19/10/2025
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 118 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎች በንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የስልጤ ዞን ውሃ ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ገለፀ
መምሪያው ይህንንም የገለፀው ዛሬ በወራቤ ከተማ ዓመታዊ ሴክቶሪያል ጉባኤ እያካሄደ በሚገኝበት ወቅት ላይ ነው፡፡
ጥቅምት09/2018 ፣አልቾ ኮሙኒኬሽን
የስልጤ ዞን ውሃ ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ የ2017 ዓመታዊ ሴክቶሪያል ጉባኤ በወራቤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡
በጉባኤው ላይ የእንኳን ደህና መጣቹሁ ንግግር ያደረጉት የስልጤ ዞን ውሃ ፣ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ዋና ኃላፊ አቶ ጨፋ ከድር እንደገለጹት የንፀህ መጠጥ ውሃ ሽፋንና ተደራሽነት ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 118 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎች በንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ ማድረግ ችለናል ብለዋል፡፡
በመድረኩ ላይ የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙበራ ከማል ፣የዞኑ ፕላን ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በድሩ ሱሩርን ጨምሮ የወረዳና ከተማ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪዎችና ምክትል ከንቲባዎች ፣የውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ፅ/ቤት ኃለላፊዎች ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ጥቅምት ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን