Woldia Fortune

Woldia Fortune መረጃ አርነት ያወጣሀል

የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄ ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል!   ይህ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወልድያ ተወላጅ እና ወዳጅ እንዲሁም የአላማጣ፣ ዋጃ፣ ቆቦ፣ አራዱም፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ዶሮ ግብር፣ ድሬ ሮቃ፣...
03/08/2025

የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄ ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል!



ይህ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የወልድያ ተወላጅ እና ወዳጅ እንዲሁም የአላማጣ፣ ዋጃ፣ ቆቦ፣ አራዱም፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ዶሮ ግብር፣ ድሬ ሮቃ፣ ሀሮ፣ ሀራ፣ ዶሮ ግብር፣ ስሪንቃ፣ መርሳ፣ መሀል አምባ፣ ሊብሶ፣ ጊራና፣ ውርጌሳ፣ ውጫሌ፣ ሳንቃ፣ እስታይሽ፣ ሙጃ ... እና አጎራባች ቀበሌዎች የተወለዳችሁ፣ የምትኖሩ እና ወዳጅ የሆናችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ይመለከታል።

በዚህ የ10 ቀን ዘመቻ የምንሰራው የወልድያ ኤርፖርት እንዲፈቀድ እና ስራ እንዲጀመር ዘመቻውን በሚከተለው መንገድ መቀላቀል እና ማሳለጥ እንችላለን :-

1. የወልድያ ኤርፖርት ጥያቄን የተመለከቱ ማንኛውንም ፖስት ላይክ ማድረግ፣ ኮሜንት ማድረግ እና ሼር ማድረግ፣

2. እነዚህን ፖስቶች ቲክቶክ ላይ ወስደን መልቀቅ፣ የተለቀቁ ፖስቶችን ❤ ማድረግ፣ ኮሜንት እና Copy Link ማድረግ፣

3. በያንዳንዱ ፖስታችን ውስጥ እነዚህን ሀሽታጎች ወስደን መጠቀም፣ ኮሜንት ላይ እነዚህን ሀሽታጎች መጠቀም፣ ይሄም አንዱን ሀሽታግ የተጫነ ሰው ይሄን ሀሽታግ የተጠቀሙ ሰዎች ፖስቶችን ስለሚያመጣልን ተደራሽ እንዲሆን ያደርጋል።
የምንጠቀማቸው ሀሽታጎች እነዚህ ናቸው :-


















4. በየፖስታችሁ እና ኮሜንቱ Woldia_Times ን ኮሜንት ላይ ሜንሽን አድርጓት። ፖስታችሁን ሼር እናደርጋለን። ፅሁፎችን እና ፎቶዎችን በገፃችን ከዛሬ ጀምሮ እናቀርባለን። ይህ የ1 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ጥያቄ እስኪመለስ ከፊት ቆመን እናስተባብራለን!

ወልድያዎች፣ የአካባቢው ተወላጆች እና ወዳጆች የት ናችሁ? እስኪ እጃችሁን አሳዩን?

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እ...
25/06/2025

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።

መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።

ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።

ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::ከዚሁ ጋር በተ...
25/06/2025

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ክፍያ በ400% ሊጨምር እንደሚችል ተሰምቷል።

ከሦስት ዓመታታ በኃላ የኤሌክትሪክ አግልግሎት ታሪፍ በ400 ፐርሰንት እንደሚጨምር የዘገበው ሪፖርተር ነው::

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በመጭው መስከረም ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ:-
📌ለኤርትራ 42 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሊያ 51 ሜጋ ዋት
📌ለሶማሌ ላንድ 7 ሜጋ ዋት
📌ለየመን 240 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ የሚያስችል አዲስ መስመር ለመፍጠር ታቅዶ እየተሰራ ነው ተብሏል።

የ25 ቀናት እስር ተወሰነበት‼በቅርቡ የትራፊክ ፖሊስ እንዲሁም የመንግስት ስራተኛ የሆነ ግለሰብ የደበደበው ተከሳሽ ታማኝ አስማማው አንዳርጌ 3 ዓመት የተፈረደበት ሲሆን ነገር ግን:- ተከሳሽ...
25/06/2025

የ25 ቀናት እስር ተወሰነበት‼

በቅርቡ የትራፊክ ፖሊስ እንዲሁም የመንግስት ስራተኛ የሆነ ግለሰብ የደበደበው ተከሳሽ ታማኝ አስማማው አንዳርጌ 3 ዓመት የተፈረደበት ሲሆን ነገር ግን:-

