Arts Tv World

Arts Tv World Arts Tv World - Digital Media and Satellite Television Service
(2)

የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር እንዲሁም በፈጠራ መስክ አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪ መሆን ይጠበቅባቸዋል ተባለ።በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ...
04/08/2025

የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር እንዲሁም በፈጠራ መስክ አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪ መሆን ይጠበቅባቸዋል ተባለ።

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።

በጉኤው ላይ ንግግር ያደረጉት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮሪ ጡሹኔ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ለማሳደግ ጥረቶች ቢኖሩም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን በርካታ ስራዎች ይጠበቃሉ ብለዋል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ጉባኤው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70ኛ ዓመትና የማስተማሪያ ሆስፒታሉ 100ኛ ዓመት እያከበረ በሚገኝበት ወቅት መካሄዱ ልዩ ያደርገዋል ነው ያሉት።

የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የለውጥ ሐዋሪያ ናቸው ያሉት ፕሬዜዳንቱ በዚህ ረገድ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ብዙ ርቀት መጓዙን ይናገራሉ።

በቃል ኪዳን ቤተሰብ ዙሪያ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምርት ተቋማት የልምድ ልውውጥ መድረክ ተዘጋጅቶ የፋሲለደስ ስምምነት መፈራረማቸው አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የምርም ዩኒቨርሲቲ በመባል ከፍተኛ ቦታ የያዘ ሲሆን ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው።

ዩኒቨርሲቲዎች አለም አቀፍ ጠባይ አላቸው ከውጭ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ያለው አብሮ የመስራት ልምድ በሀገር ውስጥም መጠናከር
እንዳለበት ፕሬዜዳንቱ ተናግረዋል።
በዩኒቨርሲቲዎች መካከል ለሚደረገው ሁለገብ የልምድ ልውውጥ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቂርጠኝነት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በአብነት ታምራት

ሶረኔ : ምዕራፍ አንድ ክፍል አንድ !!
03/08/2025

ሶረኔ : ምዕራፍ አንድ ክፍል አንድ !!

and follo...

5ኛው ዙር የ ኬር ኦድ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሄደ5ኛው ዙር የ ኬር ኦድ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል፡፡ዛሬ ማለዳ ላይ በተደረገው የኬር ኦድ 15 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድ...
03/08/2025

5ኛው ዙር የ ኬር ኦድ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሄደ

5ኛው ዙር የ ኬር ኦድ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል፡፡

ዛሬ ማለዳ ላይ በተደረገው የኬር ኦድ 15 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር በወንዶች አትሌት ሀጎስ እዮብጋረድ ከዘቢደር አትሌቲክስ ክለብ አሸናፊ ሆኗል፡፡

በሴቶች የ15 ኪ.ሜ ውድድር ደግሞ ጉተኒ ሻንቆ ከኦሮሚያ ፖሊስ አንደኛ በመሆን አጠናቅቃለች፡፡

በውድድሩ ታዋቂ ስፖርተኞችን ጨምሮ ከአካባቢው እና ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ አትሌቶች ተሳትፈዋል።

የ"ኬር ኦድ" የሩጫ ውድድር ተተኪ አትሌቶችን ከማፍራት በተጨማሪ አካባቢውን በማስተዋወቅ ረገድ አስተዋጽዖን ማበርከት የቻለ ታላቅ የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር መሆኑ ተመላክቷል።

ለ5ኛ ጊዜ የተካሄደውን "ኬር ኦድ" የ15 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ኬር ኦድ የልማት እና ስፖርት ማህበር ከዞኑ አስተዳደር ጋር በመተባበር ነው ያዘጋጀው።

በጌታሁን አበበ

በአሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዲሲ ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል ለኤግዚቪሺን ጨዋታ ወደ ሀገረ አሜሪካ ያቀናዉ የኢትዮጲያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ በኢትዮጲያ ስዓት አቆጣጠር ምሽ...
02/08/2025

በአሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዲሲ ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል

ለኤግዚቪሺን ጨዋታ ወደ ሀገረ አሜሪካ ያቀናዉ የኢትዮጲያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ በኢትዮጲያ ስዓት አቆጣጠር ምሽት 6 ስዓት በአዉዲ ፊልድ ስታዲየም ከዲሲ ዩናይትድ ክለብ ጋር ጨዋታዉን ያከዉናል።

