Woldia Times

Woldia Times ሕዝባዊና አካባቢያዊ ችግሮችን እንዳስሳለን፣ መረጃ እናቀርባለን እንዲሁም የመፍትሄ አቅጣጫ እናሳያለን! ግባችን ሕዝባዊ ተጠቃሚነት ነው።
(1)

  ያልተከፈለበት ማስታወቂያሂሶጵ የፅዳት አገልግሎት ወልድያ~~~~~~~~~~~በዘመናዊ እና በሠለጠኑ ባለሞያዎች ቤትዎን፣ ህንፃዎን ፣ ሆቴልዎን ፣የስራ ቦታዎን ያፀዱ። የምንሰጣቸው አገልግሎቶች...
09/07/2025

ያልተከፈለበት ማስታወቂያ
ሂሶጵ የፅዳት አገልግሎት ወልድያ
~~~~~~~~~~~
በዘመናዊ እና በሠለጠኑ ባለሞያዎች ቤትዎን፣ ህንፃዎን ፣ ሆቴልዎን ፣የስራ ቦታዎን ያፀዱ። የምንሰጣቸው አገልግሎቶች

📍የምንጣፍ ፣ የሶፋ፣ የመጅሊስ እጥበት

📍ለድርጅቶች ፣ ለሆቴሎች ፣ለጌም ዞኖች፣ ለቢዝነስ ሴንተሮች የሠለጠኑ ባለሞያዎችን ፣ አላቂ የፅዳት እቃዎችን ጨምሮ በቋሚነት እናቀርባለን

📍የሆቴል ፣ የካፌ ፣ የሬስቶራንት ጠቅላላ ፅዳት

📍የመኖሪያ ቤት ጠቅላላ ፅዳት

📍የሪል ስቴት ፣የአፓርትመንት ፅዳት

📍የስፖርት ቤቶች ፣ የሱቆች ፅዳት እኛ ዘንድ ያገኛሉ
____________
አድራሻ: ወልድያ መነሀሪያ አንደኛ ፖሊስ ጣቢያ ጎን

☎️0901836910/0908873925

የሂሶጵ ፅዳት አገልግሎት ወልድያ የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።

® Tiktok :https://vm.tiktok.com/ZMHbrBJ7T33BK-1RMnf/

® Facebook: https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR

® Telegram: https://t.me/+Qn_y5YuSPAVmZWJk

ከወልድያ አዳዲስ ስራ ፈጣሪዎችን እያየን ነው - ሊበረታቱ ይገባል! (ለሌሎች ከተሞች ወጣቶችም ይጠቅማል) ወልድያ ላይ አዳዲስ የስራ ፈጠራ ሀሳብን ይዘው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች አሉ ፣ ከነዚ...
09/07/2025

ከወልድያ አዳዲስ ስራ ፈጣሪዎችን እያየን ነው - ሊበረታቱ ይገባል!
(ለሌሎች ከተሞች ወጣቶችም ይጠቅማል)

ወልድያ ላይ አዳዲስ የስራ ፈጠራ ሀሳብን ይዘው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች አሉ ፣ ከነዚህም መካከል :-

✌ ቤት ለቤት የፊዚዮቴራፒ አገልግሎት የሚሰጡ ፣
✌ የዴሊቨሪ አገልግሎት የሚሰጡ ፣
✌ ቤት ለቤት የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ፣
✌ ቤት ለቤት የፅዳት አገልግሎት የሚሰጡ ፣
✌ ሰርፕራይዝ እና ጊፍት ፕላነር ለተለያዩ ፕሮግራሞች የሚሰጡ ፣
✌የወዳደቁ ፕላስቲኮችን በመፍጨት መልሰው ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚያደርጉ፣ እንዲሁም ሌሎችም።

Woldia Times በከተማችን የሚገኙ ስራ ፈጠሪዎች ምርት እና አገልግሎታቸውን በነፃ በማስተዋወቅ ታበረታታለች። ማስታወቂያችሁን ላኩልን!

ይገርመናል‼አስራት ቴሌቭዥንን እኛ ካልመራነው ብለው አፈረሱት። አብንን እኛ ካልመራነው ብለው ለማፍረስ ሞከሩ ግን ከሸፈባቸው። የመጀመሪያውን የፋኖ አንድነት እስክንድር መሪ ሆኖ ቢመረጥም እኛ...
