/2025

ለግንዛቤ ??? የኦሮሚያ ልዩ ሀይል ትጥቅ እና በተለያዩ ጊዜያት የሰለጠኑ ልዩ ሀይል ተመራማሪዎች !!!

በዚህ ደረጃ የልዩ ሀይል ተወዳዳሪ ክልል ከትግራይ ውጪ ይኖር ይሆን ?

ከናይሮቢ - አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት ተጀመረ አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት በቅርቡ ከናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ የአውቶብስ ጉዞ መ...
06/08/2025

ከናይሮቢ - አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት ተጀመረ

አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት በቅርቡ ከናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ የአውቶብስ ጉዞ መጀመሩን አስታውቋል።

አንድ የአውቶብስ ትኬት ዋጋ 7,500 የኬንያ ሽልንግ ሲሆን፣ ለደርሶ መልስ ጉዞ ደግሞ 15,000 የኬንያ ሽልንግ ያስከፍላል። ይህ ዋጋ በኢትዮጵያ ብር ሲሰላ 16,000 ብር ገደማ ይሆናል።

ይህ አገልግሎት የተጀመረው በአውሮፕላን ትኬት መወደድ ምክንያት በአውቶብስ ትራንስፖርት ላይ የነበረውን ክፍተት ለመሙላት መሆኑን የድርጅቱ ዳይሬክተር ሚካኤል ጄምስ ተናግረዋል።

ኩባንያው በአሁኑ ጊዜ ስምንት አውቶብሶች ያሉት ሲሆን፣ በቀን አንድ ጊዜ ከናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ጉዞ ያደርጋል።
አውቶብሱ 46 ተሳፋሪዎችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ ለተሳፋሪዎች ምቾት ሰፋፊ ወንበሮች፣ የኢንተርኔትና የመዝናኛ አገልግሎቶች እንዲሁም የተለያዩ መጸዳጃ ቤቶች ተዘጋጅተዋል።

የጉዞው መስመር ከናይሮቢ ተነስቶ ሞያሌንና የተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞችን አቋርጦ አዲስ አበባ ይደርሳል። የደህንነት ስጋት እንዳለበት ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ሚካኤል የፀጥታ ስጋት አጋጥሞኝ አያውቅም ብለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በመንገዱ ላይ የመንገዱን ደኅንነት በተመለከተ መረጃ ወስደን ነው የምንጓዘው ብለዋል። በኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ በምሽት ጉዞ አናደርግም ያሉ ሲሆን

ድርጅቱ ለወደፊት የአውቶብሶችን ቁጥር ወደ 16 የማሳደግ እቅድ እንዳለውም ገልጿል።

05/08/2025

#ደብረዘይት

ደብረ ዘይት ከተማ በታሪኳ አይታ ሰምታ በማታውቀው አውሎ ነፋስ በቀላቀለ ዝናብ ተመታለች፡፡

በተለይ ከበለጠ ፋንታ እስከ አየር ኃይል ያሉ በርካታ ቤቶች እጅግ በጣም ተጎደተዋል፡፡

ወደ ጌት እሸት አካባቢም በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ዘንቦ ጉዳት አድርሷል፡፡በእዚህ ምክንያትም ብዙ ነዋሪዎች፣ ቤታቸው ፈርሶ ፣ ቆርቆሮ ተገንጥሎ ሌሊቱን ውጭ ማደራቸው ተሰምቷል።

የኤሌክትሪክ ፖሎችና መሰል መስመሮች መሬት ላይ ወዳድቀዋል።

Address


20036

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Akiya Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share