Yeju fortune

Yeju fortune We speak what we see, we testify what we hear!

✡️ላጲሶ ጌዴሌቦ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ #ጥቅምት 30፣ 2018  #የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌዴሌቦ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡ #ላጲሶ ጌዴሌቦ (ፕ/ር) ባደረባቸው ...
09/11/2025

✡️ላጲሶ ጌዴሌቦ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

#ጥቅምት 30፣ 2018

#የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌዴሌቦ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡

#ላጲሶ ጌዴሌቦ (ፕ/ር) ባደረባቸው ሕመም ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ቤተሰቦቻቸው ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

#ነብስይማር‼️

ለትምህርት ፈላጊዎች  የ2018 ዓ.ም አዲስ ምዝገባ በወልድያ ከተማ ጀመረየዲፕሎማ ትምህርት በሦስት ዓመት የሚጠናቀቅበቀን መርሃ-ግብር፡- #በነርሲንግ (Nursing) ደረጃ- IV #በፋርማሲ(...
23/10/2025

ለትምህርት ፈላጊዎች

የ2018 ዓ.ም አዲስ ምዝገባ በወልድያ ከተማ ጀመረ

የዲፕሎማ ትምህርት በሦስት ዓመት የሚጠናቀቅ
በቀን መርሃ-ግብር፡-
#በነርሲንግ (Nursing) ደረጃ- IV
#በፋርማሲ(Pharmacy ) ደረጃ- IV
(Medical Laboratory) ደረጃ- IV
(Accounting & Finance) ደረጃ- IV
አድሜንስትሬሽን (Web development and Database Administration) ደረጃ- IV

በኤክስቴሽን መርሃ-ግብር፡-
#በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ (Accounting & Finance) ደረጃ- IV
አድሜንስትሬሽን (Web development and Database Administration) ደረጃ- IV

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፡-
- ለወንድ 135 ለሴት 122
ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ውጤትና ትራንስክሪፕት 1 ኮፒ
2 ጉርድ ፎቶ ግራፍ
#የምዝገባ ጊዜ፡- ከጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት

#ትምህርቱ ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ እና በቂ እውቀት ባላቸው ስመጥር መምህራኖች ይሰጣል፤ ይምጡ፣ ይመዝገቡ፣ ይማሩ በቂ ዕውቀት አስጨብጠን ተፈላጊ ባለሙያ እናደርግዎታለን፡፡

#አድራሻችን፡-
ወልድያ ሙጋድ ወደ ጎንደር በር በሚወስደው መንገድ አማራ ባንክ ጎን

#ለበለጠ መረጃ
ስልክ፡- +251947312010
+251920486235
+251922918501

ከዛሬ 400 ዓመት በፊት የትራንስፖርት አገልግሎት ሳይዘምን በንጉስ ፋሲለደስ ዘመን 1,000km ርቀት ላይ የተደረገ ተዓምር ልንገራችሁማ👉🏼50 ኪሎ ግራም የሚመዝን ደወል(መረዋ) ከጎንደር ከ...
08/09/2025

ከዛሬ 400 ዓመት በፊት የትራንስፖርት አገልግሎት ሳይዘምን በንጉስ ፋሲለደስ ዘመን 1,000km ርቀት ላይ የተደረገ ተዓምር ልንገራችሁማ

👉🏼50 ኪሎ ግራም የሚመዝን ደወል(መረዋ) ከጎንደር ከተማ ተነስቶ 1’000 km አቆራርጦ በምዕራብ ኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል ወንጪ ለሚገኘዉ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን እንደተሰጠ ማየት ግርምትን አይጭርም?? ይህ ደወል የዛሬ 400 ዓመት ለቅዳሴ አገልግሎት እንዲዉል በንጉስ ፋሲለደስ የተሰጠ መባ ነዉ::ደወሉ ላይ የተቀረፀዉን ጹሑፋን ተመልከቱ
ለካ ያስተሳሰረን ገመድ ጥብቅነዉ💕

