Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

  • Home
  • Ethiopia
  • Werabe
  • Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ  መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። ይህ ፔጅ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

አመራሩ ጠንካራ ተቋማዊ የአመራር ስርኣትን ተከትሎ ተጨባጭ ውጤትን ማስመዝገብ ይጠበቅበታል- ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፓርቲ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።...
02/07/2025

አመራሩ ጠንካራ ተቋማዊ የአመራር ስርኣትን ተከትሎ ተጨባጭ ውጤትን ማስመዝገብ ይጠበቅበታል- ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)

ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፓርቲ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።

በየደረጃው ያለ አመራር ጠንካራ ተቋማዊ የአመራር ስርኣትን ተከትሎ ተጨባጭ ውጤትን በማስመዝገብ የህዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አለበት ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) ተናግረዋል ።

ላለፉት ሶስት ቀናት በሆሳዕና ከተማ ሲሰጥ የነበረው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፓርቲ አመራሮች ስልጠና ተጠናቋል።

ዶክተር ዲላሞ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ እንዳሉት ተቋማዊ አሰራርንና ውጤታማነትን ያጣመረ የአመራር ስርኣት ለመፍጠር እየተሰራ ይገኛል። ከዚህ መነሻ ሁሉም አመራር የአመራር መርህን ተከትሎ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ ውጤት ሊያስመዘግብ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የዳበረ የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ መጎልበት እንዳለበት የገለጹት ዶ/ር ዲላሞ ለዚህ ስኬት የአሰራር ግልጸኝነትና አሳታፊነት ቁልፍ ሚና አላቸው ሲሉም አክለዋል። አመራሩ ችግር ፈቺና ተጠያቂነትን የተላበሰ መሆን እንደሚኖርበትም አስረድተዋል ።

በየደረጃው ያለው አመራር የፖሊሲና የፓርቲ እሳቤዎችን በተግባርም በሀሳብም አስርጾ ውህደትና አንድነት መፍጠር አለበት ሲሉም ተናግረዋል ።

በቀጣዩ በጀት አመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በተለይም ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ከወዲሁ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት መደረግ እንዳለበትም አሳስበዋል ።

Ethiopia Government Communication Affairs

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ነገ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ ሰኔ 25፣ 2017 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም  በሕዝ...
02/07/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ነገ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ

ሰኔ 25፣ 2017 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሚሰጡ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምክር ቤቱ ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል፡፡(ኤም.ኤፍ.ሲ)

‎በስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ በአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ከተረጂነት መሸጋገሪያ ፕሮጀክት የአፈጻጸም ግምገማ  መድረክ በምስራቅ ስልጢ ወረዳ እየተካሄደ ነው==================...
02/07/2025

‎በስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ በአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ከተረጂነት መሸጋገሪያ ፕሮጀክት የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ በምስራቅ ስልጢ ወረዳ እየተካሄደ ነው
=================================
ሰኔ 25/2017 (አልቾ ኮሙኒኬሽን)‎ በዞኑ በዘላቂነት ከተረጂነት ለመላቀቅ 11 የተለያዩ የሴፍቲኔት ልማት ፕሮጀክቶች ተቀርፀው ሲከናወኑ ቆይቷል።

‎በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ ፕሮጀክቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ከማድረግ አንጻር ያሉበት ሂደት የመስክ ምልከታ መደረጉ ይታወቃል።

‎የከሰኣቱ ከተረጂነት መሸጋገሪያ ፕሮጀክት የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እና የስልጤ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት ወ/ሮ ወሲላ አሰፋ እየየመሩት ሲሆን የዞን፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር የስራ ሀላፊዎች እየተሳተፉበት ይገኛል።

‎በመረኩ ዞናዊ ከተረጂነት መሸጋገሪያ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት እየተደረገበት ነው በማለት የዘገበው የስዞመኮመ ነው።

