
01/09/2025
የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ሂደት የአ/አደር ማሰልጠኛ ተቋማትን የአዳዲስ የቅመማ ቅመም ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
ቃዋቆቶ ነሐሴ 26/2017{ አልቾ ኮሙኒኬሽን}
በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ወዚር 1 ቀበሌ የሚገኘው የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰንና የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ምልከታ አድርገዋል።
በወረዳው የሚገኙ የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከሎችን በሁሉም ዘርፍ ሞዴል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ የገለፁት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን በወዚር-1 ቀበሌ የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከል እየለሙ ያሉ የቅመማ ቅመም ስራዎች በአርሶ አደሮችም በመስፋት የአርሶ አደሩን የገቢ አማራጮችን ለማሳደግ በትኩረት መሰረት አለበት ብለዋል ።
የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ ሙዘይን መሀመድ በበኩላቸው አከባቢው ለቅመማ ቅመም ምርት ምቹ እንደሆነ አንስተው የአረሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከሎች ሞዴል በመሆን በዘርፉ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ መስራት እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
በእለቱ በወዚር -1ቀበሌ የሮዝመሪን፣ የላቤንደርና የኮሰረት ስራን ምልከታ ማድረግ ተችሏል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘትከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ
በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338
በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/
፦
በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk
በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication
በቲክቶክ https://vm.tiktok.com/ZM6BRmsNa/
ኢንስታግራም https://www.instagram.com/p/C1Za_1HtXH1/?igsh=YWYwM2I1ZDdmOQ==