Abay Dar

Abay Dar ኑ ስለሁሉም ነገር እናውራ!!! ማንኛዉንም ነገር !!!

16/09/2020
23/03/2020
21/02/2020

Thanks to the Prime Minister ... Prime Minister Abby Ahmed is in talks with 1,000 community representatives from the woredas in the zone. Earlier in the disc...

04/02/2019
15/11/2018
አረሱትን ተጋበዙልኝ ወዳጆቸ
12/11/2018

አረሱትን ተጋበዙልኝ ወዳጆቸ

28/07/2018
26/07/2018
26/07/2018

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ አካባቢ መኪናቸው ውስጥ ሞተው ተገኙ፡፡

ስለአሟሟታቸው ሁኔታ ፖሊስ ምርመራ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ኢንጂነር ስመኘው በቀለ በኢትዮጵያ የሃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ስራዎች ላይ አሻራቸውን ያሳረፉ ሲሆን ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስም የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው ሲያገለግሉ ነበር፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስትያን የክፍፍል እና የውህደት ጉዞየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን የተገቢነት ሙግት በሚያነሱ ሁለት ሲኖዶሶች ተከፍላ ስትወዘወዝ ከሁለት አ...
25/07/2018

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስትያን የክፍፍል እና የውህደት ጉዞ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን የተገቢነት ሙግት በሚያነሱ ሁለት ሲኖዶሶች ተከፍላ ስትወዘወዝ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ጊዜ ተቆጥሯል።
በመጀመሪያ በቀድሞው ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ፣ ከእርሳቸው ኅልፈተ ህይወት በኋላ ደግሞ በብፁዕ አቡነ ማቲያስ በሚመራው እና መቀመጫውን አገር ውስጥ ባደረገው ሲኖዶስ እንዲሁም ብፁዕ አቡነ መርቆሪዮስም ፓትርያርኩ አድርጎ በሚቆጥረውና ሰርክ 'ስደተኛው' እየተባለ በሚጠራው ሲኖዶስ መካከል ሰላም አውርዶ እርቅ ለመፍጠር ተደጋጋሚ ሙከራዎች መደረጋቸው ባይቀርም እስካሁን ድረስ ስኬት ሲናፍቃቸው ቆይቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አንዲት ቤተ ክርስትያንን እና አማኞቿን እንወክላለን የሚሉትን ሁለቱን የእምነት አስተዳዳር መዋቅሮች ዓይን ለዓይን ከመተያየት ሲከለክል የቆየው ቁርሾ ተወግዶ ወደአንድነት እንዲመጡ ፍላጎታቸውን ከገለፁ በኋላ የተጀመረው እንቅስቃሴ ግን ፍሬ የያዘለት ይመስላል።

ከትናንት አመሻሹ አንስቶ ሲኖዶሶች እርቀ ሰላም ይዘገብ ይዟል። ውህደቱ ምን ፋይዳ እና ትርጉም አለው? ቀጣይ እርምጃዎችስ ምን ይሆናሉ ስንል የእምነቱን ሊቃውንት አነጋገረናል።
የቤተ ክርስትያኗ አመራር እንዴት ለሁለት ተከፈለ?
በ1983 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) የደርግን ስርዓት ጥሎ ስልጣን ላይ ሲወጣ፣በአራተኛው ፓትርያርክ አቡነ መርቆርዮስ ደስተኛ እንዳልነበር በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ማኅበረ ካህናት ሥራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ ይናገራሉ።

"በቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ ልዩነት መፈጠር የተጀመረው ብፁዕ አቡነ መርቆሪዮስ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ተደርጎ ብፅዕ አቡነ ጳውሎስ በስፍራቸው እንዲተኩ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ ነው፤" ይላሉ ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ።

ቀሲስ ኤፍሬም እንደሚሉት አዲሱ መንግሥት የፖለቲካ ጉልበቱን በመጠቀም ፓትርያርኩ ከመንበራቸው እንዲነሱ በጉምቱ ባለስልጣናቱ ሳይቀር ጥረት አድርጓል።

በዚህ አስተያየታቸው የሚስማሙት የቀድሞው የማኅበረ ቅዱሳን አመራር ዲያቆን ዳንዔል ክብረት ናቸው።

እርሳቸው እንደሚሉት በወቅቱ ብፁዕ አቡነ መርቆሪዮስ መንግስታዊውን ጫና መቋቋም ካለመቻላቸውም ባሻገር፤ አንዳንድ የኃይማኖት አባቶች የእርሳቸው መንበራቸውን መልቀቅ ብቸኛው መፍትሄ ነው ማመናቸው አልቀረም።

የፓትርያሪኩን ከአገር መውጣት ተከትሎም ሌላ ምርጫ ተካሄደና ሌላ ፓትርያሪክ ተሾመ፤ አንዳንድ ጳጳሳት ስደተኛውን ፓትርያሪክ መከተልን መረጡ፤ ከጥቂት ዓመታት በኋላም በአገረ አሜሪካ ሌላ ሲኖዶስ መሰረቱ፤ ሌሎቹ ደግሞ አገር ውስጥ በነበረው ሲኖዶስ ለመቀጠል ወሰኑ።

"ከዚህም የተነሳ ቤተ ክርስትያኒቷ በሁለት ሲኖዶስ፣ በሁለት ፓትርያሪክ የምትመራ ሆነች" ይላሉ ዲያቆን ዳንዔል።

ለእርሳቸው ይህ ሂደት ሁለት የቤተ ክርስትያኒቷን አስተምህሮዎች የጣሰ ነው እንደሆነ ዲያቆን ዳንኤል ይናገራሉ። እንደ እርሳቸው አባባልም በመጀመሪያ "አንድ አባት ልጆቹን ትቶ መሄድ ተገቢ አይደለም፤" በመቀጠል "እኝህ አባት ከአገር ቢወጡም እርሳቸውን እና ሌሎቹን ከስደት ለመመለስ ጥረት መድረግ ሲገባው ሌላ አባት ተሾመ። ከበፊትም የሚመዘዝ ችግር ቢኖርም ይህንን ችግር በትዕግስት እና በብልሃት ማለፍ ቢቻል ኖሮ ይ. ነገር አይፈጠርም ነበር። የቤተክርስያኒቱ ስርዓት አንድ አባት በህይወት እያለ ሌላ አባት መሾም አይፈቅድምና።"
ክፍፍሉ ምን ዳፋ አስከተለ?
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን አሁንም ትልቋ የአገሪቱ የእምነት ተቋም ትሁን እንጅ የአማኞቿ ቁጥር ከአጠቃላዩ ምዕመን ያለው የመቶኛ ድርሻ እያሽቆለቆለ ነው የሚገኘው።