"አሰብ ቀይ ባህር የኢትዮጵያ ነው!  የትኛውንም ዋጋ ከፍለን እናስመልሰዋለን" ሜጀር ጀነራል ተሾመ ገመቹ።"አሰብ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ግዛት ነው የኢትዮጵያም ህልውና ነው ፤በኢትዮጵያ ጉዳ...
01/09/2025

"አሰብ ቀይ ባህር የኢትዮጵያ ነው! የትኛውንም ዋጋ ከፍለን እናስመልሰዋለን" ሜጀር ጀነራል ተሾመ ገመቹ።

"አሰብ የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ግዛት ነው የኢትዮጵያም ህልውና ነው ፤በኢትዮጵያ ጉዳይ የመወሰን መብት ባልነበረው የሽግግር ቡድን አሳልፎ የተሰጠ ራስ ገዝ የባህር በራችን ነው፤ በዚህም ብዙ ሃገራት በናንተ ድክመት ነው እስካሁን ያልተመለሰው እንጂ እስካሁን መቆየት ያልነበረበት ነው ይሉናል ፤ አሁን ላይ የቀይ ባህር ጉዳይ የህልውናችን ጉዳይ ሆኗል ለህልውናችን ስንልም የትኛውን ዋጋ ከፍለን አሰብን እናስመልሰዋለን::"
ሜጀር ጀነራል ተሾመ ገመቹ ሰሞኑን ፕራይም በተሰኘ ሚዲያ በነበራቸው ቆይታ ሲናገሩከተሰማው የተወሰደ

ከ645 ሚለዬን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የቦሩ አጠቃላይ ሆስፒታል የሱስ ማገገሚያ ማዕከል  ግንባታው የደረሰበት አፈፃፀም፦የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በአሜሪካ ሚሲዮናውያን  1947 የተመ...
12/08/2025

ከ645 ሚለዬን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የቦሩ አጠቃላይ ሆስፒታል የሱስ ማገገሚያ ማዕከል ግንባታው የደረሰበት አፈፃፀም፦

የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በአሜሪካ ሚሲዮናውያን 1947 የተመሠረተ ሲሆን ለስጋ ደዌ፣ የቆዳና የአይን ህክምና ለመስጠት ታልሞ በልዑል አልጋወራሽ አስፋወሰን ኃ/ስላሴ ተመርቆ የተከፈተ መሆኑ ይታወቃል።

ሆስፒታሉ በአገራችን ካሉ ዝነኛና የህዝብ እምነትን ካተረፉ የጤና ተቋማት በቀዳሚነት የሚጠቀስ ሲሆን ለአካባቢያችን ማህበረሰብም ከፍተኛ አገልግሎት እየሰጠ ያለ ተቋም ነው። በአገር አቀፍ ደረጃ በተደጋጋሚ ጊዜ የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ እውቅናና ሽልማት ያገኘ ተቋም ነው።

የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በአማራ ክልል መድሃኒት የተላመደ ቲቪን በማከም የመጀሪያው ሆስፒታል ሲሆን የተሻለ ማይክሮ ባዮሎጂካል ላብራቶሪ ያለው በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል። ላብራቶሪው መድሃኒት የተለማመደን ቲቪ በተሻለ መንገድ ለመለዬት ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተገልጿል።

ሆስፒታሉ እየሰጠ ካለው አገልግሎት በተጨማሪ የሱስ ማገገሚያ ህክምና ማዕከል ግንባታ እየተገነባ ያለ ሲሆን ሲጠናቀቅ በ120 አልጋዎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የአዕምሮ ህሙማን ማከም ያስችላል ተብሏል።

ወልድያ~~~~~~ወልዲያ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ ስትሆን ከደሴ በተሰሜን 120 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች። ወልድያ ከአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህርዳር በ360 ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ...
12/08/2025