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ  በሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት በማህበራዊ  ሚዲያ አጠቃቀምና በኢትዮ ኮደርስ ለወረደው ሴት ፐብሊክ ሰርቫንት አባለት ስልጠና ሰጠቃዋቆቶ: ሰኔ 25/10/20...
02/07/2025

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ በሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና በኢትዮ ኮደርስ ለወረደው ሴት ፐብሊክ ሰርቫንት አባለት ስልጠና ሰጠ

ቃዋቆቶ: ሰኔ 25/10/2017{አልቾ ኮሙኒኬሽን}

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ የሴቶች ክንፍ የፐብሊክ ሰርቫንት የሴት አባላት የ4ኛ ሩብ አመት ኮንፈረንስ አካሂዷል።

በመድረኩም በኢትዮ ኮደርስና በሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ከስልጠና በተጨማሪ የ2017 በጀት አመት በሴቶች ክንፍ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት በወረዳው ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ሃላፊ በወ/ሮ ፋጡማ ሸምሰዲን ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በወረዳው ሰይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽህፈት ቤት ባለሙያ በሆነው በአቶ ሰይፈዲን ሽፋ ተሰጥቷል።

በስልጠናው ላይ የሴቶች ተሳትፎ የጎለ ሚና ያለው በመሆኑ ሁሉም ሴት በኢትዮ ኮደርስ ተመዝግቦ ሰርቲፋይ መሆን እንደሚገበው በስልጠናው ላይ ተብራርተዋል።

የማህበራዊ ሚዲያ ለሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ሚና እንደለው ያነሱት የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ፋጡማ ሸምሰዲን ሴቶች በኢኮኖሚያዊ፣በማህበራዊ ፣በፖለቲካዊ እንቅስቀሴ የጎላ ሚና እንዳላቸው አንስተው በሁሉም ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

በበጀት አመቱ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ያነሱት የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሽቱ ከድር የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ሁሉም መውሰድ እንዳለበት አንስተው ስልጠናው ግልጽ እስኪሆንላችሁ ድረስ የሳይቴክ ባለሙያዎች ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ዋና አፈ-ጉባኤዋ አክለው የእርስ በርስ ግንኙነታችንን አጠናክረን በቻልነው አቅም የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸው እናቶችን ማገዝ አለብን ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በመድረኩ ሁሉም ሴቶች ዲጂቲል መታወቂያ እንዲወስዱ መልዕክት ተላልፏል።

በመጨረሻም የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች የጽዳት ዘመቻ በማድሰግ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

‎በስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ የተመራ የአመራሮች ቡድን በ2017 በስልጢና ምስራቅ ስልጢ ወረዳዎች  ከተረጂነት ማሸጋገሪያ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።‎‎በጉ...
02/07/2025

‎በስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ የተመራ የአመራሮች ቡድን በ2017 በስልጢና ምስራቅ ስልጢ ወረዳዎች ከተረጂነት ማሸጋገሪያ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።

‎በጉብኝቱ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣የማአከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮምሽን ኮሚሽነር ማረጉ ማቲዮስ፣ የስልጤ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ወሲላ አሰፋን ጨምሮ የተለያዩ የዞን፣የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

‎በዞኑ 12 ሺህ 298 የሴፍቲኔት ተረጂዎችን በዘላቂነት ከተረጂነት ለማላቀቅ ወደ አራት መቶ ሚሊዮን ብር ተመድቦ በዘላቂነት ከችግር እንዲላቀቁ የሶላር ፓም፣ጀነሬተር፣የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸው ላሞች፣ዶሮዎችን፣ገዝቶ የማቅረብ ስራዎች ተሰርተዋል።

‎ዛሬ በስልጢና ምስራቅ ስልጢ ወረዳዎች የዚሁ አካል የሆነው ተረጂዎች ከተረጂነት ለመላቀቅ በመስኖ ልማት፥በንብ ማነብ፣በአትክልትና ፍራፍሬ፣በእንሣት እርባታ፣በችግኝ ማፍላት፣በዶሮ እርባታና በተለያዩ የስራ መስኮች የተሰማሩ አካላት ተጎብኝተዋል።

‎የስልጢ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከድር እና የምስራቅ ስልጢ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሎ በወረዳቸው ተረጂዎችን ከተረጂነት በዘላቂነት ለማላቀቅ ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት አብራርተዋል።

‎ በመርሃ-ግብሩ ላይ በሰዳ በረንጎ ቀበሌ የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞች የመትከል ስነ-ስርኣት ተካሂዷል።

‎በጉብኝቱ የተገኙት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እና የማአከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮምሽን ኮሚሽነር አቶ ማረጉ ማቲዮስ በጋራ ባደረጉት ንግግር በሁለቱም ወረዳዎች የሴፍቲኔት ተረጂዎችን ከተረጂነት ለማላቀቅ የተሰሩ ስራዎች አበረታችና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን በመግለጽ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ መልእክት አስተላልፈዋል።ስዞመኮመ ዘግቦታል።

ለመላው የወረዳችን ግብር ከፋዮች በሙሉ በመጀመሪያ እንኳን ለ2017/18 ዓመታዊ የግብር መክፈያ ጊዜ  በሰላም  አደረሳችሁ እያለበወረዳችን የ2017 ግብር ዘመን ዓመታዊ ግብር ከሃምሌ 1/20...
01/07/2025

ለመላው የወረዳችን ግብር ከፋዮች በሙሉ

በመጀመሪያ እንኳን ለ2017/18 ዓመታዊ የግብር መክፈያ ጊዜ በሰላም አደረሳችሁ እያለ

በወረዳችን የ2017 ግብር ዘመን ዓመታዊ ግብር ከሃምሌ 1/2017 ጀምሮ በሁሉም የማዘጋጃ ቤት ከተማዎችና ሌሎች በየ ቀበሌው በሚገኙ የንግድ ማዕከላት በይፋ ይጀመራል።

ግብር የዜጎችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ለማሟላትና የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ የሚያግዝ ቁልፍ መሳሪያ ነው።

ይህ እቅድ ውጤት እንዲያመጣ በአካባቢው የሚመነጨው ገቢ በተገቢው አሟጦ መሰብሰብ ሲችል ብቻ ነው።

በወረዳችን በሁሉም አከባቢዎች በሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውስጥ ከግብር የሚገኘው ገቢ የራሱ ወሳኝ ድርሻ አለው።

ስለሆነም የወረዳችን የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ማለትም የንግድ ትርፍ ግብር, የአከራይ ተከራይ ግብር, የተሽከርካሪ ቁርጥ ግብር, እንዲሁም የማዘጋጃ ቤታዊ ሁሉም አይነት አመታዊ ክፍያዎች ከሀምሌ 1/2017 ጀምሮ አመታዊ ግብር መሰብሰብ ይጀምራል።

በመሆኑም በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ፍቃድ እንዲሁም የንግድ ማስፋፊያ ወስዳቹህ የንግድ እንቅስቃሴ የምታደርጉ ግብር ከፋዮቻችን ከሐምሌ 1/2017ዓ.ም ጀምሮ በተመረጡ አምስት ማዕከሎችን በሚቀርባቹ ማዕከል በመቅረብ ግብራቹሁን እና ሌሎች ማዘጋጃ ቤታዊ ክፍያዎችን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ በመክፈል የዜግነት ግዴታችሁን እንድትወጡ ስንል ለመላው የወረዳችን የንግዱ ማህበረሰብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

የተመረጡት የግብር ማስከፈያ ማዕከላት ቃወቆቶ ኩተሬ ጠረጋ ጣንዤ እንዲሁም ዳምዛገር ከተሞች ለይ በአካል በመገኘት ግብራቹሁን መክፈል ትችላላቹህ።