ለመጨረሻ ጊዜ በ1999 ዓ.ም በተደረገው የህዝብና ቤት ቆጠራ መሰረት ከአገሪቱ አጠቃላይ ህዝብ ከአርባ ሦስት በመቶ ከፍ የሚለው የእምነቱ ተከታይ ሲሆን፤ ቤተ ክርስትያኗ በ1977 ዓ.ም ቆጠራ ወቅት ከነበራት አገር አቀፍ የምዕመናን ድርሻ ግን ሃምሳ አራት በመቶ ገደማ ነበር።

ዲያቆን ዳንዔል ለዚህ አብዩ ተጠያቂ "የቤተ ክህነቱ መዳከም ነው" ይላሉ።

"ቤተ ክህነቱ ቤተ ክርስትያንዋን መሸከም ከሚችልበት አቅም በታች ነው። አሁን ላለው ቤተ ክህነት፣ አሁን ላለችው ኢትዮጵያ እና አሁን ላለው ትውልድ የሚመጥን አይደለም። ሁለቱም ቦታ፤ አሜሪካም ያለው እዚህም ያለው። ለዚህ የሚመጥን አቅም የለውም" ሲል ያብራራል።

ለቤተ ክህነቱ መዳከም ደግሞ የሲኖዶስ፣ የኃይማኖት መሪዎችን እና የአማኞችን መከፋፈል ተወቃሽ ያደርጋሉ።

ቤት ክህነቶች ዋና ተግባራቸውን "ውጊያ" ላይ በማድረጋቸው ምክንያት ተቀዳሚ ሥራቸው ሊሆን ይገባው የነበረው "ወንጌልን የማዳረስ ስራ፣ የሐዋርያዊነትን ስራና ምዕመናንን የመጠበቅን ስራ ተረስቷል" ይላሉ።

ቀሲስ ኤፍሬም በበኩላቸው የሁለት የተኮራርፉ አስተዳደሮች መኖር፣አንድ እምነት እና አንድ ስርዓት ያላቸው ምዕመናን እና ካህናት ለመራራቃቸው ምክንያት ከመሆኑም ባሻገር ይህም በፋንታው በርካታ ችግሮችን ወልዷል ይላሉ።

"ቤተ ክርስትያኗ በአጠቃላይ አሁን ላለባት ድክመት፣ ለምዕመናኗ ቁጥር መቀነስ፣ ለአስተዳደሯ መበላሸት፣ ሙስና እና ዝርፊያ [በጓዳዋ] ለመሰልጠናቸው፣ ሙያው እና ስነ ምግባሩ የሌላቸው ሰዎች በልዩ ልዩ መዋቅሮች ለመሰግሰጋቸው ሁሉ በር የከፈተው ይህ በአባቶች መካከል ያለው ልዩነት ነው" ሲሉ ይናገራሉ።

አሁንስ ከቤተ እምነት ላይ የቤተ መንግሥት ጥላ ተገፏል?

ሲኖዶሶቹ አንዳቸው ሌላኛቸውን የእምነቱን ህግ እንደጣሱ ወይንም ኃይማኖታዊ ቅቡልነት እንደሌላቸው ያዩዋቸው የነበረ ለመሆኑ አንደኛው መገለጫ እርስ በራሳቸው መወጋገዛቸው ነው።

አሁን ይካሄድ በያዘው ሽምግልና ላይ በጋራ ሲፀልዩ መስተዋላቸው ይሄንን ውግዘት በይፋዊ ባይሆን በተግባር ቀድመው ለማንሳታቸው ምስክር ነው የሚሉት ቀሲስ ኤፍሬም ናቸው።

እርስ በእርስ የሚተያዩባቸው መንገዶች ምናልባትም በተደጋጋሚ የተደረጉትን የእርቅ ሙከራዎች የማክሰም ድርሻ ቢኖራቸውም፤ የአገሪቱ ፖለቲካዊ መልክ ጉልህ ሚና እንደነበረው ግን ሁለቱም ይስማማሉ።

የአሁኑ እርቀ ሰላም ስኬትንም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አስተዳደር አቋም ጋር የሚያያይዙት ብዙ ናቸው።

ቀሲስ ኤፍሬም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን በሌሎች የዓለም ክፍሎች ካሉ የክርስትና እምነቶች በተለየ መንግስታዊ ትስስር ከምስረታዋ አንስቶ እንዳላት ያስረዳሉ።

"በሌሎች አገራት በአብዛኛው እምነቱ በህዝቡ ዘንድ ከሰረፀ በኋላ መንግስታት እንደተቀበሉት ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ግን የሆነው በተቃራኒው መንግስት እምነቱን ተቀብሎ ነው ከዚያ ወደሕዝቡ ያሰረፀው። ስለዚህም ከዚያ የሚመዘዝ መንግስታዊ ቁርኝት አለ" ይላሉ።

በየዘመኑ የመጡ መንግስታት ቤተ ክርስትያኒቷን ዓላማቸውን ለማስፈፀሚያ ተጠቅመውባታል የሚሉት ቀሲስ እሸቴ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አስተዳደር መንግስት እና እምነትን ላንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የሚለያይ እርምጃ እንደሚወስድ ተስፋቸውን ይገልፃሉ።
ከዚህ በኋላስ?
ዲያቆን ዳንዔል የፖለቲካዊ ፍላጎት መጥፋት እንጅ ሲኖዶሶቹን በእርቅ ማጨባበጥ እስካሁንም የሚከብድ ነገር ሆኖ እንዳልነበር ያምናሉ።