ወልድያ
~~~~~~
ወልዲያ የሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ ስትሆን ከደሴ በተሰሜን 120 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።

ወልድያ ከአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህርዳር በ360 ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን ከጥንታዊ የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት መገኛ ላሊበላ ከተማ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በቅርብ እርቀት ላይ ትገኛለች።

የወልድያ ከተማ ከተቆረቆረች ከ230 አመት በላይ ያስቆጠረች ሲሆን የቆረቆሯትም የጁና ጎንደርን አጣምረው ያስተዳድሩ በነበሩት ታላቁ ራስ አሊ በ1777ዓ.ም እንደሆነ የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡

ከ1880ዎቹ እስከ 1950ዎቹ ወልደያ የየጁ አውራጃ ማዕከል ነበርች። በዘመኑ ከተሞች የሚመሰረቱት ከየአቅጣጫው የሚመጣ ጠላትን በርቀት ለመቆጣጠር ከሚያስችል ቦታ ላይ ስለነበር ወልድያ ከተማ ተራራን ተንተርሳ እንድትቆረቆር ምክንያት እንደሆነ ይነገራል፡፡

ስለ ወልዲያ ከተማ ስያሜ ሁለት አፈታሪኮች ይነገራሉ፡፡

አንደኛው አፈታሪክ ታላቁ ራስ አሊ ቤተ- መንግስታቸውን ካሰሩበት ገብርኤል ተራራ ላይ ሆነው ቁልቁል ሲመለከቱ የቀድሞው አዋጅ መንገሪያ የዛሬው ማክሰኞ ገበያ ላይ ነጭ ነገር ይመለከታሉ፡፡ በጊዜው አሁን ከተማው ያለበት ቦታ በደን የተሞላና የውሀ ምንጭ ይበዛበት እንደነበር ይነገራል፡፡

በዚህም ንጉሱ አሽከራቸውን ከጫካው ሆኖ የሚታየው ምን እንደሆነ አጣርቶ እንዲመጣ ይልኩታል፡፡ አሽከሩም በቦታው ሲደርስ የአራስ ጨርቅ ታጥቦ የተሰጣ መሆኑን አይቶ ያየውንም ነገር ተመልሶ ለንጉሱ ነገራቸው ንጉሱም አሽከሩ የነገራቸውን ነገር አስረግጠው ሲናገሩ «ወልዳ›› ሲሉ የአካባቢውን የአነጋገር ዘዮ ተከትሎ «ወልድያ›› የሚለውቃል የቦታው ስያሜ ሆነ ይባላል፡፡

ሁለተኛው አፈታሪክ ከተለያዩ አቅጣጫ የሚመጡ የሲራራ ነጋዴዎች የሚገናኙባት ቦታ ስለነበረች በዚህም «ወልድያ›› የሚል ስያሜ እንደሰጧት ይነገራል፡፡ ከተማዋ በራስ አሊ ብትመሰረትም በኋላ ላይ መንበረ መንግስታቸውን ደብረ ታቦር በማድረጋቸው የየጁ ነዋሪ በንጉሱ ትኩረት ተነፍጎ ነበር። በመሆኑም ብዙ ሽፍቶች ሀብት ንብረቱ ሲዘረፉና ሰላሙ ሲደፈርስ እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡ ለዚህም የአካባቢዉ ህብረተሰብ ብሶቱን በስነ- ቃል ሲገለፅ፦
«ማማው ደብረ-ታቦር ደጋሌቱ የጁ ወንጭፍ አጠረና ወፎች እህል ፈጁ››ይባል ነበር፡፡

ወልድያ አራት ዋናዋና የመንገድ በሮችን አማክላ የያዘች የቱሪስቶች መተላለፊያ ኮሪደር በመሆኗ ዛሬም በመገናኛነቷ የምትታወቅ ከተማ ነች፡፡

በከተማዋና ከከተማዋ በቅርብ እርቀት የሚገኙ በርካታ የቱሪስት መስህቦች ያሉ ሲሆን በቅርብ ርቀት ከሚገኙ የቱርስት መስህቦች ውስጥ የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት ዋናው ነው። የወልድያ ከተማ ወደ አክሱም ፣ ላሊበላ ፣ ጎንደርና ጂቡቲ የሚሄዱ ቱሪስቶች ማረፊያ ናት

እምዬ ወልደያ 😍

