Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

  • Home
  • Ethiopia
  • Werabe
  • Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ  መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። ይህ ፔጅ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ሂደት የአ/አደር ማሰልጠኛ ተቋማትን የአዳዲስ የቅመማ ቅመም ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀቃዋቆቶ ነሐሴ 26/2017{ አልቾ ኮሙኒኬሽን} በስልጤ ዞን አ...
01/09/2025

የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ሂደት የአ/አደር ማሰልጠኛ ተቋማትን የአዳዲስ የቅመማ ቅመም ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

ቃዋቆቶ ነሐሴ 26/2017{ አልቾ ኮሙኒኬሽን}

በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ወዚር 1 ቀበሌ የሚገኘው የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰንና የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ምልከታ አድርገዋል።

በወረዳው የሚገኙ የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከሎችን በሁሉም ዘርፍ ሞዴል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ የገለፁት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን በወዚር-1 ቀበሌ የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል እየለሙ ያሉ የቅመማ ቅመም ስራዎች በአርሶ አደሮችም በመስፋት የአርሶ አደሩን የገቢ አማራጮችን ለማሳደግ በትኩረት መሰረት አለበት ብለዋል ።

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ ሙዘይን መሀመድ በበኩላቸው አከባቢው ለቅመማ ቅመም ምርት ምቹ እንደሆነ አንስተው የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከሎች ሞዴል በመሆን በዘርፉ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ መስራት እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

በእለቱ በወዚር -1ቀበሌ የሮዝመሪን፣ የላቤንደርና የኮሰረት ስራን ምልከታ ማድረግ ተችሏል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘትከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ
በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338

በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/

በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk

በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication

በቲክቶክ https://vm.tiktok.com/ZM6BRmsNa/

ኢንስታግራም https://www.instagram.com/p/C1Za_1HtXH1/?igsh=YWYwM2I1ZDdmOQ==

ሀበይ ተስ ባለሙ/ባለነ! እንኳን ደስ አላችሁ/አለን!የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ በከፍተኛ አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ!የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖ...
01/09/2025

ሀበይ ተስ ባለሙ/ባለነ!
እንኳን ደስ አላችሁ/አለን!

የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ በከፍተኛ አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ነሃሴ 26/2017 በወራቤ ከተማ ባዘጋጀው የ2017 አፈጻጸም ግምገማና የ2018 እቅዶች መድረክ ላይ የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ በአጠቃላይ አፈጻጸም 2ኛ በመውጣት ሽልማት ተበርክቶለታል።

በዚሁ መሰረትም የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ በ2017 በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና 2ኛ በተቋማዊ ተግባራት አፈጻጸምም 2ኛ በአጠቃላይ ስራዎች ከክልሉ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች 2ኛ ደረጃ በመውጣት የኮምፒውተር፣ የዋንጫና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል።

የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ለተገኘው ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ሴክተሮች ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የዞንና የየመዋቅሩ አስተባባሪዎች ልባዊ ምስጋናውን በማቅረብ በሁሉም ደረጃዎች የሚደረጉ ጥረቶች፣ ድጋፎችና ክትትሎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪውን ያስተላልፋል።

መረጃው:-የስልጤ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው!

የትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ የተጀመሩ የግብርና ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለፀ ቃዋቆቶ ነሐሴ 26/2017{ አልቾ ኮሙኒኬሽን}የትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ የተጀ...
01/09/2025

የትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ የተጀመሩ የግብርና ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው ተገለፀ

ቃዋቆቶ ነሐሴ 26/2017{ አልቾ ኮሙኒኬሽን}

የትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ የተጀመሩ የግብርና ስራዎች በተለይ የቅመማ ቅመም ልማት ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል

በወዚር 1 ቀበሌ አቦጀቦ ትምህርት ቤት የውስጥ ገቢውን ለማሳደግ በቅመማ ቅመም ልማት የተከናወኑ ተግባራትን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰንና የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ምልከታ አድርገዋል።

በምልከታው ወቅት የስራ ሀላፊዎቹ በትምህርት ቤቱ የተጀመረው የሮዝመሪ ልማት የውስጥ ገቢውን ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ አንስተው ተግባሩን ከቋሚ ሰብል ጎን ለጎን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘትከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ
በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338

በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/

በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk

በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication

በቲክቶክ https://vm.tiktok.com/ZM6BRmsNa/

ኢንስታግራም https://www.instagram.com/p/C1Za_1HtXH1/?igsh=YWYwM2I1ZDdmOQ==

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሳው በወራቤ ከተማ እየተሰሩ የሚገኙ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶችንና የኮሪደር ልማት ስራወችን ምልከታ አደረጉ።ነሃሴ26/...
01/09/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሳው በወራቤ ከተማ እየተሰሩ የሚገኙ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶችንና የኮሪደር ልማት ስራወችን ምልከታ አደረጉ።