ከዚህ ቀደም የተደረጉ የእርቅ ጥረቶች "ላለመሳካታቸው አንዱ እንቅፋት የአገሪቱ ፖለቲካ ነው" ይላሉ አክለው "ምክንያቱም ሁለቱም በየራሳቸው የሚደግፏቸው የፖለቲካ አዝማሚያዎች አሏቸው። የአገር ቤቱ ሲኖዶስ የአገር ቤቱን ፖለቲካ፣ የውጭው ሲኖዶስ ደግሞ የውጭውን ፖለቲካ ስለሚደግፉ እና በፖለቲካው ጫና ውስጥ በመውደቃቸው ነው።"

በውጭ አገር ያለው ሲኖዶስ በአማኞች ቁጥር ከተመዘነ ያለው አቅም በጣም ትንሽ ይሁን እንጅ በሚያንቀሳቅሰው የገንዘብ መጠን እና ባለው ተፅዕኖ ትከሻው የደረጀ ነው እንደ ዲያቆን ዳንዔል አስተያየት።

ከሁለቱ ፓትርያሪኮች መካከል የስልጣን መንበሩ ላይ መቀመጥ ያለበት የሚለው ጥያቄ ሌላኛው ማነቆ ሆኖ የቆየ ቢሆንም እርሱን አሁን መፍታት ብዙም አይገድም ይላሉ።

ብፁዕ አቡነ ማቲያስ የአስተዳደሩን ስራ እየሰሩ፤ አቡነ መርቆሪዮስን ደግሞ በመንበራቸው ሆነው ከአስተዳደሩ ስራ ግን ገለል እንዲሉ ስማቸውም በቅዳሴ እየተጠራ በሲኖዶሱም እየተገኙ እንዲቀጥሉ ማድረግ አማራጭ ሆኖ እንደሚታያቸው ይናገራሉ።

"አቡነ መርቆሪዮስን የአስተዳደር ስራ ላይ እንዲሳተፉ ቢደረግ ከጤናም ከዕድሜም፣ከአገሪቱ ከሃያ ዓመት በላይ ርቀው ከመቆየታቸውም አንፃር ሊቸገሩ ይችላሉ።" ይላሉ።

ቀሲስ ኤፍሬም በበኩላቸው በውጭ አገር ያሉት ፓትርያርክ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም አባቶችና ካህናት ወደአገር ቤት ተመለሰው በየአገር ስብከቱ እንዲመደቡና የአገልግሎት መዋሃድ እንዲፈጠር ይጠብቃሉ።

ከዚህም ባለፈ ተመሳሳይ ክፍፍል እንዳይፈጠር "ህጎች ይወጣሉ፣መመሪያዎች ይወጣሉ፤ በተለይ ከመንግሥት ጋር ያለው ግንኙነት ምን ዓይነት መሆን እንዳለበት ቤተ ክርስትያን ህግ ታወጣለች ብለን ተስፋ እናደርጋለን።" ብለዋል።

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን የተገቢነት ሙግት በሚያነሱ ሁለት ሲኖዶሶች ተከፍላ ስትወዘወዝ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ጊዜ ተቆጥሯል። በመጀመሪያ በቀድሞው ፓትር....

በወልዲያ እና ፍኖተ ሰላም ማረሚያ ቤቶች በተነሳ እሳት በንብረትና ሰው ላይ ጉዳት ደረሰበምዕራብ ጎጃም ፍኖተ-ሰላም እና በሰሜን ወሎ ወልዲያ ከተሞች ውስጥ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የተቀሰ...
25/07/2018

በወልዲያ እና ፍኖተ ሰላም ማረሚያ ቤቶች በተነሳ እሳት በንብረትና ሰው ላይ ጉዳት ደረሰ
በምዕራብ ጎጃም ፍኖተ-ሰላም እና በሰሜን ወሎ ወልዲያ ከተሞች ውስጥ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የተቀሰቀሰን ግርግር ተከትሎ ባጋጠመ የእሳት ቃጠሎ በንብረት ላይ ውድመት መድረሱን የማረሚያ ቤቶቹ ኅላፊዎች ለቢቢሲ ተናገሩ።
በፍኖተ-ሰላም ከተማ ውስጥ የሚገኘው ማረሚያ ቤት ዛሬ ጠዋት 2 ሰዓት ላይ በወንዶች ማረሚያ ቤት ቆጠራ ሊካሄድ ሲል በታራሚዎች መካከል አምቧጓሮ መነሳቱን የሚናገሩት የማረሚያ ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ረዳት ሳጅን ግርማ ሙሉጌታ ምክንያታቸው የአቃቢ ህጉ በቴሌቪዥን ቀርበው የሰጡት መግለጫ እንደሆነ ይናገራሉ።

ታራሚው ለምን አንፈታም በሚል ተቃውሞ ማሰማቱን የሚናገሩት ረዳት ሳጅን ግርማ አንቆጠርም በማለት ማስቸገራቸውን ገልፀዋል። የፖሊስ አባላት የታራሚውን ማመፅ ሲያዩ ወጥተው ጥበቃ ማጠናከራቸውን ወዲያውም በማረሚያ ቤቱ የሚገኘው የሸማ ማምረቻ ክፍል በእሳት እንደተያያዘ ያስረዳሉ።

ጨምረውም 26 የታራሚዎች ማደሪያ ክፍሎች ሙሉ በሙሉ በእሳት መውደማቸውን፤ በእሳቱ የታራሚዎች አያያዝና የሬጅስትራር ቢሮም መቃጠሉንም ተናግረዋል።

በቢሮው ውስጥ የነበሩት ኮምፒውተሮችን ማውጣት በመቻላቻው ከውድመት እንደተረፉ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ ዜና በወልዲያ ማረሚያ ቤት ዛሬ ጠዋት 2 ሰዓት ላይ እሳት መነሳቱንና ሙሉ በሙሉ የወንዶች ማደሪያ እንዲሁም የስልጠና ማዕከሉ መሳሪያዎችና ማዕከሉ መውደሙን የማረሚያ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ኮማንደር እንዳለ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ተቃውሞው የጀመረው ሰሞኑን ስኳር ባለመኖሩ ሻይ ስላልነበራቸው ሻይ ይግባልን በማለት እንደሆነ ያስረዱት ኮማንደሩ አስከትለውም ታራሚዎቹ ድንጋይ ውርወራ መጀመራቸውን ገልፀዋል።

እስካሁን ድረስ ሁለት ታራሚዎች መቁሰላቸውንም ጨምረው ነግረውናል።

በትናንትናው ዕለት በደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት ቃጠሎ መድረሱም የሚታወስ ሲሆን አዲስ አበባ ቃሊቲና አርባ ምንጭ ውስጥ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ ታራሚዎች ተመሳሳይ የእንፈታ ጥያቄ በማቅረብ አለመረጋጋት እንደነበር ተገልጿል።

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

በምዕራብ ጎጃም ፍኖተ-ሰላም እና በሰሜን ወሎ ወልዲያ ከተሞች ውስጥ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የተቀሰቀሰን ግርግር ተከትሎ ባጋጠመ የእሳት ቃጠሎ በንብረት ላይ ውድመት መድረሱን የማረ...