ከምናኔያቸዉ ጽናት የተነሳ ጫማ የማያደርጉት የወልደያ ተወላጅ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ታዴዎስ ቀዳማዊ ሊቀ ጳጳስ /1888 - 1957 .ዓ.ም/የጁ (ወልደያ )  ገነተ ልዑል ማርያም ተወለዱ  ...
12/08/2025

ከምናኔያቸዉ ጽናት የተነሳ ጫማ የማያደርጉት የወልደያ ተወላጅ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ታዴዎስ ቀዳማዊ ሊቀ ጳጳስ /1888 - 1957 .ዓ.ም/

የጁ (ወልደያ ) ገነተ ልዑል ማርያም ተወለዱ ። የታላቁ ሊቅ የአለቃ ድንቁ አጎት ናቸዉ ።
ብፁነታቸዉ ብዙ ትምህርትን ተምረዋል ፍትሐ ነገሥት ና አቡሻህርን ጨምሮ ትምህርት በቃኝ ሳይሉ በብዙ ቦታ በመንቀሳቀስ ሊቃዉንትነትን ደረጃ ይዘዋል ። ትህትናቸዉ: የአገልግሎት ትጋታቸዉ ና ሊቅ እነታቸዉ በቤተ መንግስቱ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ና በቀዳማዊት እቴጌ ጨምሮ መነጋገሪያ ሁኖ ስለነበር ተጠርተዉ ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ወደ አከበራት በእየሩሳሌም ገዳማት ላይ አስተዳዳሪ ሁነዉ ተሾሙ ። ብፁዕነታቸዉ ኢትዮጽያ በወራሪ ኢጣሊያን ፋሽስት በተወረረች ጊዜ ድምጻቸዉን ለዓለም ሕዝብ ሲያሰሙና በጸሎት በመትጋት ሀገራቸዉን ሲረዱ ቆይተዋል። ብፁዕነታቸዉ ያላቸዉ እዉቀትና መንፈሳዊ አገልግሎታቸዉ ን የወዱ የነበሩት አጼ ኃይለ ሥላሴ ከእየሩስ አሌም አሰጠርተዋቸዉ ለጽጽስና እንዲወዳደሩ አደረጎቸዉ ። በዚህ በተደረገዉ ምርጫ ላይ በከፍተኛ ድምፅ አንደኛ በመሆን በብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሊቀ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ አንብሮተ እድ ብፁዕ አቡነ ታዲዎስ ተብለዉ የጎሬ ሀገር ጳጳስ ሁነዉ ተሾሙ ።
እኒህ ጳጳስ ለትዉልድ ሀገራቸዉ ወልደያ ልዩ ፍቅር የነበራቸዉ በመሆኑ የሚያገኞትን ደመወዝ በማጠራቀም ወደ ትዉልድ ሀገራቸዉ ወልደያ የጁ በመምጣት በ1948 ዓ.ም ስልሳ ሺህ ብር ያጠራቀሞትን በማዉጣት ጉባርጃ ገነተ ልዑል ማርያምን
ቤተክርስቲያኖች በጎጆ በነበሩበት ዘመን ለእመቤታችን እና ለወልደያ ባላቸዉ ፍቅር የተነሳ ዉብ አድርገዉ በግንብ አሳንጸዋል ።
ብፁእነታቸዉ እረፍታቸዉ ሲቃረብ ወደ ቀድሞዉ ቦታቸዉ እየሩሳሌም በመሄድ እራሳቸዉን ዝቅ በማድረግ በተራ መናኝነት ሲኖሩ ቆይተዉ ታኀሣሥ 10 ቀን 1957 .ዓ.ም ከቀኑ በ12 ሰዓት ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ። ሥርዓተ ቀብራቸዉም በቅድስት ሀገር እየሩሳሌም ተፈጽሞል ።
የብፁዕነታቸው ረድኤት አይለየን ። አሜን !
/ብርሐነሥላሴ/

"ወላሂ ማርያም ነች":- አነጋጋሪው የቅድስት ድንግል ማርያም ምስል❗️ሰሞኑን በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የታየው ሁኔታ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። በሰማይ ላይ በድንገት ብቅ ያለው ደመና የቅድስት ድ...
08/08/2025

"ወላሂ ማርያም ነች":- አነጋጋሪው የቅድስት ድንግል ማርያም ምስል❗️

ሰሞኑን በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የታየው ሁኔታ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። በሰማይ ላይ በድንገት ብቅ ያለው ደመና የቅድስት ድንግል ማርያም ምስል ብዙዎች ተመልክተዋል።

