Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

  • Home
  • Ethiopia
  • Werabe
  • Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።

Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ  መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። ይህ ፔጅ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የወጣቶችን ስራ አጥነት በመቀነስ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ቃዋቆቶ ህዳር 26/2018  አልቾ ኮሙኒኬሽንበአልቾ ውሪሮ ወረዳ የወጣቶችን ስራ አጥነ...
05/12/2025

የወጣቶችን ስራ አጥነት በመቀነስ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ቃዋቆቶ ህዳር 26/2018 አልቾ ኮሙኒኬሽን

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ የወጣቶችን ስራ አጥነት በመቀነስና በተለያዩ የስራ መስኮች በማደራጀት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በወረዳው በተደራጁ ማህበራት የተሰሩ ተግባራትን የዞን እና የወረዳ አመራር አካላት የመስክ ምልከታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በመስክ ምልከታው የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህድያ ሀሰን የስልጤ ዞን ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ መምሪያ ምክትል እና የገጠር ዘርፍ ሃላፊው አቶ አብዱልመናን ሁሴን የመምሪያው ምክትል እና የከተማ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ናስር ጀማል የመምሪያው ምክትል እና የማኒፋክቸሪንግ ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ዘምዘም መሀመድ የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል እና እንስሳት ዘርፍ አቶ ነጃ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ሱልጣን በርጋ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙባረክ አሊ እና ሌሎች የጽ/ቤት ሃላፊዎች እና የተደራጁ ማህበራት ተገኝተዋል፡፡

በስልጤ ዞን ለ20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች: ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል የሚሳተፉ ታደሚዎችን በብሄረሰቡ  የእንግዳ አቀባበል መሰረት ለመቀበል ልዩ ዝግጅት ተደርጎ እየተጠበቁ ናቸው!‎ወራ...
05/12/2025

በስልጤ ዞን ለ20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች: ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል የሚሳተፉ ታደሚዎችን በብሄረሰቡ የእንግዳ አቀባበል መሰረት ለመቀበል ልዩ ዝግጅት ተደርጎ እየተጠበቁ ናቸው!

‎ወራቤ - ህዳር 26/2018-ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን
‎20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን '' ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ይከበራል።

‎በበአሉ ላይ ለመሳተፍ ከተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የሚመጡ እንግዶችን በስልጤ ብሄረሰብ የክብር እንግዳ አቀባበል መሰረት እንግዶችን ለመቀበል በወራቤ ከተማ ልዩ ዝግጅት ተደርጎ እንግዶችን በመጠባበቅ ላይ ነው።

ዞን ኮሙኒኬሽን

ከ5 አመት በታች የሆኑ ሁሉም ህፃናትን ቤት ለቤት ክትባት በመስጠት ጤናማ ትውልድ መፍጠር ይገባል፦ አቶ ሸምሱ ሀይረዲን!ከታህሳስ 3-6/2018 ጀምሮ እድሜያቸው ከ5 አበመት በታች ለሆኑ ህፃ...
05/12/2025

ከ5 አመት በታች የሆኑ ሁሉም ህፃናትን ቤት ለቤት ክትባት በመስጠት ጤናማ ትውልድ መፍጠር ይገባል፦ አቶ ሸምሱ ሀይረዲን!

ከታህሳስ 3-6/2018 ጀምሮ እድሜያቸው ከ5 አበመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚሰጠው የ4ኛ ዙር nopv2 ክትባት ዘመቻ የአሰልጣኞች ስልጠና በስልጤ ዞን ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝ ሆስፒታል አዳራሽ ላይ እየተሰጠ ይገኛል።

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ ሀይረዲን ለሰልጣኞች ባስተላለፉት መልዕክት በጤናው ተግባር ቱክረት ከተሰጣቸው ዋና ዋና ተግባራት የህፃናት ክትባት ቀዳሚ እንደሆነ እና ሁሉም ህፃናትን ቤት ለቤት ክትባት መስጠት ይጠበቃል ብለዋል።