ነሃሴ26/ 2017

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሳው በወራቤ ከተማ እየተሰሩ የሚገኙ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶችንና በግንባታ ላይ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ምልከታ አድርገዋል።

በምልከታውም ወቅት በወራቤ ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶችንና ፣የስልጤ ዞን የአስተዳደር ህንፃ ግንባታ ፣የወራቤ ከተማ የውስጠ ለውስ የአስፓልት መንገድ ግንባታንና በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላን ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋዬ፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ዘይኔ ቢልካና የስልጤ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊና የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ነኢማ ሙኒርና ሌሎች የክልልና የዞን አመራሮች በተገኙበት ምልከታውን አድርገዋል።

በከተማዋ እየተሰሩ የሚገኙ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችና የኮሪደር ልማት ስራዎች ከተማዋን ውብና ፅዱ ከማድረጋቸውም በላይ ፕሮጀክቶቹ በከተማዋ ጤናው የተጠበቀ ማህበረሰብ ለመገንባት የጎላ ሚና እንዳለው የገለፁት ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሳው በከተማዋ የተጀመሩ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችና ሌሎች ግንባታዎች አሁን ያሉበት ደረጃ ይበል የሚያሰኝ እንደሆነ በምልከታው ወቅት ገልፀዋል።የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት

"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር  በተሻገረ ህልም በላቀ ትጋት አስተማማኝ ነገን መስራት" በሚል መሪ ቃል የፐብሊክ ሰርቫንት የብልጽግና ህብረት አባላት  የስልጠናና የውይይት መድረክ ጀመረ !...
01/09/2025

"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በተሻገረ ህልም በላቀ ትጋት አስተማማኝ ነገን መስራት" በሚል መሪ ቃል የፐብሊክ ሰርቫንት የብልጽግና ህብረት አባላት የስልጠናና የውይይት መድረክ ጀመረ !

ነሀሴ 26/2017 ዓ.ም (አልቾ ኮሙኒኬሽን)

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ የፐብሊክ ሰርቫንት የብልጽግና ህብረት አባላት "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በተሻገረ ህልም በላቀ ትጋት አስተማማኝ ነገን መስራት" በሚል መሪ ቃል የስልጠናና የውይይት መድረክ በዛሬው እለት እያካሄደ ይገኛል ።

ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናቶች የሚቆይ ሲሆን ስልጠናው በየማህበራዊ መሠረቱ ነው እየተሰጠ የሚገኘው።

በአልቾ ወሪሮ ወረዳ"የአገልግሎት ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት"በሚል መሪ ቃል በየደረጃው ከለው አመራር የመልካም አስተዳደር የውይይት መድረክ ተካሄደ።ቃዋቆቶ ነሃሴ 25 /2017 አልቾ ኮሙኒ...
31/08/2025

በአልቾ ወሪሮ ወረዳ"የአገልግሎት ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት"በሚል መሪ ቃል በየደረጃው ከለው አመራር የመልካም አስተዳደር የውይይት መድረክ ተካሄደ።

ቃዋቆቶ ነሃሴ 25 /2017 አልቾ ኮሙኒኬሽን

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ"የአገልግሎት ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት"በሚል መሪ ቃል በየደረጃው ከለው አመራር የመልካም አስተዳደር የውይይት መድረክ ተካሂደዋል።

በእለቱም ለውይይት መነሻ የሚሆን የተፈቱ እና ያልተፈቱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ላይ ሰነድ ተዘጋጅቶ በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ረዳት የመንግስት ተጠሪ በአቶ ጀማል ሻሚል ለተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

በመድረኩም አመራሩ ንቁ እና ብቁ በመሆን ወቅቱ የሚጠይቀውን ተልእኮ በአግባቡ መወጣት እንደሚገባ የተናገሩት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን ዛሬን ሳይሆን ነገን አሻግሮ የሚያይ አመራር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት መድረኩ ሚናው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

በወረዳ ደረጃ ይስተዋሉ የነበሩ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ምላሽ እየተሰጣቸው መሆኑን ያሳወቁት ዋና አስተዳዳሪዋ ወረዳዊ የገቢ አቅምን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡

በግብርናው ዘርፍ አዳዲስ ኢንሼንቲቮችን በመፍጠር የአርሶ አደሮችን ምርት እና ምርታማነት ማሳደግ እንደተቻለ የገለጹት ወ/ሮ መህድያ በቀጣይ የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቅንጅት እንደሚሰራ አስታውቀዋል ፡፡