08/07/2025

ይገርመናል‼

አስራት ቴሌቭዥንን እኛ ካልመራነው ብለው አፈረሱት። አብንን እኛ ካልመራነው ብለው ለማፍረስ ሞከሩ ግን ከሸፈባቸው። የመጀመሪያውን የፋኖ አንድነት እስክንድር መሪ ሆኖ ቢመረጥም እኛ ካልመራነው ብለው አፈረሱት።

ከስንት ጥረት በኋላ አፋብሀ ተመሠርቶ ጀኔራል ተፈራ ለመሪነት ቢመረጥም አንቀበልም ካሉ በኋላ በ13 ኮሚቴ እየተመራ ቢቆይም አሁንም እኛ ካልመራነው ብለው ከአፋብሀ መገንጠላቸውን በመሳወቅ አፈረሱት።

በአጠቃላይ የትኛውም ተቋም ይሁን አደረጃጀት እነሱ እስካልመሩት ድረስ እንዲኖር አይፈቅዱም። የአማራ ክልልንም በቀጣይ ከወሳኝ የሥልጣን ቦታወች ከተነሱ ክልሉን በማፍረስ ቀድመው የሚያውጁት እነሱው ናቸው።

ኢትዮጵያንም ቢሆን የእኛ ጥቅም እስካልተጠበቀ ድረስ ውልቅልቋ ይውጣ ብለው ከአፍራሾች ጋር አብረው እያፈረሷት ይገኛሉ።

ይሄን ሁሉ ሲያደርጉ ግን የወጡበትን ማህበረሰብ ገጽታውን እያበላሸን ነው ብለው ለአፍታ አስበውት እንኳን አያውቅም።

ለነገሩ ለእነሱ እስከጠቀመ ድረስ አይደለም ህዘብ ይቅርና ለቤተሰባቸውም ቅንጣት ያክል አያሳስባቸውም። ይገርመናል‼

የወልድያችን የህክምና ማዕከልነት እያደገ መጥቷል! በቅርቡ ወልድያ ሆስፒታል የተረከበው የሲቲ ስካን (CT scan) ማሽን ትልቅ ችግርን የሚቀርፍ እና ከተማችንንም  የህክምና ማዕከል እንድትሆ...
08/07/2025

የወልድያችን የህክምና ማዕከልነት እያደገ መጥቷል!

በቅርቡ ወልድያ ሆስፒታል የተረከበው የሲቲ ስካን (CT scan) ማሽን ትልቅ ችግርን የሚቀርፍ እና ከተማችንንም የህክምና ማዕከል እንድትሆን የሚያግዝ ትልቅ ሀብት ነው።

እንደሚታወቀው ከተማችን ወልድያ በግሉ የህክምናው ዘርፍም የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጨምሮ የተለያዩ የህክምና ማዕከላትን የያዘች ናት።

እነዚህ የህክምና ማዕከላት መኖር ለከተማችን እድገት ትልቅ አስተዋፅኦ ስላላቸው Woldia Times ማገዝ ባለባት ሰዓት ከጎናችሁ መሆኗን መግለፅ ትፈልጋለች!

ወልድያችን ዓይናችን!

ሰው በስልጣን ላይ ቆይቶ እንዲህ ሲመሰከርለት ደስ ይላል !ስለ ቀድሞው የወመዘክር ዋና ዳይሬክተር ይኩኖአምላክ መዝገቡማ ይሄን ማወቅ አለባችሁ።ይኩኖአምላክ ዝም ብሎ ሹም አልነበረምተጓዡ ጋዜጠ...
08/07/2025

ሰው በስልጣን ላይ ቆይቶ እንዲህ ሲመሰከርለት ደስ ይላል !