እንደ ዞን ለህፃናት ክትባት ፕሮግራም በተሰጠው ትኩረት ህፃናቶች ክትባት ማግኘት መቻላቸውን በመጠቆም በዚህም ወረርሽኝን መከላከል መቻሉን አንስተው ህፃናትን በሁሉም የክትባት አይነቶች ተደራሽ በማድረግ ጤናማ ትውልድ የማፍራቱ ተግባር ውጤታማ መሆኑን ገልጸዋል።

ከታህሳስ 3-6/2018 ጀምሮ እድሜያቸው ከ5 አበመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚሰጠው የ4ኛ ዙር nopv2 የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ይካሄዳል ያሉት ኃላፊው በሚሰሩ የጤና የክትባት ዘመቸ ስራዎችን በመረጃ በማስደገፍ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

ጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አብዱልሃኪም ሻፊ የስልጠና ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት ፖሊዮ ሁሉንም የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ የህብረተሰብ ክፍል ያጠቃል በዋናነት ግን ከ5 አመት በታች የሆኑ ህፃናትን ነው የሚያጠቃው ብለዋል።
ዞን ኮሙኒኬሽን

ህዳር 29- የኢትዮጵያዊያን አብሮነት ሁነኛ ማሳያ ነው- አቶ ዘሪሁን እሸቱ - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ(ቃዋቆቶ፣ ህዳር 25/2018)፣ ህዳር 29-...
04/12/2025

ህዳር 29- የኢትዮጵያዊያን አብሮነት ሁነኛ ማሳያ ነው- አቶ ዘሪሁን እሸቱ - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ

(ቃዋቆቶ፣ ህዳር 25/2018)፣ ህዳር 29- የብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የመላው ኢትዮጵያዊያን አብሮነት ሁነኛ ማሳያ ነው ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ አስታውቀዋል ።

አቶ ዘሪሁን በነገው እለት ህዳር 26/2018 ተከብሮ የሚውለውን 'የአብሮነት ቀን" በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት የኢትዮጵያ ህዝቦች ዘመናትን የተሻገረ የአብሮነት እሴቶች ባለቤቶች ናቸው። ክፉውንም፣ ደጉንም አንድ ላይ ሆነው በመተሳሰብ በጋራ በመሆን በማሳለፍ ይታወቃሉ ብለዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዝሃነት ተዝቆ የማያልቅ ጸጋ ቁልፍ መገለጫቸው ከሆኑ የአለም ሀገራት ውስጥ አንዷ ናት ያሉት የቢሮ ሃላፊው ብዝሃነት ያስጌጣቸው በርካታ ህዝቦች አንድ ሆነው፣ በአብሮነት የፈጠሯት ሀገር ናት ሲሉም አክለዋል።

ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ መላው የሀገራችን ህዝቦችን በህብር ቀለማት፣ ባሸበረቁ ባህላዊ እሴቶች በአንድ ቦታ የሚያሰባስበው የብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ትልቁ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብሮነት፣ የጋራ መጻኢ እድል ማሳያ እንደሆነም በመልዕክታቸው አመልክተዋል።

ይህን ታላቅ ኩነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ በነገው እለት ህዳር 26/2018 "የአብሮነት ቀን" ን በጋራ እናከብራለን።" ሲሉም ጠቁመዋል።

አብሮነት- የኢትዮጵያ ህዝቦች ድምር አቅም ነው ሲሉ የገለጹ ሲሆን ይህን ድንቅ የህዝቦች የጋራ እሴት ማጎልበትና ዘላቂነቱን ማረጋገጥ ከዚህ ትውልድ የሚጠበቅ ሃላፊነት እንደሆነ ተናግረዋል ።

"የህዝቦች (የብዙዎች) አንድነትና ወንድማማችነት የማይፈታው ችግር አይኖርም፣ ዘላቂ አብሮነትና ዴሞክራሲያዊ ትብብር ስኬታማ የማያደርገው የለውጥ መንገድ፣ የጋራ ብልጽግና ጉዞ ሊኖር አይችልም!" ሲሉም አቶ ዘሪሁን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