ተከሳሽ:-

1. አረንጓዴ አሽራ በችግኝ ተከላ አስተዋጽኦ ያደረገ ስለሆነ

2.የቤተሰብ አስተዳዳሪ ስለሆነ

3. ታማሚ ስለሆነ

4. ከዚህ በፊት ምንም አይነት የወንጀል ክስ የሌለበት እና ፀባዩ በጣም ጥሩ የሆነ ግለሰብ ስለሆነ ከሌላ የተዘርዘሩትን በሙሉ ታይተው
ከ3 ዓመት ወደ 25 ቀን ወርዶ ተከሳሽ " ታማኝ አስማማው አንዳርጌ " የ25 ቀን እስር እንዲታሰር ተፍርዶበታል::

የኢራን የኑክሌር ተቋማትና የትራምፕ እርግጠኝነት!? አሜሪካ ባለፈው ቅዳሜ ሌሊት በኢራን የኒኩሌር ተቋማት  ላይ ጥቃት መሰንዘሯን ተከትሎ፣ ኢራን  የኒኩክሌር ተቋሞቿን ለማደስ ቅድመ ዝግጅት ...
24/06/2025

የኢራን የኑክሌር ተቋማትና የትራምፕ እርግጠኝነት!?

አሜሪካ ባለፈው ቅዳሜ ሌሊት በኢራን የኒኩሌር ተቋማት ላይ ጥቃት መሰንዘሯን ተከትሎ፣ ኢራን የኒኩክሌር ተቋሞቿን ለማደስ ቅድመ ዝግጅት ላይ መሆኗን ያስታወቀች ሲሆን፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ግን ኢራን በደረሰባት አውዳሚ ጥቃት ሳቢያ ከዚህ በኋላ የኒኩሌር ተቋማቷን እንደማትገነባ አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ "ኢራን መቼም ቢሆን የኒኩሌር ተቋሞቿን መልሳ አትገነባም" ብለዋል፡፡

የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ኃላፊ መሀመድ ኢስላሚ በቴሌቪዥን ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገራቸው ጥቃት የደረሰባቸውን የኒኩሌር ተቋማት ወደ ስራ ለማስገባት ማቀዷን አስታውቀዋል፡፡

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ  37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁበሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢ...
20/06/2025

ዜና፡ በሳዑዲ_አረቢያ 37 ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁ

በሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ይጠብቃቸዋል ሲሉ 31 የሲቪል ማህበረሰብ እና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ዜጎችን ጨምሮ መቶዎች በሚቆጠሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግባቸው እንደሚችል ተገልጿል።

ደርጅቶቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ከህገ ወጥ አደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እየጨመረ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ በእስር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ፣ #ሶማሊያና #ግብፅ ዜጎች ህይወት "ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው" ገልጸዋል።

መግለጫው፤ በተያዘው ዓመት ሰባት ኢትዮጵያውያን እና 19 የሶማሊያ ዜጎች “ሃሺሽ በማዘዋወራቸው” ግድያ እንደተፈጸመባቸው ገልጿል። በተጨማሪም “ሰኔ 9 ፣ 2017 ዓ/ም ሶስት የኢትዮጵያ ዜጎች እንደተገደሉ" እና ሌሎች ደግሞ በማንኛውም ጊዜ ልንገደል እንችላለን በሚል ስጋት ውስጥ እንዳሉ አመላክተዋል።

 #ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባ...
12/06/2025

#ከ10ሺ ብር በላይ ካሽ መያዝ ያስቀጣል ተባለ‼️

በግብይት ወቅት ከ 10 ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብን መጠቀም፣ለከፋዩ በወጪነት፣ለተቀባዩ ደግሞ አስተዳደራዊ ቅጣት እንዲጣልበት ያደርጋል ተባለ።

የገንዘብ ሚኒስቴር የህግ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊው አቶ ተወዳጅ መሐመድ እንዳሉት አዋጁ ተግባራዊ የሚደረገው በጥሬ ገንዘብ የሚፈፀም ግብይትን መገደብን ታሳቢ አድርጎ ነው።

በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ሲጸድቅ ከ10,000 ብር በላይ ግብይትን በጥሬ ገንዘብ መፈጸም እንደሚማስቀጣ ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል።