20ሺህ ተመልካቾችን ማስተናገድ በሚችለው ኦዲ ፊልድ ስታድየም በሚደረገው ጨዋታ ከ13ሺህ በላይ ተመልካቾች እንደሚገኙ የሚጠበቅ ሲሆን በአካባቢው የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ይታደሙበታል ተብሎ ይጠበቃል ።

ዋሊያዎቹ ከጨዋታዉ አስቀድሞ ትናንት የመጨረሻ ልምምዳቸዉን ያደረጉ ሲሆን የሎንደን ዩናይትዱን ስራፌል ዳኛቸዉ በጉዳት ከስብስቡ ዉጭ ሲሆን ሌሎች የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።

ብሔራዊ ቡድኑ ጨዋታውን በማድረጉ ብቻ 25 ሺህ ዶላር የሚያገኝ ሲሆን ጨዋታውን የሚያሸንፍ ከሆነ ደግሞ ተጨማሪ 25 ሺህ ዶላር ያገኛል ።

የተለያዩ ክለቦች ተጫዋቾችን ለመመልመል በሜዳ እንደማገኙ የተገለፀ ሲሆን የዲሲ ዩናይትድ ክለብ ባለድርሻ የሆነው ባለሀብቱ አቶ ኢዮብ ማሞ ለብሔራዊ ቡድኑ የእራት ግብዣ ባደረጉበት ወቅት በግልም ጥሩ ብቃት ለሚያሳዩ ተጫዋቾች ሽልማቶች መዘጋጀታቸውን መግለጻቸው ይታወቃል ።

በዮናስ ግርማ

ክራፍት ሲልከን ቴክኖሎጂ ፀደይ ባንክን በአገሪቱ ካሉ ባንኮች በቴክኖሎጂ ቀዳሚው አደርገዋለው ሲል አስታወቀ  ። ፀደይ ባንክ በአለም ላይ በ 45 አገራት ከ ሶስት መቶ በላይ የፋይናንስ ተቋማ...
31/07/2025

ክራፍት ሲልከን ቴክኖሎጂ ፀደይ ባንክን በአገሪቱ ካሉ ባንኮች በቴክኖሎጂ ቀዳሚው አደርገዋለው ሲል አስታወቀ ።

ፀደይ ባንክ በአለም ላይ በ 45 አገራት ከ ሶስት መቶ በላይ የፋይናንስ ተቋማት ጋር አብሮ ከሚሰራው ክራፍት ሲልከን ቴክኖሎጂ ጋር የባንኩን የኮር ባንኪንግ ቴክኖሎጂ ለማሳደግ ስምምነት ፈፅመዋል።

ፀደይ ባንክ እራሱን በባንክ ቴክኖሎጂ ከፍ ያለ ደረጃ ለማድረስ እንዲሁም ባንኩ የሚሰጠውን አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሳሰረ ለማድረግ ያግዘው ዘንድ ላለፉት 20 አመታት በተለያዩ አገልግሎቶች አብሮት ይሰራ ከነበረው ክራፍት ሲልከን ቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር የባንኩን ኮር ባንኪንግ ቴክኖሎጂ ለማሳደግ የሚረዳ ስምምነት ነው የፈፀሙት ።

የፀደይ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መኮንን የለውምወሰን ባንኮች ጊዜውን ተከትለው ማደግ ካልቻሉ እራሳቸውን ወደ ገደል ለመክተት እንደመወሰን ነው ያሉ ሲሆን ባንኩ እራሱን ለማዳን ይህን ስምምነት እንደፈፀመ ገልፀዋል ።

በአለም ላይ በ45 አገራት ከ300 በላይ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ አቅርቦት እና አገልግሎት በመስራት የሚታወቀው የክራፍት ሲልከን ቴክኖሎጂ ዋና ስራ አስፈፃሚ ከማል ቡድሃቲ በስምምነቱ ወቅት እንደገለፁት ከፀደይ ባንክ ጋር ለረጅም አመታት በመስራት እዚህ መድረሳቸውን ገልፀው ዘመኑ ባንኮች እራሳቸውን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ጭምር ማሳደግ የሚገባቸው ጊዜ በመሆኑ ለባንኩ የምናቀርባቸው አገልግሎቶች የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ያካተተ ይሆናል ብለዋል ። በዚህ ስምምነትም ፀደይ ባንክን በአገሪቱ ካሉ ባንኮች በቴክኖሎጂ ቀዳሚው ለማድረግ እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል ።

