Wollo herald

Wollo herald We speak what we see, we testify what we hear!

ተጨማሪ የነዳጅ መያዣ የገጠሙ 13 አሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼በግልገል በለስ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመቆጣጠር በተደረገ ክትትል፣ ከፋብሪካ ስሪት ውጭ ተጨማሪ የነዳጅ መያዣ (...
23/03/2026

ተጨማሪ የነዳጅ መያዣ የገጠሙ 13 አሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼

በግልገል በለስ ከተማ ህገወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመቆጣጠር በተደረገ ክትትል፣ ከፋብሪካ ስሪት ውጭ ተጨማሪ የነዳጅ መያዣ (ሳልቫቶ) የገጠሙ 13 የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታውቋል።

የከተማው ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ታዬ ጉርሜሳ እንደገለጹት፤ ተሽከርካሪዎቹ እስከ 600 ሊትር የሚይዝ ተጨማሪ ታንከር በሕገወጥ መንገድ የተገጠመላቸው ናቸው ብለዋል።

በዕለቱ በተደረገ ቁጥጥር 16 ሳልቫቶዎች ከተሽከርካሪው ላይ ተፈቶ ገቢ የተደረጉ ሲሆን፣ በነዳጅ ማደያዎችና በኬላዎች ላይ የሚደረገው ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኃላፊው ተናግረዋል።

ሰልቫቲዮ ተፈቶ የተወሰደባቸው ተሽከርካሪዎች ቆመው እንደሚገኙ ተሰምቷል።

ክልከላው ተራዝሟል‼​የደሴ ከተማን አንፃራዊ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል፣ የከተማዋ ፖሊስ መምሪያ ቀደም ሲል ያስተላለፈው የምሽት የጉዞ ክልከላ ለላተወሰነ ጊዜ ያራዘመው መሆኑን አሳውቋል።​ክልከ...
18/03/2026

ክልከላው ተራዝሟል‼

​የደሴ ከተማን አንፃራዊ ሰላምና ልማት ለማስቀጠል፣ የከተማዋ ፖሊስ መምሪያ ቀደም ሲል ያስተላለፈው የምሽት የጉዞ ክልከላ ለላተወሰነ ጊዜ ያራዘመው መሆኑን አሳውቋል።

​ክልከላው የሚመለከታቸው ተሽከርካሪዎች፦

📌​የሕዝብ ማመላለሻ ባጃጅ
📌​የጭነት ባጃጅ
📌​ዳማስ (Damas)
📌​ሞተር ሳይክል

ተሽከርካሪዎቹ ​ከምሽቱ 12:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ማንኛውም እንቅስቃሴ የተከለከለ ነው።

የፖሊስ ​ጥብቅ ማሳሰቢያ፦

'አንዳንድ አሽከርካሪዎች ክልከላውን በመጣስ ስራ ላይ ተሰማርታችሁ የምትገኙ ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እናሳስባለን።'

' መመሪያውን በማይተገብሩ አካላት ላይ አስፈላጊው እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እየገለጽን፤ አሽከርካሪዎችና መላው የከተማዋ ማህበረሰብ ለከተማችን ሰላምና ደህንነት መረጋገጥ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

​የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ

አሁን ባለው ውድድር ከ31ዱ የንግድ ባንኮች 25ቱ መቀጠል የሚያስችላቸው ቁመና ላይ አይደሉም-   ብሄራዊ ባንክወሎ ሔራልድበሀገሪቱ ካሉት 31 የንግድ ባንኮች ውስጥ 25ቱ አሁን ባለው ከባድ ...
18/03/2026

አሁን ባለው ውድድር ከ31ዱ የንግድ ባንኮች 25ቱ መቀጠል የሚያስችላቸው ቁመና ላይ አይደሉም- ብሄራዊ ባንክ
ወሎ ሔራልድ
በሀገሪቱ ካሉት 31 የንግድ ባንኮች ውስጥ 25ቱ አሁን ባለው ከባድ የገበያ ውድድር ውስጥ መቀጠል ስለማይችሉ ተዋህደው ጠንካራ ባንኮችን መፍጠር ብቸኛው አማራጭ መሆኑን ብሔራዊ ባንክ ገለፀ፡፡

ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ እንዳይሄዱ ተከለከሉ‼️➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ዛሬ ጠዋት ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ፥ በሁለት ባሶች  የተሳፈሩ መንገደኞች ከትግራይ እንዳይወጡ ተከለከሉ። በመውጫ መ...
15/03/2026

ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ እንዳይሄዱ ተከለከሉ‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ዛሬ ጠዋት ከመቐለ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ፥ በሁለት ባሶች የተሳፈሩ መንገደኞች ከትግራይ እንዳይወጡ ተከለከሉ።

በመውጫ መንገዶችም የፍተሻ ኬላዎች መደረጋቸውም ከመቐለ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የትግራይ ወጣት ጦርነት በመጠየፍ ከትግራይ ክልል በገፍ እየሸሸ መሆኑ መዘገባችን አይዘነጋም።

የምግብ ሸቀጦች ዋጋ መናር እና የመብራት መቆራረጥን ለመቃወም አደባባይ የወጡ ኩባውያን የኮምኒስት ፓርቲ ሕንጻ ላይ ጉዳት አደረሱ።በኩባ በተከታታይ መብራት ከመጥፋቱ በተጨማሪ የምግብ፣ የመድኃ...
15/03/2026

የምግብ ሸቀጦች ዋጋ መናር እና የመብራት መቆራረጥን ለመቃወም አደባባይ የወጡ ኩባውያን የኮምኒስት ፓርቲ ሕንጻ ላይ ጉዳት አደረሱ።

በኩባ በተከታታይ መብራት ከመጥፋቱ በተጨማሪ የምግብ፣ የመድኃኒት እና የነዳጅ እጥረት ተባብሷል። የእነዚህ ችግሮች መባባስ ዋነኛው ምክንያት አሜሪካ የኩባ ነዳጅ ላይ የጣለችው ማዕቀብ ነው።

 : ኢራን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ "በህይወት የሉም" ማለቷ አለም አቀፉን ማህበረሰብ አስደንግጧል !የቴህራን ባለስልጣናት በአሁኑ ጊዜ እስራኤል ሞራል ለመጠበቅ እና የ...
14/03/2026

: ኢራን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ "በህይወት የሉም" ማለቷ አለም አቀፉን ማህበረሰብ አስደንግጧል !

የቴህራን ባለስልጣናት በአሁኑ ጊዜ እስራኤል ሞራል ለመጠበቅ እና የአመራር ችግርን ለመደበቅ የተራቀቀ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ጥልቅ የውሸት ቴክኖሎጂን በመጠቀም በአደባባይ ቪዲዮ ላይ "አሻንጉሊት" እየተጠቀመች ነው ብሏል።

አዲሱን የኢራን መንፈሳዊ መሪ ለመያዝ ዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ወሮታ እንደምትከፍል ገለፀች። የሟቹ አያቶላህ አሊ ኻመኔይ  ልጅ ሞጅታባ ኻመኔይ  እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት የ...
14/03/2026

አዲሱን የኢራን መንፈሳዊ መሪ ለመያዝ ዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ወሮታ እንደምትከፍል ገለፀች። የሟቹ አያቶላህ አሊ ኻመኔይ ልጅ ሞጅታባ ኻመኔይ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት የት እንዳሉ መረጃ ለጠቆመ እስከ አስር ሚሊዮን ዶላር እንደሚከፈል ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በኢንተርኔት ባሰራጨው ማስታወቂያ ከኻመኔይን በተጨማሪ የሀገር ውስጥ ሚኒስትሩን፣ የኢራን ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ እና የስለላ ሚኒስትሩን በጠቅላላ 10 ከፍተኛ ባለስልጣናትን እያፈላለገ ይገኛል።

የ56 ዓመቱ ሞጅታባ ኻመኔይ የአባታቸውን ቦታ ከተረከቡ ጊዜ አንስቶ በመገናኛ ብዙኃን ቀርበው አያውቁም። እንደ ዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሮቢዮ እና መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት ከሆነ ኻመኔይን ጉዳት ሳይደርስባቸው አልቀረም። ይህ ግን በየትኛውም ወገን አልተረጋገጠም።

"ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባህር (Sea of Japan) አቅጣጫ 10 ያህል ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኮሰች።ሚሳኤሎቹ የተተኮሱት በፒዮንግያንግ አቅራቢያ ከሚገኘው የሱናን (Sunan) አካባቢ ሲሆን...
14/03/2026

"ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባህር (Sea of Japan) አቅጣጫ 10 ያህል ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኮሰች።

ሚሳኤሎቹ የተተኮሱት በፒዮንግያንግ አቅራቢያ ከሚገኘው የሱናን (Sunan) አካባቢ ሲሆን፣ ያረፉትም ከጃፓን የኢኮኖሚ ክልል (EEZ) ውጭ በሆነ የባህር ክፍል ላይ ነው። እስካሁን ባለው መረጃ በአደጋው የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት የለም።"

