Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

  • Home
  • Ethiopia
  • Werabe
  • Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ  መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። ይህ ፔጅ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 118 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎች በንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የስልጤ ዞን ውሃ ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ገለፀመምሪያው ይህንንም የገለፀው ዛሬ በወራቤ ...
19/10/2025

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 118 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎች በንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የስልጤ ዞን ውሃ ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ገለፀ

መምሪያው ይህንንም የገለፀው ዛሬ በወራቤ ከተማ ዓመታዊ ሴክቶሪያል ጉባኤ እያካሄደ በሚገኝበት ወቅት ላይ ነው፡፡

ጥቅምት09/2018 ፣አልቾ ኮሙኒኬሽን

የስልጤ ዞን ውሃ ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ የ2017 ዓመታዊ ሴክቶሪያል ጉባኤ በወራቤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡

በጉባኤው ላይ የእንኳን ደህና መጣቹሁ ንግግር ያደረጉት የስልጤ ዞን ውሃ ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ዋና ኃላፊ አቶ ጨፋ ከድር እንደገለጹት የንፀህ መጠጥ ውሃ ሽፋንና ተደራሽነት ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል፡፡

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 118 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎች በንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ ማድረግ ችለናል ብለዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙበራ ከማል ፣የዞኑ ፕላን ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በድሩ ሱሩርን ጨምሮ የወረዳና ከተማ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪዎችና ምክትል ከንቲባዎች ፣የውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ፅ/ቤት ኃለላፊዎች ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ጥቅምት ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 ዓመታዊ ጉባኤ እየተካሄደ ነው!ጥቅምት 9/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ " በባለቤትነት ላይ የተመሰረተ እውቅና ተጠያቂነት ለጠንካራ የ...
19/10/2025

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 ዓመታዊ ጉባኤ እየተካሄደ ነው!

ጥቅምት 9/2018 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ " በባለቤትነት ላይ የተመሰረተ እውቅና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ" በሚል መሪ ሀሳብ የ2017 ዓመታዊ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።

በጉባኤው ላይ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ዘይኔ ቢልካ፣ የስልጤ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ ነዒማ ሙኒር፣ የስልጤ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ መህዲያ ቡሴር፣ የዞን አስተባባሪ አካላት፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የአስተዳደርና ፋይናንስ ዘርፍ ሀላፊ አቶ መሐመድ ዓሚን በደዊ፣ የአስሩ ወረዳዎችና የአምስቱ ከተማ አስተዳደር የጤና ሴክተር ማኔጅመንት፣ የየመዋቅሩ አስተዳዳሪዎችና ከንቲባዎች እንዲሁም የመንግስት ዋና ተጠሪዎች እና የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ሴክተር ሀላፊዎች፣ የጤና ጣቢያ ሀላፊዎች፣ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች፣ የእምነት አባቶች የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል።
የስልጤ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን!

ከፍጆታ አልፎ ለማዕከላዊ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አርሶ አደሩ  ተጠቃሚ እየሆነ ነው- አቶ ሙበራ ከማል
18/10/2025

ከፍጆታ አልፎ ለማዕከላዊ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እየሆነ ነው- አቶ ሙበራ ከማል

አርሰናል ፉልሀምን 1 ለ 0 አሸነፈ***********በ8ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በለንደን ደርቢ ከሜዳው ውጭ ከፉልሀም የተጫወተው አርሰናል ወሳኝ ሦስት ነጥብ አግኝቷል፡፡በክራቨን ...
18/10/2025

አርሰናል ፉልሀምን 1 ለ 0 አሸነፈ
***********
በ8ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በለንደን ደርቢ ከሜዳው ውጭ ከፉልሀም የተጫወተው አርሰናል ወሳኝ ሦስት ነጥብ አግኝቷል፡፡

በክራቨን ኮቴጅ በተደረገው ጨዋታ ሌአንድሮ ትሮሳርድ ብቸኛዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡

6ኛ ድላቸውን ያስመዘገቡት መድፈኞቹ ሊጉን በ19 ነጥብ እየመሩም ይገኛሉ፡፡

ግብ ጠባቂው ዴቪድ ራያ በሊጉ ለ5ኛ ጊዜ ግብ ሳይቆጠርበት የወጣ ሲሆን ተከላካዩ ጋብርኤል ማጋሌሽ በአርሰናል መለያ 20 ግቦች ላይ ተሳትፎ አድርጓል፡፡

18/10/2025

የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ በአልቾ ውሪሮ ወረዳ በካሄደው የ2017 አመታዊ ማጠቃለያ መርሀ-ግብር በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች የተደረገ የመስክ ምልከታ በፎቶ

በተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ ላይ ርብርብ በማድረግ የዞኑን ህዝብ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል፦የስልጤ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ
18/10/2025

በተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ ላይ ርብርብ በማድረግ የዞኑን ህዝብ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል፦የስልጤ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ

‎በቀጣይ በዞኑ ለግብርናው ዘርፍ ያሉ ምቹ አቅሞችን ለይቶ በማልማት በዘርፉ ስፔሻላዝድ ያደረጉ መዋቅሮችን ለመፍጠር በልዩ ትኩረት ይሰራል _አቶ ዘይኔ ቢልካ!‎‎በስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የ...
18/10/2025

‎በቀጣይ በዞኑ ለግብርናው ዘርፍ ያሉ ምቹ አቅሞችን ለይቶ በማልማት በዘርፉ ስፔሻላዝድ ያደረጉ መዋቅሮችን ለመፍጠር በልዩ ትኩረት ይሰራል _አቶ ዘይኔ ቢልካ!

