Akiya Media

Akiya Media Akiya Media አኪያ ሚዲያ welcome to our YouTube Channel Subscribe now and gat more benefits.

አዶናይ ከፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መፈታቱ ተሰማ!ለአዶናይ አድናቂዎች መልካም ዜናአዲስ አበባ – በማኅበራዊ ሚዲያ በስፋት የሚታወቀው ቲክቶከር አዶናይ በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ከቆየ...
15/12/2025

አዶናይ ከፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መፈታቱ ተሰማ!

ለአዶናይ አድናቂዎች መልካም ዜና

አዲስ አበባ – በማኅበራዊ ሚዲያ በስፋት የሚታወቀው ቲክቶከር አዶናይ በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ከቆየ በኋላ አሁን ከእስር መፈታቱን የቅርብ ምንጮች አመለከቱ።

መረጃው ይፋ የተደረገው በአዶናይ የቅርብ ሰው አማካኝነት ሲሆን፣ ድምፃዊ መርከብ ቦኒቷ ፋስት መረጃ ጉዳዩን አረጋግጠዋል ተብሏል።

ይህ ዜና ለቲክቶከሩ አድናቂዎች እና የማኅበራዊ ሚዲያ ተከታታዮች ደስታን የፈጠረ ትልቅ ዜና ሆኗል::

15/12/2025

አንተ ተማር እንጂ ሰዎች እና ጊዜ ከትምህርት ቤት በላይ ብዙ ያስተምሩሀል ።

13/12/2025

ዛሬ ንግድ ባንክ የአብዛኛውን ሰው አካውንት አግዷል ከቴሌ ብር ብድር በተያያዘ ?
እናንተስ ደርሶባችዋል ወይ ?

13/12/2025

ብዙ ሰዎች ሌሎችን ለመማር እና ለማሰደሰት ሲሉ የማይፈልጓቸውን ነገሮች በመግዛት ወጥመድ ውስጥ ይወድቃሉ ነገር ግን .. እኛ የተጨነቅንላቸው ሰዎች ግን ጨራሽ ግድ ለእኛ ግድ የላቸውም ።

ለምን ትክክለኛውን ምክንያት አትነግሩንም? አዶናይና ጃኒ ምንም ልክ ያልሆነ ልብስ አልለበሱም። ወይስ ጋቢ አልደረባችሁም ነው? 🤨Akiya Media
13/12/2025

ለምን ትክክለኛውን ምክንያት አትነግሩንም? አዶናይና ጃኒ ምንም ልክ ያልሆነ ልብስ አልለበሱም። ወይስ ጋቢ አልደረባችሁም ነው? 🤨

Akiya Media

12/12/2025

ሰበር ዜና
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ !

12/12/2025

ነዳጅ እና ቲክቶክ
ለካ አቋራጭ የሚባል ነገር አለ !!
ያው ስልክም ዳይቨርት ይደረግ አይደል 👏👏👏

11/12/2025

የዚህን እንጠብቃለን እንግዲህ ወይስ ?

11/12/2025

አዶናይ ውይስ ሳፊኒያስ
የሀገር የህዝብ እሴት የነኩት ?

በረከት ገበሬዋ' ለእስር የተዳረገችበት ምክንያት ምንድነው? ዝርዝሩን ይዘናል ።***********************************************ከቅርብ ግዜ ወዲህ ስማቸው በመደበኛው...
11/12/2025

በረከት ገበሬዋ' ለእስር የተዳረገችበት ምክንያት ምንድነው? ዝርዝሩን ይዘናል ።
***********************************************
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ስማቸው በመደበኛው ሚድያ እና በማህበራዊ ሚድያ ገዝፎ ከወጡ ባለሀብቶች መሀል በቅፅል ስሟ 'በረከት ገበሬዋ'፣ ሙሉ ስሟ ደግሞ በረከት ወርቁ አደራ በመባል የምትታወቀው ግለሰብ ትገኝበታለች።