ስለ ቀድሞው የወመዘክር ዋና ዳይሬክተር ይኩኖአምላክ መዝገቡማ ይሄን ማወቅ አለባችሁ።
ይኩኖአምላክ ዝም ብሎ ሹም አልነበረም

ተጓዡ ጋዜጠኛ /ሄኖክ ስዩም/

ይኩኖአምላክ መዝገቡን አለማመስገን በፍርድ ቀን ያስፈርድብኛል። የማውቀው ሳይሾም በፊት ነበር፣ ሲሾም ያልተቀየረ ትሁት ኾኖ ቀጠለ። ደግሞ ከመሾሙ በፊት "የተሾመ ለምን ይሄንን አይሰራም?" ሲል ቁጭቱን ሰምቻለሁ። እንደተሾመ በተቆጨበት ላይ ሲዘምት ያየሁ ምስክር ነኝ።

ለመሆኑ ዝም ብሎ ሹም አለ? ትሉኝ ይሆናል። በደንብ ነዋ እላችኋለሁ። ልጆቹን ለማሳደግ የሚሾም። የተሾመበትን ደብዳቤ ያኽል ሲሻር ትርጉም የሌለው። ዳሩ ምን ያደርጋል! ባህል ነው እና ሲሄድ ወይም ሲሞት እንደምንለው የሄደ ሰው ላደንቅ መጣሁ።

ከበደ ሚካኤል፣ ሲልቪያ ፓንክረስት፣ ተክለፃድቅ መኩሪያ እያልን ወመዘክርን የመሩ ባለውለታዎች ስንቆጥር ይኩኖአምላክ መዝገቡ የሚለው ስም በክብር የሚቆጠር፣ ሊዘለል የማይችል እንደሆነ አልጠራጠርም።

ይኮኖአምላክ ወጣት መሪ ነው። ብዙዎች ዘንድ ባልተለመደ መልኩ ወደ ሕይወቱ የመጣው የሹመት ኑሮ፤ ብርቅ ሆኖ አላሳከረውም። ለንባብ ተሾመ፣ ስለ ንባብ ኖረ። ሲመስለኝ ደግሞ ፓርቲና ስብሰባ ይሸሻል።

በግሌ ከየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ መጻሕፍት ድጋፍ ፍለጋ "እስቲ የሰውዬውን ስልክ" ለሚሉኝ ደረቴን ነፍቼ አቀብላለሁ። "አላነሳ አለ" ካሉ “መልእክት ላኩለት” እላለሁ። ተልኮ ሜዳ የቀረ መልእክት የለም። ይኩኖ ይደውላል-ውጤቱ ደግሞ የኾነ አካባቢ መጻሕፍትን በድጋፍ ማድረስ ይሆናል።

ይኩኖአምላክ አንድ መጽሐፍ ላነበበ ታራሚ፤ ለምን ከእስር ቀኑ አንድ ቀን አይቀነስም ሲል ንቅናቄ የጀመረ ሰው ነው፤ ይኩኖአምላክ ነው መጽሐፍ ለማድረስ ሄዶ ጨንቻ ቀርቀሃ ላይ የሚያድረው፤ በእርግጥም ሰውዬውን አለማድነቅ፣ ማን እንደለቀቀ አለመናገር በፈጣሪ ስም ያስጠይቃል።

ይሄ በግሉ የተደረገለት ሰው ምስክርነት አይደለም። ስለ ሀገር ለተደረገ አበርክቶ የቀረበ እማኝነት ነው። ጎንደር መጻሕፍት ጭነን ሄደናል፣ ቦንጋም እንዲሁ፣ መቀሌ ገብተናል። ሀረርም በተመሳሳይ ደብረ ታቦር ዘልቀናል። ድሬድዋም፤ የት ነው ያልተደረሰው ጅግጅጋ ወይስ ጅንካ? ታርጫ ወይስ ሚዛን አማን፤ ከማርቆስ እስከ ሰመራ ከባህር ዳር እስከ ሮቤ ብቻ በመላ ኢትዮጵያ ተቋሙ ደርሷል። በዚህ ይኩኖአምላክም ሆነ መላው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመጻሕፍት እና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ ሰራተኞች ሊመሰገኑ ይገባል።

