Woldia Standard

Woldia Standard ኑ! በጋራ መረጃዎችን እንቋደስ!

"ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባህር (Sea of Japan) አቅጣጫ 10 ያህል ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኮሰች።ሚሳኤሎቹ የተተኮሱት በፒዮንግያንግ አቅራቢያ ከሚገኘው የሱናን (Sunan) አካባቢ ሲሆን...
14/03/2026

"ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባህር (Sea of Japan) አቅጣጫ 10 ያህል ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኮሰች።

ሚሳኤሎቹ የተተኮሱት በፒዮንግያንግ አቅራቢያ ከሚገኘው የሱናን (Sunan) አካባቢ ሲሆን፣ ያረፉትም ከጃፓን የኢኮኖሚ ክልል (EEZ) ውጭ በሆነ የባህር ክፍል ላይ ነው። እስካሁን ባለው መረጃ በአደጋው የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት የለም።"

የካሜኔይ ልጅ ከግድ*ያ ተረፉ‼️እሁድ:የካቲት 29 ቀን 2018 ዓም(ወልዲያ ስታንዳርድ)የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አላ ካሜኔይ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት መሞታቸውን ተከትሎ ልጃቸው ሞ...
08/03/2026

የካሜኔይ ልጅ ከግድ*ያ ተረፉ‼️

እሁድ:የካቲት 29 ቀን 2018 ዓም(ወልዲያ ስታንዳርድ)

የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አላ ካሜኔይ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት መሞታቸውን ተከትሎ ልጃቸው ሞጅታባ ካሜኔ አባቱን ተክቶ የኢራን መሪ ይሆናል ተብሎ የታቀደ ቢሆንም በትናንትናው ዕለት በእስራኤል አየር ኃይል በተፈፀመ ጥቃት ከግድያ መትረፉን ነገር ግን የመቁሰል አደጋ እንደደረሰበት እስራኤል ቻናል 12 እንዲሁም ኒውዮርክ ፖስት አስነብቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የእስራኤል ባለስልጣናት በይፋ ያሉት ነገር የለም።

በሰሜን ወሎ ራያ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው። ሐሙስ:የካቲት 28 ቀን 2018 አም(ወልዲያ ስታንዳርድ))በሰሜን ወሎ ዞን  ቆቦ ከተማ  የመምረጥ እና የመመረጥ መብትን የሚጠይቅ ሕዝ...
07/03/2026

በሰሜን ወሎ ራያ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ሐሙስ:የካቲት 28 ቀን 2018 አም(ወልዲያ ስታንዳርድ))

በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ የመምረጥ እና የመመረጥ መብትን የሚጠይቅ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉ "የመምረጥ እና የመመረጥ መብት ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው" በሚል መልዕክት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። በሰልፉ የአምስት ወረዳ ሕዝብ የተሳተፈ ነው።

በሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉ የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ አላማጣ ከተማ፣ ኮረም ከተማ እና የኦፍላ ወረዳ ነዋሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን"የመምረጥና የመመረጥ መብት ህገመንግስታዊ መብታችን ነው" በሚል ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።(ወልቃይት ኮሙኒኬሽን)
05/03/2026

ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን"የመምረጥና የመመረጥ መብት ህገመንግስታዊ መብታችን ነው" በሚል ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
(ወልቃይት ኮሙኒኬሽን)

ምርጫ ቦርድ በ5 የምርጫ ክልሎች ጉዳይ ለቀረበበት ክስ ለፍርድ ቤት ምላሽ ማቅረቡ ተነገረ::የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአምስት የምርጫ ክልሎች ጉዳይ በስምረት ፓርቲ ለቀረበበት ክስ ዛሬ...
04/03/2026

ምርጫ ቦርድ በ5 የምርጫ ክልሎች ጉዳይ ለቀረበበት ክስ ለፍርድ ቤት ምላሽ ማቅረቡ ተነገረ::

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአምስት የምርጫ ክልሎች ጉዳይ በስምረት ፓርቲ ለቀረበበት ክስ ዛሬ ምላሽ እንዲያቀርብ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በታዘዘው መሠረት ምላሹን አቀረበ።

03/11/2025

ለትምህርት ፈላጊዎች

የ2018 ዓ.ም አዲስ ምዝገባ በወልድያ ከተማ ጀመረ

የዲፕሎማ ትምህርት በሦስት ዓመት የሚጠናቀቅ
በቀን መርሃ-ግብር፡-
#በነርሲንግ (Nursing) ደረጃ- IV
#በፋርማሲ(Pharmacy ) ደረጃ- IV
(Medical Laboratory) ደረጃ- IV
(Accounting & Finance) ደረጃ- IV
አድሜንስትሬሽን (Web development and Database Administration) ደረጃ- IV

በኤክስቴሽን መርሃ-ግብር፡-
#በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ (Accounting & Finance) ደረጃ- IV
አድሜንስትሬሽን (Web development and Database Administration) ደረጃ- IV

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፡-
- ለወንድ 135 ለሴት 122
ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ውጤትና ትራንስክሪፕት 1 ኮፒ
2 ጉርድ ፎቶ ግራፍ
#የምዝገባ ጊዜ፡- ከጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት

#ትምህርቱ ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ እና በቂ እውቀት ባላቸው ስመጥር መምህራኖች ይሰጣል፤ ይምጡ፣ ይመዝገቡ፣ ይማሩ በቂ ዕውቀት አስጨብጠን ተፈላጊ ባለሙያ እናደርግዎታለን፡፡

#አድራሻችን፡-
ወልድያ ሙጋድ ወደ ጎንደር በር በሚወስደው መንገድ አማራ ባንክ ጎን

#ለበለጠ መረጃ
ስልክ፡- +251947312010
+251920486235
+251922918501

የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄ ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል!   ይህ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወልድያ ተወላጅ እና ወዳጅ እንዲሁም የአላማጣ፣ ዋጃ፣ ቆቦ፣ አራዱም፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ዶሮ ግብር፣ ድሬ ሮቃ፣...
03/08/2025

የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄ ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል!



