በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wolkite
  • በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ  የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች  ጽ/ቤት ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለዜጎች!

የተቀዳሚ ሙፍቲህ ሐጂ ዑመር እድሪስ ህልፈትን በማስመልከት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክትየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳ...
19/10/2025

የተቀዳሚ ሙፍቲህ ሐጂ ዑመር እድሪስ ህልፈትን በማስመልከት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በማረፋቸው ኀዘን ተሰምቶኛል።
ሐጂ ዑመር በአመራር ዘመናቸው የተለያዩ ወገኖች ወደ አንድነት እንዲመጡ እና የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሕግ ዕውቅና እንዲኖረው ያደረጉትን አስተዋጽዖ ሁሌም እናስታውሰዋለን።

ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላ ኢትዮጵያ ሙስሊሞች መጽናናትን እመኛለሁ።

ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም።።።።።።።።።።።።በህዝባችንና መንግስት መካከል መተማመን በመፍጠር የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የምሁር አክሊል ወረዳ አስተዳደር ገለጸ።ተሳ...
18/10/2025

ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም
።።።።።።።።።።።።በህዝባችንና መንግስት መካከል መተማመን በመፍጠር የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የምሁር አክሊል ወረዳ አስተዳደር ገለጸ።

ተሳትፏችን እናሳድጋለን ፣ምሁር አክሊል እናለማለን ፣የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ለማሳካት በምሁር አክሊል ወረዳ በሀዋሪያት ከተማ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ እንደገለፁት መላው ህዝባችን ወቅታዊ የፖለቲካና የልማት ሥራዎች በተመለከተ የተሟላ መረጃ እንዲያገኝ ግልፀኝነት ለመፍጠር የታሰበ መድረክ መሆኑ ገልፀዋል፡፡

የፖለቲካና የልማት ስራዎችን በማጠናከርና ምንም ዓይነት ፈተናዎችንና ስጋቶችን ቢያጋጥሙ ታግሎ የማሸነፍና ወደ ዕድል በመለወጥ የተጀመረውን ወረዳዊ ሁሉዓቀፍ እንቅስቃሴ በአስተሳሰብ ጥራት ለማስቀጠል ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

የህዝባችን አስተሳሰብ ከትናንሽ ጉዳዮችን ዕይታ የወጣና ወደ ከፍታ ማሻገር የሚችል ልባዊ ተግባቦት መፍጠር የውይይቱ ግብ ነው ሲሉም ገልፀዋል፡፡

በተደራጀና በነቃ እውነተኛ የህዝብ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሂደቱም ወረዳችን ለማልማት ያመለጡንን ጊዜያትና ዕድሎችን በመረዳት ቁጭት ፈጥረን ልማታችን የሚደግፉ ዋና ዋና ተግባራት በንቅናቄ ይመራሉ ብለዋል።

የወረዳው ሰላማችን የተረጋገጠ እንዲሆንና ዜጎቻችን በፍትህ ስርዓቱ በእኩል የሚታዩበትን ሁኔታ እንዲፈጠር በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

በወረዳው ተጀምሮ ያልተጠናቀቀው ፕሮጀክቶች በዋናነት የከሬብ መስኖ ፕሮጀክት፣የዋና መንገድ አስፓልት ጥያቄ በተጨማሪ የመንገድ ጥገና፣የከሬብ ወንዝ ድልድይ፣የሀዋሪያት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቁሳቁስ ማሟላት፣የውሀና የመብራት ተደራሽነት በቀጣይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተግባቦት ይሰራል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል እንደተናገሩት በየደረጃ ያለው አመራርና ህዝብ በወረዳው ውስጥ ያሉ የልማት አቅሞችንና ፀጋዎቻችን በቅጡ በመገንዘብና አማራጮችንና አቅሞቻችን ሁሉ በመጠቀም የወረዳውን ልማት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

ከዚህ በፊት በነበሩ ስርዓቶች የነበሩ ጠንካራ ስራዎችን በማጠናከር ስህተቶችን በማረም እየሰራ ያለው ብልፅግና ፓርቲን በመደገፍ በወረዳውን የተጀመሩት የልማት እንቅስቃሴ ይበልጥ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንደተናገሩት በወረዳው ተወላጅ ባለሀብቶች ከመንግስት ጋር በመሆን በሁሉም ዘርፎች ላይ በወረዳው ለውጦች መመዝገብ መቻላቸው ተናግረዋል።