ዋና ከተማ ብቻ የሚፏልል አይደለም፤ ያ ቢሆን ጋሞ ኤዞ ቤተመጻሕፍት ባልደረሰ፤ እንፍራንዝ ባልገባ፣ ስልጤ ገርቢበር ባልሄደ፣ ይርጋጨፌ ታንብብ ብሎ ባልወሰነ፣

ደግሞ ይኩኖአምላክ ተጀምሮ ቆመ ሲሉት የማይወድ ሰው ነው። ለምሳሌ የግዕዝ ጉባዔ በባህል ሚኒስቴር መሪነት እንደ ሀገር ጀመርን ውሎ አድሮ አመላችን ተነሳበትና ሰው ሲቀየር ይቁም ተባለ። ይኩኖአምላክ ምን ሲደረግ ብሎ ቀጠለው። እነኛ ያስቆሙት ዛሬ በስልጣን ቦታቸው የሉም፣ ይኩኖአምላክም እንዲሁ፤ ታሪካቸው ግን "ማስቆም" እና "ማስቀጠል" ተብሎ እየወገኑ ቆሞ ይኖራል።

እርግጥ ነው ይኩኖአምላክ መዝገቡ የቤተክህነትም ሰው ነው፤ የቤተመንግሥት ሰው ሲኾን ግዕዝ ጉባኤ ብሎ ወደ ጉዳዩ የገባ እንዳይመስለን፤ እንደ ሀገር የመንዙማ ኩነትን የደገሰ ልዩ ሰው ነው። ደግሞ እንደ ብራናው ለኪታቡ ልቡ የደነገጠ፤ ለዚህ ዘቢሞላ ምስክሬ ናት።

ራሳቸውን እንደ ንስር የሚቆጥሩት ጥንብ አንሳዎች!የአማራን ጥያቄ ሲያነሱ የቆዩ፣ እያነሱ ያሉ ንስሮች አሉ። ወደፊት ይኖራሉም። የአማራ ሕዝብ ደግሞ አገዛዞች፣ የውጭ ወረራ ያልበገረው የግዙፍ ...
07/07/2025

ራሳቸውን እንደ ንስር የሚቆጥሩት ጥንብ አንሳዎች!

የአማራን ጥያቄ ሲያነሱ የቆዩ፣ እያነሱ ያሉ ንስሮች አሉ። ወደፊት ይኖራሉም። የአማራ ሕዝብ ደግሞ አገዛዞች፣ የውጭ ወረራ ያልበገረው የግዙፍ ስብዕና ባለቤት ነው። አሁን አሁን የአማራን ህዝብ ጉዳይ "አክቲቪስትም" ቅብጥርጥስም ነን ብለው ራሳቸውን እንደ ንስር እየሳሉ፣ ጥንብ አንሳ የሆኑ ሞልተዋል። አንድ ብቻ ምሳሌ ላንሳ።

የአገር ቤትም ሆነ የውጭ ወራሪዎች እንዲሁም በቅርብ የተፈራረቁ አገዛዞች የአማራን ህዝብ በውስጠ ባሉ ጥቃቅን እንዲሁም ድርብ ማንነቶች መሃል ልዩነት እየፈጠሩ ለማሳነስ ብዙ ሰርተዋል። የትህነግን ፀረ አማራ ፖሊሲ ያነገቡ፣ የእነዚህን ክፉዎች ጥንብ አስተሳሰብ እያነሱ ራሳቸውን የአማራ ብሔርተኛ መለያ የሆነው ንስር ነን የሚሉት እየተከተሉት ያለው ይህን መንገድ ነው።

እነዚህ አካላት ከክልል ውጭ ለሚሰቃየው አማራ ጥብቅና እንቆማለን ይሉና፣ ክልል ውስጥ የተወለደውን አማራ በሀሳብ ስላልተስማማቸው ትህነግ ጎጆ ያወጣቸውን፣ ብልፅግና እያጎለመሳቸው ያሉትን አዲስ ማንነት ይሰጡታል።

የትም ይወለድ አማራ ሆኖ ከአገዛዝ ጋር የሚቆም፣ በህዝቡ መብትና ጥቅም የሚራመድ ይኖራል። የዚህን አካል ፀረ አማራነት ለመግለፅ ሌላ ማንነት መሸለም የግድ አይደለም። ተግባራቸውን መግለፅ በቂ ነው። ሌባ ከሆነ ሌባ ነው። ሌላም።

ነገር ግን፦

ከሸዋና ከወሎ አካባቢ የተወለደን አማራ በሀሳባቸው ካልተስማማ ኦሮሞ፣ አርጎባ ብለው ከምንም ተነስተው አማራ ማንነቱን ይነጥቁትና በራሳቸው ፈቃድ አዲስ መታወቂያ ይሰጡታል።

