Ethio Media Net

  • Home
  • Ethio Media Net

Ethio Media Net ኢትዮጵያዊነት የአኩሪ ታሪክ ባለቤቶች ለምለም ሀገር ያለን ኩሩኢትዮጵያዊያን ህዝቦች ነን።

የ11 ባንክ አካውንቶችን በቀላሉ ያገናኙ‼በኦንላይን የባንክ ሒሳብን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር  ከታች ያሉትን ሊንኮች መጠቀም ትችላላችሁ።ልብ ይበሉ፦ ሲስተም ላይ በነበረ መጨ...
10/01/2026

የ11 ባንክ አካውንቶችን በቀላሉ ያገናኙ‼

በኦንላይን የባንክ ሒሳብን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር ከታች ያሉትን ሊንኮች መጠቀም ትችላላችሁ።

ልብ ይበሉ፦ ሲስተም ላይ በነበረ መጨናነቅ ለቀናት ቆይቶ የነበረውም የመዘግየት ችግር በመፈታቱ ፣ ደንበኛ የሆኑበትን ባንክ ከታች በተዘረዘሩት ዝርዝር በመምረጥ ባለ 16 አኃዝ የፋይዳ ቁጥርዎን (FAN/FCN) በመጠቀም ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ለማጣመር (Harmonization) በነዚህ ሊንኮች ይጠቀሙ።

💸 አቢሲኒያ ባንክ: cs.bankofabyssinia.com/fayda_connect

💸 አዋሽ ባንክ : fayda.awashbank.com

💸 የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ: my.coopbankoromiasc.com/harmonization

💸 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ cbefayda.cbe.com.et

💸 ኦሮሚያ ባንክ ፡ obfayda.oromiabank.com

💸 ወጋገን ባንክ : fayda.wegagenbanksc.com.et/harmonization

💸 ንብ ባንክ፡ fayda.nibbank.com.et

💸 ፀሀይ ባንክ፡fayda.tsehaybank.com.et/FAYDA/home

💸 ስንቄ ባንክ : fayda.siinqeebank.com:7443

💸 ዘምዘም ባንክ : fayda.zamzambank.com.et

💸 አማራ ባንክ : fayda.amharabank.com.et

መውረጃው Official የናሽናል መታወቂያ መስሪያቤት የX አካውንት ነው።

07/01/2026

የእናት ��

የገና ስጦታ ሎተሪ 2018  ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በእድል አዳራሽ በህዝብ ፊት የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮችም ከዚህ ጋር ተያይዟልለተጨማሪ መረጃ ይ...
06/01/2026

የገና ስጦታ ሎተሪ 2018 ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በእድል አዳራሽ በህዝብ ፊት የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮችም ከዚህ ጋር ተያይዟል
ለተጨማሪ መረጃ ይህን ሊንክ ይጫኑ፡ https://linktr.ee/etiopianlotteryservice

ባሉበት የሒሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ መታወቂያዎ ጋር ያስተሳስሩ!****************ውድ የባንካችን ደንበኞች፡የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኅዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መመሪያ መሠረት፤...
30/12/2025

ባሉበት የሒሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ መታወቂያዎ ጋር ያስተሳስሩ!
****************

ውድ የባንካችን ደንበኞች፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኅዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መመሪያ መሠረት፤ ሁሉም ደንበኞች የባንክ አገልግሎቶች ለማግኘት እና ሒሳብ ለማንቀሳቀስ የፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል::

በዚህ መሠረት ባንካችን ደንበኞች ወደቅርንጫፍ ቀርበው የሒሳብ ቁጥራቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ከሚያጣምሩበት አሠራር በተጨማሪ ባሉበት አገልግሎቱን የሚያገኙበትን አማራጭ አመቻችቷል።