የወረዳው የልማት እንቅስቃሴዎች ይበልጥ ለማጠናከር ለኢንቨስትመት ምቹ ሁኔታዎች በመፍጠር ባለሀብቶች በወረዳው ገብተው እንዲሰሩ በማድረግ የወጣቱ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

የአካባቢ ፅዱና ውብ መንደር በመፍጠር የባህላዊ እሴቶችን በማጠናከር ጀፎሮን ተጠብቆ ለማቆየትና የገጠር ኮሪደር ልማትን በወረዳው የተሻለ ስራዎች መሰራታቸው ተናግረዋል።

ተሳትፏችን በማሳደግ የወረዳው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ለመቅረፍ እንዲሁም የወረዳውን ልማት ይበልጥ ለመጨመር የወረዳው ህዝብ ከመንግስት ጎን በመቆም ለሀገራችን እድገት አስተዋፅኦ ማድረግ እንደሚገባም ገልፀዋል።

የከሬብ መስኖ ፕሮጀክት፣የዋና መንገድ አስፓልት ጥያቄ እንዲሁም ማህበረሰቡ በየደረጃው የሚያነሱት የልማት ጥያቄዎች ለመፍታት ከክልልና ከፌደራል መንግስት ጋር ዞኑ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዞኑ በአንዳንድ አካባቢዎች እየተከሰቱ ያሉ የሰላም እጦት ችግሮች አካባቢዎችን በመለየት የክልሉ መንግስት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑ ገልፀዋል።

ከዚህ በፊት በነበሩ የተሳሳቱ አስተሳሳቦችን በማረም የወረዳው ህዝብ የልማት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት በጋራ መስራት እንደሚገባ በምክክር መድረክ የተገኙት ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

በሀገር ደረጃ የተጀመሩትን የልማት ስትራቴጂዎች መሠረት በማድረግ የወረዳው ማህበረሰብ ከመንግስት እና ከብልፅግና ፓርቲ ጎን በመቆም የሀገራችን እድገት እውን ለማድረግ አስተዋፅኦ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በውይይት መድረኩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ፣የጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል የምሁር፣የጉራጌ ዞን የአደረጃጀት ዘርፍ እና የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ፈይሰል ሀሰን የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ ፣የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሰይፈ ይልማ ፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣የሀይማኖት አባቶች ምሁራን እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የተመረቀው የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት በምስል፡-
18/10/2025

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የተመረቀው የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት በምስል፡-

ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም # # #ተሳትፏችን እናሳድጋለን ምሁር አክሊል እናለማለን በሚል መሪ ሀሳብ በምሁር አክሊል ወረዳ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።በወረዳው በባለፉት አመታት ማህበ...
18/10/2025

ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም # # #ተሳትፏችን እናሳድጋለን ምሁር አክሊል እናለማለን በሚል መሪ ሀሳብ በምሁር አክሊል ወረዳ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በወረዳው በባለፉት አመታት ማህበረሰቡን በማሳተፍ በሁሉም ዘርፍ በተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት አበረታች ስራዎች ሲሰሩ መቆየቱ የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ በመክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል።

የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማስቀጠልና ውጤታማነታቸውን ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።

በባለፉት አመታት በወረዳው በልማትና በመልካም አስተዳደር የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል።

በውይይት መድረኩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል፣ የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ፣ የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሰይፈ ይልማ፣ የዞንና ወረዳው የስራ ሀላፊዎች፣ የቀበሌ አመራር፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ዝርዝር መረጃ ይኖረናል።

ጥቅምት 7/2018ዓ.ም=========ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር ) በሆሳዕና ከተማ  እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ አደረጉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳ...
17/10/2025

ጥቅምት 7/2018ዓ.ም
=========ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር ) በሆሳዕና ከተማ እየተገነቡ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ አደረጉ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ ግንባታቸው እየተካሔደ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ምልከታ አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች በኣል የሚከበርበትን የአቢዮ ኤርሳሞ ሁለገብ ስታዲየም ጥገናና ተጨማሪ ስራዎች ተመልክተዋል።