ከጎንደር ከሆነ ቅማንት ወይንም የትግሬ ዲቃላ እያሉ አዲስ ማንነት ያድሉታል።

ከጎጃም ከሆነ አገው፣ አገው ሸንጎ የሚል መለያን በራሳቸው ተነሳሽነት ይሰጡታል።

ሁሉም በየፊናው በየአማራ ግዛቶች ያለውን የተጣላውን፣ የአይኑ ውሃ ያላማረውን የፈለገውን ማንነት ሲሰጥ የግለሰቦችን ማንነት ብቻ አይደለም የሚክደው።

አካባቢውን፣ የአማራን ግዛት ለሌላ ይሰጠዋል። ማንነቱን ይክደዋል። በግለሰቦች ፀብ አማራነትን፣ የአማራ ህዝብ ማንነትን ጭምር ነው የሚክደው። የኦነግና የትህነግ ብሔርተኞች ወሎና ሸዋ እንዲህ ነው፣ ጎንደር እንዲህ ነው፣ ጎጃም እንዲህ ነው እያሉ ለንዑስ ማንነት ግዛት እንደሚያድሉት ንስር ነን ባዮችም ያልተስማማቸውን ሁሉ እየጠቀሱ ማንነት ሲነጥቁ እያነሱ ያሉት የትህነግና የኦነግን ጥንብ ትርክት ነው። ጥንብ አንሳ የምላቸው ለዚህ ነው።

የአንድ ብሔርተኛ አንዱ አላማ የህዝብን የውስጥ አንድነት ማስጠበቅ ነው። እነ አጅሬ ግን ግለሰብም፣ ቡድንም አካባቢም እያነሱ አማራን ቅማንት፣ ሽናሻ፣ ወይጦ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ ሲያደርጉት ይውላሉ። የአማራ ደመኛ ጠላት ለአማራ የጎን ውጋት አድርጎ የፈጠረውን የሴራ ፖለቲካ ከቆየበት አንስተው ይጠቀሙበታል። በአማራ ላይ ማንፌስቶ ያወጡ አካላት "ይህ እንትን ስለሆነ ለእንትን ክልልነት እናቋቁማለን፣ እስከዚህ እንትን ነው፣ አማራ የሚባል አያዋስነንንም" ወዘተ የሚሉትን አማራን አብሮትና ተከባብሮ በኖረ ድርብም ይሁን ንዑስ ማንነት እየተኩና እያሳነሱ ነው።

ጥንብ አንሳው ደግሞ የጠላትን ጥንብ እያነሳ የተጣለውን አማራ ሁሉ ማንነት እየቀማ የንዑስ ማንነት ያድለዋል። ጉዳዩ አማራን ማሳነስ ብቻ አይደለም። አማራ ጋር አብሮ የኖረ፣ በመከባበር ሊኖር የሚገባውን ወገኑን ጭምር በጠላትነት እየፈረጀ ነው። አማራ አገውም፣ ቅማንትም ሌላውም የራሴ ወገን ነው ሲል ጠላቶቹ ደግሞ አይደለም ብለው ጥይት እንዲታኮስ ይፈልጋሉ።

ጥንብ አንሳውም የጠላቸው ሰዎች ላይ አማራነትን ነጥቆ ንዑስ ማንነት ሲሰጣቸው እየተኮሰባቸው ነው። ጠላት ናቸው እያለ ነው። አገው፣ ቅማንነት፣ ሽናሻም የአማራ ህዝብ አካልና አብሮ የሚኖር ወገኑ ሆኖ እያለ ጠላት ያደርጉታል። ጥንብ አንሳዎቹ። የአማራን የውስጥ አንድነት ማናጋት፣ እረፍት መንሳት፣ የጠላትን ትርክት መተግበር ማለት ይህ ነው። የጥንብ አንሳዎች ፖለቲካ።