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ከምንጊዜም ምርጥ ኢትዮጵያውያን የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ...
11/06/2025

ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ከምንጊዜም ምርጥ ኢትዮጵያውያን የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው ሙሉጌታ ከበደ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኮከብ ሙሉጌታ ከበደ ባጋጠመው ህመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሕይወቱ አልፏል፡፡

ሙሉጌታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ለበርካታ ዓመታት በድንቅ ብቃት ተጫውቶ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ በነበረው ቆይታ አምበል ሆኖም መጫወት የቻለ ድንቅ ተጫዋች ነበር።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ለበርካታ ዓመታት በመጫወት የሚታወቀው ሙሉጌታ ከበደ (ወሎየዉ) ባጋጠመው ህመም ምክንያት በህክምነ ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል።

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።   በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ንግድና ገበ...
13/04/2025

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረን ሽንኩርት መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታውቋል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኀላፊ አዲሱ ወንድሙ ሁለት አይሱዙ መኪና ሽንኩርት በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ሥር መዋሉን ተናግረዋል። ሽንኩርቱ በቁጥጥር ሥር የዋለው ለጅምላ ንግድ ባልተፈቀደ እና ከሽንኩርት ንግድ ጋር ባልተገናኘ የንግድ ፈቃድ ሲንቀሳቀስ መኾኑንም ገልጸዋል።

በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘው ሽንኩርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለኅብረተሰቡ እንደሚቀርብም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት  መርሃ- ግብር አካሄደ።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልድያ ዲስትሪክት 1446ኛውን የረመዷን ወርን ምክን...
28/03/2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት መርሃ- ግብር አካሄደ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወልድያ ዲስትሪክት 1446ኛውን የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ “አብሮነት ለበጎነት ፣ በረመዷን” በሚል መሪ ቃል የማዕድ ማጋራት መርሃ -ግብር አካሂዷል።

በመርሃ ግብሩም በወልድያ ከተማ ለሚኖሩ 120 አቅመ ደካሞች 384,000 ብር ወጭ በማድረግ የአይነት ድጋፍ አድርጎል ።

ባንኩ የረመዷን ወርን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ያደረገው የማዕድ ማጋራት (ሶደቃ) አበረታች እና በአላህ ዘንድ ተወዳጅ ነው ያሉት የወልድያ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሟህሙድ ኑርየ ሳኒ በቀጣይም ባንኩ ከማህበረሰቡ ጎን በመቆም ይህን መሰል ማህበራዊ ሀላፊነትን የመወጣት እንቅስቃሴን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ለተደረገው ማዕድ ማጋራትም በሙስሊሙ ማህበረሰብ ስም ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው ብለዋል።

የወልድያ ዲስትሪክት ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ይልማ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመደበኛው የፋይናንስ አገልግሎት በተጨማሪ ማህበራዊ ሃላፊነቱን ለመወጣት በዚህ በተቀደሰ እና የአብሮነት መገለጫ በሆነው የረመዷን ወር በወልድያ ከተማ ለሚኖሩ አቅመ ደካማ ወገኖች ማዕድ ማጋራት መርሃግብር ሲያከናውን ባንኩ ለማህበረሰቡ ያለውን አጋርነት እና ጥብቅ ቁርኝነት የበለጠ ከፍ እንደሚያደርግ በማመን ነው ብለዋል፡፡

በማዕድ ማጋራት (ሶደቃ) ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖችም ለባንኩ ምስጋናቸውን ገልፀዋል።

የወንድ ዘር ፈሳሽ ልገሳን ሊጀመር ነው።በኢትዮጵያ ኩላሊት እና የወንድ ዘር ፈሳሽን ጨምሮ የተለያዩ የአካል ክፍሎች ልገሳን ለማስጀመር እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ደምና ሕብረ-ህዋስ...
27/03/2025

የወንድ ዘር ፈሳሽ ልገሳን ሊጀመር ነው።

በኢትዮጵያ ኩላሊት እና የወንድ ዘር ፈሳሽን ጨምሮ የተለያዩ የአካል ክፍሎች ልገሳን ለማስጀመር እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ደምና ሕብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታውቋል።