በመሆኑም ከታች በተቀመጠው የአሠራር ቅደም ተከተል መሠረት የፋይዳ ተለዋጭ ቁጥርዎን (16 አሀዝ-FAN Number) በማስገባት የባንክ ሒሳብ ቁጥርዎን ከፋይዳ መታወቂያዎ ጋር ያጣምሩ::

1. ይህን ማስፈንጠሪያ 👉 https://cbefayda.cbe.com.et/ በመጫን/ በማስገባት ገፁን ይክፈቱ፣
2. የሂሳብ ቁጥርዎን አስገብተው ‘Get OTP’ የሚለውን ይጫኑ፣
3. ሒሳብ ሲከፍቱ ያስመዘገቡትን የስልክ ቁጥር በሚጠቀሙበት የተንቀሳቃሽ ስልክ የተላከልዎትን የአንድ ጊዜ የሚስጥር ቁጥር (OTP) አስገብተው “Verify OTP” የሚለውን በመጫን ያረጋግጡ፣
4. “Log with OTP” የሚለውን ይጫኑ፤
5. የፋይዳ ተለዋጭ ቁጥርዎን (16 አሀዝ-FAN Number) አስገብተው ‘Get OTP’ የሚለውን ይጫኑ፣
6. በድጋሚ በተንቀሳቃሽ ስልክዎ የተላከልዎትን የአንድ ጊዜ የሚስጥር ቁጥር (OTP) አስገብተው “Verify” የሚለውን በመጫን ያረጋግጡ፣
7. “Allow” የሚለውን ይጫኑ፣
8. “Accept and Update” የሚለውን ሲጫኑ “Update complete. Pending Approval” የሚል መልእክት ይመጣልዎታል። ጨርሰዋል።

*****
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!

🔵ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የቦርድ አባላት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ከተመሰረተችበት ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለ...
10/12/2025

🔵ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የቦርድ አባላት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ

አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ከተመሰረተችበት ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በዜናና ወቅታዊ እንዲሁም በመዝናኛ ዝግጅቶች መረጃዎችን በቴሌቪዥን እና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ስታደርስ ቆይታለች፡፡
ይሁን እንጂ አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ስራዋን ለመቀጠል አቅም ስለሌላት በቴሌቪዥንም ሆነ በየትኛውም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ከዛሬ ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በይፋ ስርጭት ማቆሟን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

ስለሆነም ከተጠቀሰው ጊዜ ጀምሮ የአሻም ሚዲያ መታወቂያ በመያዝ ወይም የሚዲያዋን ሎጎ በመጠቀም በየትኛውም ሁነት (Event) ፣ በእቅድ ዜና ወይም ፕሮግራም ፣ በስልጠና መድረክ ፣ ቃለ-መጠይቅ እና በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚገኙ (የሚሳተፉ) ባለሞያዎች የሚዲያ ተቋሙን እንደማይወክሉ ለሁሉም የግልና መንግስታዊ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች ጭምር በትህትና ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

ባለፉት 8 ዓመታት ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ጋር አብራችሁ ለዘለቃችሁ ለውድ ተመልካቶቻችንና ተከታታዮቻችን ልባዊ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው፡፡

አሻም ለሁላችን!

የአለም ዋንጫ ድልድል ይህን ይመስላል የሞት ምድብ የሚባሉትን ኮሜንት ስር አስቀምጡልን እናመሰግናለን🙏
05/12/2025

የአለም ዋንጫ ድልድል ይህን ይመስላል የሞት ምድብ የሚባሉትን ኮሜንት ስር አስቀምጡልን እናመሰግናለን🙏

አቶ ታዬ ደንደአ የ7 ዓመት ከ2 ወር እስር ተፈረደባቸው።የቀድሞው የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የ7 ዓመት ከ2 ወር እስር ...
05/12/2025

አቶ ታዬ ደንደአ የ7 ዓመት ከ2 ወር እስር ተፈረደባቸው።

የቀድሞው የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የ7 ዓመት ከ2 ወር እስር ተፈረደባቸው።

