Yeju Standard

Yeju Standard መረጃ መሠረታዊ ፍጆታ ነው

"ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባህር (Sea of Japan) አቅጣጫ 10 ያህል ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኮሰች።ሚሳኤሎቹ የተተኮሱት በፒዮንግያንግ አቅራቢያ ከሚገኘው የሱናን (Sunan) አካባቢ ሲሆን...
14/03/2026

"ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባህር (Sea of Japan) አቅጣጫ 10 ያህል ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኮሰች።

ሚሳኤሎቹ የተተኮሱት በፒዮንግያንግ አቅራቢያ ከሚገኘው የሱናን (Sunan) አካባቢ ሲሆን፣ ያረፉትም ከጃፓን የኢኮኖሚ ክልል (EEZ) ውጭ በሆነ የባህር ክፍል ላይ ነው። እስካሁን ባለው መረጃ በአደጋው የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት የለም።"

የካሜኔይ ልጅ ከግድ*ያ ተረፉ‼️እሁድ:የካቲት 29 ቀን 2018 ዓም(ነጁ ስታንዳርድ)የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አላ ካሜኔይ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት መሞታቸውን ተከትሎ ልጃቸው ሞጅታ...
08/03/2026

የካሜኔይ ልጅ ከግድ*ያ ተረፉ‼️

እሁድ:የካቲት 29 ቀን 2018 ዓም(ነጁ ስታንዳርድ)

የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አላ ካሜኔይ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት መሞታቸውን ተከትሎ ልጃቸው ሞጅታባ ካሜኔ አባቱን ተክቶ የኢራን መሪ ይሆናል ተብሎ የታቀደ ቢሆንም በትናንትናው ዕለት በእስራኤል አየር ኃይል በተፈፀመ ጥቃት ከግድያ መትረፉን ነገር ግን የመቁሰል አደጋ እንደደረሰበት እስራኤል ቻናል 12 እንዲሁም ኒውዮርክ ፖስት አስነብቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የእስራኤል ባለስልጣናት በይፋ ያሉት ነገር የለም።

በሰሜን ወሎ ራያ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው። ሐሙስ:የካቲት 28 ቀን 2018 አም(የጁ ስታንዳርድ)በሰሜን ወሎ ዞን  ቆቦ ከተማ  የመምረጥ እና የመመረጥ መብትን የሚጠይቅ ሕዝባዊ ...
07/03/2026

በሰሜን ወሎ ራያ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ሐሙስ:የካቲት 28 ቀን 2018 አም(የጁ ስታንዳርድ)

በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ የመምረጥ እና የመመረጥ መብትን የሚጠይቅ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉ "የመምረጥ እና የመመረጥ መብት ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው" በሚል መልዕክት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። በሰልፉ የአምስት ወረዳ ሕዝብ የተሳተፈ ነው።

በሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉ የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ አላማጣ ከተማ፣ ኮረም ከተማ እና የኦፍላ ወረዳ ነዋሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን"የመምረጥና የመመረጥ መብት ህገመንግስታዊ መብታችን ነው" በሚል ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።(ወልቃይት ኮሙኒኬሽን)
05/03/2026

ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን"የመምረጥና የመመረጥ መብት ህገመንግስታዊ መብታችን ነው" በሚል ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
(ወልቃይት ኮሙኒኬሽን)

ምርጫ ቦርድ በ5 የምርጫ ክልሎች ጉዳይ ለቀረበበት ክስ ለፍርድ ቤት ምላሽ ማቅረቡ ተነገረ::የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአምስት የምርጫ ክልሎች ጉዳይ በስምረት ፓርቲ ለቀረበበት ክስ ዛሬ...
04/03/2026

ምርጫ ቦርድ በ5 የምርጫ ክልሎች ጉዳይ ለቀረበበት ክስ ለፍርድ ቤት ምላሽ ማቅረቡ ተነገረ::

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአምስት የምርጫ ክልሎች ጉዳይ በስምረት ፓርቲ ለቀረበበት ክስ ዛሬ ምላሽ እንዲያቀርብ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በታዘዘው መሠረት ምላሹን አቀረበ።

የእስራኤል ጥቃት በሊባነን። ። ። ። ። ። ። ። እስራኤል በሊባኖስ ሃዝሚህ ውስጥ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ የቦምብ ድብደባ ማካሄዷን ዘገባዎች አመላክተዋል።የሊባኖስ ብሔራዊ የዜና ኤጀንሲ እ...
04/03/2026

የእስራኤል ጥቃት በሊባነን

። ። ። ። ። ። ። ።
እስራኤል በሊባኖስ ሃዝሚህ ውስጥ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ የቦምብ ድብደባ ማካሄዷን ዘገባዎች አመላክተዋል።

የሊባኖስ ብሔራዊ የዜና ኤጀንሲ እስራኤል በቤሩት አቅራቢያ በሚገኝ ሃዝሚህ ሆቴል ላይ ጥቃት እንደፈጸመች ዘግቧል። አምቡላንስ ወደ ቦታው መላኩን አስታውቋል።

በአልጀዚራ የተረጋገጠ ቀረጻ የፈረሱ መስኮቶችና ግድግዳዎች እንዲሁም ፍርስራሾች በየቦታው ተበትነው አሳይቷል።

እንደ አልጀዚራ ዘገባ የእስራኤል ሀይሎች የፈፀሙት ጥቃት ያለ ምንም ማስጠንቀቂያ ሲሆን ምናልባትም የግድያ ሙከራ ሊሆን እንደሚችል ግምቱን አስቀምጧል።

