Woldia Standard

Woldia Standard ኑ! በጋራ መረጃዎችን እንቋደስ!

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እ...
25/06/2025

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።

መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።

ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።

ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::ከዚሁ ጋር በተ...
25/06/2025

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።

ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመጭው መስከረም ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ:-
📌ለኤርትራ 42 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሊያ 51 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሌ ላንድ 7 ሜጋ ዋት
📌ለየመን 240 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ የሚያስችል አዲስ መስመር ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ ነው ተብሏል።

የ25 ቀናት እስር ተወሰነበት‼በቅርቡ የትራፊክ ፖሊስ እንዲሁም የመንግስት ስራተኛ የሆነ ግለሰብ የደበደበው ተከሳሽ ታማኝ አስማማው አንዳርጌ 3 ዓመት የተፈረደበት ሲሆን ነገር ግን:- ተከሳሽ...
25/06/2025

የ25 ቀናት እስር ተወሰነበት‼

በቅርቡ የትራፊክ ፖሊስ እንዲሁም የመንግስት ስራተኛ የሆነ ግለሰብ የደበደበው ተከሳሽ ታማኝ አስማማው አንዳርጌ 3 ዓመት የተፈረደበት ሲሆን ነገር ግን:-

ተከሳሽ:-

1. አረንጓዴ አሽራ በችግኝ ተከላ አስተዋጽኦ ያደረገ ስለሆነ

2.የቤተሰብ አስተዳዳሪ ስለሆነ

3. ታማሚ ስለሆነ

4. ከዚህ በፊት ምንም አይነት የወንጀል ክስ የሌለበት እና ፀባዩ በጣም ጥሩ የሆነ ግለሰብ ስለሆነ ከሌላ የተዘርዘሩትን በሙሉ ታይተው
ከ3 ዓመት ወደ 25 ቀን ወርዶ ተከሳሽ " ታማኝ አስማማው አንዳርጌ " የ25 ቀን እስር እንዲታሰር ተፍርዶበታል::

ኢራን በሶሪያ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈር በሞርታር ደበደበች*************************የኢራን መንግሥት በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ካደረሰ ከጥቂት ጊ...
23/06/2025

ኢራን በሶሪያ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈር በሞርታር ደበደበች
*************************

የኢራን መንግሥት በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ካደረሰ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ማምሻውን በሶሪያ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈርም በሞርታር ደብድቧል።

በሶሪያ ምዕራብ ሀሳካ ግዛት በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ጥቃት መድረሱን ተከትሎ በአካባቢው ጥብቅ የፀጥታ ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን የኢራኑ መህር ዜና አገልግሎት ዘግቧል።

"ህወሃት በሰማዕታት ሽፋን ጦርነት እየጎሰመ ነዉ" አቶ ጌታቸዉ ረዳ ‼️*****የቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ጌታቸዉ ረዳ  ጽንፈኛው የህዉሓት ቡድን በሰማዕታት ስም ውድቀቱን ለመሸፈ...
22/06/2025

"ህወሃት በሰማዕታት ሽፋን ጦርነት እየጎሰመ ነዉ" አቶ ጌታቸዉ ረዳ ‼️
*****
የቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ጌታቸዉ ረዳ ጽንፈኛው የህዉሓት ቡድን በሰማዕታት ስም ውድቀቱን ለመሸፈን በሕዝባችን ላይ የበለጠ መስዋዕትነት እንዲከፍል ለማድረግ እየተጣደፈ የሚገኝ የኋላ ቀር ስብስብ መሆኑን ተናግሯል፡፡
አቶ ጌታቸዉ ህዉሃት ሰሞኑን ሰማዕታት በሚል ሽፋን ህብረተሰቡን እያስገደደ ሲያካሄድ የነበረዉ ሰልፍ ለጦርነት ጉሰማ መሆኑን አጋልጧል ፤ ቡድኑ ከተጠያቂነት ለማምለጥ የጀመረውን የጥፋት አካሄደ ወቅሷል፡፡
ጌታቸዉ የትግራይ ህዝብ ከቡድኑ የጥፋት እንቅስቃሴ እንዲርቅ በአፅንኦት አሳስቧል ፡፡

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ  37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁበሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢ...
20/06/2025

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ 37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁ

በሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ይጠብቃቸዋል ሲሉ 31 የሲቪል ማህበረሰብ እና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ዜጎችን ጨምሮ መቶዎች በሚቆጠሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግባቸው እንደሚችል ተገልጿል።

ደርጅቶቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ከህገ ወጥ አደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እየጨመረ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ በእስር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ፣ #ሶማሊያና #ግብፅ ዜጎች ህይወት "ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው" ገልጸዋል።

መግለጫው፤ በተያዘው ዓመት ሰባት ኢትዮጵያውያን እና 19 የሶማሊያ ዜጎች “ሃሺሽ በማዘዋወራቸው” ግድያ እንደተፈጸመባቸው ገልጿል። በተጨማሪም “ሰኔ 9 ፣ 2017 ዓ/ም ሶስት የኢትዮጵያ ዜጎች እንደተገደሉ" እና ሌሎች ደግሞ በማንኛውም ጊዜ ልንገደል እንችላለን በሚል ስጋት ውስጥ እንዳሉ አመላክተዋል።