ይህ አስደናቂ ትዕይንት ሲነገር በቪዲዮም ተቀርጿል። በተለይም አንድ ወጣት ከልቡ "ወላሂ ማርያም" ነች እያለ ሲደመጥ፣ ክስተቱ ምን ያህል አስገራሚ እንደነበር ያሳያል።

ብዙዎች እንደሚሉት፣ በደመናው መካከል የድንግል ማርያም ምስል መታየቱ እጅግ መንፈሳዊ ስሜት ቀስቅሷል።

ይህ ያልተለመደ የሰማይ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ብዙዎችን እያነጋገረ ሲሆን፣ ተአምር ነው የሚሉ አስተያየቶች እየተሰጡበት ይገኛል።

የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄ ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል!   ይህ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወልድያ ተወላጅ እና ወዳጅ እንዲሁም የአላማጣ፣ ዋጃ፣ ቆቦ፣ አራዱም፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ዶሮ ግብር፣ ድሬ ሮቃ፣...
03/08/2025

የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄ ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል!



ይህ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወልድያ ተወላጅ እና ወዳጅ እንዲሁም የአላማጣ፣ ዋጃ፣ ቆቦ፣ አራዱም፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ዶሮ ግብር፣ ድሬ ሮቃ፣ ሀሮ፣ ሀራ፣ ዶሮ ግብር፣ ስሪንቃ፣ መርሳ፣ መሀል አምባ፣ ሊብሶ፣ ጊራና፣ ውርጌሳ፣ ውጫሌ፣ ሳንቃ፣ እስታይሽ፣ ሙጃ ... እና አጎራባች ቀበሌዎች የተወለዳችሁ፣ የምትኖሩ እና ወዳጅ የሆናችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ይመለከታል።

በዚህ የ10 ቀን ዘመቻ የምንሰራው የወልድያ ኤርፖርት እንዲፈቀድ እና ስራ እንዲጀመር ዘመቻውን በሚከተለው መንገድ መቀላቀል እና ማሳለጥ እንችላለን :-

1. የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄን የተመለከቱ ማንኛውንም ፖስት ላይክ ማድረግ፣ ኮሜንት ማድረግ እና ሼር ማድረግ፣

2. እነዚህን ፖስቶች ቲክቶክ ላይ ወስደን መልቀቅ፣ የተለቀቁ ፖስቶችን ❤ ማድረግ፣ ኮሜንት እና Copy Link ማድረግ፣

3. በያንዳንዱ ፖስታችን ውስጥ እነዚህን ሀሽታጎች ወስደን መጠቀም፣ ኮሜንት ላይ እነዚህን ሀሽታጎች መጠቀም፣ ይሄም አንዱን ሀሽታግ የተጫነ ሰው ይሄን ሀሽታግ የተጠቀሙ ሰዎች ፖስቶችን ስለሚያመጣልን ተደራሽ እንዲሆን ያደርጋል።
የምንጠቀማቸው ሀሽታጎች እነዚህ ናቸው :-


















4. በየፖስታችሁ እና ኮሜንቱ Woldia_Times ን ኮሜንት ላይ ሜንሽን አድርጓት። ፖስታችሁን ሼር እናደርጋለን። ፅሁፎችን እና ፎቶዎችን በገፃችን ከዛሬ ጀምሮ እናቀርባለን። ይህ የ1 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ጥያቄ እስኪመለስ ከፊት ቆመን እናስተባብራለን!

ወልድያዎች፣ የአካባቢው ተወላጆች እና ወዳጆች የት ናችሁ? እስኪ እጃችሁን አሳዩን?

በመኪና አደጋ የሰው ህይወት አለፈ ከደሴ ወደ ኮምቦልቻ  ሲጓዝ የነበረ አይሱዚ  መኪና በተለምዶ ሀረጎ ተብሎ በሚጠራ ቦታ  ላይ በዛሬው እለት ከቀኑ 7:00 ሰአት  በደረሰበት የመገልበጥ አደ...
