Yeju fortune

Yeju fortune We speak what we see, we testify what we hear!

አሁን ባለው ውድድር ከ31ዱ የንግድ ባንኮች 25ቱ መቀጠል የሚያስችላቸው ቁመና ላይ አይደሉም-   ብሄራዊ ባንክበሀገሪቱ ካሉት 31 የንግድ ባንኮች ውስጥ 25ቱ አሁን ባለው ከባድ የገበያ ውድ...
18/03/2026

አሁን ባለው ውድድር ከ31ዱ የንግድ ባንኮች 25ቱ መቀጠል የሚያስችላቸው ቁመና ላይ አይደሉም- ብሄራዊ ባንክ
በሀገሪቱ ካሉት 31 የንግድ ባንኮች ውስጥ 25ቱ አሁን ባለው ከባድ የገበያ ውድድር ውስጥ መቀጠል ስለማይችሉ ተዋህደው ጠንካራ ባንኮችን መፍጠር ብቸኛው አማራጭ መሆኑን ብሔራዊ ባንክ ገለፀ፡፡

ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ እንዳይሄዱ ተከለከሉ‼️➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ዛሬ ጠዋት ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ፥ በሁለት ባሶች  የተሳፈሩ መንገደኞች ከትግራይ እንዳይወጡ ተከለከሉ። በመውጫ መ...
15/03/2026

ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ እንዳይሄዱ ተከለከሉ‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ዛሬ ጠዋት ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ፥ በሁለት ባሶች የተሳፈሩ መንገደኞች ከትግራይ እንዳይወጡ ተከለከሉ።

በመውጫ መንገዶችም የፍተሻ ኬላዎች መደረጋቸውም ከመቐለ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የትግራይ ወጣት ጦርነት በመጠየፍ ከትግራይ ክልል በገፍ እየሸሸ መሆኑ መዘገባችን አይዘነጋም።

 : ኢራን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ "በህይወት የሉም" ማለቷ አለም አቀፉን ማህበረሰብ አስደንግጧል !የቴህራን ባለስልጣናት በአሁኑ ጊዜ እስራኤል ሞራል ለመጠበቅ እና የ...
14/03/2026

: ኢራን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ "በህይወት የሉም" ማለቷ አለም አቀፉን ማህበረሰብ አስደንግጧል !

የቴህራን ባለስልጣናት በአሁኑ ጊዜ እስራኤል ሞራል ለመጠበቅ እና የአመራር ችግርን ለመደበቅ የተራቀቀ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ጥልቅ የውሸት ቴክኖሎጂን በመጠቀም በአደባባይ ቪዲዮ ላይ "አሻንጉሊት" እየተጠቀመች ነው ብሏል።

አዲሱን የኢራን መንፈሳዊ መሪ ለመያዝ ዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ወሮታ እንደምትከፍል ገለፀች። የሟቹ አያቶላህ አሊ ኻመኔይ  ልጅ ሞጅታባ ኻመኔይ  እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት የ...
14/03/2026

አዲሱን የኢራን መንፈሳዊ መሪ ለመያዝ ዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ወሮታ እንደምትከፍል ገለፀች። የሟቹ አያቶላህ አሊ ኻመኔይ ልጅ ሞጅታባ ኻመኔይ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት የት እንዳሉ መረጃ ለጠቆመ እስከ አስር ሚሊዮን ዶላር እንደሚከፈል ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በኢንተርኔት ባሰራጨው ማስታወቂያ ከኻመኔይን በተጨማሪ የሀገር ውስጥ ሚኒስትሩን፣ የኢራን ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ እና የስለላ ሚኒስትሩን በጠቅላላ 10 ከፍተኛ ባለስልጣናትን እያፈላለገ ይገኛል።

የ56 ዓመቱ ሞጅታባ ኻመኔይ የአባታቸውን ቦታ ከተረከቡ ጊዜ አንስቶ በመገናኛ ብዙኃን ቀርበው አያውቁም። እንደ ዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሮቢዮ እና መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት ከሆነ ኻመኔይን ጉዳት ሳይደርስባቸው አልቀረም። ይህ ግን በየትኛውም ወገን አልተረጋገጠም።