አቶ ታዬ ዛሬ አርብ ኅዳር 26/2018 ዓ.ም. የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ መንግሥት እና በሕገ መንግሥት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ችሎት ጥፋተኛ በተባሉበት ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ነው።

የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን እና የክልል ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ታዬ ሕገ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት እንዲሁም ፍቃድ ሳይኖራቸው በቤታቸው ውስጥ አንድ ታጣፊ ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከ60 ጥይቶች ጋር ተገኝቷል በሚል ክስ ቀርቦባቸው ነበር።

መረጃው የቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ነው።

01/12/2025
የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ  የአሸናፊዎች ዝርዝር📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ አነቃቂ አዶናይ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የህክምና ይዘት ተሸላሚ ዶክተር ዐቢይ ታደሰ📌የ2025 የ...
30/11/2025

የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአሸናፊዎች ዝርዝር

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ አነቃቂ አዶናይ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የህክምና ይዘት ተሸላሚ ዶክተር ዐቢይ ታደሰ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የላይቭ ስትሪመር ተሸላሚ ናሆም ፎንቲ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የማህበራዊ ኃላፊነት በመወጣት ተሸላሚ ዶክተር አብይ ታደሰ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የኢንፎርማቲቭ አሸናፊ ብሩክ ኒውስ (ብሩክ ጫላ)

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ ተስፋ የተጣለበት ቲክቶከር ባምሌ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ዳንሰኛ ተሸላሚ ዳዊት ታዬ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ የጉዞ ተሸላሚ ሰያ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ላይፍ ስታየል አሸናፊ አዶናይ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ የ STEM አሸናፊ መምህር ዳኒ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ የጭላሎ ቻሌንጅ አሸናፊ በረከት ታደሰ (ቤኪ 4kilo)

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የG-Power ቻሌንጅ አሸናፊ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ሴት ኮሜዲ ተሸላሚ ንጹ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ወንድ ኮሜዲ ዶሚኔት ኑሪ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ አጭር ፊልም አሸናፊ ቤንጂ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ሪቪው ይዘት ተሸላሚ ጃኒ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የስማይል ቻሌንጅ አሸናፊ ዩቲ ናስ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ ምርጥ ሚመር ተሸላሚ ፓትሮን

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ Life Time አሸናፊ ዩቲ ናስ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የስፖርት መረጃ ይዘት አሸናፊ አቢ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ ምርጥ አለባበስ በሴት አሸናፊ ዩቲ ናስ

📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ቲክቶከር አሸናፊ አዶናይ

ከአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት የመካኒሳ ቅርጫፍ ፅ/ቤት ውስጥ 2.5 ሚሊየን በላይ ብር የዘረፉ ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር አውሎ ምርመራ ማጣራቱን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍ...
13/11/2025

ከአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት የመካኒሳ ቅርጫፍ ፅ/ቤት ውስጥ 2.5 ሚሊየን በላይ ብር የዘረፉ ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር አውሎ ምርመራ ማጣራቱን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አሰታወቀ፡፡
***
ተጠርጣሪዎቹ ወንጀሉን የፈፀሙት ከሌሊቱ 7 ሰባት ሰዓት ገደማ ጥቅምት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት የመካኒሳ ቅርጫፍ ፅ/ቤት ውስጥ ነው፡፡
ቅዱስ ሀይለየሱስ ፣ ዮናስ ግርማይ ፣ ኤርምያስ ሰንበት እና ኪሮስ ግርማይ የተባሉ ወንጀል ፈፃሚዎች ከድርጅቱ የጥበቃ ሰራተኞች ጋር ተመሳጥረው የድርጅቱን ካዝና በፌሮ ብረትና በሌሎች መርጃ መሳሪያ በመፈልቀቅ 2ሚሊየን 597ሺ 635ብር በመዝረፍ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C አዲስ አበባ 71417 ቪትዝ እና ኮድ 2A አዲስ አበባ 79207 ሚኒባስ ተሽከርካሪዎች በማዳበሪያ ጭነው ይሰወራሉ።