ጥቃቱ የኮምፎርት ሆቴልን ኢላማ ያደረገ ሲሆን እስካሁን ድረስ በሰዎች ላይ ስለደረሰ አደጋ የተገለፀ ነገር የለም። የእስራኤል ጦር ማንን ወይም ምን ኢላማ ለማድረግ እንደሞከረ በትክክል እስካሁን አልተናገረም።

ሌሊቱን በተከሰቱ ጥቃቶች በአራሙን በአንድ የመኖሪያ ህንፃ ውስጥ ስድስት ሰዎች መሞታቸውን የሊባኖስ የጤና ሚንስቴር ይፋ ሲያደርግ በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ ላይ በምትገኘው ባልቤክ ሌላ የመኖሪያ ህንፃ ላይ አራት ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ 11 ሰዎች ቆስለዋል።

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እ...
25/06/2025

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።

መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።

ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።

ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::ከዚሁ ጋር በተ...
25/06/2025

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።

ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመጭው መስከረም ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ:-
📌ለኤርትራ 42 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሊያ 51 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሌ ላንድ 7 ሜጋ ዋት
📌ለየመን 240 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ የሚያስችል አዲስ መስመር ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ ነው ተብሏል።

የኢራን የኑክሌር ተቋማትና የትራምፕ እርግጠኝነት!? አሜሪካ ባለፈው ቅዳሜ ሌሊት በኢራን የኒኩሌር ተቋማት  ላይ ጥቃት መሰንዘሯን ተከትሎ፣ ኢራን  የኒኩክሌር ተቋሞቿን ለማደስ ቅድመ ዝግጅት ...
24/06/2025

የኢራን የኑክሌር ተቋማትና የትራምፕ እርግጠኝነት!?

አሜሪካ ባለፈው ቅዳሜ ሌሊት በኢራን የኒኩሌር ተቋማት ላይ ጥቃት መሰንዘሯን ተከትሎ፣ ኢራን የኒኩክሌር ተቋሞቿን ለማደስ ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆኗን ያስታወቀች ሲሆን፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ግን ኢራን በደረሰባት አውዳሚ ጥቃት ሳቢያ ከዚህ በኋላ የኒኩሌር ተቋማቷን እንደማትገነባ አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ "ኢራን መቼም ቢሆን የኒኩሌር ተቋሞቿን መልሳ አትገነባም" ብለዋል፡፡

የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ኃላፊ መሀመድ ኢስላሚ በቴሌቪዥን ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገራቸው ጥቃት የደረሰባቸውን የኒኩሌር ተቋማት ወደ ስራ ለማስገባት ማቀዷን አስታውቀዋል፡፡

የኢራንን የበቀል ማስጠንቀቂያ ተከትሎ በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ፍንዳታዎች ተሰሙ*************************ኢራን የአሜሪካን ጥቃት እንደምትበቀል ማስጠንቀቋን ተከትሎ በኳታር ዋና ከ...
23/06/2025

የኢራንን የበቀል ማስጠንቀቂያ ተከትሎ በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ፍንዳታዎች ተሰሙ
*************************

ኢራን የአሜሪካን ጥቃት እንደምትበቀል ማስጠንቀቋን ተከትሎ በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ፍንዳታዎች መሰማታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ኢራን ኳታር በሚገኘው የአሜሪካን የጦር ሰፈር ላይ 6 ሚሳኤሎችን ተኩሳለች ሲሉ የእስራኤል ባለስልጣናት ገልጸዋል።

ኳታር የአየር ክልሏን ከዘጋች ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ከኢራን የሚሳኤል ጥቃት ማስተናገዷን ሮይተርስ ዘግቧል።

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ  37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁበሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢ...
20/06/2025

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ 37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁ

በሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ይጠብቃቸዋል ሲሉ 31 የሲቪል ማህበረሰብ እና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ዜጎችን ጨምሮ መቶዎች በሚቆጠሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግባቸው እንደሚችል ተገልጿል።

ደርጅቶቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ከህገ ወጥ አደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እየጨመረ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ በእስር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ፣ #ሶማሊያና #ግብፅ ዜጎች ህይወት "ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው" ገልጸዋል።

መግለጫው፤ በተያዘው ዓመት ሰባት ኢትዮጵያውያን እና 19 የሶማሊያ ዜጎች “ሃሺሽ በማዘዋወራቸው” ግድያ እንደተፈጸመባቸው ገልጿል። በተጨማሪም “ሰኔ 9 ፣ 2017 ዓ/ም ሶስት የኢትዮጵያ ዜጎች እንደተገደሉ" እና ሌሎች ደግሞ በማንኛውም ጊዜ ልንገደል እንችላለን በሚል ስጋት ውስጥ እንዳሉ አመላክተዋል።

 #ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባ...
12/06/2025

#ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️

በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባለ።

የገንዘብ ሚኒስቴር የህግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊው አቶ ተወዳጅ መሐመድ እንዳሉት አዋጁ ተግባራዊ የሚደረገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን መገደብን ታሳቢ አድርጎ ነው።

በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ሲጸድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈጸም እንደሚማስቀጣ ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል።

Address

Al Amudin
Woldia

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeju Standard posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yeju Standard:

Share