ግለሰቧ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን አስመልክቶ ከጥቂት ወራት በፊት "እኔን ሁሌ የሚያስጨንቀኝ የሚያሳስበኝ ነገር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ደከመኝ በቃኝ ትንሽ ልረፍ እስቲ እንደ አባት ወደ ልጆቼ ወደ ቤተሰቤ ልመለስ ቢል ምን ይውጠናል? ማነው እሱን የሚተካው? ማነው ይሄን ሁሉ ውጥንቅጡ የወጣ ፖለቲካ የሚያቻችለው?ማነው? እግዚአብሔር ለኢትዮጵያ ሲል ከኔ እድሜ ቀንሶ ይስጥህ'' በሚል ንግግሯ የብዙዎች መነጋገርያ ሆና ነበር።

በረከት በእርሻ ስራ ላይ የተሰማራች፣ የብርታት ተምሳሌት የሆነች፣ የኢትዮጵያ ሴት ባለሀብቶች ተምሳሌት እና የሥራ ዕድል ፈጣሪ ተደርጋ በብዙዎች ዘንድ ትወሰድ ስለነበር የመታሰሯ ዜና ከሶስት ሳምንት በፊት ይፋ ሲሆን ብዙዎችን አስገርሞ ነበር።

እስሩ ይፋ በሆነበት ቅፅበት አንዳንዶች ''በረከት ገበሬዋ እስር ቤት የገቡት በሹፌሯ ምክንያት በተፈጠረ ቀላል ችግር ነው፣ በቅርቡ ትፈታለች'' የሚል ማረጋጊያ የሚመስል መረጃ ማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት ሲለቁ ተስተውለው ነበር።

መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ ያደረገው ክትትል እንደሚያሳየው ግን ጉዳዩ ከሹፌርም ሆነ ከሌላ አካል ጋር የተገናኘ ሳይሆን ግለሰቧ በከባድ፣ አመታትን በፈጀ እና ረጅም ሰንሰለት ባለው የማጭበርበር ድርጊት ላይ ተሳትፋለች በሚል ተጠርጥራ መሆኑን አረጋግጧል።

ጉዳዩ ምን ይሆን?

ዋናው ጉዳይ የግብርና ምርቶችን የሚያመርተው እና የሚያከፋፍለው ድርጅቷ ውስጥ ለበርካታ ሺህ ሰው በረከት ገበሬዋ የሸጠችው ሼር እንደሆነ ሚድያችን ከመንግስት እና ጉዳዩን ከሚያውቁ ሌሎች የመረጃ ምንጮቹ አረጋግጧል።

"በመጀመርያ 45 ሰዎች ገደማ ከፍተኛ መጠን ያለው ብር ይዛ ተሰወረችብን በሚል የተጀመረ ምርመራ ነበር። በኋላ ሲጣራ ለማየት እንደተቻለው በሼር ሽያጭ ዙርያ የወጡ ደንቦችን በመተላለፍ ጭምር ሁለት የሸርክና ውሎችን በማዘጋጀት ሲትሸጥ ተገኝታለች' የሚሉት የመንግስት ምንጫችን ናቸው።

በዚህም መሰረት በመጀመርያው ምድብ 1 ሚልዮን ብር፣ በሁለተኛው ምድብ 500 ሺህ ብር ሽ በስፋት ሲሸጥ መቆየቱ ታውቋል።

45 ሰዎች የመጀመርያዎቹ ሆኑ እንጂ ምናልባትም በመቶዎች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች የድርጊቱ ሰለባ ሳይሆኑ እንዳልቀረ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

ይህም ከበርካታ መቶ ሚሊዮኖች እስከ ቢሊዮኖች በዚህ መልኩ በግለሰቧ ሳይሰበሰብ እንዳልቀረ ተገምቷል።

ስራው እንደ 'pyramid scheme' ቀድመው ሼር የገዙ ሰዎች ሌሎች ሰዎችን እንዲያመስ የማድረግ አካሄድ እንደነበረው አንድ ጉዳዩን በቅርበት የተከታተሉ የመረጃ ምንጭ ያስረዳሉ፡

"ከአንድ ቤተሰብ በሁለት፣ ሶስት እና አራት ሰው ስም ሼር የገዙ አሉ። ግለሰቧ ደግሞ ለዚህ አንዱ እና ዋናው ማሳመኛዋ ከመንግስት ጋር በቅርበት እንደምትሰራ መናገሯ እና ከባልስልጣናት ጋር አብራ የተነሳቻቸውን ፎቶዎች በስፋት መልቀቋ ነው'' ይላሉ።