የአማራ ህዝብ በራሱ ግዛት አብሮት የሚኖረውን ብቻ አይደለም። በኢትዮጵያም ብቻ አይደለም። የፓን አፍሪካዊነት ቀንዲል ነው። መለያውም ስለ ልቦናውም ፓን አፍሪካዊነት የሚቀበለውና ግዙፍ ነው። ጥንብ አንሳዎቹ ግን በአማራ ህዝብ ስም እየማለ አብሮት ቡና የሚጠጣው ወገኑ ጋር ሁሉ ሊያቃርኑት ይፈልጋሉ። ቤተሰቡን ሊበትኑ ይሰራሉ። ንዑስ ማንነትን ጠላትነት አድርገው ይስሉታል።

እነዚህ ጥንብ አንሳዎች ሲዞሩ የሚያገኙትን የኦነግም የትህነግም ትርክት ከወደቀበት አምጥተው አማራው ላይ ይበትኑታል። ከሆኑ አመት፣ ወራትም ሆነ ቀናት በፊት አማራን ጠላት በአማራ ላይ ያዝረከረከውን ጥንብ አስተሳሰብ አንስቶ በአማራ ስም የተጣላውን አማራ ሲፈርጅበት ካያችሁ ጥንብ አንሳው ነው። ራሱን ግን እንደ ንስር ነው የሚያስበው።

አማራ በሌላ ክልል የሚኖረውን የራሱን ህዝብ መብት በማስከበር ብቻ አይደለም ከፍ የሚለው። አብሮት የሚኖረውን የንዑስም ሆነ ድርብ ማንነትን አክብሮ፣ የጠላት እጅ እንዳይገባ አድርጎ፣ የግዛት አንድነትና መስተጋብሩን ጠብቆ ጭምር ነው። ዋና ጠላቶቹም ጥንብ አንሳዎቹም እንደሚያደርጉት የራሱን ወገን በመፈረጅ አይደለም። አማራ የራሱ ልጅ ነውር ከሰራ በአደባባይ ለፍርድ የሚያቀርብ ነው። ወንጀልም ነውርም ሰርቷል ለማለት ሌላ ማንነት የሚደርብ ህዝብ አይደለም። ሲያፍርበትም፣ ሲኮራበትም ማንነት ቀይሮለት አይደለም። ጥንብ አንሳዎቹ ከህዝብ ስነ ልቦና የተለዩና የጠላት የገደል ማሚቶ የሆኑትም ለዚህ ነው።

የአማራ ህዝብ በንፁስ ማንነት ስም ጠላቶቹ የሚያቦኩትን ፕሮጀክት ማክሸፍ የሚችለው አብሮት የሚኖረውን ወገኑን አክብሮ፣ ከጥቃትም፤ ከሴራም ተከላክሎት እንጅ የሰይጣን ስም እየሰጠ አይደለም። ጥንብ አንሳዎቹ ከህዝብ ተቃራኒ ናቸው። የአማራ ብሔርተኝነት ደቀ መዝሙር ብለው ያሞካሹትን በነጋታው በአካባቢው አጠጋግተው ማንነት ሌላ ሊያድሉት ይችላሉ። ለአማራ እቆማለሁ የሚል አገው፤ ቅማንት፣ አርጎባ ወዘተን ማሸማቀቂያ፣ መስደቢያ አድርጎ የሌላ ብሔር ህዝብ ጋር መኖርና ተባብሮ መታገል፣ ከሌላ አገር ጋር ዲፕሎማሲ መስራት አይቻለውም! አይቻልማ!

06/07/2025

ፋኖ ህወሓትን እዋጋለሁ ብሎ ሲሠለጥን እና ሲፎክር ቆይቶ በመጨረሻው ዘመን የህወሓት ድሽቃና ሞርታር ተሸካሚ አህያ ሆኖ አረፈው። የዘረፋችሁትን እንኳን ሳትበሉት መቃብራችሁን መቆፈራችሁ ይገርመናል።

06/07/2025

ህወሓት ጦርነቱን ከትግራይ አውጥታ አማራ ምድር ላይ ለማድረግ ዲሽቃና ሞርታሮቿን ለእኛዎቹ አህዮች አሸክማ ግሸን ደርሳለች። አማራ በታሪኩ የፋኖ አይነት ከምድሩ የወጣ የአህያ ስብስብ ገጥሞት አያውቅም።

የምድጃ አፉ አሳየ ደርቤ ነገር🚬=================እንደ ትርክርኩ አሳየ ደርቤ አይነት ደደብ ደንቆሮ ሰው በህይወቴ አይቸ አላውቅም። የአማራን ትግል መሳቂያና መሳለቂያ በማድረግ በሚዲ...