 #ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባ...
12/06/2025

#ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️

በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባለ።

የገንዘብ ሚኒስቴር የህግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊው አቶ ተወዳጅ መሐመድ እንዳሉት አዋጁ ተግባራዊ የሚደረገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን መገደብን ታሳቢ አድርጎ ነው።

በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ሲጸድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈጸም እንደሚማስቀጣ ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል።

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ከምንጊዜም ምርጥ ኢትዮጵያውያን የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ...
11/06/2025

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ከምንጊዜም ምርጥ ኢትዮጵያውያን የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኮከብ ሙሉጌታ ከበደ ባጋጠመው ህመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሕይወቱ አልፏል፡፡

ሙሉጌታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ለበርካታ ዓመታት በድንቅ ብቃት ተጫውቶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ በነበረው ቆይታ አምበል ሆኖም መጫወት የቻለ ድንቅ ተጫዋች ነበር።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ለበርካታ ዓመታት በመጫወት የሚታወቀው ሙሉጌታ ከበደ (ወሎየዉ) ባጋጠመው ህመም ምክንያት በህክምነ ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል።

ለትንሳኤ በዓል በ12 ሺህ በር የተገዛን በግ ሰርቀው በ5 ሺህ ለመሸጥ ሲደራደሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።የሸካ ዞን ቴፒ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ሚያዚያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ...
14/04/2025

ለትንሳኤ በዓል በ12 ሺህ በር የተገዛን በግ ሰርቀው በ5 ሺህ ለመሸጥ ሲደራደሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የሸካ ዞን ቴፒ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ሚያዚያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በቴፒ ከተማ አንድነት ቀበሌ ልዩ መጠሪያው ጎንደሬ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አከባቢ አንድ ግለሰብ ለትንሳኤ በዓል ብሎ በ12 ሺህ ብር የገዛው በግ መሰረቁን ለፖሊስ ቀርቦ ማመልከቱን ተከትሎ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልፆአል።

የቴፒ ከተማ ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው መረጃ መሰረት ሁለቱ ተጠርጣሪዎች የሰረቁት በግ በአምስት ሺህ ብር ለመሸጥ ሲደራደሩ የነበሩ ግለሰቦችሁለቱ የስርቆት ወንጀል ፈፃሚዎችና የተሰረቀ በግ የገዛው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እነንደሚገኝ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን ዘግቧል።
===================

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።   በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ንግድና ገበ...
13/04/2025

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታውቋል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኀላፊ አዲሱ ወንድሙ ሁለት አይሱዙ መኪና ሽንኩርት በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ሥር መዋሉን ተናግረዋል። ሽንኩርቱ በቁጥጥር ሥር የዋለው ለጅምላ ንግድ ባልተፈቀደ እና ከሽንኩርት ንግድ ጋር ባልተገናኘ የንግድ ፈቃድ ሲንቀሳቀስ መኾኑንም ገልጸዋል።

በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘው ሽንኩርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለኅብረተሰቡ እንደሚቀርብም አስታውቀዋል።

"በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ካላችሁ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው" - አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋበአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ...
03/04/2025

"በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ካላችሁ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው" - አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በአምባሳደሩ ኤርቪን ማሲንጋ አማካኝነት መልዕክት አስተላልፏል።

በህገወጥ መንገድ ወደ አሜሪካ መግባት፣ ቪዛ ለማግኘት መዋሸት፣ ያለ ህጋዊ የስራ ፍቃድ ስራ መስራትና የቪዛ ጊዜ ካበቃ በኋላ በአሜሪካ መቆየት ከባድ ቅጣት ያስከትላል።

ቅጣቶቹ እስርን፣ ወደ ሃገር መመለስን እና ዳግም ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ መከልከልን እንደሚያካትት ነው አምባሳደሩ የተናገሩት።

አክለውም፥ "በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ካላችሁ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

መልዕክቱ፥ የአሜሪካ መንግስት ሌሎች በህገወጥ መንገድ እንዲገቡ የሚተባበሩት ላይም ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።

አሜሪካ በቅርቡም ህገወጥ ስደትን መከላከል አልቻሉም ባለቻቸው የሃገራት ባለስልጣናት ላይ የቪዛ ገደብ መጣሏን አስታውሰዋል።

በህገወጥ መንገድ መግባት ከሚያስገኘው ጥቅም በላይ ጉዳቱ ያመዝናል ያለው ኤምባሲው ዜጎች የወደፊት ህይወታችን ከመጉዳት እንዲታጠቀቡ እና በህገወጥ መንገድ በአሜሪካ ያሉ ቤተሰቦቻቸውንም በጊዜ እንዲመለሱ ጥሪ እንዲያደርጉ አምባሳደሩ አሳስበዋል::

ጨረቃ ዛሬ በመታየቷ የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ ይከበራል የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ቅዳሜ በመታየቷ 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከ...
29/03/2025

ጨረቃ ዛሬ በመታየቷ የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ ይከበራል

የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ቅዳሜ በመታየቷ 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ 1 ሺህ 446ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት፤ ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር አስተምኅሮቱን በመተግበር ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የዘንድሮው የረመዷን ጾም ፍቅርና አብሮነትን የሚያሳዩ የጋራ የኢፍጣር መርሐ-ግብሮች የታዩበት እንደነበረም ገልጸዋል።

Address

Woldia

Telephone

+251920212223

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Standard posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Woldia Standard:

Share