የግብፅ ወታደር በሱዳን‼️ግብፅ ለሱድኑ ወታደራዊ መሪ አልቡርሃን የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ የቀጠለች ሲሆን የሱዳንን የእርስ በርስ ጦርነት እየመራ የተገደለው ግብፃዊ ጄነራል መነጋገሪያ ሆ...
14/03/2026

የግብፅ ወታደር በሱዳን‼️
ግብፅ ለሱድኑ ወታደራዊ መሪ አልቡርሃን የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ የቀጠለች ሲሆን የሱዳንን የእርስ በርስ ጦርነት እየመራ የተገደለው ግብፃዊ ጄነራል መነጋገሪያ ሆኗል።
ከቀናት በፊት የግብፅ ወታደራዊ መሪ የሆነው ብርጋዴር ጀነራል አህመድ ሰሚር ከ3 የግብፅ ወታደሮች ጋር ከሱዳን ጦር ጋር በመሆን በሰው አልባ አውሮፕላኖች አጠቃቀም ላይ የቴክኒክ የማማከር ዘመቻ ሲያደርጉ ከቀናት በፊት በሱዳን ግዛት ውስጥ በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ጥቃት መገደሉን ከአፍሪካን ኢንተለጀንስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

በወልዲያ ከተማ ዳቦ ቤት ኬላ 102 ጀሪካ ናፍጣ የጫነ የጭነት መኪና በቁጥጥር ስር ዋለ❗የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አበራ ካሳው እንደገለጹት፣ መነሻውን ከአዲስ ...
08/03/2026

በወልዲያ ከተማ ዳቦ ቤት ኬላ 102 ጀሪካ ናፍጣ የጫነ የጭነት መኪና በቁጥጥር ስር ዋለ❗
የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አበራ ካሳው እንደገለጹት፣ መነሻውን ከአዲስ አበባ አድርጎ ወደ መስመር ሲጓዝ የነበረው ሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 - 25975 አ.አ የሆነ የጭነት መኪና በቁጥጥር ስር የዋለው በደረሰ ጥቆማ መሠረት ነው።

መኪናው በላዩ ላይ በርከት ያለ ፍራሽና የሞተር ዘይት ጭኖ የነበረ ቢሆንም በውስጡ ተደብቆ የተገኘው ህገ-ወጥ ነዳጅ መሆኑ ታውቋል።
=====================

 #አስቸኳይ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ፤ ለባለፉት ሰባት ተከታታይ ዓመታት ፓርቲውን በመሪነት ያገለገሉትን ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋን ከኃ...
08/03/2026

#አስቸኳይ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ፤ ለባለፉት ሰባት ተከታታይ ዓመታት ፓርቲውን በመሪነት ያገለገሉትን ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋን ከኃላፊነታቸው አሰናብቷል።

የካሜኔይ ልጅ ከግድ*ያ ተረፉ‼️እሁድ:የካቲት 29 ቀን 2018 ዓም(የጁ ፎርቹን)የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አላ ካሜኔይ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት መሞታቸውን ተከትሎ ልጃቸው ሞጅታባ ...
08/03/2026

የካሜኔይ ልጅ ከግድ*ያ ተረፉ‼️

እሁድ:የካቲት 29 ቀን 2018 ዓም(የጁ ፎርቹን)

የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አላ ካሜኔይ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት መሞታቸውን ተከትሎ ልጃቸው ሞጅታባ ካሜኔ አባቱን ተክቶ የኢራን መሪ ይሆናል ተብሎ የታቀደ ቢሆንም በትናንትናው ዕለት በእስራኤል አየር ኃይል በተፈፀመ ጥቃት ከግድያ መትረፉን ነገር ግን የመቁሰል አደጋ እንደደረሰበት እስራኤል ቻናል 12 እንዲሁም ኒውዮርክ ፖስት አስነብቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የእስራኤል ባለስልጣናት በይፋ ያሉት ነገር የለም።

በሰሜን ወሎ ራያ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው። ሐሙስ:የካቲት 28 ቀን 2018 አም(የጁ ፎርቹን)በሰሜን ወሎ ዞን  ቆቦ ከተማ  የመምረጥ እና የመመረጥ መብትን የሚጠይቅ ሕዝባዊ ሰላ...
07/03/2026

በሰሜን ወሎ ራያ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ሐሙስ:የካቲት 28 ቀን 2018 አም(የጁ ፎርቹን)

በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ የመምረጥ እና የመመረጥ መብትን የሚጠይቅ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉ "የመምረጥ እና የመመረጥ መብት ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው" በሚል መልዕክት ነው እየተካሄደ የሚገኘው። በሰልፉ የአምስት ወረዳ ሕዝብ የተሳተፈ ነው።

በሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉ የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ አላማጣ ከተማ፣ ኮረም ከተማ እና የኦፍላ ወረዳ ነዋሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ምክንያት እስከ 13.5 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያጣ ገለፀአርብ:የካቲት 27 ቀን 2018 ዓም(የጁ ፎርቹን)የኢትዮጵያ አየር መ...
06/03/2026

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ምክንያት እስከ 13.5 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያጣ ገለፀ

አርብ:የካቲት 27 ቀን 2018 ዓም(የጁ ፎርቹን)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመካከለኛው ምሥራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት በሳምንት እስከ 13.5 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያጣ ለቢቢሲ ተናግሯል።

በመካከለኛው ምሥራቅ አሜሪካ እና እስራኤል ቅዳሜ ዕለት በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስር መዳረሻዎች የሚያደርጋቸውን በረራዎች መሰረዙን ገልጿል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር "ለሰላም ዘብ እንቆማለሁ ለልማት አርበኛ እሆናለሁ! " በሚል መሪ መልዕክት ከጠቅላላ መንግስት ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል።በመድረኩም እንደ ሀገርና እንደ ክልል...
05/03/2026

የወልድያ ከተማ አስተዳደር "ለሰላም ዘብ እንቆማለሁ ለልማት አርበኛ እሆናለሁ! " በሚል መሪ መልዕክት ከጠቅላላ መንግስት ሰራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩም እንደ ሀገርና እንደ ክልል ያጋጠመንን አሁናዊ የሰላም እጦት ስጋት የሚያሳይ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በሰሜኑ ጦርነት የማንነታችን መገለጫዎች ናቸው ብለን ዋጋ የከፈልን ባቸውን ዛሬ ላይ በጠላት ሊያዙ ነው ሲባል ገሸሽ ማለት የስሜትና የኩርፊያ ፖለቲካ መገለጫ ነው ያሉት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጉስ ዝናቡ ናቸው።

እንዳትጠጡ ተብሏል‼“ፋይን” የታሸገ ውሃ የምርት ቁጥር 620 እንዳይጠጣ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ የአዲስ አበባ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን “ፋይን” (Fine) የታሸገ ውሃ ላይ ባደረገው ምርመራ...
05/03/2026

እንዳትጠጡ ተብሏል‼

“ፋይን” የታሸገ ውሃ የምርት ቁጥር 620 እንዳይጠጣ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ

የአዲስ አበባ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን “ፋይን” (Fine) የታሸገ ውሃ ላይ ባደረገው ምርመራ፣ ምርት ቁጥር 620 ጥራትና ደህንነቱን ያልጠበቀ መሆኑን አረጋግጧል።

ኅብረተሰቡ ይህንን የምርት ቁጥር ያለውን ውሃ እንዳይጠቀም ጥብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ባለስልጣኑ ምርመራውን ያካሄደው ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ሲሆን፣ በውሃው ውስጥ ዝልግልግ ያለ ባዕድ ነገር መገኘቱንና የማምረት ሂደቱም የጤና መስፈርቶችን ያልተከተለ መሆኑን ገልጿል።የተላለፉ ውሳኔዎች፦

📌 ድርጅቱ ችግሩን በቋሚነት ማስተካከሉ ተረጋግጦ በጽሁፍ ፈቃድ እስካላገኘ ድረስ ከየካቲት 24 ጀምሮ ምርት ወደ ገበያ እንዳያሰራጭ ታግዷል።

የጁ ፎርቹን
📌 በገበያ ላይ የሚገኘው የምርት ቁጥር 620 ውሃ በ 5 ቀናት ውስጥ ተሰብስቦ ለባለስልጣኑ ሪፖርት እንዲደረግ ታዟል።

📌 ኅብረተሰቡ ይህንን የምርት ቁጥር በገበያ ላይ ሲያገኝ በነፃ ስልክ መስመር 8864 ላይ በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ዳይሬክተር እስጢፋኖስ ጌታቸው አሳስበዋል።

Address

Woldia

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeju fortune posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yeju fortune:

Share