ፀደይ ባንክ ላለፉት ሰላላ አመታት በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ አገልግሎት እየሰጠ ያለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ሃብቱ 74,6 ቢሊዮን ብር የደንበኞቹ ብዛት ደግሞ ከ12 ሚሊዮን በላይ ደርሷል ። በተጨማሪም ከ630 በላይ ቅርንጫፎች እንዳሉት የገለፀው ባንኩ አጠቃላይ የሰጠው ብድር ከ 45 ቢሊዮን በላይ ሆኗል ተብሏል ።

የ30 ዓመቱ ቢሊየነርወጣቱ አቶ ፍቅሬ አስፋው የሬማ ጀነራል ቢዝነስ መሠራች እና ባለቤት ሲሆኑ በተቋሙ ስር ከሚተዳደሩ ድርጅቶች አንዱ ሬማ ኮንስትራክሽን ከስድስት ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወ...
31/07/2025

የ30 ዓመቱ ቢሊየነር

ወጣቱ አቶ ፍቅሬ አስፋው የሬማ ጀነራል ቢዝነስ መሠራች እና ባለቤት ሲሆኑ በተቋሙ ስር ከሚተዳደሩ ድርጅቶች አንዱ ሬማ ኮንስትራክሽን ከስድስት ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ይገኛል ብለዋል።

ሬማ ኮንስትራክሽን በአሁኑ ወቅት የአማራ ክልላዊ መንግሥት መቀመጫ በሆነችው ባህርዳር ከተማ ደረጃቸውን የጠበቀ መንገድ ፤ ለግንባታ ዝግጁ የሆኑ የባለአምስት ኮከብ ሆቴል መሥሪያ ቦታ፣ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ሥራዎችና ሌሎችም በአጠቃላይ የ6 ቢሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ሥራዎችን እያከናወነ የሚገኝ ግዙፍ ድርጀት ነውም ነው የተባለው።

እነዚህን ፕሮጀክቶችን የሚመሩት ባለኀብት ፍቅሬ አስፋው የ30 ዓመት ወጣት ናቸው።

አቶ ፍቅሬ ሥራ የጀመሩት በአጎታቸው የኮንስትራክሽን ድርጅት ውስጥ በጎንደር ከተማ ሲሆን ከጉልበት ሠራተኝነት እስከ ፎርማን ደረጃ ማገልገላቸው ወደ ዘርፉ ተስቤ እንድገባ ምክንያት ሆኖኛል ይላሉ።

በግላቸው የመጀመሪያ የኮንስትራክሽን ሥራ ጨረታ አሸንፈው የሠሩባት ሬማ ከተማ ለድርጅታቸው መጠሪያ ሥም ማድረጋቸውንም ይናገራሉ።

ወጣቱ ባለሃብት ከመ'ሰረቷቸው ኩባንያዎች በድምሩ 3 ነጥብ 2 ቢልየን ብር ዓመታዊ ገቢ ያላቸው ሲሆን ከከፍተኛ ግብር ከፋዮች መካካልም አንዱ መሆናቸውን ተናግረዋል።

እኚሁ ባለኀብት እስካሁን ባሏቸው ፕሮጀክቶች ወደ 2 ሺ 500 ገደማ ለሚሆኑ ሠራተኞች የሥራ እድል ፈጥረው እያስተዳደሩ ይገኛሉ።

ድርጅታቸው ሬማ ኮንስትራክሽን በኤሌክትሮ መካኒካል፣ በውሀ ሥራዎች የደረጃ አንድ ፈቃዶች ያ'ሉት ሲሆን በሪልስቴት ዘርፍ፣ በአስመጪና ላኪነት፣ በሆቴል፣ በትራንስፖርት ዘርፍና በመሳሰሉ ግንባታና ቢዝነስ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ስለመሆኑም ነግረውናል።

አቶ ፍቅሬ አስፋው በቡና ኤክስፖርት ዘርፍ በዘንድሮው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳትፈው ከ 11 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ለጣቢያችን ገልጸዋል።

ሷሊህ መሐመድ ከባህርዳር

ሶረኔ : አዲስ ተከታታይ ድራማ !
31/07/2025

ሶረኔ : አዲስ ተከታታይ ድራማ !