የኢትዮጵያ ህዝቦች መጻኢ እድልም በመሰል አብሮነት፣ ወንድማማችነትና መተሳሰብ ላይ መሰረቱን ያደረገ መሆን እንደሚኖርበት ገልጸው መላው ኢትዮጵያዊያን ብዙም አንድም ሆነው በአብሮነት እሳቤ ችግሮቻቸውን ሊፈቱ፣ በአብሮነት ወደ ብልጽግና ሊሻገሩ ግድ ይላቸዋል ብለዋል።

በነገው እለት የአብሮነት ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች ከማክበር ጎን ለጎን ለኢትዮጵያ ብሄርና ብሄረሰቦች የባህል አምባሳደሮች በሁሉም የክልሉ መግቢያ በሮች ደማቅ አቀባበል እንደሚደረግ የጠቆሙት አቶ ዘሪሁን የክልሉ ህዝቦች እንግዶቻቸውን ለመቀበል ከወዲሁ የተሟላ ዝግጅት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል ።

"አብረን ስንሆን የማናልፈው ፈተና የለምና፣ ከሚነጣጥሉ ነጠላ ትርክቶች ይልቅ አንድ በሚያደርጉ በጋራ ጉዳዮች፣ በወል ትርክቶች፣ የጋራ አቅሞቻችንን በሚያሰባስቡ አጀንዳዎችች፣በጥቅሉም በመላው ኢትዮጵያዊያን አብሮነት ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ሀገርን እናስረክብ!" ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ።የመኢክመኮ

በየቀበሌው የሚከናወኑ ተግባራትን አቀናጅቶ በመምራት ማህበረሰቡን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፦  ክብርት ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን ቃዋቆቶ ህዳር 25/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}በየቀበሌው...
04/12/2025

በየቀበሌው የሚከናወኑ ተግባራትን አቀናጅቶ በመምራት ማህበረሰቡን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፦ ክብርት ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን

ቃዋቆቶ ህዳር 25/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}

በየቀበሌው የሚከናወኑ ተግባራትን አቀናጅቶ በመምራት ማህበረሰቡን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክብርት ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን ገለጹ።

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር ወቅታዊ የመንግስት እና የፓርቲ የቀበሌ ተግባራትን ከቀበሌ አስተዳዳሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

በወረዳ ደረጃ የሚከናወኑ የልማት ተግባራትን ቀጣይነት እንዲኖራቸው እና ተደራሽ እንዲሆኑ በመስራት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚገባ ያነሱት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን በ2017 ከገጠር መሬት ግብር አሰባሰብ ላይ ያጋጠሙ ችግሮች በ2018 እንዳይደገም መረጃዎችን በማጣራት ከወዲሁ ቅድመ-ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

አልቾ ውሪሮ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ በበኩላቸው የመስኖን ሁሉንም የውሃ አማረጮችን በአግባቡ በመጠቀም እና በስፋት በማልማትእና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአረሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመራሩ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

በሁሉም ቀበሌዎች የብልጽግና ፓርቲ የህብረት ጽ/ቤቶችን ለመገንባት እየተደረገ ያለው እንቅቃሴ የሚበረታታ እንደሆነ የገለጹት አቶ ሙዘይን ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ የጽ/ቤቶችን ቀሪ ስራዎችን ባጠረ ጊዜ ተጠናቀው መመረቅ እንዳለባቸው አክለው አንስተዋል።

በውይይት መድረኩ በወቅታዊ የመስኖ ተግባር፣የገጠር ኮሪደር ልማት፣የስራ ዕድል ፈጠራ በትምህርት እንዲሁም በገቢ አሰባሰብ እና በተለያዩ ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ በጥልቀት ውይይት በማድረግ መድረኩ ተጠናቋል።