የወንጀሉ መፈፀም መረጃ የደረሰው የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የክትትል እና ኦፕሬሽን ክፍሉ ከወንጀል ምርመራ ክፍሉ ጋር በመቀናጀት ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ክትትል ወንጀሉ በተፈጸመ በሁለተኛው ቀን ወንጀል ፈፃሚዎችን እና ሁለት ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር በማዋል 569ሺ,595 ብር ማስመለሱን አስታውቋል፡፡

ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ በወንጀል ፈፃሚዎቹ ላይ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ፈጣን ችሎት/RTD/ ምድብ ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በመታየት ላይ መሆኑን መምሪያው ጨምሮ ገልጿል ፡፡
በዚህ የወንጀል ድርጊት ላይ የተሳተፉ የጥበቃ ሰራተኞች የጠበቃ አገልግሎት በሚሰጥ ተቋም አማካኝነት የተቀጠሩ እንደሆነ ፖሊስ አስታውቆ ኤጀንሲዎች የሚቀጠሯቸው ሰራተኞች በሚፈፅሙት ወንጀል የፍትሀብሔርና የወንጀል ተጠያቂነት ከማስከተሉም ባሻገር ፍቃድ ሠጪው አካል ፍቃዳቸውን እስከ መንጠቅ የሚያደርስ ጠንካራ ዕርምጃ የሚያስከትል ጥፋት መሆኑን በመገንዘብ ሰራተኞችን ሲቀጥሩ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ለውጡን ተከትሎ ባከናወናቸው ልዩ ልዩ ተግባራት ወንጀል ፈፅመው የሚሰወሩ ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር የማዋል አቅሙ እያደ መሆኑን አስታውቆ ህብረተሰቡ ሆነ ግለሰቦች የወንጀል ድርጊት ሲያጋጥማቸው ፈጥነው ለፖሊስ የማሳወቅ ልምድ ሊያዳብሩ እንደሚገባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
*
በም/ሳጅን:-አባይነህ እኔማየሁ

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የሞባይል ስልክ ስርቆት ፈፅመው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡...
13/11/2025

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የሞባይል ስልክ ስርቆት ፈፅመው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው በተለምዶ "ሿሿ” የተባለውን ወንጀል በመፈፀም ሞባይል ስልክ ሰርቀው ለማምለጥ ሲሞከሩ በተያዙ 7 ተጠርጣሪዎች ላይ የምርመራ ስራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ናትናኤል አለሙ ፣ አቤል ኮርሳ ፣ ዕድላዊት መላከ፣ መቅደስ አቡሽ፣ ኢዛና ባህሩ፣ ፀጋ ታደሰ እና መቅደስ አምዴሳ የተባሉ ሲሆኑ ሽፈራው ገበየሁ በተባለ ግለሰብ ላይ ወንጀሉን የፈፀሙት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ኮዬ ቂሊንጦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡

ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ተጠርጣሪዎቹ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 89261 ኦ.ሮ በሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው የግል ተበዳይን ጭነው እየተጓዙ ሞባይል ስልኩን ከኪሱ ከሰረቁ በኋላ "ትራፊክ ይቀጣናል ጋቢና ግባ ብለው" እንዳስወረዱት እና ከወረደ በኋላ ጥለውት እንዳመለጡ ተገልጿል፡፡