መላው የወረዳችን ነዋሪዎች የ''ሐ'' ግብር በአጭር ቀናት ለማጠናቀቅ እንዲሁም በመጨረሻ ከሚፈጠር መጨናነቅ እና አላስፈላጊ ቅጣት ለመዳን በጊዜ በመገኘት ግብራችሁን በታማኝነት እንድትከፍሉ ዲከፈል የወትሮው ሲል የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ገቢዎች ቅርጫፍ ጽ/ቤት ጥሪውን ያቀርባል።

‎ በወረዳው በኢንቨስትመንት የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ‎‎(ቃዋቆቶ ሰኔ 24/2017 አልቾ ኮሙኒኬ...
01/07/2025

‎ በወረዳው በኢንቨስትመንት የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

‎(ቃዋቆቶ ሰኔ 24/2017 አልቾ ኮሙኒኬሽን)

‎በኢንቨስትመንት የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ከተማ ልማትና ቤቶች ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ገልጿል፡፡

‎ጽ/ቤቱ ከስልጤ ዞን ኢንቨስትመንት መምሪያ ከመጡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በቃዋቆቶ ከተማ በኢንቨስትመንት የተላለፋ ፕሮጀክቶችን ተዟዙረው ምልከታ አድርገዋል፡፡

‎የመስክ ምልከታው በዋናነት በወረዳው በኢንቨስትመንት የተላለፋ ፕሮጀክቶችን ምልከታ በማድረግ በአጠረ ጊዜ ማጠናቀቅ እና የተጠናቀቁትን ደግሞ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያግዝ መሆኑም ተገልጿል፡፡

‎የመምሪያው ባለሞያዎች በመስክ ምልከታው ወቅት ባለፋት አመታት ለኢንቨስትመንት ተላልፈው ወደስራ ሳይገቡ ተጓተው የነበሩ ፕሮጀክቶችን ወደስራ ለማስገባት የተኬደበት ሂደትና ፕሮጀክቶች ያመጡት ለውጥ በጥንካሬ አንስተዋል።

‎በመስክ ምልከታው በሆቴል በገበያ ማእከል እና በነዳጅ ማደያ እየተሰሩ የሚገኙ ኢንቨስትመንቶችን ምልከታ ተደርጎባቸዋል፡፡

‎በምልከታው የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽ ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ጃቢር ኑሪ የቃዋቆቶ ማዘጋጃ ስራ አስኪያጅ መሀመድ አብዱልሰመድ የስልጤ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ባለሙያዎች እንዲሁም የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ ነጃ ጃቢርን ጨምሮ የማኔጅመንት አካላት ተገኝተዋል ፡፡

‎ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘትከስር ያሉትን ሊንኮች ይንኩ
‎በፌስ ቡክ=https://www.facebook.com/profile.php?id=100064217195338

‎በዩቲዩብ= https://www.youtube.com/

‎በቴሌግራም =https://t.me/+fLx2gB554XkyYTJk

‎በድረ ገጽ http://www.google.com/AlichoCommunication

‎በቲክቶክ https://vm.tiktok.com/ZM6BRmsNa/

‎ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/Alichocomm25.

በክልሉ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ለ1ነጥብ 2 ሚሊየን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር እየተሰራ ነው :-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር ) ( ሰኔ 24/2017)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
01/07/2025

በክልሉ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት ለ1ነጥብ 2 ሚሊየን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር እየተሰራ ነው :-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር )

( ሰኔ 24/2017)
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሞዴል ኢንተርፕራይዞች እውቅና ፣ደረጃ ሽግግር እና የማትጊያ መርሐ ግብር በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በመድረኩ ማጠቃለያ በሰጡት የስራ መመሪያ እንደገለጹት በቀጣይ ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ ከ9 ነጥብ 15 ሚሊየን በላይ ለሆኑ ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዷል።

በክልሉ በ2017፣በ2018 እንዲሁም በ2019 በጀት ዓመትለ1ነጥብ 2 ሚሊየን ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጠር ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።

ሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከምትመሰርትባቸው አበይት የትኩረት መስኮች ውስጥ ግብርና፣ማኑፋክቸሪንግ፣ቱሪዝም፣የማዕድን ዘርፍ እንዲሁም ዲጂታል ኢትዮጵያን መፍጠር ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

በክልሉ እውቅና የተሰጣቸው ሞዴል ኢንተርፕራይዞች በዘርፉ የጀመሩትን ሁሉን አቀፍ ጥረት በማሳደግ ከመንግስት የሚደረግላቸውን ድጋፍ በተገቢው መንገድ በመጠቀም ጠንክረው መስራት እንዳለባቸውም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

በክልሉ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ሚናቸውን እንዲወጡም ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያን በቤተሰብ ፣በማህበረሰብ ብሎም በሀገር ደረጃ ለማበልጸግ የኢንተር ፕራይዞች ሚና ከፍተኛ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው አመላክተዋል።

ለዘርፉ እድገት ከመንግስት የሚደረገውን ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ርዕሰ መስተዳድሩ በስራ መመሪያቸው አብራርተዋል።

በመድረኩ በክልሉ የሞዴልነት መስፈርት ላሟሉ ለ100 ኢንተርፕራይዞች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን 147 ኢንተር ፕራይዞች ደግሞ የደረጃ ሽግግር አድርገዋል።
ሲል የዘገበው የክልሉ ኮሙኒኬሽን ነው

የFSRP ፕሮግራም የ2017 የስራ እንቅስቃሴና የቀጣይ በጀት አመት ጠቋሚ እቅድ እየተገመገመ ነው!ሰኔ 24/2017 በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም...
01/07/2025

የFSRP ፕሮግራም የ2017 የስራ እንቅስቃሴና የቀጣይ በጀት አመት ጠቋሚ እቅድ እየተገመገመ ነው!

ሰኔ 24/2017
በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የክልል አብይ ኮሚቴ ሀላባ ቁሊቶ ላይ እየመከረ ይገኛል።

ግብርናን ለማዘመን በሚሰሩ ስራዎች ፕሮግራሞች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ተናግረዋል።

በክልሉ ግብርና ቢሮ የተቀረፁ 6ቱ የግብርና ሴክተር ምሶሶዎችን ለማሳካት የ FSRP ፕሮግራም ሚና ከፍተኛ መሆኑን ያነሱት አቶ ኡስማን የስትሪንግ ድጋፍና ክትትል እያደረጉ ለሚገኙ ስትሪንግ ኮሚቴ አባለት ምስጋና አቅርበዋል።

በክልሉ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ፕሮግራም ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያሉት አቶ ኡስማን በቀጣይም አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።

የፕሮግራሙ ማናጀር አቶ ከድር መሀመድ በፕሮግራሙ በግብርናው ዘርፉ ብዙ ኢንሼቲቮች ታቅደው ተግባራዊ እየሆኑ እንደሆነ አብራርተዋል።

ከ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በ 4 ዞኖችና በ 10 ወረዳዎች ላይ ፕሮግራሙ እየሰራ እንደሆነም ማናጀሩ ገልፀዋል።

FSRP ፕሮግራም ከግብርናው ሴክተር በተጨማሪ 23 ተቋማትን እንደሚደግፉ አብራርተዋል።

በበጀት አመቱ የተሰሩ ስራዎች ዝርዝር ሪፖርት ከቀረበ በኋለ ውይይት እንደሚካሄድ ይጠበቃል።

የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የክልል አብይ ኮሚቴ አባለት በምክክር መድረኩ ላይ እየተሳተፉ ነው።

ስልጤ ኤፍ ኤም

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የክንፍ አደረጃጀቶችን የ2017 ዓ.ም አፈጻጸም ግምገማና የ2018ዓ.ም ዕቅድ ግምገማ  ላይ የውይይት መድረክ  አካሄደ ።  ‌‎ሰኔ 23 /2017 ዓ.ም የ...
30/06/2025