የሶማሌ ክልል ፖለቲካዊ ቀዉስበምሥራቃዊ የኢትዮጵያ በሶማሌ ክልል በኅብረተሰቡ እና በአስተዳደሩ መካከል አለመግባባቱ መባባሱን የአካባቢው ተወላጆች ይናገራሉ። ትናንት በክልሉ ዋና ከተማ ጅግጅጋ...
25/07/2018

የሶማሌ ክልል ፖለቲካዊ ቀዉስ
በምሥራቃዊ የኢትዮጵያ በሶማሌ ክልል በኅብረተሰቡ እና በአስተዳደሩ መካከል አለመግባባቱ መባባሱን የአካባቢው ተወላጆች ይናገራሉ። ትናንት በክልሉ ዋና ከተማ ጅግጅጋ ተደረገ የሚሉት የተቃውሞ ሠልፍም የዚሁ ነፀብራቅ ነው። በወቅቱም የክልሉ ልዩ ፖሊስ ሠልፈኞችን ለመበተን በወሰደው ርምጃ የተጎዱ ጥቂት አይደሉም።

የክልሉ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ በበኩላቸው ትናንት ተፈጠረ የተባለውን ግጭትም ሆነ የተቃውሞ ሠልፍ ከማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያነት የዘለለ እውነት አይደለም ይላሉ።

የሶማሌ ክልል ተወላጆች እንደሚሉት ሰሚ አላገኙም እንጂ በክልሉ አስተዳደር ያደረባቸውን ቅሬታ ለፌደራል መንግሥት ሳይቀር ለማሰማት ዋና ከተማ አዲስ አበባ ድረስ ሄደዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለማግኘት ለወራት ያደረጉት ደጅ ጥናት አለመሳካቱ ደግሞ ችላ ተብለን የሚል ስሜትን ፈጥሮባቸዋል። በመቶዎች ከሚቆጠሩ የአካባቢው ሽማግሌዎች፤ ምሁራን እና ወጣቶች ጋር አዲስ አበባ እንደነበሩ የገለፁልን አንዱ ትናንት ጅግጅጋ ላይ ነበረ የሚሉት ተቃውሞም የዚያው ነፀብራቅ ነው ይላሉ።

«ጂግጂጋ ትናንት ከትናንት ወዲያ ሕዝቡ ተቃውሞ አደረገና መቶ ምናምን ወጣቶች የታሠሩትን ሕዝቡ ኡኡ ብሎ አስወጣቸው። ዛሬ ደግሞ ችግር አለ፤ ይሄ ችግር ሌላ አይደለም ሰውየውን ለመጣል ነው። ሕዝቡ ትልቅ ተቃውሞ ለማሳየት እየሞከረ ነው።»

እኝህኛው የሶማሌ ክልል ነዋሪ ደግሞ ጅግጅጋ ቆይተው ወደ አዲስ አበባ መሄዳቸውን ገልፀው ትናንት ተደረገ የሚሉትን እንዲህ ያስረዳሉ።

«ትናንት ሰው ሰልፍ ወጥቶ በልዩ ፖሊስ በትኖ ነበር፤ የታሰሩ ልጆችም አሉ፤ ስማቸውን ራሱ መጥቀስ ይቻላል። አብረን የተማርን ናቸው ሦስቱም የክልሉ ምሁራን ናቸው። የእስረኞቹን መፍታት ጥያቄ ይዞ ነው ሕዝቡ ሰልፍ የወጣው።»

ትናንት ተካሄደ ባሉት ሰልፍ እና ግጭት የታሠሩም የተደበደቡም ሰዎች መኖራቸውንም ጠቅሰዋል። ጉዳዩን ለማጣራት የደወልንላቸው የክልሉ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ኢድሪስ ሰኢድ የተባለው ሁሉ «ሃሰት ነው» ባይ ናቸው።

«ኮምፕሊትሊ ውሸት ነው፤ ውሸት ነው ምንም የተከሰተ ነገር የለም። የታሰረም እኮ የለም።» «ፕሬዝደንቱን የሚቃወም ምንም አይነት እንቅስቃሴ በጅጅጋ የለም?» «እየነገርኩሽ ያለሁት እውነቱን ነው። ምንም አይነት ነገር የለም።»

አቶ ኢንድሪስ አያይዘውም በሶማሌ ክልል ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ ሁሉ የፊታችን ሐምሌ 29 ቀን በክልሉ በሚካሄድ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ሃሳባቸውን ማጋራት እንደሚችሉም ገልጸዋል።

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

በምሥራቃዊ የኢትዮጵያ በሶማሌ ክልል በኅብረተሰቡ እና በአስተዳደሩ መካከል አለመግባባቱ መባባሱን የአካባቢው ተወላጆች ይናገራሉ። ትናንት በክልሉ ዋና ከተማ ጅግጅጋ ተደረገ የሚሉት ....