በግል ተበዳይ ላይ ወንጀል እንደተፈፀመ የተመለከቱ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ፖሊስ በጋራ ባደረጉት ክትትል ወንጀሉን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 5 ሴቶች እና 2 ወንዶች ሳሪስ አቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ ከተሽከርካሪው ወርደው ሊሰወሩ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በወቅቱ በተሽከርካሪው ላይ በተደረገ ፍተሻ ከተለያዩ ግለሰቦች ላይ በተመሳሳይ መልኩ የተሰረቁ ዘጠኝ ሞባይል ስልኮች የተያዙ ሲሆን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ በተጠርጣሪዎቹ ላይ የጀመረውን የምርመራ ስራ አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ በተጠቀሰው ተሽከርካሪ እና በተያዙት ተጠርጣሪዎች ተመሳሳይ ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚል ግለሰብ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመቅረብ ከተያዙት ስልኮች መካከል የእሱ ንብረት ስለመኖሩ በማረጋገጥ እንዲወስድ እና ለፖሊስ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል፡፡

መሰል የወንጀል አፈፃፀሞችን ለመከላከል በየጊዜው የሚገለፁ የጥንቃቄ መልዕክቶችን ተግባራዊ በማድረግ በከተማችን ሊፈፀሙ የሚችሉ ወንጀሎችን አስቀድሞ መከላከል እና መቆጣጠር እንደሚቻል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውሶ አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥም ህብረተሰቡ ለፖሊስ መረጃ በመስጠት ተባባሪነቱን ማጠናከር እንደሚጠበቅበት ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።

መልዕክተኛው በሰይፉ ሾው ቀርቦ ከተናገረው ፦★ ስሜ ስነጊዮርጊስ እሸቱ ይባላል።★ለ5 ዓመት ያህል ፊቴን ደብቄ ሰርቻለሁ።★ አብዛኛው ዕድሜዬን በእግር ኳስ ነው ያሳለፍኩት።የባህርዳር ከተማ ተ...
10/11/2025

መልዕክተኛው በሰይፉ ሾው ቀርቦ ከተናገረው ፦

★ ስሜ ስነጊዮርጊስ እሸቱ ይባላል።

★ለ5 ዓመት ያህል ፊቴን ደብቄ ሰርቻለሁ።

★ አብዛኛው ዕድሜዬን በእግር ኳስ ነው ያሳለፍኩት።
የባህርዳር ከተማ ተጨዋች ነኝ።

★ ባህርዳር ከተማን ፕሪሚየር ሊግ አስገብተን መሬት
ተሸልሚያለሁ።

★ የባህርዳር ከተማ ግብ ጠባቂ ( በረኛ ) ነኝ።

★ እናትም አባትም የለኝም። እናቴ ( አያቴ ) መነኩሴ ነች።
እናትም አባትም የለኝም። አያቴ ነች ያሳደገችኝ።

★ የአያቴን ደግነት አይቼ ነው የደግነት ስራ የጀመርኩት።

★ ቪዲዮው ላይ ትርፍራፊ ምግብ ከሚረዱት ሰዎች ጋር
ስመገብ ሰዎች ይገረማሉ። እኔ ግን ይኼንን ታሪክ
አሳልፌዋለሁ።

★ሰዎች መልዕክት ይልኩልኛል። የኔ ስራ ማድረስ ነው።

★ ሀሳቡን አመጣሁት ብዙ ሚስክኖች ተረዱ። ብዙ ሰዎች
በሚሊየን የሚቆጠር ብር ይገባላቸዋል።

★ አንድ ሰው ባላደራው ነኝ ብሎ አንድን አባት አጭበርብሯቸዋል። ለእኚህ አባት 20 ሺህ ብር
ሰጥቻቸው በርካታ ሰው ብዙ ገንዘብ አስገባላቸው።

