Wanzaye press ዋንዛዬ ፕሬስ

Wanzaye press ዋንዛዬ ፕሬስ እውነቱን እውነት ሀሰቱን ሀሰት እንላለን!

ለፋኖ ሕክምና አልሰጠንም - ዓይደር ሆስፒታል (መቐለ)-------"ለፋኖ ቁስለኞች ህክምና አልሰጠንም" ሲል አይደር ሆስፒታል ገለፀ፡፡ በሰሞኑን በአማራ ክልል ቆቦ ውስጥ በፋኖ ታጣቂዎችና በመ...
12/08/2025

ለፋኖ ሕክምና አልሰጠንም - ዓይደር ሆስፒታል (መቐለ)
-------
"ለፋኖ ቁስለኞች ህክምና አልሰጠንም" ሲል አይደር ሆስፒታል ገለፀ፡፡ በሰሞኑን በአማራ ክልል ቆቦ ውስጥ በፋኖ ታጣቂዎችና በመንግስት ሀይሎች መካከል የተደረገውን ጦርነት ተከትሎ ቁስለኛ ታጣቂዎችን መቀሌ የሚገኘው አይደር ሆስፒታል እንዳከመ ሲገለፅ መቆየቱን ወጋህታ ፋክትስ አውስቷል፡፡
እንደዘገባው ቅዳሜ ነሀሴ 3 ቀን 2017 በቆቦ ከተማ በተፋላሚዎቹ መካከል ከፍተኛ ውጊያ የተከናወነ ሲሆን ይህንን ተከትሎ በውጊያው የቆሰሉ ታጣቂዎች በመቀሌ አይደር ሆስፒታል ተኝተው እየታከሙ ስለመሆኑ በማህበራዊ ሚዲያዎች በስፋት ተገልጿል፡፡
ስለጉዳዩ የአይደር አጠቃላይ ሪፈራል ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ቢሮን ማነጋገሩን ዘገባው ጠቅሷል፡፡ ቢሮው በሰጠው መልስም ‹‹ሰሞኑን በአማራ ክልል ከተከናነው ውጊያ ጋር በተያያዘ እኛ ጋር ተኝቶ የታከመ አንድም ቁስለኛ የለም›› ብሏል፡፡ የዜና ምንጩ እንዳለው የሆስፒታሉ የድንገተኛ ክፍል ሰራተኞችም እንዲህ አይነት ታካሚ እንዳላዩ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እ...
25/06/2025

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።

መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።

ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።

ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::ከዚሁ ጋር በተ...
25/06/2025

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።

ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመጭው መስከረም ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ:-
📌ለኤርትራ 42 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሊያ 51 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሌ ላንድ 7 ሜጋ ዋት
📌ለየመን 240 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ የሚያስችል አዲስ መስመር ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ ነው ተብሏል።

ሽኝት‼️ኢራን በእስራኤል ጥቃት ለሞቱ ለሁሉም ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖቿ እና የኑክሌር ሳይንቲስቶቿ በመጪው ቅዳሜ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሽኝት ፕሮግራም ለማካሄድ ወስናለች።በእስራኤል ጥቃት ከ...
25/06/2025

ሽኝት‼️
ኢራን በእስራኤል ጥቃት ለሞቱ ለሁሉም ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖቿ እና የኑክሌር ሳይንቲስቶቿ በመጪው ቅዳሜ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሽኝት ፕሮግራም ለማካሄድ ወስናለች።
በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት ውስጥ የኢራን ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ መሪ እና የሪያቶላህ አሊ ካሜኒ ከፍተኛ አማካሪ የነበሩት ሁሴን ሳላሚ የሚገኙበት ሲሆን ከቅዳሜው ሽኝት ቀደም ብሎ በነገው ዕለት በልዩ ሁኔታ የሽኝት ፕሮግራም ይካሄድላቸዋል ተብሏል።
ሁሴን ሳላሚ የእስራኤል እና የኢራን ግጭት በተጀመረ በመጀመሪያው ቀን መገደላቸው ይታወሳል።

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ  37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁበሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢ...
20/06/2025

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ 37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁ

በሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ይጠብቃቸዋል ሲሉ 31 የሲቪል ማህበረሰብ እና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ዜጎችን ጨምሮ መቶዎች በሚቆጠሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግባቸው እንደሚችል ተገልጿል።

ደርጅቶቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ከህገ ወጥ አደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እየጨመረ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ በእስር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ፣ #ሶማሊያና #ግብፅ ዜጎች ህይወት "ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው" ገልጸዋል።

መግለጫው፤ በተያዘው ዓመት ሰባት ኢትዮጵያውያን እና 19 የሶማሊያ ዜጎች “ሃሺሽ በማዘዋወራቸው” ግድያ እንደተፈጸመባቸው ገልጿል። በተጨማሪም “ሰኔ 9 ፣ 2017 ዓ/ም ሶስት የኢትዮጵያ ዜጎች እንደተገደሉ" እና ሌሎች ደግሞ በማንኛውም ጊዜ ልንገደል እንችላለን በሚል ስጋት ውስጥ እንዳሉ አመላክተዋል።

 #ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባ...
12/06/2025

#ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️

በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባለ።

የገንዘብ ሚኒስቴር የህግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊው አቶ ተወዳጅ መሐመድ እንዳሉት አዋጁ ተግባራዊ የሚደረገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን መገደብን ታሳቢ አድርጎ ነው።

በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ሲጸድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈጸም እንደሚማስቀጣ ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል።

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ከምንጊዜም ምርጥ ኢትዮጵያውያን የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ...
11/06/2025

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ከምንጊዜም ምርጥ ኢትዮጵያውያን የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኮከብ ሙሉጌታ ከበደ ባጋጠመው ህመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሕይወቱ አልፏል፡፡

ሙሉጌታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ለበርካታ ዓመታት በድንቅ ብቃት ተጫውቶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ በነበረው ቆይታ አምበል ሆኖም መጫወት የቻለ ድንቅ ተጫዋች ነበር።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ለበርካታ ዓመታት በመጫወት የሚታወቀው ሙሉጌታ ከበደ (ወሎየዉ) ባጋጠመው ህመም ምክንያት በህክምነ ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል።

05/06/2025

ጌዜው ባይሆንም ልናመሰግንህ ግድ ይለናል!

የተከበሩ የወልዲያ ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ጋር በተያያዘ ሰሞኑን ከፍተኛ ስም ማጥፋት ዘመቻ እየተካሄደ ስንመለከት፡ የስም አጥፊዎችን ማንነትና አላማቸውን ጠንቅቀን ብናውቅም፣ ከንቲባውን እየሰራ ላለው ስራ ማመስገን ባንችል እንኳን እንዴት በመሬት ወራሪዎች ስሙ ሲጠፋ ዝም ማለት ግን አንችልም።

በወልዲያ ከተማ ለሙስሊም ማህበረሰቡ ከዚህ በፊት የተወሰነ እና በእነዚሁ የመሬት ወራሪዎች ምክንያት እየተስተጓጎለ ቆይቶ፣ ዛሬ ውሳኔው ተግባራዊ ሆኖ፣ ህዝበ ሙስሊሙም ሆነ የወልዲያ ህዝብ ደስተኛ ሁኗል። ህዝበ ሙስሊሙም የተሰጠውን ቦታ(መቻሬ አደባባ አካባቢ) ተረክቦ አጥሯል።

ይሄን ተከትሎ ግን፣ መሬቱን በህገ ወጥ መንገድ አየር ላይ ሸንሽነው ይዘውት የነበሩና ሙሉ የከተማውን መሬት ሰብስበው በእጃቸው የያዙ ሌቦች፣ አቶ ዱባለ ውሳኔውን ተፈፃሚ በማድረጉ ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ናቸው።
አቶ ዱባለ ገና የትውልድ ከተማው ከንቲባ ሁኖ ሲመጣ፣ ሁላችንም የከተማው ነዋሪዎች ይሄን የመሬት ወረራ እንደሚያስቆም ተስፋ አድርገን ነበር። እውነቱን ለመናገር አቶ ዱባለ ህዝብ በይፋ እያየ የእነዚህን ሌቦች ጉሮሮ አንቆ፣ የመሬት ወረራውን ማስቆሙን በጫጫታውና ዘመቻው ብቻ መረዳትም ይቻላል።

እነዚህ ነውረኞች በከንቲባው ላይ ብቻ አላቆሙም፣ ከተማው ውስጥ ከነሱ ቡድን ጋር የማይስማሙ/ወይም ተጠይቀው አድማውን አንቀላቀልም ያሉ/ ወጣቶችን እና ባለሃብቶችን ጭምር የማይጨበትና የውሸት ታርጋ እየለጠፉ፣ የሚችሉትንም ከከተማው እንዲለቅ አድርገዋል። ነገ ሁሉም ወገን መብቱን ሚያስከብርበት ጊዜ ሲመጣ፣ እውነቱን ህዝብ የሚያውቀው ቢሆንም፣ እስከዛው ግን የወልዲያ ህዝብ የእነዚህን የማይረቡ ሴረኞች ተግባር እንዲረዳው ያስፈልጋል።

አቶ ዱባለ አብራሬ፡ ከተማችን እና አካባቢያችን ሰላም ባይኖርም፣ አጠቃላይ ለስራ ምቹ ሁኔታ ባይኖርም፣ የወልዲያ ከተማ በተለይም የመሬት ወራሪውን ቡድን ጉሮሮ ይዘህ ስላንጫጫህልን እያመሰገንህ፣ ወደፊትም ከነዚህ ሌቦች የተረፈውን መሬት፣ ህዝቡን እና አካባቢውን የሚጠቅሙ ፕሮጀክቶች እንዲቀመጡበት እንደምትሰራ ተስፋ እናደርጋለን።

በርታ!!!!