በመድረኩ የወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠራ አቶ ሙዘይን መሀመድ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽ/ቤት ዋና ሃለፊ አቶ ሱልጣን በርጋ የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሙባሪክ አሊ፣ የወረዳው ገቢ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መህዲን ሽፋ እና የቀበሌ ዋና አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል።

03/12/2025
03/12/2025
በተጠባቂው ጨዋታ ሶበላን ቃዋቆቶ ከነማን 2ለ1  በሆነ ውጤት አሸነፈ፡፡በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ወጣቶችን እና ስፖርት አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የበጋ ወራት የቀበሌዎች የበጋ ወራት የውስጥ ...
03/12/2025

በተጠባቂው ጨዋታ ሶበላን ቃዋቆቶ ከነማን 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸነፈ፡፡

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ ወጣቶችን እና ስፖርት አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የበጋ ወራት የቀበሌዎች የበጋ ወራት የውስጥ ለውስጥ እግር ኳስ ውድድር በተጠባቂው ጨዋታ ሶበላን ቃዋቆቶ ከነማን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የሶበላንን ግቦች ጃፈር እና ነስረዲን ሲያስቆጥሩ የከነማን ግብ መሀመድ ( ደረሳው) አስቆጥሯል፡፡

ጣንዤ ላይ በተደረገ ጨዋታ ጣንዤ ቀበሌ ቀጡጫን ቀበሌን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የሁሉም እግር ኳስ ቡድኖች የምድብ ጨዋታ የተጠናቀቀ ሲሆን በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ ጀምሮ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ የሚጀምር መሆኑም ተገልጿል፡፡

ከ6 ሚልየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የጊንዶ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቤተ-ሙከራ ተጠናቆ ርክክብ ተደረገቃዋቆቶ ህዳር 24/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ...
03/12/2025

ከ6 ሚልየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የጊንዶ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቤተ-ሙከራ ተጠናቆ ርክክብ ተደረገ

ቃዋቆቶ ህዳር 24/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}

ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ከ6 ሚልየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የጊንዶ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የፊዚክስ፣ ባዮሎጂ እና ኬሚስትሪ የቤተ-ሙከራ ባጠረ ጊዜ ተጠናቆ ርክክብ ተደርጓል።

በወረዳው የሚገኙ የትምህርት ቤቶችን ስታንዳርድ ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ያነሱት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን የጊንዶ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስታንዳርድን ለማሻሻል ከ6 ሚልየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የወረዳው አስተዳደር የቤተ-ሙከራውን መገንባቱን ገልጸዋል።

የቤተ-ሙከራው ግንባታ ባጠረ ጊዜ በመጠናቀቁ ተማሪዎችን ተግባር ተኮር እውቀት በማግኘት ለቀጣይ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ያግዛቸዋል ያሉት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ተማሪዎችም በተመቻቸላቸው እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በርክክቡ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ፣ የትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ካሚል ፈረጃ እንዲሁም የወረዳው ፋይናንስ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙህዲን ከድር ተገኝተዋል።

በጎነት ከበጎ ልቦና የሚመነጭ፣ ያለ ጥቅም  ስሌት፣ የመስጠት መሰጠት ነው!የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ስራ አስፈፃሚዎች በኩተሬ ከተማ ዛሬ እሮብ ገበያ ላይ በኩላሊት ህ...
03/12/2025

በጎነት ከበጎ ልቦና የሚመነጭ፣ ያለ ጥቅም ስሌት፣ የመስጠት መሰጠት ነው!