በከተማው በመገንባት ላይ የሚገኙ የክልል ተቋማት የቢሮ ግንባታ ስራ ርዕሰ መስተዳድሩ ምልከታ አድርገዋል።

በመስክ ምልከታው የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች ዋና አስተዳዳሪዎች እና የክልሉ ካቢኔ አባላት ተገኝተዋል ሲል የዘገበው የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው ።

17/10/2025

ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም
በ2007 ዓ.ም ተጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ሲደነቃቀፍ የነበረው የአበጅ ቀበሌ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ዛሬ በሙከራ ስርጭት ላይ ይገኛል።

ጥቅምት 7/2018ዓ.ም===========የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የህግ የበላይነት የማረጋገጥ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ...
17/10/2025

ጥቅምት 7/2018ዓ.ም
===========የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የህግ የበላይነት የማረጋገጥ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ

የክልሉ ህዝብ የተጀመረውን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራ ቀጣይነት ለማረጋገጥ የበኩሉን ሚና እንዲወጣም ቢሮው ጥሪ አቅርቧል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በወቅታዊ ክልላዊ የጸጥታ ጉዳይ ላይ ለመገናኛ ብዙሀን በጽ/ቤታቸው በሰጡት መግለጫ እንዳሉት የክልሉ መንግስት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የሰዎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ተረጋግጦ ሰላምና የህግ የበላይነት የማስፈን ስራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።

በክልሉ የዜጎች ኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የገለጹት ኃላፊው በሂደቱም የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ስለመከናወናቸውም አብራርተዋል።

የክልሉ ነዋሪዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ 24 ሰዓታት በመንቀሳቀስ ሙሉ ጊዜያቸውን ስራ ላይ ማዋል እንዲችሉ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ረገድ ክልሉ ቀደም ሲል ከነበረበት ውስብስብ የሰላም ስጋት እንዲወጣ ስለመደረጉም አቶ ተመስገን በመግለጫቸው አመላክተዋል።

በክልሉ የሰላምና የህግ የበላይነት እንዲሰፍን በተደረገ ጥረት ለረጅም ጊዜ የቆዩ የህዝብ ጥያቄዎች በተግባቦትና በአሳታፊነት እንዲፈታ መደረጉን ኃላፊው ጠቅሰዋል።

የህዝቦች የስልጣንና የሃብት ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ በመደረጉ፣ ተያያዥ አለመግባበቶችም በጠብ ሳይሆን በምክክርና በተሟላ መረጃ ላይ በተመሰረተ በውይይት መፈታት እንደሚቻል ከሚመለከታቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተደጋጋሚ ምክክር በማድረግ ተግባቦት መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።

ከዚያ ውጪ በጠብና በጉልበት የሚንቀሳቀሱና ነፃና ዲሞክራሲያዊ የልዩነት ሀሳብ ያላቸውን ግለሰቦች ወይም ህዝብ በማስፈራራትና በማጥቃት ፍላጎታቸውን ለማስፈፀም የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን ህዝቡ ራሱ እንዲያወግዝና እንዲገስጽ መግባባት ተችሏል ሲሉም አቶ ተመስገን ጠቁመዋል።

ህግና ስርዓቱን በመተላለፍ ሀይልን አማራጭ በማድረግ በቀጥታና በተዘዋዋሪ በተላይም በማህበራዊ ሚዲያና በድብቅ ፌስ ቡክ ገጾች ህዝብን ከህዝብ ጋር በማጋጨት ለሰው ልጆች ሞትና ንብረት ውድመት ምክንያት በመሆን የፈጸሙና ያስፈፀሙ አካላትን ህብረተሰቡ እንዲያጋልጥ የጋራ ተግባቦት መፈጠሩን ነው ኃላፊው በመግለጫቸው የጠቆሙት።

ወንጀለኞችን በተጠናከረ የጸጥታ ሀይላችን እጅ ከፍንጅ በመያዝ፣ በጥቆማና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በምርመራ በማረጋገጥ ለህግ አቅርቦ ማስጠየቅ ተችሏል ብለዋል፡፡