አቢሲኒያ ባንክ በመላው አገሪቱ ወረቀት አልባ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ይፋ አደረገ ። ይህ ወረቀት አልባ ልዩ የባንክ አገልግሎት ዘመናዊ የባንክ አሠራሮችን እንዲይዝ ተደርጎ በአዲ...
26/07/2025

አቢሲኒያ ባንክ በመላው አገሪቱ ወረቀት አልባ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ይፋ አደረገ ።

ይህ ወረቀት አልባ ልዩ የባንክ አገልግሎት ዘመናዊ የባንክ አሠራሮችን እንዲይዝ ተደርጎ በአዲስ መልክ በተዋቀረው የባንኩ ራስ ልዩ ቅርንጫፍ (Ras Premium Branch) በዛሬው ዕለት በተከናወነ ይፋዊ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት አገልግሎቱን መስጠት ጀምሯል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ ኢትዮጵያ የባንክ ዘርፉን ለውጭ ባንኮች ክፍት ማድረጓን ተከትሎ በአገር ውስጥ ያሉ ባንኮች በቴክኖሎጂ ያላቸውን አቅም ማሳደግ ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን አቢሲኒያ ባንክ ያስጀመረው ወረቀት አልባ አገልግሎት ለዘርፉ ፈር ቀዳጅ እንደሚሆን ተናግረዋል።

በዚህ አዲስ አሠራር ደህንነቱ የተጠበቀ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት የሚቻል ሲሆን፤ ገንዘብ ማስተላለፍ፣ ጥሬ ገንዘብ ማስገባትና ማውጣት፣ ሒሳብ መክፈትና ሌሎች ከቅርንጫፍ አገልግሎት ጋር የተገናኙ ማናቸውንም አገልግሎቶች በራስ ወይም በባንኩ ሠራተኞች በመታገዝ መጠቀም ይቻላል ሲሉ የአቢሲኒያ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ በቃሉ ዘለቀ በማስጀመሪያ መርሃግብሩ ላይ ተናግረዋል ፡፡

አገልግሎቱ የእንግሊዝኛ ቋንቋን ጨምሮ በተለያዩ አገራዊ የቋንቋ አማራጮች (በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ፣ በሱማሌኛ፣ በትግርኛ፣ በአፋርኛ እና በሲዳምኛ) የቀረበ ሲሆን፣ ሁሉንም ደንበኞች ማዕከል ባደረገ መልኩ የዕድሜ፣ የትምህርት ደረጃ ወይም ሰዎች ለቴክኖሎጂ ባላቸው የክህሎት መጠን የማይገደብ ቀላል፣ እመቺ እና ተስማሚ ተደርጎ የቀረበ ነው ተብሏል ።

ኢትዮ ቴሌኮም እጅግ ከፍተኛ ነው የተባለውን 162 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ ። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የተቋሙን የሦስት ዓመት መሪ እድገት ስትራቴጂ ማ...
24/07/2025

ኢትዮ ቴሌኮም እጅግ ከፍተኛ ነው የተባለውን 162 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ ።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የተቋሙን የሦስት ዓመት መሪ እድገት ስትራቴጂ ማጠቃለያ ሪፖርት እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት ሪፖርት ማጠቃለያ ይፋ ባደረጉበት መድረክ ላይ ተቋሙ በዚህ በጀት አመት ለማግኘት ካስቀመጠው 163 ቢሊዮን ብር ውስጥ 162 ቢሊዮን ብሩን በማግኘት የእቅዱን 99 በመቶ ማሳካቱን ገልፀዋል ።

በዚሁ ወቅት ሌላው የተነሳው ጉዳይ በተቋሙ ላይ ስለተሞከረው የሳይበር ጥቃት ሲሆን በዚህ አመት ከ462 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ሙከራ ተደርጎብኛል ያለ ሲሆን ነገር ግን አንድም ጥቃት አልፎ ጉዳት አለማደረሱን እና በሙከራ ላይ እያለ ማስቆም መቻሉን ይፋ አድርገዋል ።

ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን በቅናሽ ዋጋ ለደንበኞች በማቅረቡ ከተወዳዳሪ አገልግሎት አቅራቢዎች ክስ ቀርቦበታል ያሉ ሲሆን ተቋሙ የተቋቋመው ለኢትዮጵያዊያን በመሆኑ ቅናሽ ማድረጉን እንደሚቀጥል እና ከዚህ ቀደም ውድ ናችሁ ተብለን ነበር ምንከሰሰው አሁን ደግሞ በጣም ርካሽ ዋጋ ታቀርባላችሁ ተብለን መከሰስ የለብንም ብለዋል ።

Address

Bole Medhanialem, Awlo Business Center, 8th & 9th Floors, Cameroon Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arts Tv World posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Arts Tv World:

Share

Category