30/07/2025

በመኪና አደጋ የሰው ህይወት አለፈ

ከደሴ ወደ ኮምቦልቻ ሲጓዝ የነበረ አይሱዚ መኪና በተለምዶ ሀረጎ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ላይ በዛሬው እለት ከቀኑ 7:00 ሰአት በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የሰው ህይወት አልፏል።

የኮምቦልቻ ከተማ አሰተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንገድ ትራፍሪክ ደህንነት ማረጋገጫ ዋና ክፍል ሀላፊው ኮ/ር ብርሀኑ ተሾመ ለፔጃችን እንደተናገሩት በአደጋ አሸከርካሪውና ረዳቱን ጨምሮ የ3 ስዎች ህይወት ማለፉን አንስዋል።

የአደጋው ምክንያት ምርመራ ላይ መሆኑን ተነስቷል።

20/07/2025

ቀድመን ለመከላከል የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት!!

ሰሞኑን አንዳንድ ሰዎች ከማይታወቁ ግለሰቦች ስልክ ጥሪ እየደረሳቸው እንደሆነና ስልክ ቁጥሮቹም፣
Tel: +375602605281
Tel: +37127913091
Tel: +37178565072
Tel: +56322553736
Tel: +37052529259
Tel: +255901130460
ወይም ማንኛውም ቁጥር በ+371,+375,+381 የሚጀምሩ እንደሆነ ለመንግስት አካላት አሳውቀዋል።
እነዚህን ስልክ ቁጥሮች የሚጠቀሙት ግለሰቦች ሲደውሉ አንዴ ብቻ ከጠራ በኋላ ይዘጉታል።

እርስዎ መልሰው ሲደውሉ የርስዎን Contact List በ 3sec ውስጥ ወደ ራሳቸው ኮፒ በማድረግ እንዲሁም ሞባዬልዎ ላይ ስለ እርስዎ ባንክ ወይም ክሬዲት ካርድ መረጃ በአንዴ በመጥለፍ የማጭበርበር ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።

ከላይ በተጠቀሱት ስልክ ቁጥር ከተደወለሎት አይመልሱ ፡ወይም መልሰው አይደውሉ።እንዲሁም በማንኛውም ደዋይ #90 or #09 በመስመር እንዲነኩ ከተጠየቁ አይንኩ።

ምክንያቱም በቀላሉ ሲማችሁን አክሰስ በማድረግ በናንተ ስም የፈለጉት ወንጀል በመስራት እራሳቸውን ስለሚሸሽጉ ነው።
ይህንን መልዕክት ለቻላችሁ ሰው ፎርዋርድ በማድረግ ህዝባችንን ከዚህ መሰል ማጭበርበሮች እንታደግ።
ደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

በወላይታ ሶዶ ከተማ የ35 አመት ወጣትን በቀንዱ ወግቶ የገደለው በሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገለጹ።ገዳዩን በሬ በቁጥጥር ስር ለማዋል በ...
29/06/2025

በወላይታ ሶዶ ከተማ የ35 አመት ወጣትን በቀንዱ ወግቶ የገደለው በሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገለጹ።

ገዳዩን በሬ በቁጥጥር ስር ለማዋል በርካታ አባል ፖሊስ ተመድበው በሬው ላይ ከባድ የሚባል ጉዳት መድረሱን የደረሰን መረጃ ያሳያል።

የበሬው ባለቤት ከበሬው ጋር አብሮ መያዝ መቻሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ መረጃ ክፍል ገልጿል ሲል ዜና ወላይታ ዘግቧል።

Address

Woldia

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeju fortune posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yeju fortune:

Share