ከኢቲዮ-ጉራጌ እንወያይበት

ከኢቲዮ-ጉራጌ እንወያይበት yes/no

19/12/2023
29/08/2022

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጉራጌ ዞን ያሉ ቅርንጫፎቹ ሰሞኑ በነበሩ ቤት የመቆየት አድማዎች ምክንያት ስለተዘጉ ለጉራጌ ህዝብ አገልግሎት አልሰጥም አለ። ባንኩ የመንግስትና የፖለቲካ እንጂ የነጋዴና የንግድ አለመሆኑ አረጋገጠ። እኛም ደብተሩን እንመልስለታለን። ዝግጁ ነን ?!
ምንጭ Tano Geter
ቡታጅራ ላይ ይገነባል ያለው ህንፃ ጉዳይም አረሳንም ቻውውውውው 🚶

13/08/2022

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር እና የመስቃን ወረዳዎች ውሳኔ በተመለከተ ከህገመንግስቱ አንጻር ሲታይ:-

በምንተስኖት መቻል

በዛሬው እለት ሁለቱ የመስቃን ወረዳዎች እና የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ምክርቤቶች በክላስተር ለመደራጀት በሙሉ ድምፅ አጽድቀዋል። ውሳኔያቸውን አከብራለሁ። ግን ደግሞ ውሳኔው የብልጽግና ፓርቲ ከTPLF የወረሰው የሴራ ፖለቲካ ውጤት እና ጉራጌን የመከፋፈል እቅድ እንደሆነ ለአፍታም አልጠራጠርም።

የሆነ ሆኖ ዋናው ነገር ውሳኔያቸው ህገመንግስቱን መሠረት ያደረገ ነው ወይስ አይደለም? የጉራጌ ዞን ምክር ቤት በ2011 ዓ.ም በክልል ለመደራጀት በሙል ድምጽ ባጸደቀው ውሳኔ ላይስ አሉታዊ ተጽእኖ አለው ወይስ የለውም የሚሉት ነጥቦች ማየቱ አስፈላጊ ሲሆን በዚህ በጣም አጭር ጽሁፍ ይህንኑ ለመዳሰስ እሞክራለሁ።
1. እንደሚታወቀው የጉራጌ ዞን ምክርቤት በክልል ለመደራጀት አስፈለጊ መስፈርቶች ተብለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 46 ስር የተደነገጉትን መስፈርቶች በማሟላት ህዳር 17/2011 ዓ.ም በክልል ለመደራጀት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

ይህም ማለት በወቅቱ የቡታጀራም ሆነ የመስቃን ወረዳ ተወካዮች ድምጻቸውን ሰጥተዋል ማለት ነው። የሆነ ሆኖ ጥያቄው በህገመንግስቱ አንቀፅ 47 መሠረት ለክልሉ ምክርቤት ቢቀርብም ምክር ቤቱ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ ባለማደራጀቱ ምክንያት በወቅቱ በነበረው የፌዴሬሽን ምክርቤት ስልጣን በሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 251/2001 አንቀጽ 19 መሠረት የጉራጌ ዞን ምክርቤት ቅሬታውን ለፌዴሬሽን ምክርቤት አቅርቦ መልስ በመጠበቅ ላይ ነው።

እንግዲህ በዚህ መልክ ህግና ስርዓት ጠብቆ የቀረበ ጥያቄ ወደኋላ ሊመለስ የሚችልበት ምንም አይነት የህግ አግባብ እንደሌለ መረዳት ያስፈልጋል።