★ ገንዘቡን ከአባባ የበላው ልጅ ፎቶው አለኝ። ማስረጃ አለኝ። ወደህግ አቅርበን ይፋ እናደርገዋለን።

★ አባባ ከእኔ መኪና ወጥተው እስከሚሄዱ ስልክ አልሰጠኋቸውም።

★ በዚህ አጋጣሚ ከጎኔ የቆሙ ሰዎችን አመሰግናቸኋለሁ።

★ እንደሰው እኔም ባላደራውም ልባችን ተሰብሯል።

★ ያ ሁሉ ነገር ተረስቶ እንደቀማኛ መቆጠራችን ልቤን
ሰብሮታል።

★ የሰው ትችት ሊያስቆምህ አይገባም። ይኼንን ስራ እቀጥላለሁ። በጭራሽ አላቆምም።

★ ኳስ ተጨዋች ነበርኩኝ። ትንሽ ሳንቲም አገኛለሁ። ከደሃ
ላይ አንስቼ የምበላበት ምክንያት የለኝም። መተዳደሪያ
የሚሆነኝ ሞባይል ቤት አለኝ።

★ ስልክ ቤት የከፈተው በደሃ ገንዘብ ነው የምትሉኝ ከሆነ
ይሁን ነው የምለው። እሱን እግዚአብሔር ያውቃል።

★ እራሴን ለመከላከል እዚህ ቦታ ላይ በመቀመጤ አፍራለሁ።

★ እኔና ባላደራው እንተዋወቃለን። እንደአርአያ ነው የሚቆጥረኝ።

★ ባላደራው የሚለውን ስም ያወጣነው ከእኔ ጋር ተወያይተን ነው።

★ ፊቴን መግለፄ ተፅእኖ ያሳድርብኛል።

★ ስራ ቦታ ሰው መጥቶ እርዳኝ ቢለኝ አልረዳም። ድንገት በመንገድ ስሄድ መንገድ ላይ ሰው መርዳት ደስ ይለኛል።

★ ይኼንን ስራ የምሰራው ለነፍሴ ነው። ለምን የደሃ ገንዘብ
እወስዳለሁ?

★ ከአንዲት ጥሩ ሴት አምነን የሚባል አንድ ልጅ አለኝ።
አሁን ከልጄ እናት ጋር አብረን አይደለንም። እሱን የመሰለ
ልጅ ስለሰጠችኝ አመሰግናታለሁ።
ሁለታችንም የየራሳችን ምዕራፍ ላይ ነን።

★ እናቴ ዩኒቨርሲቲ ፅዳት ትሰራ ነበር።

★ እኔም ቤት ማፅዳትና አትክልተኝነት ሰርቻለሁ።
የተራረፈ ምግብም እበላ ነበር።

★ የቀን ስራ 1 ዓመት ተኩል 15 ብር እየተከፈለኝ ሰርቻለሁ።

★ በዕርዳታ ስራው በጣም የሚሳተፉት የዓረብ ሀገር ሴቶች ናቸው። የሚከፈላቸው ደሞዝ ከኔ በታች ነው።

★ ለመጀመሪያ ጊዜ 8 ሺ ብር የላኩልኝ ዓረብ ሀገር የሚኖሩ ሰዎች ናቸው። አመሰግናቸኋለሁ።

★ ቲክቶክ አዋርድ ላይ ታጭቻለሁ። ሰው የተመቸውን ጥሩ ሰርቷል የሚለውን ይምረጥ። እኔ ግን ምረጡኝ ብዬ አልቀሰቅስም። ከፈለጉ ግን ይምረጡኝ።

★ ሰይፉ እናንተን የመሳሰሉ ደጋጎች እያሉ እኛ መመረጥ የለብንም። በደግነትህ ቀጥል።

★ ፌስቡክ ላይ 780 ሺህ ፣ ኢንስታግራም ላይ 164 ሺህ ፣
ቲክቶክ ላይ 1.7 ሚሊዮን ተከታዮች አሉኝ።
ሰዎችን ኮንታክት የማደርገው 1.7 ሚሊዮን ተከታዮች ባለው
ቲክቶች አካውንቴ ላይ ብቻ ነው።

★ እናቴ ለኔ ትልቁን ድርሻ ትወስዳለች። ዕድሜና ጤና ይስጥልኝ። እናንተም ፀሎት አድርጉልኝ።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Media Net posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share