የግብፅ ወታደር በሱዳን‼️ግብፅ ለሱድኑ ወታደራዊ መሪ አልቡርሃን የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ የቀጠለች ሲሆን የሱዳንን የእርስ በርስ ጦርነት እየመራ የተገደለው ግብፃዊ ጄነራል መነጋገሪያ ሆ...
14/03/2026

የግብፅ ወታደር በሱዳን‼️
ግብፅ ለሱድኑ ወታደራዊ መሪ አልቡርሃን የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ የቀጠለች ሲሆን የሱዳንን የእርስ በርስ ጦርነት እየመራ የተገደለው ግብፃዊ ጄነራል መነጋገሪያ ሆኗል።
ከቀናት በፊት የግብፅ ወታደራዊ መሪ የሆነው ብርጋዴር ጀነራል አህመድ ሰሚር ከ3 የግብፅ ወታደሮች ጋር ከሱዳን ጦር ጋር በመሆን በሰው አልባ አውሮፕላኖች አጠቃቀም ላይ የቴክኒክ የማማከር ዘመቻ ሲያደርጉ ከቀናት በፊት በሱዳን ግዛት ውስጥ በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ጥቃት መገደሉን ከአፍሪካን ኢንተለጀንስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ኮካ-ኮላ (ወይም ኮካ) በአለም ዙሪያ የሚሸጥ ለስላሳ መጠጥ ነው።ኮካ-ኮላ መጀመርያ የተፈጠረው እአአ በ1878 በአትላንታ አሜሪካ ነበር። ፈልሳፊው ዶ/ር ጆን ፔምበርቶን ይባላል ። ኮካ-ኮላ ...
14/03/2026

ኮካ-ኮላ (ወይም ኮካ) በአለም ዙሪያ የሚሸጥ ለስላሳ መጠጥ
ነው።

ኮካ-ኮላ መጀመርያ የተፈጠረው እአአ በ1878 በአትላንታ
አሜሪካ ነበር። ፈልሳፊው ዶ/ር ጆን ፔምበርቶን ይባላል ።

ኮካ-ኮላ መጀመሪያ ሲሰራ እንደ ማነቃቂያ መድኃኒት ይሆናል ተብሎ ነበር የታሰበው። ሳይታሰብ ግን በዓለም ላይ ተወዳጁ የለስላሳ መጠጥ ሆኖ ቁጭ ብሏል።

ኮካ-ኮላ የሚለው ስያሜ የመጣው በውስጡ ይዞት በነበረው የኮካ ቅጠልና የኮላ ፍሬ ምክንያት ሲሆን ዛሬ ላይ ግን እነዚህ የህጽዋት ክፍሎች በውስጡ አይገኙበትም።

ኢትዮጵያ ውስጥ ኮካ-ኮላ በጠርሙስ ታሽጎ ለገበያ መቅረብ የጀመረው በ1951/52 ዓም ነበረ።

የነ ደብረፅዮን ቡድን ፥ ፕሬዝዳንት  ታደሰ ወረደ በሃይል ከስልጣን ለማውረድና በምትካቸው አቶ አማኑኤል  ለማድግ በመንቀሳቸው በትግራይ ክልል ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል።
12/03/2026

የነ ደብረፅዮን ቡድን ፥ ፕሬዝዳንት ታደሰ ወረደ በሃይል ከስልጣን ለማውረድና በምትካቸው አቶ አማኑኤል ለማድግ በመንቀሳቸው በትግራይ ክልል ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል።

ሰብዓ ድጋፍ የተቋረጠባቸው በሐይቅ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎች ከረመዳን ፆም በኋላ ከዱር በሚሰበሰብ ፍሬ ለማፍጠር እየተገደዱ መሆኑን ተናገሩ “መጠለያዎቹ ከሰባት ዓመት በፊት የቆሙ የሸራ ድ...
12/03/2026

ሰብዓ ድጋፍ የተቋረጠባቸው በሐይቅ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎች ከረመዳን ፆም በኋላ ከዱር በሚሰበሰብ ፍሬ ለማፍጠር እየተገደዱ መሆኑን ተናገሩ

“መጠለያዎቹ ከሰባት ዓመት በፊት የቆሙ የሸራ ድንኳኖች በመሆናቸው አርጅተው ተቀዳደዋል፣ ይህንን እንኳ ጠግነን ለመኖር የሚያስችል ድጋፍ ልናገኝ አልቻልንም”- ተፈናቃዮች

Address

Woldia
26

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo herald posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share