24/07/2018

አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ የደቡብ ክልል ርእሰ መስተዳደር ሆነው ተሾሙ
የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት በ5ኛ ዙር 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔው አቶ ሚሊዮን ማቲዮስን የክልሉ ርእሰ መስተደሳድር አደርጎ ሾማል።

አቶ ሚሊዮን ቃለ መሃላ በመፈፀም ቀደም ሲል ክልሉን በርዕሰ መስተዳደርነት ሲያገለግሉ ከነበሩት አቶ ደሴ ዳልኬ ሃላፊነቱን ተረክበዋል።

አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ በቅርቡ ክልሉን የሚያስተዳድረው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ደኢህዴን/ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመራጠቸው ይታወሳል።

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

በባሌ ጎባ ከተማ በተከሰተው ግጭት ዙሪያ ዶ/ር ነገሪ የሰጡት ማብራሪያhttps://www.youtube.com/watch?v=JJHSfaHNvFgFor more news visit our website h...
24/07/2018

በባሌ ጎባ ከተማ በተከሰተው ግጭት ዙሪያ ዶ/ር ነገሪ የሰጡት ማብራሪያ
https://www.youtube.com/watch?v=JJHSfaHNvFg

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

በባሌ ጎባ ከተማ በተከሰተው ግጭት ዙሪያ ዶ/ር ነገሪ የሰጡት ማብራሪያ July 24, 2018 PoliticalSocial Previous Post የእነአቶ መለስ ዜናዊ የቂም በትር ያረፈባቸው ምሁራን

የእነአቶ መለስ ዜናዊ የቂም በትር ያረፈባቸው ምሁራንጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ በትላንትናው ዕለት ከ50 የግል እና የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 3ሺ 175 መምህራንና ምሁራን ጋር ው...
24/07/2018

የእነአቶ መለስ ዜናዊ የቂም በትር ያረፈባቸው ምሁራን
ጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ በትላንትናው ዕለት ከ50 የግል እና የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 3ሺ 175 መምህራንና ምሁራን ጋር ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ላይ በ1985 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተባረሩ 42 ምሁራን ወደ ስራቸው እንዲመለሱ መወሰኑን አብስረዋል፡፡

ይህንኑ ያበሰሩት፣ ‹‹ወደ ስራቸው የሚመለሱት ይቅርታ ጠይቀውን ሳይሆን ጠይቀናቸው ነው›› ማለታቸው እንደተለመደው ብዙዎችን አስገርሟል፡፡

ከምሁራኑ መካከል ስመ-ጥሩ ሐኪምና ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር ዶክተር ዓስራት ወልደየስ እንዲሁም በ1982 ዓ.ም ኮሌኔል መንግስቱን ኃይለማርያምን ስልጣን እንዲለቁ ፊት ለፊት በአደባባይ የጠየቁት ዶ/ር ሃይሉ አርአያ እንዲሁም የነባሩ የኢትዮጽያ መምህራን ማህበር ሊቀመንበር የነበሩት ዶ/ ር ታዬ ወልደሰማያት፣ በአሁኑ ሰዓት የዛሚ ራድዮ ባለቤት አቶ ዘሪሁን ተሾመ ይገኙበታል፡፡

ምሁራኑ የተባረሩት በወቅቱ የመንግሥት ታጣቂዎች በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ላይ የወሰዱትን የኃይል እርምጃ በመቃወም መንግሥት ግድያውን የሚያጣራ ገለልተኛ አካል እንዲያቋቁም በመጠየቃቸውና ዩኒቨርሲቲዎች ከፖለቲካ ነፃ እንዲሆኑ በመታገላቸው ነበር፡፡

የ42ቱ ምሁራን ስም ዝርዝር:-

ሀ). ከማኅበራዊ ሳይንስ (Social Science) ትምህርት ክፍል

1. ፕ/ር መኮንን ቢሻው
2. ፕ/ር ሰለሞን ተፈራ
3. ፕ/ር መሳይ ከበደ
4. ፕ/ር ስብሃት መርስዔኃዘን
5. ፕ/ር ታዬ ወልደሰማያት
6. ፕ/ር ፀሐዬ ብርሃኔ

7. ዶ/ር ፈቃደ ሸዋቀና
8. ፕ/ር ፍስሃ ዘውዴ
9. ምንዳርያለው ዘውዴ
10. አየለ ታረቀኝ
11. ዓይንዓለም አሸብር
12. ዘሪሁን ተሾመ
13. መስከረም አበበ

ለ). ከተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) ትምህርት ክፍል

1. ፕ/ር ዐየነው እጅጉ
2. ፕ/ር ዓለማየሁ ኃይሌ
3. ፕ/ር መኮንን ዲልጋሳ
4. ፕ/ር ታምሬ ሁዋንዳ
5. ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ

ሐ). ከቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል

1. ፕ/ር ዓለማየሁ ተፈራ
2. ፕ/ር አድማሱ ዋሴ
3. ሁሉአንተን አባተ

መ). ከሕክምና ትምህርት ክፍል

1. ፕ/ር ዶ/ር ዓስራት ወልደየስ
2. ፕ/ር ዳዊት ዘውዴ
3. ፕ/ር አስፋው ደስታ
4. ፕ/ር ታዬ መኩሪያ

ሠ). ከንግድና ምጣኔ ሀብት (Business and Economics) ትምህርት ክፍል

1. ፕ/ር አየለ ትርፌ
2. ፕ/ር በፍቃዱ ደግፌ
3. ዶ/ር አክሊሉ ታደሰ
4. ብርሃኑ ባንቃሼ
5. ለዓለም ብርሃኑ

ረ). ከቋንቋዎች ጥናት ትምህርት ክፍል

1. ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ
2. ፕ/ር ዓለማየሁ ኃይሌ
3. ፕ/ር ታዬ አሰፋ
4. ታደሰ በየነ
5. ተስፋዬ ሸዋዬ
6. ሰይፉ መታፈሪያ

ሰ). ከስነ-ትምህርት ክፍል

1. መኩሪያ አሰፋ
2. ፈለቀ ደስታ

ሸ). ከሕግ ትምህርት ክፍል

1. ፕ/ር ወርቁ በተፈራ
2. ፕ/ር ንጋቱ ተስፋዬ

ቀ). ከሌሎች ትምህርት ክፍሎች

1. ሰለሞን የወንድወሰን (በአፍሪካ ኢንፎርሜሽን ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህር) እና
2. ሽፈራው አጎናፍር (የሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ክፍል መምህር) ናቸው።

ከምሁራኑ መካከል ብዙዎች በውጭ አገራት ትልልሽ ዩኒቨርስቲዎች በማስተማርና በምርምር ሥራ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ፕሮፌሰር ዶክተር ዓስራት ወልደየስ፣ ፕ/ር መኮንን ቢሻውና ዶ/ር ፈቃደ ሸዋቀና ጨምሮ አንዳንዶቹ አርፈዋል። ( የመረጃውን ምንጭ እስክንድር መርሃጽድቅ ነው)

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

ጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ በትላንትናው ዕለት ከ50 የግል እና የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 3ሺ 175 መምህራንና ምሁራን ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ ላይ በ1985 ዓ.ም ከአዲስ አበ....