ለአብነት የቀቤና፣ የማረቆ፣ የጠምባሮ፣ የምስራቅ ጉራጌ፣ የየም ህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ጋር በተያያዘ በፀጥታ ስጋትነቱ ከፍተኛውን ቦታ ይዘው የነበሩ የምስራቅ መስቃንና ማረቆ፣ በወልቂጤ ከተማና አካባቢዎች የተፈጠሩ ችግሮች ህብረተሰቡን ባሳተፈ ጥናትና በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረተ ህጋዊ መፍትሄ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በአካባቢው የተስተዋሉ ችግሮችን በህዝቡና በመንግስት መሪነት ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ተመስገን ከዚህ ባለፈ ህብረተሰቡ የአካባቢዉን ሰላም በማስጠበቅ ከዚህ ቀደም የነበረውን የወንድማማችናትና እህትማማችነት እሴት አጠናክሮ እንዲቀጥል ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

በክልሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተወሰኑ አካባቢዎች በተላይም በተወሰኑ በመዋቅሮች ወሰን አካባቢዎች ያሉ ህዝቦች አለመግባባቶች እንዲሁም የህዝቦች የባህልና የማንነት ጥያቄዎች አብዛኞቹ በህግ የበላይነትና በውይይት ከመንግስት ምላሽ የሚጠብቁ ያሉ ሲሆን ጥቂቶቹ ግን ህግን፣ የውይይትንና የምክክር አማራጭን ብቸኛ አማራጭ ባለማድረግ የሚንቀሳቀሱ አካላትን ኃላፊው በመግለጫቸው አጠቅሰዋል።

ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን ባለመጠበቅና በአሳቻ ሰዓት የመንግስት ማህበራዊ ተቋማት ላይ ጉዳት በማድረስ፣ ማህበራዊ አገልግሎቶችን በማደናቀፍ አልፎም ሀይል በመጠቀም የሰው ህይዎት እንዲጠፋና ንብረት እንዲወድም ምክንያት እየሆኑ ያሉ አካላት በቀጥታና በሀሰተኛ ስሞች በተፈጠሩ ማህበራዊ ሚዲያ በመታጀብ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ ብለዋል፡፡

እኒዚህ አካላት ሀይል ለማሰባሰብ ከዚህ ቀደም በማህበራዊ ሚዲያ ህዝብን ከህዝብ ጋር በማጋጫት በተላይም በምስራቅ መስቃንና ማረቆ አካባቢ ለሰው ልጆች ሞትና ንብረት ውድመት ምክትያት መሆናቸውን ኃላፊው አስረድተዋል።

በፖሊስ ምርመራ ተረጋግጦ፣ በፍርድ ቤት ውሳኔ እስከሚያገኝ በይግባኝ ሰሚ አካላት ተረጋግጦ፣ ተፈርዶባቸው በህግ እየታረሙ ያሉ ወንጀለኞችን የክልሉን ከፍተኛ አመራር ስለተሳደበ የታሰሩ በማስመሰል የሀሰት ወሬ በማሰራጨት በሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ከሚኖሩ አካላት ጋር በማበር በከፍተኛ የሚዲያ ዘመቻ የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ እየተሰራ ይገኛል ሲሉም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

በመሆኑም ሰላም ወዳዱ ማህበረሰብ ምክክርን፣ ውይይትን፣ ህግንና ስርዓትን፣ ሰላማዊ እንቅስቃሴን ብቸኛ አማራጭ በማስቀጠል የተጀመረው የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ወደ ላቀ ከፍታ ላይ ለማድረስ ተሳትፎውንና ተዋናይቱን በማስቀጠል ወንጀልን በመከላከል፣ ወንጀለኞችን ለህግ አሳልፎ በመስጠት የየአካባቢውን ሰላም ሊጠብቅ እንደሚገባም ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

መረጃው የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው

ጥቅምት 7፣ 2018ዓ.ም===========ርዕሰ መስተዳድር እንዳሸው ጣሰው (ዶ/ር ) በተገኙበት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅዶች አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነዉ፣የማዕከላዊ  ኢት...
17/10/2025

ጥቅምት 7፣ 2018ዓ.ም
===========ርዕሰ መስተዳድር እንዳሸው ጣሰው (ዶ/ር ) በተገኙበት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅዶች አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነዉ፣