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ስራ አስፈፃሚዎች በኩተሬ ከተማ ዛሬ እሮብ ገበያ ላይ በኩላሊት ህመም ላይ ለምትገኘዋ ለኢንጂነር ረወዳ ሱልጣን የህክምና ገንዘብ እያሰባሰበ ይገኛል፡፡

ይህንንም በማሰብ እና ፓርቲያችን ብልፅግና በእሴቱና መርሆቹ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ብሎ ሲያስቀምጥ በእርግጥም መተሳሰብን ፣ አንድነትን ፣ ከራስ አልፎ ለሌሎች የመሆንን ፣ አሳቢነትን አካፋይነት እንዲሁም ፍቅርን የሚያጠናክሩ ተግባራት በዘላቂነት እንዲተባበሩ በማድረግ ነው።

ለበጎ ፈቃደኞች ትንሽ የምትመስል ተግባር የተቸገሩትን ሰዎች ህይወት ለውጣ ፣እነሱም በተራቸው ለሌሎች ለጋሶች እንዲሆኑ ተነሳሽነትን የሚፈጥር ነው ።

በጎነት ከበጎ ልቦና የሚመነጭ ያለ ጥቅም ስሌት የመስጠት መሰጠት መሆኑን በመገንዘብ በተዘረጉ መደበኛ ሰው ተኮር ስራዎች በንቃት በመሳተፍ፣ በዙሪያችን የሚገኙ አቅመ ደካሞች ራሳቸውን ከገጠማቸው ህመም ለመዳን እና ለመለወጥ የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ ፣ ለአገራችን ሁለንተናዊ ብልፅግና አሻራችንን እናሳርፍ !

ለኢንጂነር ረውዳ ሱልጣን የህክምና ገንዘብ የማሰባሰቡ ስራ በቀጣይ በሌሎች በገበያ ቀናትም ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ለመርዳት:-

በባንክ ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ:-

ንግድ ባንክ:-1000363435948 ረውዳ ሱልጣን
አቢሲኒያ:-108143843 ረውዳ ሱልጣን
ንብ ባንክ:-7000018618597 ረውዳ ሱልጣን

ለተጨማሪ መረጃ:-
0934547187 ረውዳ ሱልጣን

የስልጤ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የአምስት ወር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና በተለያዩ ርዕሶች የስልጠና መድረክ እያካሄደ ይገኛል፡፡ቃዋቆቶ ህዳር 24/2018 አልቾ ...
03/12/2025

የስልጤ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የአምስት ወር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና በተለያዩ ርዕሶች የስልጠና መድረክ እያካሄደ ይገኛል፡፡

ቃዋቆቶ ህዳር 24/2018 አልቾ ኮሙኒኬሽን

በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ዋና ኃላፊ አቶ ኢስማኤል ዲላ በ2018 በጀት ዓመት ታቅዶ እስካውን በአምስት ወር የተመዘገቡ ውጤቶችና በሂደቱም ያጋጠሙ ችግሮችን በመገምገም ለማረም ያለመ ስለመሆኑ ገልጸዋል፡፡

ኃላፊው አያይዘውም በሂደቱ የተገኙ መልካም ልምዶችን ለማስፋትና ሁሉንም መዋቅሮች ተቀራራቢና ተመጣጣኝ አፈጻጸም እንዲኖራቸው ለማስቻል መሆኑን አክለዋል፡፡

ከአፈጻጸም ባሸገር የተለያዩ የስልጠና መርሃ ግብሮች መኖሩን የጠቆሙት ኃላፊው በስነ-ምግባር ፣በኢ-ትሬዲንግ ዙሪያ ስልጠና እንደሚሰጥም አስታውቀዋል፡፡

በንግድ ስራ ላይ ፈተና የሆኑት የስነ-ምግባር ጥሰት ፣ሌብነትና ብለሹ አሰራር በር ዘግቶ መሄድ ከልተቻለ የንግድ ስራ ማሳካት አይቻልም ያሉት ኃላፊው ኃላፊው ለዚህም በየግዜው በስነ-ምግባርና በፀረ-ሙስና መርህዎች በዘርፉ ለተመደቡ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በመድረኩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በንግድ ምዝገባና ፍቃድ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በወ/ሮ ሰውዳ ስርሞሎ እና በንግድ ፍቃድ አገልግሎት የዳታ ቤዝና የአንድ መሶብ አገልግሎት ከፍተኛ ኢክስፐርት ሀቢብ ናስር በንግድ ኦንላይን ምዝገባ በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

