
02/07/2025
አመራሩ ጠንካራ ተቋማዊ የአመራር ስርኣትን ተከትሎ ተጨባጭ ውጤትን ማስመዝገብ ይጠበቅበታል- ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)
ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፓርቲ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።
በየደረጃው ያለ አመራር ጠንካራ ተቋማዊ የአመራር ስርኣትን ተከትሎ ተጨባጭ ውጤትን በማስመዝገብ የህዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አለበት ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) ተናግረዋል ።
ላለፉት ሶስት ቀናት በሆሳዕና ከተማ ሲሰጥ የነበረው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፓርቲ አመራሮች ስልጠና ተጠናቋል።
ዶክተር ዲላሞ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ እንዳሉት ተቋማዊ አሰራርንና ውጤታማነትን ያጣመረ የአመራር ስርኣት ለመፍጠር እየተሰራ ይገኛል። ከዚህ መነሻ ሁሉም አመራር የአመራር መርህን ተከትሎ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ ውጤት ሊያስመዘግብ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የዳበረ የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ መጎልበት እንዳለበት የገለጹት ዶ/ር ዲላሞ ለዚህ ስኬት የአሰራር ግልጸኝነትና አሳታፊነት ቁልፍ ሚና አላቸው ሲሉም አክለዋል። አመራሩ ችግር ፈቺና ተጠያቂነትን የተላበሰ መሆን እንደሚኖርበትም አስረድተዋል ።
በየደረጃው ያለው አመራር የፖሊሲና የፓርቲ እሳቤዎችን በተግባርም በሀሳብም አስርጾ ውህደትና አንድነት መፍጠር አለበት ሲሉም ተናግረዋል ።
በቀጣዩ በጀት አመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በተለይም ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ከወዲሁ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት መደረግ እንዳለበትም አሳስበዋል ።
Ethiopia Government Communication Affairs