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።   በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ንግድና ገበ...
13/04/2025

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታውቋል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኀላፊ አዲሱ ወንድሙ ሁለት አይሱዙ መኪና ሽንኩርት በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ሥር መዋሉን ተናግረዋል። ሽንኩርቱ በቁጥጥር ሥር የዋለው ለጅምላ ንግድ ባልተፈቀደ እና ከሽንኩርት ንግድ ጋር ባልተገናኘ የንግድ ፈቃድ ሲንቀሳቀስ መኾኑንም ገልጸዋል።

በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘው ሽንኩርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለኅብረተሰቡ እንደሚቀርብም አስታውቀዋል።

"በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ካላችሁ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው" - አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋበአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ...
03/04/2025

"በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ካላችሁ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው" - አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በአምባሳደሩ ኤርቪን ማሲንጋ አማካኝነት መልዕክት አስተላልፏል።

በህገወጥ መንገድ ወደ አሜሪካ መግባት፣ ቪዛ ለማግኘት መዋሸት፣ ያለ ህጋዊ የስራ ፍቃድ ስራ መስራትና የቪዛ ጊዜ ካበቃ በኋላ በአሜሪካ መቆየት ከባድ ቅጣት ያስከትላል።

ቅጣቶቹ እስርን፣ ወደ ሃገር መመለስን እና ዳግም ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ መከልከልን እንደሚያካትት ነው አምባሳደሩ የተናገሩት።

አክለውም፥ "በህገ ወጥ መልኩ በአሜሪካ የሚኖር ቤተሰብ ወይም ጓደኛ ካላችሁ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ የምትነግሩበት ጊዜ አሁን ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

መልዕክቱ፥ የአሜሪካ መንግስት ሌሎች በህገወጥ መንገድ እንዲገቡ የሚተባበሩት ላይም ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።

አሜሪካ በቅርቡም ህገወጥ ስደትን መከላከል አልቻሉም ባለቻቸው የሃገራት ባለስልጣናት ላይ የቪዛ ገደብ መጣሏን አስታውሰዋል።

በህገወጥ መንገድ መግባት ከሚያስገኘው ጥቅም በላይ ጉዳቱ ያመዝናል ያለው ኤምባሲው ዜጎች የወደፊት ህይወታችን ከመጉዳት እንዲታጠቀቡ እና በህገወጥ መንገድ በአሜሪካ ያሉ ቤተሰቦቻቸውንም በጊዜ እንዲመለሱ ጥሪ እንዲያደርጉ አምባሳደሩ አሳስበዋል::

ጨረቃ ዛሬ በመታየቷ የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ ይከበራል የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ቅዳሜ በመታየቷ 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከ...
29/03/2025

ጨረቃ ዛሬ በመታየቷ የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ ይከበራል

የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ቅዳሜ በመታየቷ 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ 1 ሺህ 446ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት፤ ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር አስተምኅሮቱን በመተግበር ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የዘንድሮው የረመዷን ጾም ፍቅርና አብሮነትን የሚያሳዩ የጋራ የኢፍጣር መርሐ-ግብሮች የታዩበት እንደነበረም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት  መርሃ- ግብር አካሄደ።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልድያ ዲስትሪክት 1446ኛውን የረመዷን ወርን ምክን...
28/03/2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት መርሃ- ግብር አካሄደ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልድያ ዲስትሪክት 1446ኛውን የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ “አብሮነት ለበጎነት ፣ በረመዷን” በሚል መሪ ቃል የማዕድ ማጋራት መርሃ -ግብር አካሂዷል።

በመርሃ ግብሩም በወልድያ ከተማ ለሚኖሩ 120 አቅመ ደካሞች 384,000 ብር ወጭ በማድረግ የአይነት ድጋፍ አድርጎል ።

ባንኩ የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ያደረገው የማዕድ ማጋራት (ሶደቃ) አበረታች እና በአላህ ዘንድ ተወዳጅ ነው ያሉት የወልድያ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሟህሙድ ኑርየ ሳኒ በቀጣይም ባንኩ ከማህበረሰቡ ጎን በመቆም ይህን መሰል ማህበራዊ ሀላፊነትን የመወጣት እንቅስቃሴን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ለተደረገው ማዕድ ማጋራትም በሙስሊሙ ማህበረሰብ ስም ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው ብለዋል።

የወልድያ ዲስትሪክት ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ይልማ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመደበኛው የፋይናንስ አገልግሎት በተጨማሪ ማህበራዊ ሃላፊነቱን ለመወጣት በዚህ በተቀደሰ እና የአብሮነት መገለጫ በሆነው የረመዷን ወር በወልድያ ከተማ ለሚኖሩ አቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ ማጋራት መርሃግብር ሲያከናውን ባንኩ ለማህበረሰቡ ያለውን አጋርነት እና ጥብቅ ቁርኝነት የበለጠ ከፍ እንደሚያደርግ በማመን ነው ብለዋል፡፡

በማዕድ ማጋራት (ሶደቃ) ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖችም ለባንኩ ምስጋናቸውን ገልፀዋል።

Address

Woldia

Telephone

+251920212223

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wanzaye press ዋንዛዬ ፕሬስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wanzaye press ዋንዛዬ ፕሬስ:

Share