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የክንፍ አደረጃጀቶችን የ2017 ዓ.ም አፈጻጸም ግምገማና የ2018ዓ.ም ዕቅድ ግምገማ ላይ የውይይት መድረክ አካሄደ ።

‌‎ሰኔ 23 /2017 ዓ.ም የአልቾ ኮሙኒኬሽን

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ የ2017 ዓ.ም አፈጻጸም ግምገማና የ2018ዓ.ም ዕቅድ ከስረ አስፈፃሚዎች ጋር የግምገማ መድረክ አካሄደዋል ።

መድረኩን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ በህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሁሴን ጀማል የመሩት ሲሆን ለመድረኩ የሚሆን ሪፖርትና ዕቅድ ያቀረቡት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ሀላፊ በአቶ ተውፊቅ በድሩና በወ/ሮ ፋጤ ሸምሰዲን ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል ።

በመድረኩ ላይ በበጀት አመቱ የነበሩ ጥንካሬዎችና ጉድለቶች በዝርዝር ተነስተው በጥልቀት ውይይት ተደርጎባቸው በቀረበው ሪፓርት መነሻነት ጥያቄና አስተያየት ከተሳታፊዎች ተሰጥቷል።

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ሀላፊ አቶ ተውፊቅ በድሩ በተሰጠው ጥያቄና አስተያየ መሰረት የገለጹት በወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀት ተግባራት ከወረዳ እስካ ቀበሌ ድረስ ከተቀየሩ የስም ስያሜዎች ጀምሮ ሌሎችንም ተግባራት ከዚህ በተሻለ ሁኔታ መፈጸም እንደሚገባም ገልጿል ።

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የዴሞክራሲ በህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሁሴን ጀማል እንደገለፁት፦ የሴቶችንና የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊ ፣ፖለቲከዊ ተጠቃሚነትና ተሳታፊነትን ለማረጋገጥ ሁሉም አደረጃጀቶች ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸውና በተለይም የወጣቶች ፌዴሬሽን ፣የወጣቶች ማህባር ፣ የወጣቶች ክንፍና የሴቶች ክንፍ ባላድርሻ አካላት በቅንጅት በመሰራት የወጣቶችን ስብዕና መገንባት ላይ በትኩረት መስረት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

በመጨረሻም በተግባር አፈፃፀም ላይ የታዩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል እንደሚገባ እና በተግባር አፈጻጸሙ ላይ በጉድለት የተመለከቱ ጉዳዮችን ለቀጣይ የዕቅድ አካል በመድረግ መታረም እንዳለባቸው የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መድረኩን አጠናቀዋል ።

መድረኩ ላይ የፓርቲ ኮማንድ ፖስት አካላትና ስረ አስፈጻሚ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል ።

በወረዳው የአቅም ውስንነት ያለባቸውን አካላት በመለየት ከ350 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ድጋፍ መደረጉ ተገለጸ(ቃዋቆቶ ሰኔ 23/2017 አልቾ ኮሙኒኬሽን)የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/...
30/06/2025

በወረዳው የአቅም ውስንነት ያለባቸውን አካላት በመለየት ከ350 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ድጋፍ መደረጉ ተገለጸ

(ቃዋቆቶ ሰኔ 23/2017 አልቾ ኮሙኒኬሽን)

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ከዘላቂ የመሬት አያያዝ (SLM) በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ከ350 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ሰማኒያ በጎችን ግዥ በመፈጸም ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል ፡፡

በድጋፉ ወቅት የተገኙት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን ድጋፉ አቅመ ደካሞች በዘላቂነት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚያግዝ አንስተዋል፡፡

ለተደረገላቸውን ድጋፍ አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ማሳደግ ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪዋ ተቋሙ የሚፈጽመውን ተግባር አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡

ፕሮግራሙ የአፈር ለምነትን ከመጠበቅ እና ዘላቂ የማይበገር አረንጓዴ ከመፍጠር ጎን ለጎን አቅመ ደካማ የሆኑ ግለሰቦች በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የእንስሳት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሻሚል የሱፍ ተናግረዋል፡፡