ይህ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወልድያ ተወላጅ እና ወዳጅ እንዲሁም የአላማጣ፣ ዋጃ፣ ቆቦ፣ አራዱም፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ዶሮ ግብር፣ ድሬ ሮቃ፣ ሀሮ፣ ሀራ፣ ዶሮ ግብር፣ ስሪንቃ፣ መርሳ፣ መሀል አምባ፣ ሊብሶ፣ ጊራና፣ ውርጌሳ፣ ውጫሌ፣ ሳንቃ፣ እስታይሽ፣ ሙጃ ... እና አጎራባች ቀበሌዎች የተወለዳችሁ፣ የምትኖሩ እና ወዳጅ የሆናችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ይመለከታል።

በዚህ የ10 ቀን ዘመቻ የምንሰራው የወልድያ ኤርፖርት እንዲፈቀድ እና ስራ እንዲጀመር ዘመቻውን በሚከተለው መንገድ መቀላቀል እና ማሳለጥ እንችላለን :-

1. የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄን የተመለከቱ ማንኛውንም ፖስት ላይክ ማድረግ፣ ኮሜንት ማድረግ እና ሼር ማድረግ፣

2. እነዚህን ፖስቶች ቲክቶክ ላይ ወስደን መልቀቅ፣ የተለቀቁ ፖስቶችን ❤ ማድረግ፣ ኮሜንት እና Copy Link ማድረግ፣

3. በያንዳንዱ ፖስታችን ውስጥ እነዚህን ሀሽታጎች ወስደን መጠቀም፣ ኮሜንት ላይ እነዚህን ሀሽታጎች መጠቀም፣ ይሄም አንዱን ሀሽታግ የተጫነ ሰው ይሄን ሀሽታግ የተጠቀሙ ሰዎች ፖስቶችን ስለሚያመጣልን ተደራሽ እንዲሆን ያደርጋል።
የምንጠቀማቸው ሀሽታጎች እነዚህ ናቸው :-


















4. በየፖስታችሁ እና ኮሜንቱ Woldia_Times ን ኮሜንት ላይ ሜንሽን አድርጓት። ፖስታችሁን ሼር እናደርጋለን። ፅሁፎችን እና ፎቶዎችን በገፃችን ከዛሬ ጀምሮ እናቀርባለን። ይህ የ1 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ጥያቄ እስኪመለስ ከፊት ቆመን እናስተባብራለን!

ወልድያዎች፣ የአካባቢው ተወላጆች እና ወዳጆች የት ናችሁ? እስኪ እጃችሁን አሳዩን?

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እ...
25/06/2025

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።

መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።

ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።

ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::ከዚሁ ጋር በተ...
25/06/2025

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።

ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመጭው መስከረም ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ:-
📌ለኤርትራ 42 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሊያ 51 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሌ ላንድ 7 ሜጋ ዋት
📌ለየመን 240 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ የሚያስችል አዲስ መስመር ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ ነው ተብሏል።

የ25 ቀናት እስር ተወሰነበት‼በቅርቡ የትራፊክ ፖሊስ እንዲሁም የመንግስት ስራተኛ የሆነ ግለሰብ የደበደበው ተከሳሽ ታማኝ አስማማው አንዳርጌ 3 ዓመት የተፈረደበት ሲሆን ነገር ግን:- ተከሳሽ...
25/06/2025

የ25 ቀናት እስር ተወሰነበት‼

በቅርቡ የትራፊክ ፖሊስ እንዲሁም የመንግስት ስራተኛ የሆነ ግለሰብ የደበደበው ተከሳሽ ታማኝ አስማማው አንዳርጌ 3 ዓመት የተፈረደበት ሲሆን ነገር ግን:-

ተከሳሽ:-

1. አረንጓዴ አሽራ በችግኝ ተከላ አስተዋጽኦ ያደረገ ስለሆነ

2.የቤተሰብ አስተዳዳሪ ስለሆነ

3. ታማሚ ስለሆነ

4. ከዚህ በፊት ምንም አይነት የወንጀል ክስ የሌለበት እና ፀባዩ በጣም ጥሩ የሆነ ግለሰብ ስለሆነ ከሌላ የተዘርዘሩትን በሙሉ ታይተው
ከ3 ዓመት ወደ 25 ቀን ወርዶ ተከሳሽ " ታማኝ አስማማው አንዳርጌ " የ25 ቀን እስር እንዲታሰር ተፍርዶበታል::

ኢራን በሶሪያ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈር በሞርታር ደበደበች*************************የኢራን መንግሥት በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ካደረሰ ከጥቂት ጊ...
23/06/2025

ኢራን በሶሪያ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈር በሞርታር ደበደበች
*************************

የኢራን መንግሥት በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ካደረሰ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ማምሻውን በሶሪያ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ሰፈርም በሞርታር ደብድቧል።

በሶሪያ ምዕራብ ሀሳካ ግዛት በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ጥቃት መድረሱን ተከትሎ በአካባቢው ጥብቅ የፀጥታ ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን የኢራኑ መህር ዜና አገልግሎት ዘግቧል።

Address

Woldia

Telephone

+251920212223

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Standard posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Woldia Standard:

Share