23/07/2018

በባሌ ዞን በጎባ ከተማ ባለፉት ቀናት በተፈጠረ ግጭት የስድስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የከተማዋ ከንቲባ ዘይነባ ጣሀ ተናግረዋል። በርከት ያሉ ሰዎች ደግሞ በአቅራቢያ በሚገኝ የጤና ተቋም...

በባሌ ዞን ጎባ ከተማ በተፈጠረው ግጭት የስድስት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ ተገለፀበባሌ ዞን በጎባ ከተማ ባለፉት ቀናት በተፈጠረ ግጭት የስድስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የከተማዋ ከንቲባ ዘይነባ ጣ...
23/07/2018

በባሌ ዞን ጎባ ከተማ በተፈጠረው ግጭት የስድስት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ ተገለፀ
በባሌ ዞን በጎባ ከተማ ባለፉት ቀናት በተፈጠረ ግጭት የስድስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የከተማዋ ከንቲባ ዘይነባ ጣሀ ተናግረዋል። በርከት ያሉ ሰዎች ደግሞ በአቅራቢያ በሚገኝ የጤና ተቋም የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነውም ብለዋል።
ግጭቱ የተጀመረው በባሌ የኦሮሞ ገበሬዎች ትግል ወቅት ግንባር ቀደም ታጋይ የነበሩት የሀጂ አደም ሳዶን ሐውልት በከተማዋ በሚገኝ አደባባይ መገንባትን በመቃወም ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ ሐውልት የመገንባት ጥያቄው በአካባቢው ነዋሪዎች እና ሽማግሌዎች የቀረበ ነው ሲሉ ያስረዳሉ።

ይህንን ጥያቄም መንግሥት ተቀብሎት ወደ እንቅስቃሴ መገባቱን ከንቲባዋ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ሐውልቱ ሊቆም በታሰበበት አደባባይ ላይ ቀድሞ የነበረ የቀይ ቀበሮ ሐውልት አይፈርስም፤ የታሰበው ሐውልትም ሌላ ቦታ ላይ ይተከል የሚሉ ነዋሪዎች ቅሬታ ያቀረቡ መሆኑን ያስታወሱት ከንቲባዋ ይህ ቅሬታም ዞን ድረስ መድረሱን ተናግረዋል።

በከተማዋ ነዋሪ የሆነና ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ግለሰብ ለቢቢሲ ሲያስረዳ በተፈጠረው ሁኔታ ላይ ከከንቲባዋ ሀሳብ ጋር ይስማማል። "የቀይ ቀበሮው ሐውልት ቀይ ቀበሮ እንኳን አይመስልም" ሲል የተቃውሞው ወደ አላስፈላጊ አቅጣጫ መሄዱን ያስረዳል። እንደ እርሱ እምነት በዚህ ግጭት ሌሎች ኃይሎች እጃቸው አለበት ይላል።

ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የባሌ ዞን አመራሮች በዚህ ጉዳይ ላይ ከህብረተሰቡ ጋር መወያየታቸውን የተናገሩት ከንቲባዋ በስብሰባው ላይ የተሳተፉት አካላት አብዛኛዎቹ የሐውልቱን መተከል ይቃወሙት እንደነበር ያስታውሳሉ።

የሚቃወሙበትም ምክንያትም ከሐይማኖት ጋር እንደማይገናኝ አስረድተው ሀውልቱ መቆም እንደሌለበት በደፈናው ተቃውመዋል ብለዋል ከንቲባዋ።

ከንቲባ ዘይነባ ጣሀ ሐሙስ ዕለት በከተማዋ የግጭት ምልክቶች መታየታቸውን ሰዎች በየፊናቸው በመሆን ይዝቱ አንደነበር ያስታውሳሉ።

አርብ ዕለት በርከት ያሉ ከገጠር ቀበሌዎች ዱላ ይዘው የመጡ ነዋሪዎች ወደ ከተማዋ እንደገቡ፤ እንዲሁም አስተዳደሩ የመጣችሁት ለሰላም ከሆነ ዱላችሁን ጣሉ በማለት በርካቶች ዱላቸውን መጣላቸውን የተወሰኑም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።

"እነዚህ ወደ ከተማዋ የገቡ ሰዎች ቅዳሜ ዕለት መንግሥት ሳያውቅ ማለዳ ወጥተው የቀይ ቀበሮውን ሐውልት አፈራረሱት። ይህ ሲሆን ምንም አይነት ግጭት አልተፈጠረም። ሐውልቱን አፈራርሰው ከከተማዋ እየወጡ እያለ በአቅራቢያው ከሚገኝ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የደወል ድምፅ ተሰማ" የሚሉት ከንቲባዋ ይህንን የደወል ድምፅ የሰሙ የከተማዋ ነዋሪዎች መሳሪያ ታጥቀው ወጡ በማለት ግጭቱ መልኩን መቀየሩን ያስረዳሉ።

ከዚህ በኋላም ከተማዋን ለቅቀው እየወጡ ከነበሩ ሰዎች ጋር ግጭት ተፈጥሮ የሰው ህይወት ላይ አደጋ ደርሷል ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ተናግረዋል።

ከተማዋ ውስጥ የታጠቁ ኃይሎች ነበሩ የሚሉት ከንቲባዋ የኦሮሚያ ፖሊስ ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ እስከ 12 ሰዓት ድረስ ከእነዚህ ኃይሎች ጋር ሲታኮሰ መዋሉን ሁኔታውን ለመቆጣጠር ግን ከአቅም በላይ እንደሆነበት ይናገራሉ።

በዕለቱ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች አብዛኞቹ በጥይት ተመትተው እንደሆነ ለቢቢሲ ያስረዱት ከንቲባዋ አሁን መረጋጋት እንደታየም ጨምረው ተናግረዋል።

ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገው የጎባ ከተማ ነዋሪ ወደ ከተማዋ በርካታ መሳሪያ ገብቷል የሚል ወሬ በሰፊው ይናፈስ እንደነበር ያስታውሳል። ነገር ግን እርሱ በዓይኑ ያየው ምንም አይነት ነገር እንደሌለ ለቢቢሲ ገልጿል።

ከንቲባ ዘይነባ የከተማው አስተዳደር በነገው ዕለት ነዋሪዎችን ለማነጋገር እቅድ እንደያዘ ገልፀዋል።

ሐጂ አደም ሳዶ በባሌ የኦሮሞ ገበሬዎች ትግል ወቅት ግንባር ቀደም የነበሩ ግለሰብ ሲሆኑ በኋላ ላይም በእነ ጄነራል ታደሰ ብሩ የሚመራው ሜጫና ቱለማ ማህበር የቦርድ አባል ነበሩ።

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

በባሌ ዞን በጎባ ከተማ ባለፉት ቀናት በተፈጠረ ግጭት የስድስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የከተማዋ ከንቲባ ዘይነባ ጣሀ ተናግረዋል። በርከት ያሉ ሰዎች ደግሞ በአቅራቢያ በሚገኝ የጤና ተቋም...

‹‹በቀትረ-ቀላል ሹፌሮቻችን የሚነዱት… ቀላል-ባቡሮቻችን …አገራችን ላይ የመንግስት ቅጥረኛ ሆኖ ደልቶት የሚኖር የለም፡፡ ምናልባት የተለየ ህገ-ወጥ ገንዘብ ከሚያገኙ ሲቪል ሰርቫንቶች በቀር ...
23/07/2018

‹‹በቀትረ-ቀላል ሹፌሮቻችን የሚነዱት… ቀላል-ባቡሮቻችን …
አገራችን ላይ የመንግስት ቅጥረኛ ሆኖ ደልቶት የሚኖር የለም፡፡ ምናልባት የተለየ ህገ-ወጥ ገንዘብ ከሚያገኙ ሲቪል ሰርቫንቶች በቀር አብዛኛው መንግስት ሰራተኛ የሚሰራውና የሚከፈለው ደሞዝ የሚገናኝ አይደለም፡፡

ከዚህም ጋር ተያይዞ ከሰሞኑን ‹‹ማግኘት ያለብንን ጥቅማ-ጥቅም እየተከፈለን አይደለም›› የሚሉ የቀላል-ባቡር ሰራተኞች የስራ-ማቅም አድማ መትተው እንደነበር በሚዲያዎች ሲገለጽ ሰንብቷል፡፡ ይሄም ሆኖ ግን የድርጅቱ ስራ አስኪያጆችና ዳይሬክተሮች የሰራተኞቹን ጥያቄ በተገቢው ሁኔታ በማዳመጥ ‹‹ችግሮቹን ፈትተናል›› በማለት የገለጹ ቢሆንም… ሰራተኞቹ ግን ‹‹ጥያቄያችን አልተመለሰም›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ እናም ከእነ ቅሬታቸው ወደ ስራ የተመለሱት የባቡር ሹፌሮች ስራቸውን ብቻ ሳይሆን ተገልጋዮቻቸውንም በመበደል ስራ ላይ ተጠምደዋል፡፡ እዚህ ላይ… እንደ’ኔ የባቡር ደንበኛ ያልሆናቸው ሰዎች ‹‹እኮ እንዴት?›› የሚል ጥያቄ ማንሳታችሁ ስለማይቀር ስለጉዳዩ ባጭሩ ልንገራችሁ፡፡

ወደ ‹አያት› የሚሄደውን ባቡር ለመሳፈር ‹ለገሃር› ጣቢያ ላይ ቆሜ አረንጓዴውን ባቡር እጠብቃለሁ፡፡
እናም ከሰላሳ ደቂቃ ጥበቃ በኋላ የምጠብቀው ባቡር ከአፍ እስከ ገደፉ ሞልቶ በመምጣቱ እንደምንም ብዬ ወደ ውስጥ ስገባ… ተሳፋሪው ሁሉ በብስጭት ውስጥ ሆነው ሹፌሩን ያማርራሉ፡፡ ዋነኛ ምሬታቸው ደግሞ ባቡሩ ባልተለመደ ሁኔታ በየጣቢያው ከሃያ ደቂቃ በላይ እየቆመ መምጣቱ ሲሆን ተሳፋሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ ‹‹ባቡሩ በየስፍራው የሚገተረው የቴክኒክ ችግር አጋጥሞት ሳይሆን ሹፌሮቹ ያቀረቡት ቅሬታ ባለመፈታቱ ምክንያት ነው›› ብለው ደምድመዋል፡፡ ስለዚህም ሹፌር ላይ የሚሰነዘር እርግማን ለተሳፋሪው እንደሚተርፍ ያልገባቸው ሰዎች ‹‹እድሜህ ይጠር›› በማለት ነጂውን ይራገማሉ፡፡

ለገሃር ላይ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ከቆመ በኋላ ባቡሩ ተንቀሳቀሰ፡፡ ወደተሳፋሪው ህብረተሰብ ዓይኔን ስልከው ከሙቀቱ የተነሳ ሁለት ህጻናቶች አስታውኳቸው ተመለከትኩኝ፡፡ ከዚህ ባለፈ ደግሞ ‹‹ኧረ ታፍኜ ሞትኩኝ፣ ወይኔ እናቴ ድረሽልኝ›› የሚሉ የሴት ድምጾች ከየቦታው ይሰማሉ፡፡

ባቡሩ ስቴዲየም ላይ ሲደርስ ቆመ፡፡ ሆኖም ግን አቋቋሙ ተሳፋሪዎችን ለማውረድና ለማውጣት አልነበረም፡፡ ይልቅስ በቴክኒክ ብልሽት በሚል ሰበብ ወደአያትና ወደ ቃሊቲ መስመር የሚሄዱትን ባቡሮች ለማገት የተወጠነ ሴራ ነበረ፡፡