‎በስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ማጠቃለያና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ዝግጅት አመታዊ ጉባኤ በቃዋ ቆቶ ከተማ ተካሂዷል።

‎በጉባኤው ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ በ2018 የምርት ዘመን በዞኑ የሚገኙ መዋቅሮች ለግብርናው ልማት ያለቸውን አቅም በመለያት በዘርፉ በተሻለ ጥራትና ብዛት እንዲያመርቱ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

‎በጉባኤው የተለዩ ጉድለቶችን ፈጥኖ በማረምና ጥንካሬዎችን ይበልጥ በማስፋት በቀጣይ በየዘርፉ የተጀመሩ የግብርና ልማት ስራዎች ዕውን መሆን በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት በዘርፉ የተቀናጀና የተደራጀ ስራ ሊሰሩ እንደሚገባም ዋና አስተዳዳሩው አሳስበዋል።

እንኳን ደስ አለሽ/አለን!!ሀበይ ተስ ባለሽ!!ጠንክረን ከሰራን ከድህነት መላቀቅ እንደሚቻል ሰርታ ያሳየችው ሴት ሞዴል አርሶ አደር ፈዲላ ከማል ተሸላሚ ሆነች!!በዛሬው ዕለት በተካሄደው የስል...
18/10/2025

እንኳን ደስ አለሽ/አለን!!
ሀበይ ተስ ባለሽ!!

ጠንክረን ከሰራን ከድህነት መላቀቅ እንደሚቻል ሰርታ ያሳየችው ሴት ሞዴል አርሶ አደር ፈዲላ ከማል ተሸላሚ ሆነች!!

በዛሬው ዕለት በተካሄደው የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ ላይ ባካሄደው የ2017 አፈፃፀምና ማጠቃለያ ጉባኤ መድረክ ወ/ሮ ፈዲላ ከማል በተቀናጀ የግብርና ስራዎች ባደረጉት ጥረት የዕውቅና ሰርተፊኬትና ዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በድጋሚ እንኳን ደስ አለሽ/አለን!!

እንኳን ደስ አላችሁ /አለን!!!ሀበይ ተስ ባለሙ!!የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ  በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ ባካሄደው የ2017 በጀት አመታዊ ጉባኤ  የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የአል...
18/10/2025

እንኳን ደስ አላችሁ /አለን!!!
ሀበይ ተስ ባለሙ!!

የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ ባካሄደው የ2017 በጀት አመታዊ ጉባኤ የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አንደኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫና ሰርተፊኬት ተሸላሚ መሆን ችሏል።

ጥቅምት 8/2018 አልቾ ከሙኒኬሽን

በዛሬው ዕለት የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ ባካሄደው የ2017 በጀት አመታዊ ጉባኤ የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አንደኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫ ና ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል።

ለተመዘገበው ውጤት የድርሻችሁን አስተዋጽኦ ለበረከታችሁ አካላት በሙሉ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ።

ሁሉም አርሶ አደር የሚሸጠው ምርት ሊኖረው ይገባል፦ አቶ ዘይኔ ቢልካ !በመድረኩ ማጠቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ሁሉም አርሶ አደር ከምግብ ፍጆታ...
18/10/2025

ሁሉም አርሶ አደር የሚሸጠው ምርት ሊኖረው ይገባል፦ አቶ ዘይኔ ቢልካ !

በመድረኩ ማጠቃለያ መልዕክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ሁሉም አርሶ አደር ከምግብ ፍጆታው በተጨማሪ የሚሸጠው ምርት ሊኖረው ይገባል ሲሉ ተናግረዋል ።

አዳዲስ የግብርና ኢንሼቲቮችን ተግባራዊ ማድረግ የቤተሰብ የስነ-ምግብ ጉድለትን የሚሞላ መሆኑንም አቶ ዘይኔ ተናግረዋል ።

የወጪ ምርትን ለመተካት፣ ለፋብሪካ ግብዓት የሚሆኑ ተፈላጊ ምርቶችን በማምረት የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