አክለውም እኛው በኛው ለእኛው በሚል የተጀመሩ ወረዳዊ ፕሮጀክቶችን በአጠረ ጊዜ ማጠናቀቅ እና ለአገልግሎት ለማብቃት እየተሰራ መሆኑንም ዋና አስተዳዳሪዋ ተናግረዋል ፡፡

የስልጤ ዞን ውሃ ማእድን እና ኢነርጂ መምሪያ ዋና ሃላፊ አቶ ጨፋ ከድር የባህር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ ህዝቦች የህልውና ጉዳይ መሆኑን በማንሳት ሀገራችን የባህር በር ባለቤት እንድትሆን ሰላማዊ በሆነ እና ሰጥቶ በመቀበል መርህ እየተሰራ እንደሆነ አሳስበዋል፡፡

የአገራችንን ጥቅም እና ሉኣላዊነትን ባስጠበቀ መልኩ በተሰሩ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ እድገቶች መመዝገባቸውን የተናገሩት አቶ ጨፋ በቀጣይ የስራ አጥ ቅነሳ እና የኑሮ ውድነቱ ላይ ተጨባጭ ለውጦች ለማስመዝገብ መንግስት በትኩረት እየሰራ እንደሆነም አንስተዋል።

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ በበኩላቸው አመራሩ የአገልግሎት አሰጣጡን በማሳደግ በወረዳው በሁሉም ዘርፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡

የተጀመረውን የከተሞች መልሶ ማልማት አጠናክሮ በማስቀጠል ለነዋሪዎቹ ምቹ ማድረግ እንደሚገባ የተናገሩት ዋና የመንግስት ተጠሪው ህገ ወጥ ግንባታን መቆጣጠር እና ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በትኩረት እየተሰራ እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡

ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ አመራሩ ቁርጠኛ ሆኖ መስራት እንዳለበት ያነሱት አቶ ሙዘይን በወረዳው በውሃ በመንገድ በጤና እንዲሁም በትምህርት ቤቶች ግንባታ የተጀመሩትን ተግባራት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ መልእክት አስተላልፈዋል ፡፡

በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ በአዲስ ኢኒሼቲቭ የተጀመረው ንቅናቄ ለማሳካት ወሳኝ ሚና ያለው  ስራ በጉግሶ ቀበሌ  በአርሶ አደር   አብደላ ኢብራሂም የለማ የነጭ ሽንኩርት ተስፋ ሰጪ እንቅ...
31/08/2025

በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ በአዲስ ኢኒሼቲቭ የተጀመረው ንቅናቄ ለማሳካት ወሳኝ ሚና ያለው ስራ በጉግሶ ቀበሌ በአርሶ አደር አብደላ ኢብራሂም የለማ የነጭ ሽንኩርት ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ አሁናዊ ገፅታ በፎቶ

ነሃሴ 25/2017 ዓም (አልቾ ኮሙኒኬሽን)

 !በስልጤ ዞን በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተከታታይ ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአመራሮች የውይይትና የስልጠና መድረክ ተጠናቀቀ። ነሃሴ፣25/2017(አልቾ  ኮሙኒኬሽን )    ...
31/08/2025

!

በስልጤ ዞን በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተከታታይ ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአመራሮች የውይይትና የስልጠና መድረክ ተጠናቀቀ።

ነሃሴ፣25/2017(አልቾ ኮሙኒኬሽን )

በመድረኩም ላይ ባለፉት ሰባት አመታት በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ስኬቶችን ይበልጥ ለማስቀጠል ፣ ጉድለቶችን በማረም እንደ ሀገር የጀመርነውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ ማሳካት በሚያስችሉ ሀሳቦች ላይ በመወያየት በላቀ ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት ለመፈፀም የጋራ መግባባት መፍጠር ተችሏል።

ባለፋት የለውጥ ዓመታት የገጠሙንን ፈተናዎች ወደ ድል በመቀየር የነበሩ ሀገራዊ ስብራቶቻችንን መጠገን የሚያስችል ሁለንተናዊ ስኬቶችን ማስመዝገብ መቻሉን በውይይቱ ተነስተዋል።

በዞናችን የብልጽግና ተምሳሌት ፣የተሞክሮ መቀመርያ ማዕከልና የሰላም ሰገነት ለማድረግ በተሰጠው ቁርጠኛ አመራር መላ ህዝቡን በተደራጀ አግባብ በማሳተፍ አመርቂ ስኬቶችን ማስመዝገብ እንደተቻለም በመድረኮቹ ተገልፀዋል።

ጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ፣ የመንግስት የማስፈፀም አቅም በማጎልበት ለጠንካራ ሀገር ግንባታ ወሳኝ መሆኑ ታምኖበት በተሰራው ሥራ ሀገራችን የጀመረችው የከፍታ ጉዞ ወደ ማንሰራራት የሚያደርሱ በርካታ ተምሳሌታዊ ስኬቶችን ማስመዝገብ ችለናል።