05/07/2025

የምድጃ አፉ አሳየ ደርቤ ነገር🚬
=================
እንደ ትርክርኩ አሳየ ደርቤ አይነት ደደብ ደንቆሮ ሰው በህይወቴ አይቸ አላውቅም። የአማራን ትግል መሳቂያና መሳለቂያ በማድረግ በሚዲያ ካቆረቆዙት ሰዎች መካከል እንደ አሳየ ደርቤ አይነቶቹ ቀዳሚዎች ናቸው! ለእሱ ከሆዱ ውጭ ሌላ ነገር ፈፅሞ ሊታየውና ሊታሰባቸው አይችልም።

በእርግጥ የሲጋራ🚬 መግዣ ትንሽ ከገቡለት አሳዬ እንደሆነ ጣጣ የለውም። ዘርጥጥ የተባለውን ይዘረጥጣል ፤ ተሳደብ የተባለውን እንደ ክፍያው መጠን ሲሳደብ የሚውል በኒያላ ጠኔ የሚመታ አመድ አፍ መደዴ ሰው ነው። አሳየ ያልገባው ነገር ይሄን ያክል ራሱን በገንዘብ ሽጦ ለራሱም ተዋርዶ እኛን ከሚያሳቅቀን ያለንን አጋርተነው መኖር ይችል ነበር።

አሳየ ደርቤ ዋና ትኩረቱ የወሎን ህዝብ በሃይማኖትና በብሄር ማጋጨት፤ ከወሎ ውስጥ ለአማራው ሕዝብ የተቆረቆረ መስሎ ሌላው ወሎዬን በመሣደብ የእነ እንትና ባሪያ ለማድረግ ኡጋንዳ ድረስ ክፍያ እየተፈጸመለት የሚሠራ መደዴ አመድ አፍ ነው።

በተደጋጋሚ አስተውላችሁት ከሆነ አፉን የሚከፍተው ወሎየዎቹ ላይ ነው። አሳየ ደርቤ ሀሣብ እና የፖለቲካ ትንታኔ ስለማይገባው ለእሱ የሚመጥን አሉባልታ የሆነ ወረድ ያለ ጽሁፍ መጻፍ ስላልቻልን በዚሁ ይብቃን።
Fikru Yimer

ትኩረትየወልድያ መንገድ ፕሮጀክት 75 በመቶ መድረሱ ሰሞኑን ተዘግቦ ነበር። መንገዱ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሱ የሚበረታታ ነው። ነገር ግን አሁንም ቢሆን ቅድመ ትኩረት የተነፈጋቸው ጉዳዮች አሉ...
05/07/2025

ትኩረት
የወልድያ መንገድ ፕሮጀክት 75 በመቶ መድረሱ ሰሞኑን ተዘግቦ ነበር። መንገዱ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሱ የሚበረታታ ነው። ነገር ግን አሁንም ቢሆን ቅድመ ትኩረት የተነፈጋቸው ጉዳዮች አሉ

👉 መንገዱ ላይ ሾፌሮችና ጎሚስታዎች ክሪክ እያነሱበት ነው። ጋራዦች እና ዘይት የሚቀይሩ መኪኖች የተቃጠለ ዘይት እያፈሰሱበት ነው።

👉 አሰፓልት ላይ ለግንባታ የሚሆን ድንጋይ፣ አሸዋ፣ አፈር፣ ጠጠር መገልበጥ ፈፅሞ መከልከል ያለበት እና በከፍተኛ ገንዘብ የሚያስቀጣ ተግባር መሆን አለበት።

👉 አስፓልት ላይ የቆመ መኪና ተገን አድርጎ ቀንም ሆነ ሌሊት መሽናት እንደ ነውር የማይቆጠር የተለመደ ተግባር ነው።

👉 በሀይላንድ ሽንት ሞልቶ ወደ አስፓልት መጣል የተለመደ እና የማያሳፍር ተግባር ሆኖል።

👉 ባለ ድርጂቶች የወጥ ቤት እና የዕቃ እጣቢ እየደፉበት ነው። ሽንት ቤታቸውንም ያገናኙ አሉ። ጽዳጁ ሄዶ ሄዶ የሚቀላቀለው መንደቅ ምንጭ ጋር ነው። ምንጩን ማን ነው የሚጠቀመው?