በሁሉም አካባቢ ቦታውን የሚያስጠራ ብራንድ የሆነ ምርት በጥናት ተመስርቶ መስራት እንደሚያስፈልግም አቶ ዘይኔ ገልፀዋል ።

አርሶ አደሩ በየአካባቢው በክላስተር ሲያለማ አካባቢው የተለያዩ መሠረተ ልማቶችን እንዲያገኝ እድል እንደሚፈጥርም አቶ ዘይኔ ገልፀዋል ።

በየቦታው ያሉ የግብርና መልካም ተሞክሮዎች ፈጥኖ ማስፋት ያስፈልጋል ያሉት አቶ ዘይኔ ከአርሶ አደር፣ ወደ የልማት ቡድን እና ቀበሌ መሸጋገር አለበት ብለዋል።

አምራች አርሶ አደሮችን እንደየምርታቸው በህብረት ስራ ማህበራት በማደራጀት የገበያ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በየደረጃው መሰራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

ለዚህ ደግሞ ሁሉም ባለድርሻ ተቋማት በየመዋቅራቸው ተቀራርበው እና ተቀናጅተው መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።

በሰርቶ ማሳያ ጣቢያዎች የተሞከሩ የተለያዩ ሰብሎች ወደ አርሶ አደሮች ማሳ መሸጋገር አለበት ብለዋል።

የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ዝግጅት አመታዊ ጉባኤ በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ እያካሄደ ነው። ጉባኤውን በንግግር ያስ...
18/10/2025

የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ዝግጅት አመታዊ ጉባኤ በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ እያካሄደ ነው።

ጉባኤውን በንግግር ያስጀመሩት የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙበራ ከማል ከፍጆታ አልፎ ለማዕከላዊ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እየሆነ ይገኛል ብለዋል።

በ2017 በጀት ዓመት የዞኑን አርሶ ደሮች ተጠቃሚ ለማረግ ሰፊ ርብርብ መደረጉንም አቶ ሙበራ ገልፀዋል ።

በነበረው ሂደትም አበረታች ለውጦች መመዝገባቸውን የገለፁት አቶ ሙበራ በበልግና በመኸር የተሰራው የግብርና ልማት ይህንኑ የሚያረጋግጥ መሆኑንም ተናግረዋል ።

ከፍጆታ አልፎ ለማዕከላዊ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የተለያዩ አዳዲስ ምርቶችን በማምረት አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እየሆነ እንደሚገኝም አቶ ሙበራ ገልፀዋል ።

በዞኑ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞችንና ቡና በማምረት ለውጭ ገበያ በማቅረብ 12.2 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማስገኘቱን እና አርሶ አደሮችንም ተጠቃሚ ማድረጉን አቶ ሙበራ ተናግረዋል።

በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን የወረዳው አግሮ ኢኮሎጂ ለተለያዩ የግብርና ልማት ስራዎች ምቹ መሆኑን ገልፀዋል።

የወረዳው አርሶ አደሮችም የአካባቢውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው የተለያዩ የግብርና ምርቶቹ በማምረት ለገበያ እያቀረበ መሆኑንም አንስተዋል።

በተለይም የሚወርዱ አዳዲስ የግብርና ኢንሼቲቮችን ተቀብሎ ስራ ላይ በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በ2017 በጀት አመት እንደ ወረዳ የነጭ ሽንኩርት፣ ባቄላ እና ካሮት ልማት በልዩ ትኩረት መሰራቱን የገለፁት ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን ምርቱንም እስከ ማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ መቻሉንም አብራርተዋል።

ጉባኤው "የተቀናጀ የግብርና ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በ ይገኛል።

‎በስልጤ ዞን በ2017 በጀት አመት በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ዋና ዋና የግብርና ልማት ስራዎች የፎቶ አውደ ርዕይ ተካሄደ።‎‎በአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋ...
18/10/2025

‎በስልጤ ዞን በ2017 በጀት አመት በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ዋና ዋና የግብርና ልማት ስራዎች የፎቶ አውደ ርዕይ ተካሄደ።

‎በአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ቃዋ ቆቶ ከተማ በተካሄደው የፎቶ አውደ ርዕይ መርሃ-ግብር ላይ የዞኑ አስተባባር አካላትን ጨምሮ ሌሎች የዞንና የወረዳ የስራ ሀላፊዎች፣የግብርና ጽ/ቤት ሀላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎችና ሞዴል አርሶ ኣደሮች የተገኙ ሲሆን በዞኑ በሚገኙ መዋቅሮች በ2017 የምርት ዘመን በግብርናው ዘርፍ የተከናወኑ ዋና ዋና ስራዎችን ተዛዙረው ተመልክተዋል።


Address

Silte
Werabe
KAWAKOTO

Opening Hours

Monday 07:00 - 19:00
Tuesday 07:00 - 19:00
Wednesday 07:00 - 19:00
Thursday 07:00 - 19:00
Friday 07:00 - 17:00
Saturday 07:00 - 17:00
Sunday 07:00 - 19:00

Telephone

+251924711807

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።:

Share