የተደረገው ውይይት ፓርቲያችን የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልጽግና እውን ለማድረግ የሰነቀውን ዓላማ እውን ለማድረግ በአመራሩ ዘንድ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት የፈጠረ መሆኑ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።

በዞኑ በሁሉም መዋቅር የሚገኘው አመራር ወቅታዊ ሀገራዊ ፣አህጉራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች በመረዳት የፓርቲያችንን ተልዕኮ በተቀናጀ መልኩ በብቃት ለመፈፀም አቅም እንደሚሆን በአመራሮቹ ተነስቷል::

በመጨረሻም ሁሉም አመራር የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰማራበት መስክ ሁሉ አርበኛ መሆን እንዳለበት የጋራ መግባባት በመፍጠር ውይይቱ ተጠናቋል።

መረጃው፦የስልጤ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ነው።

"የኩስመና ታሪክ ማብቂያ" ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የተደረገ የጉባ ላይ ወግ ነገ ሰኞ ነሐሴ 26 ፣ 2017 ከምሽቱ 2:30 ላይ ይጠብቁ።
31/08/2025

"የኩስመና ታሪክ ማብቂያ"
ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር የተደረገ የጉባ ላይ ወግ ነገ ሰኞ ነሐሴ 26 ፣ 2017 ከምሽቱ 2:30 ላይ ይጠብቁ።

ሰልጣኝ የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች ለሳዳት ጀማል 47 ሺ ብር ድጋፍ አደረጉ፡፡በአልቾ ውሪሮ ወረዳ በአልቾ ወረዳ  "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል  እየሰለጠኑ የሚገኙት ...
31/08/2025

ሰልጣኝ የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች ለሳዳት ጀማል 47 ሺ ብር ድጋፍ አደረጉ፡፡

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ በአልቾ ወረዳ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል እየሰለጠኑ የሚገኙት የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች ለሳዳት ጀማል ለህክም የሚሆን ገንዘብ 47 ሺ ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ቃዋቆቶ ነሃሴ 25/2017 አልቾ ኮሙኒኬሽን

በአልቾ ወረዳ  ሶስተኛ ቀኑን የያዘው "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል  የተጀመረው ሀገራዊ የወረዳ እና የቀበሌ የአመራር ስልጠና መድረክ ዛሬም  እንደቀጠለ ነው!ነሐሴ 25/...
31/08/2025

በአልቾ ወረዳ ሶስተኛ ቀኑን የያዘው "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ሀገራዊ የወረዳ እና የቀበሌ የአመራር ስልጠና መድረክ ዛሬም እንደቀጠለ ነው!

ነሐሴ 25/2017 (አልቾ ኮሙኒኬሽን )

ሰልጣኝ አመራሮች በሶስት ቡድን በመሆን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ በወረዳው እየተከናወኑ የሚገኙ የግብርና ስራዎችን ምልከታ አደረጉቃዋቆቶ ነሃሴ 24/2017 አልቾ ኮሙኒኬሽንየስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ...
30/08/2025

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ በወረዳው እየተከናወኑ የሚገኙ የግብርና ስራዎችን ምልከታ አደረጉ

ቃዋቆቶ ነሃሴ 24/2017 አልቾ ኮሙኒኬሽን

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል የስልጤ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ ወ/ሮ ነይማ ሙኒር እንዲሁም የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን እና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ የወረዳው ደጋፊ የስልጤ ዞን ውኃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጨፋ ከድር በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ኤዶ አንድ ቀበሌ የለማ የካሮት ምርት እንዲሁም ባህርዛፍን በማንሳት እየለማ የሚገኘውን የመንገድ ዳር ፍራፍሬን ምልከታ አድርገዋል፡፡

በወረዳው የተጀመረው የካሮት ምርትን ተሞክሮ በመስራት የማስፋፋት ስራ በመስራት አርሶ አደሮችን የበለጠ ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባም አቶ ዘይኔ ገልጸዋል፡፡

ባህርዛፍን በማንሳት በመንገድ ዳር የተጀመረውን የፍራፍሬ እና የቅመማ ቅመም ልማትን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ተግባሩን በሁሉም ቀበሌዎች አስፍቶ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ

‎በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338

‎በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/

‎በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk

‎በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication

‎በቲክቶክ
http://www.tiktok.com/

‎ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/Alichocomm25.



Address

Silte
Werabe
KAWAKOTO

Opening Hours

Monday 07:00 - 19:00
Tuesday 07:00 - 19:00
Wednesday 07:00 - 19:00
Thursday 07:00 - 19:00
Friday 07:00 - 17:00
Saturday 07:00 - 17:00
Sunday 07:00 - 19:00

Telephone

+251924711807

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።:

Share