በሌላ በኩል በስነ-ምግባር መርህዎች ዙሪያ በዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ በስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ ፊጣ አወል እየተሰጠ ነው፡፡

ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን ኮሙኒኬሽን
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

የእርዳታ ጥሪመሀመድ ሳኒ ይባላል ፡፡ ተወልዶ ያደገው በስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ አልከሶ አካባቢ ነው ፡፡ ትምህርቱን ከዩንቨርሲቲ ካጠናቀቀ በሇላ በአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ግ/ፅት ቤት በተለያዩ የስ...
02/12/2025

የእርዳታ ጥሪ

መሀመድ ሳኒ ይባላል ፡፡ ተወልዶ ያደገው በስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ አልከሶ አካባቢ ነው ፡፡ ትምህርቱን ከዩንቨርሲቲ ካጠናቀቀ በሇላ በአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ግ/ፅት ቤት በተለያዩ የስራ ሀላፊነቶች እየሰራ ቆይቷል ፡፡

የሆነው ሆኖ ግን ለረጅም ግዜያት በልብ ህመም ሲሰቃይ የነበረና በተለያዩ ግዜያት ህመሙን ለመታከም ብቻውን ሲታገል ቆይቷል ፡፡ በጣም በምያሳዝን መልኩ ሌላ ያልታሰበና ለብቻው ሊታገለው የማይችለው ዱብዳ የሆነ በሽታ እንዳለበት ተነገረው ፡፡

ህመሙም ከወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መሆናቸውን እና በሳምንት ብያንስ የኩላሊት እጥበት ( Dyalisis ) እንደምያስፈልገው ተነገረው ፡፡ አሁን ላይ በሳምንት 2 ግዜ Dyalisis እያደረ ገ ሲሆን ለ1 ግዜ Dyalisis #ከ5800 ብር በድምሩ #ከ11,600 ብር በላይ እየከፈለ Dyalisis እየተደረገለት ይገኛል ፡፡

የወንድማችን መሀመድ ሳኒን የኩላሊት ህመም ንቅለ ተከላ ለማድረግ ብር በላይ እንደምያስፈልግ ተነግሮኛል ፡፡ ነገር ግን ይህን ገንዘብ እኔም ሆነ ቤተሰቦቼ የመክፈል አቅም የለንምና እባካችሁን እርዱኝ እያለ ይማፀናል ፡፡

መሀመድ ሳኒ ልጆች አባት ነው ፡፡ መልካም ስራችሁን ፈጣሪ ይቀበላችሁ ፡፡ ወንድማችንን ሁላችንም እንደ አቅማችን የምንችለውን ሁሉ በማገዝ ወደቀድሞ ጤንነቱ እንዲመለስ እናድርግ

መርዳት ለምትፈልጉ ወገኖች
ንግድ ባንክ ፡- 1000449704839 የቲጋገዞት በጎ አድራጎት ማህበር አካውንት ነው

የምንሰጠው ተርፎን ሳይሆን ካለን ላይ በመቀነስ ነው

ለበለጠ መረጃ ከታች ያሉ ስልክ ቁጥሮችን እና በቴሌግራም ግሩፕ ማግኘት ይችላሉ

ይሀው ቻሌንጅ የሚደረግበት የTelegram ግሩፕ

( https://t.me/TigagezotYebegoAdragotMahber )

ስልክ ቁጥር ፡- 0910188909 የራሱ የመሀመድ ሳኒ ስልክ
፡- 0912303805 የቲጋዞት ስራ አስኪያጅ

Address

Silte
Werabe
KAWAKOTO

Opening Hours

Monday 07:00 - 19:00
Tuesday 07:00 - 19:00
Wednesday 07:00 - 19:00
Thursday 07:00 - 19:00
Friday 07:00 - 17:00
Saturday 07:00 - 17:00
Sunday 07:00 - 19:00

Telephone

+251924711807

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ። posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alicho Communication - ስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ መንግስት ኮመንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ።:

Share