መሠረት ሚድያ ገንዘባቸው ከከፈሉ ሰዎች እንደተረዳው በረከት ገበሬዋ በተለይ ከጠ/ሚርአብይ አህመድ፣ ከደህንነት ቢሮው ሀላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን እና ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነርጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ጋር የቅርብ ትውውቅ እንዳላት በስፋት ስትናገር እና ህዝብን ለማሳመን ስትጠቀምበት ነበር።

''ከእርሻዎቿ የምታመርታቸውን የግብርና ውጤቶች በቅናሽ ለህዝብ እንድናከፋፍል በሚል በሼር ስም ብዙ ሰው እንደ እኛ ገንዘቡን ሰጥቷል። ይህ ከሆነ ሁለት አመት ጭምር የሞላቸው አሉ፣ አመት ያለፋቸው ሞልተዋል፣ ምንም እንቅስቃሴ ግን የለም'' የሚሉት አንድ የድርጊቱ ሰለባ ከቅርብ ወራት ወዲህ ግለሰቧ ጭራሽ ተሰውራ እንደቆየች እና በማህበራዊ ሚድያ ብቻ ትታይእንደነበር ያስረዳሉ፡፡

ሌላ ብራቸውን እንደተበሉ የሚጠቅሱ ግለሰብ ደግሞ በረከት ገበሬዋ የኢትዮጵያ የስልክቁጥሯን ጭራሽ በማጥፋት የአየርላንድ ሀገር ስልክ በሆነ ቁጥር ዋትሳፕ ላይ ብቻ አልፎ አልፎ ትገኝ እንደነበር ያስረዳሉ።

በዚህ ድርጊት ተማልለው ገንዘባቸው በብዛት የሰጡት ሴቶች እንደሆኑ የሚናገሩት ሌላኛዋ ምንጫችን ግለሰቧ የከፍተኛ ባለስልጣናትን ስም ደጋግማ በመጥራት ሼር ገዢዎች ጥያቄ እንዳያነሱ ታደርግ እንደነበር ያስረዳሉ።

''ከባለስልጣናት ጋር ግንኙነት እና ቅርበት አለኝ የሚለውን የተጠቀመችው ለሼር ሽያጩ ብቻ ሳይሆን ከማንኛውም ሰው ጋር አለመግባባት ውስጥ ስትገባ ጭምር ነበር፣ ባለስልጣናት የሷ ማስፈራርያ ነበሩ" የሚሉት የመንግስት የመረጃ ምንጩ በዚህ ሁኔታ በርካታ ሌሎች ያልተደረሰባቸው ጉዳዮችም አሁን ወደፊት እየመጡ መሆኑን ለሚድያችን ነግረዋል፡፡

ለምሳሌ በኦሮሚያ እና በአፋር ክልል በኢንቨስትመንት ስም የወሰደቻቸው ትላልቅ ስፋት ያላቸው መሬቶች ጭምር በሽያጭ እና በማይታወቁ ውሎች ስም ስማቸው ከበረከት ገበሬዋ ወደ ሌሎች ሲተላለፍ እንደነበር መረጃዎች ለሚድያችን ደርሰዋል፡፡

በረከት ገበሬዋ የዛሬ ሁለት አመት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ''የመደመርትውልድ"መጽሀፍን በ50 ሺህ ዩሮ ገዝታ ነበር።

እንደዚህ አይነት ድርጊቶች በተለይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመሸፈን ሲውሉ ይስተዋላል የሚሉት ምንጮች በቅርቡ የኬና ሆቴል ባለቤትም በተመሳሳይ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውሰዋል።

https://t.me/AkiyaMediaB
Akiya Media

11/12/2025

በአደባባይ ስሟን የጠራት ድንግል ማርያም ዋስ ጠበቃ ትሁነው 🙏

11/12/2025

ፓሊስ አዶናይን ማሰሩ ትክክለኛና ተገቢ ውሳኔ ነው ብለው ያስባሉ ?
ስንት ለሀገር ጠንቅ የሆኑ ሰዎች ባሉበት ሆኔታ ለወጣቱ መለወጥን ያሳየ ወጣት ለምን ?

Address


20036

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Akiya Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share