እዚህ ላይ ‹ሴራ› መሆኑን ያወኩት በግምት ሳይሆን በማጣራት መሆኑን ልገልጽላችሁ አፈልጋለሁ፡፡ ታዲያ አሳዛኙ ነገር ስቴድዬም ላይ ከ25 ደቂቃ በላይ ባቡሩ ሲቆም ምንም የተባለ ነገር አለመኖሩ ነው፡፡ ለወትሮው አንድ ችግር ሲፈጠር ባቡሩ ላይ በተገጠሙት ስፒከቸሮች አማካኝነት በታላቅ ትህትና ውስጥ ሆነው ‹‹ከዚህ ጣቢያ በኋላ መሄድ አንችልም›› ወይም ደግሞ ‹‹የሚቀጥለው ጣቢያ ላይ አንቆምም›› የሚሉት ሹፌሮች ይሄንን አሰራራቸውን እርግፍ አድርገው በመተው ስለ ባቡሩ መበላሸትም ሆነ ስለቆመበት ምክንያት ምንም ነገር መናገር አልፈለጉም፡፡

በስተመጨረሻም በታፈገ ህዝብ መሃከል መቆም የሰለቻቸው አንዳድ ሰዎች ‹‹መሄዱንና አለመሄዱን›› ለማጣራት ወደ ሹፌሩ ጋር ሲሄዱ አብሬ ተከተልኳቸው፡፡ ሆኖም ግን የባቡሩ ነጂ በሩን ዘግቶ ‹‹በሞባይሉ ቻት እያደረገ›› ስለነበር የሚያነጋግረን ሰው አላገኘንም፡፡ በዚህ ሁኔታም የተበሳጩ ሰዎች ሹፌሩ ይሰማቸው ይመስል ሲሰድቡትና ሲዘልፉት ከቆዩ በኃላ ታክሲ ፍለጋ ሲበታተኑ እኔ የሚሆነውን ለመከታተል ወደ ባቡሩ ተመልሰኩኝ፡፡

ከጥቂት ቆይታ በኋላም ባቡሩ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ሆኖም ግን እንቅስቃሴው እስከሚቀጥለው ፌርማታ ድረስ ነበር፡፡ በየጣቢያዎቹ ሁሉ ቻርጅ እያደረገ የሚሄድ ይመስል ከአንዱ ጣቢያ ወደ ቀጣዩ ጣቢያ ለመንቀሳቀስ በቀላሉ አስር ደቂቃ መጠበቅ ግደታ ነው፡፡
በዚህም የተነሳ ለወትሮው እስከ ‹መገናኛ› ለመድረስ ከ20 ደቂቃ በላይ የማይወስድበት ባቡር ዛሬ ግን ከአንድ ሰዓት ተኩል በላይ ወሰደበት፡፡ እኔም ከዚህ በላይ መታገሱ ስላልሆነልኝ በብድር የተገዛውን ባቡር የሚራገሙትን ተሳፋሪዎች እየቆራረጥኩኝ ታክሲ ፍለጋ ከባቡሩ ወረድኩኝ፡፡

ትዝብቴን ሳጠቃልለው በማግስቱም ይሄንኑ የትራንስፖርት አማራጭ ለመጠቀም የሄድኩ ቢሆንም ያጋጠመኝ ክስተት ተመሳሳይ ነው፡፡ ከዚያ በኋላም ከሰዎች ማጣራት እንደቻልኩት ይሄ ሁኔታ በመቀጠሉ ብስጭቱን በእርግማን ሲገለጽ የነበረው ተሳፋሪ ሹፌሮቹን ለመደብደብ ሲጋበዝ እንደነበር ተረድቻለሁ፡፡

እናም በአጠቃላይ የባቡር ሰራተኞቻችን በህብረተሰቡ ላይ እያደረጉት ያለው ነገር ሊፈጸም ቀርቶ ሊታሰብ የሚችል አይደለም፡፡ ስራንና ደንበኛን በመበደል የግል ጥቅምን ለማስከበር መሞከርም በጣም አጸያፊ ድርጊት ነው፡፡ ባቡሩ ከተበላሸ ‹‹ተበላሽቷል›› ብሎ ማቆም ሲቻል በሺህ የሚቆጠር ህዝብ ጠቅጥቆ ከአያት እስከ ጦር-ሐይሎች ያለውን መንገድ ለመጨረስ ቀኑን ሙሉ ሲንገዋለሉ መዋል አግባብነት የለውም፡፡ ይሄን የምለው የሰራተኞቹን ስም ለማጠልሸት ፈልጌ ሳይሆን ጤነኛ ባቡሮች በበሽተኛ ሹፌሮች እጅ መዋላቸውን በማረጋገጤ ነው፡፡

ስለዚህም ይሄንን ጉዳይ የሚያዉቁት የድርጅቱ አመራሮች በአገር ብድር በተገዛ ባቡርና እልፍ-አዕላፍ መኪና የሚሄድበትን መንገድ ባጣበበ ሃዲድ ላይ እንዲህ ያለ የጅል ስራ የሚፈጽሙ ሹፌሮች ላይ ተገቢውን እርምጃ ሊወስድ ይገባል፡፡ ከዚህ ባለፈ ደግሞ የህዝብ እንግልት የሚያሳስባቸው ሚዲያዎች…. ቀላል ባቡሩን እንዲነዱ የተመደቡት ‹‹ቀትረ-ቀላል ሹፌሮች›› በህዝቡ ላይ የሚፈጽሙትን ግፍ ወደ ባቡሮቹ ገብተው በማየትና ስለጉዳዩ የሚመለከታቸውን አካላቶች በማነጋገር… ችግሩ እልባት እንዲያገኝ ማድረግ ይኖርባቸዋል›› በማለት ትዝብቴን አበቃለሁ፡፡

For more news visit our website https://abaydar.com
Like and Share Our Page
Click the link to read more

አገራችን ላይ የመንግስት ቅጥረኛ ሆኖ ደልቶት የሚኖር የለም፡፡ ምናልባት የተለየ ህገ-ወጥ ገንዘብ ከሚያገኙ ሲቪል ሰርቫንቶች በቀር አብዛኛው መንግስት ሰራተኛ የሚሰራውና የሚከፈለው .....

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abay Dar posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Abay Dar:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share

Abay Dar

We are committed to any IT business