በድጋፉ ወቅት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የእንስሳት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሻሚል የሱፍ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሪት ከድጃ ኢብሮ ተገኝተው ድጋፉን አበርክተዋል ፡፡

የስልጤ ልማት ማህበር የ2017 ዓ.ም  የጉዞ ስልማ  ሁለት አረንጓዴ አሻራ ቅድመ ዝግጅት ሂደት ጎበኘ፡፡ የጉዞ ስልማ ሁለት የአረንጓዴ አሻራ  አዘጋጅ የሆነው አልቾ ውሪሮ ወረዳ  አስተዳደር...
29/06/2025

የስልጤ ልማት ማህበር የ2017 ዓ.ም የጉዞ ስልማ ሁለት አረንጓዴ አሻራ ቅድመ ዝግጅት ሂደት ጎበኘ፡፡

የጉዞ ስልማ ሁለት የአረንጓዴ አሻራ አዘጋጅ የሆነው አልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡

የስልጤ ልማት ማህበር ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ሸምሴ ኑሪ እንደገለፁት የስልጤ ልማት ማህበር ከተቋቋመበት ዘርፈ ብዙ ዓላማዎች አንዱ የሆነው የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ አንዱ መሆኑን አንስተው ልማት ማህበሩ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የአፈር ጥበቃና እእንክብካቤ ስራዎች ከልማት ማህበሩ አባላት ጋር በመሆን በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት ማምጣት ተችሏል፡፡

ስራ አስፈፃሚው አያይዘው የስልጤ ልማት ማህበር ይህን ተግባር ውጤታማ ለማድረግ በወረዳች የችግኝ ሳይትና የስልማ ፓርክ በመመስረት የአፈር ጥበቃና እእንክብካቤ ስራ ተግባራዊ ከማድረግ ባሻገር የስልማ የስራ አመራር ቦርድ ለተግባሩ ከተሰጠው ትኩረት በ10 ዓመቱ እስትራቴጂ ዕቅድ በማካተት ይበልጡንም ለማደራጀት በማለም ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የጉዞ ስልማ አረንጓዴ አሻራ አንድ በወራቤ ከተማ አስተዳደር የስልማ የስራ አመራር ቦርድ አመራሮች ፣ በተለያየ መዋቅር የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ የልማት ማህበሩ የቅርንጫፍ ፅ/ቤት አባላት በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በማከናወን የጉዞ ሁለት ለአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዕድል መሰጠቱን ተከትሎ በዛሬው ዕለት የቅድመ ዝግጅት ሂደትን መጎብኘት የተቻለ ሲሆን የቅድመ ዝግጅት ተግባር በጥሪ ሁኔታ እየተመራ መሆኑን መመልከት መቻላቸውን ገልፀዋል ፡፡

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን በበኩላቸው የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ ተግባር እንደወረዳ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተመራ መሆኑን በማንሳት የስልማ ጉዞ ሁለት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም አዘጋጅ እንደመሆናቸው መጠን የቅድመ ዝግጅት ማለትም የችግኝ ፣ የቦታ ልየታ ፣ የጉድጓድ ቁፋሮ ጨምሮ ኮሚቴ በማዋቀር የማጠናቀቅ ስራ እያከናወኑ መሆናቸውን ገልፀው የዘንድሮው የስልማ ጉዞ ሁለት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም በወረዳው ሽልማት ቀበሌ ላይ እንደሚከናወን ገልፀዋል ፡፡

Address

Silte
Werabe
KAWAKOTO

Opening Hours

Monday 07:00 - 19:00
Tuesday 07:00 - 19:00
Wednesday 07:00 - 19:00
Thursday 07:00 - 19:00
Friday 07:00 - 17:00
Saturday 07:00 - 17:00
Sunday 07:00 - 19:00

Telephone

+251924711807

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።:

Share