የወንድ ዘር ፍሳሽ እና የሰውነት አካል ልገሳን እንዲሁም መዳን በማይችል በስቃይ ውስጥ ያሉ ታማሚዎች በሐኪሞች እርዳታ እንዲሞቱ የሚፈቅደውን ሕግ ጨምሮ አዳዲስ የጤና አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችሉ ሕጎችን የያዘው የጤና አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቀርቦ መጽደቁ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ደምና ህብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር ጤናዬ ደምሴ ለአሐዱ ሬዲዬ ሲናገሩ እንደተሰማው ከሆነ ተቋሙ ከዚህ ቀደም የደም አገልግሎትን ብቻ ይሰጥ እንደነበር አስታውሰው፤ በ2015 ዓ.ም. ጀምሮ የዓይን ብሌን ልገሳን በማካተት እየሰራበት ይገኛል ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ህብረ-ህዋስን ጨምሮ የተለያዩ የሰውነት አካል ልገሳን ለማከናወን አዲስ ኃላፊነት መቀበሉንም ጨምረው ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት ሂደቱ እንደ ዓይን ብሌን ልገሳ ሁሉ በፈቃደኝነት የተመሰረተና ሰዎች በሕይወት እያሉ በሚገቡት ቃልና ፊርማ መሠረት የሚከናወን ሲሆን፤ "ኩላሊትን ጨምሮ የተለያዩ የአካል ክፍሎችን ያጠቃለለ ነው" ብለዋል።

በመሆኑም አሁን ላይ ተቋሙ የደምና የአይን ብሌን ልገሳ ላይ በደንብ እየሰራበት እንደሚገኝ በማንሳት፤ የሰውነት አካል ልገሳን ለማስጀመር እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝና በቀጣይም በደንብ በተጠናከረ መንገድ እንደሚሰራበት ገልጸዋል።

አክለውም ይህ የሰውነት አካል ልገሳን የሚፈቅደው ሕግ እንደተቋሙም ሆነ እንደ ሀገር አዲስ በመሆኑ፤ ኅብረተሰቡ ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሮለት ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ ለማስገባት ምናልባትም ከሁለት እስከ ሦስት ዓመት ድረስ ሊወስድ እንደሚችል ም/ ዋና ዳይሬክተሯ አስታውቀዋል።

ትኩረት የሚሻው የጊምቦራ ድልድይይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድአንድ የሚጠላ አንድ የሚወደድ!መንገድ የልማቶች ሁሉ መሰረት፣የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ቁልፍ ነው።በሰሜን ወሎ ዞን ...
26/03/2025

ትኩረት የሚሻው የጊምቦራ ድልድይ

ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ
አንድ የሚጠላ አንድ የሚወደድ!
መንገድ የልማቶች ሁሉ መሰረት፣የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ቁልፍ ነው።

በሰሜን ወሎ ዞን በጉባላፍቶ ወረዳ የሚገኘው የሳንቃ/ጌሾበር/ ጊምቦራ ድልድይ በአገልግሎት ብዛት አስጊ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ጊምቦራ ድልድይ DECEMBER 1980 ተገንብቶ ለበርካታ አመታት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ድልድዩ በርካታ የትራፊክ ፍሰት የሚካሄድበትና ለአመታት አገልግሎት ከመስጠቱ ጋር ተያይዞ አሁን ላይ ድልድዩ ጥገና አስፈልጎታል። በድልድዩ የተለያዩ ቦታዎች ላይ የብልሽት መጠኑ ከፍና ዝቅ ቢልም በአይን የሚታይና በአስቸኳይ ጥገና ካልተደረገለት የትራፊክ ፍሰቱ መስተጓጎሉ አይቀሬ ነው። ስለሆነም ይህን ድልድይ ድልድዩ በፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ከወልድያ ጋሸና የሚጠገነው መንገድ አካል ቢሆንም አስቸኳይ ጥገና ካልተደረገለት ከጥቅም ውጭ ሊሆን እንደሚችል አመላካች ችግሮች አሉት።

ድልድዩ ከጥቅም ውጭ ከመሆኑ በፊት አፋጣኝ ጥገና እንድደረግለት እየጠየቅን የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችም ጫናን በመቀነስ(ድልድዩ ላይ ባለመቆም) ሀላፊነታቸውን እንድወጡ እንጠይቃለን ። ጉባላፍቶ ኮሙኒኬሽን

Address

Woldia

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Fortune posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Woldia Fortune:

Share