2. ሌላውና መሠረታዊው ነገር በህገመንግስቱ አንቀጽ 47 (2) ስር በግልጽ እንደተደነገገው በክልል መደራጀት የሚችሉት ብሔሮች: ብሔረሰቦች ወይም ህዝቦች ብቻ ናቸዉ። ህገመንግስቱ ብሄር: ብሄረሰብ እንዲሁም ህዝብን በተመለከተ የተናጥል ትርጉም ባይሰጥም በአንቀጽ 39(5) ስር ወጥ በሆነ መልኩ ትርጉም የሠጣቸው ሲሆን በዚህ ድንጋጌ መሠረት ብሔር፡ ብሔረሰብ ወይም ህዝብ ማለት ሰፋ ያለ የጋራ ባህል: የጋራ ቋንቋ: የጋራ ወይም የተዛመደ ህልውና አለን ብለው የሚያምኑ እና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖሩ ናቸዉ ብሎ ትርጉም ይሰጣል።

እንግዲህ ከዚህ ድንጋጌ መረዳት የምንችለው ሁለቱ የመስቃን ወረዳዎችም ሆኑ የቡታጀራ ከተማ አስተዳደር የብሔር: የብሔረሰብም ሆነ የህዝብ ትርጉም የማያሟሉ ሲሆን ጉራጌ በሚለው ብሔር ውስጥ የታቀፉ ናቸው። ይህ ከሆነ ደግሞ ከላይ እንደጠቀስኩት በህገመንግስቱ አንቀጽ 47(2) መሠረት ከክልል ጋር በተያያዘ እራሳቸው ችለው ምንም አይነት ህጋዊ ውጤት ሊኖረው የሚችል ውሳኔ ማሳለፍ አይችሉም።

በአጭሩ በዚህ ጉዳይ መወሰነ የሚችለው ጉራጌ የሚለውን ብሔር የሚወክለው የጉራጌ ዞን ምክርቤት በመሆኑ ውሳኔያቸው ህገመንግስታዊ መሠረት ያለው አይደለም። ከዚህ በተጨማሪ ከጅምሩ የክላስተር አደረጃጀት ህገመንግስታዊ መሠረት ያለው አይደለም። ክላስተር የሚለው ቃል እራሱ ለህገመንግስቱ ባዳ ነው። በመሆኑም ከላይ ከተጠቀሰው ምክንያት በተጨማሪ በክላስተር ለመደራጀት ማጽደቅ በራሱ ህገመንግስታዊ መሠረት ያለው አይደለም።

በመጨረሻም የጉራጌ ህዝቦች ሆይ የቤት ስራችን ብዙ ነውና ምስራቅ ምዕራብ ሳንል አንድነታችን እናጠናክር።

Emat Gurage

09/08/2022
04/08/2022
07/12/2021

ኅዳር 28/2014

ፈረንሳይ ለኢትዮጵያ የ500 ሺሕ ዩሮ ድጋፍ አደረገች

ፈረንሳይ በሰሜን ኢትዮጵያ 3ቱም ክልሎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች የሚውል የ500 ሺሕ ዩሮ የፕሮጀክት ድጋፍ አደረገች።

በፕሮጀክት መልክ የተደረገው ድጋፍ ለ60 ሺሕ አባወራዎች ዘር፣ መሳሪያና መሰረታዊ የፍጆታ ቁሳቁሶችንና ለ130 ሺሕ ተፈናቃዮች የኑሮ ሁኔታቸውን ለማሻሻል ያለመ እንደሆነ አዲስ አበባ ከሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ #ዋልታ

ዛሬ በቸሀ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ታሪክ የተሰራበት ቀን ነበር
12/06/2021

ዛሬ በቸሀ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ታሪክ የተሰራበት ቀን ነበር

ሀላባ የደቡብ ክልል ር/መ/ራን በአዲሱ ፎነተ ካርታ ( Road map) የተሰጠ ስልጠና በተመለከተ
11/05/2021

ሀላባ የደቡብ ክልል ር/መ/ራን በአዲሱ ፎነተ ካርታ ( Road map) የተሰጠ ስልጠና በተመለከተ

Address

አአአ
Wolkite

Telephone

+251923133522

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከኢቲዮ-ጉራጌ እንወያይበት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ከኢቲዮ-ጉራጌ እንወያይበት:

Share

Category