ለመሆኑ ከተማችን ላይ እነዚህንና መሠል የመንገድ ደህንነት እንዲሁም የከተማው የጽዳጅ እና ፍሳሽ አገልግሎት ጉዳዮች የሚከታተለው ማነው?

የከተማ አስተዳደሩ በችግር ውስጥ ሆኖ እንኳን ለከተማው መሠረተ ልማት መስፋፋት የሚሠራው ሥራ እጅግ የሚደንቅ መሆኑ በግልጽ የሚታይ ነው።

ነገርን ከተማን ከተማ የሚያስመስሉ የመንገድ ደህንነት ክትትል፣ የፍሳሽና ቆሻሻ አወጋገድ ክትትል ሥራዎች እጅግ ትኩረት የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ትኩረት ሊደረግባቸው ይገባል።

በተለይ ደጎስ ካለ የገንዘብ ከቅጣት ጋር የተያያዙ እርምጃዎች ቢወሰዱ የከተማውን ገቢ ከመጨመሩ በላይ ፈጣን ለውጥ ለመምጣት ወሳኝ እርምጃ ይሆናል።

እርምትትናንት የቴሌኮም ፖል ሲተክል አደጋ የደረሰበት ጥላሁን ሲሣይ አስማማው ዘመድ የሚሆን ሰው ተገኝቷል ፤ ልዩ ቦታውም ሳንቃ ጌሾ  በር እንደሆነም አውቀናል። ጥላሁን እስካሁን በኦክስጅን ...
04/07/2025

እርምት
ትናንት የቴሌኮም ፖል ሲተክል አደጋ የደረሰበት ጥላሁን ሲሣይ አስማማው ዘመድ የሚሆን ሰው ተገኝቷል ፤ ልዩ ቦታውም ሳንቃ ጌሾ በር እንደሆነም አውቀናል። ጥላሁን እስካሁን በኦክስጅን እየተረዳ ኮማ ውስጥ ነው ያለው አልነቃም።

በተጨማሪም ዛሬ ከቦታው በደረሰን መረጃ ልጁ የሳፋሪኮም ሰራተኛ ሳይሆን የኢትዮ ቴሌኮም በኮንትራት ከሚሰሩት ሰራተኞች መካከል አንዱ ነው።

ስለዚህ በትናንትናው እለት ሳፋሪኮም ብለን የለጠፍነው ስህተት በመሆኑ ይቅርታ እየጠየቅን፤ ትብብር ላደረጋችሁ በሙሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

አፋልጉንይህ በምስሉ ላይ የምታዩት ወጣት አበበ አያሌው ይባላል፡፡ ተወልዶ ያደገው በወልድያ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ሲሆን በ 1991 ዓ.ም በስራ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ እንደሄደ እስካሁን ድ...
04/07/2025

አፋልጉን
ይህ በምስሉ ላይ የምታዩት ወጣት አበበ አያሌው ይባላል፡፡ ተወልዶ ያደገው በወልድያ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ሲሆን በ 1991 ዓ.ም በስራ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ እንደሄደ እስካሁን ድረስ ያለበት አልታወቀም ፡፡

አበበ ከወልዲያ ከወጣ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ወላጅ እናቱ በከባድ ሀዘን ላይ ትገኛለች ፡፡ እባካችሁ ያያችሁት ወይም ያለበትን የምታዉቁ ከዚህ በታች ባሉት ስልክ ቁጥሮች አሳውቁን።
በ 0913445347
0920486236
0914465933
#የጠፉ #የጠፋ
ብዙ ሰው ጋር እንዲደርስ በቻላችሁት አቅም ሼር አድርጉት

Address

Woldia

Telephone

+17735642986

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Woldia Times:

Share