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሸው ጣሰው (ዶ/ር ) በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅዶች አፈጻጸም ግምገማ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በአፈፃፀም ግምገማ መድረኩ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች ዋና አስተዳዳሪዎች እና የክልሉ ካብኔ አባላት ተገኝተዋል ።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሸው ጣሰው (ዶ/ር ) እንደገለፁት ፣ የሩብ ዓመት የአፈፃፀም ግምገማው በዋናናት በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ የተቀመጡ በፈጠራና በፍጥነት የመሥራት፣ የመላዉን ህብረተሰብ ተሳትፎ የማረጋገጥ ፣ዉጤታማነትንና በየደረጃው የህዝብ ተጠቃሚነትን የማሻሻል ጉዳዮችን መሠረት ያደርጋል።

በመድረኩ የዞኖች፣ የልዩ ወረዳዎች እና የቢሮዎች የሩብ ዓመት ዕቅዶች አፈጻጸም ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን ሪፖርቶቹን መሠረት ያደረገ ዉይይት ተደርጎ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ይጠበቃል።

ጥቅምት 6 /2018ዓ.ም**************ክልሉ የጀመራቸዉን የሠላምና የልማት ግንባታ ተግባራት አጠናክሮ ይቀጥላል፦ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር )  የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክል...
16/10/2025

ጥቅምት 6 /2018ዓ.ም
**************ክልሉ የጀመራቸዉን የሠላምና የልማት ግንባታ ተግባራት አጠናክሮ ይቀጥላል፦ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር )

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር ) በተገኙበት በክልላዊ ወቅታዊ የሠላምና ፀጥታ ሁኔታና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ዉይይት ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ክልላዊ ወቅታዊ የፖለቲካ እና የሠላምና የፀጥታ አዝማሚያዎች ሁኔታሪፖርት ቀርቦ ዉይይት ተደርጓል ።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) እንደገለፁት ፣ክልሉ በሁሉም መስኮች በትክክለኛ ሀዲድ ላይ ከመሆኑም ባሻገር ፤ እንደ ሀገር ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና በሚደረገዉ ጉዞ የበኩሉን ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ማረጋገጥ ተችሏል ።

የአመራር ስርዓቱ በመደመር መንግስት ቅኝት የተመራና በመደመር ትዉልድ እሳቤ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን የተጀመሩ የፖለቲካና ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ አቅም ግንባታ ሥራዎችን በማጠናከር የአመለካከትና የተግባር ዉህደትን ከፍ በማድረግ ዉጤታማነት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሠራም አመልክተዋል ።

ለስኬቶች በቂ እዉቅና መስጠትና ስኬቶቹን ለማስቀጠል መትጋት ያሻል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ፣ የየአካባቢውን ቁልፍ ችግሮች ለመፍታት ቁርጠኛ አቋም መያዙንና በቅንጅት ለመሥራትም በዉይይት መድረኩ አቋም መወሰዱን ገልጸዋል ።

የፀጥታ ሀይሉን በማጠናከር ለተልዕኮዉ ብቁና ዝግጁ የማድረግ ተከታታይ ሥራ እንደማሠራ ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)፣የህግ የባላይነትን ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መንገድ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል ።

ክልሉ በስኬቶች ታጅቦ ወደ ፊት መራመዱ የጎረበጣቸዉ አደናቃፊ ኃይሎች ፣ነጠላ ፍላጎቶችን መነሻ ያደረጉ ነጣለ ትርክቶችን በማራገብ፣ በሐሰት ዘመቻ የሕዝቦችን አብሮነት ለመሸርሸር፣ የእርስ በርስ ጥርጣሬን ለማስፋት ፣ የሠላምና የልማት ግንባታዉን ሂደት ለማደናቀፍ ጥረት ላይ በመሆናቸዉ፣ እነዚህን ኃይሎች መላዉ የክልሉ ህዝቦች በጋራ እንዲታገሏቸዉ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ የክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የክልሉ ካብኔ አባላት፣ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች፣ የዞኖችና ልዩ ወረዳዎች አስተባባሪ ኮሚቴ አባላትና የየመዋቅሩ የሠላምና ፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል ።

መረጃው የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው

ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም  # # # #በተደራራቢ የስርቆት ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በፅኑ እስራት መቀጣቱ የምሁር አክሊል ወረዳ ፍትህ ፅ/ቤት አስታወቀ።ሸውል ደምስስ የተባለው ግለሰብ በክስ...
16/10/2025

ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም # # # #በተደራራቢ የስርቆት ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በፅኑ እስራት መቀጣቱ የምሁር አክሊል ወረዳ ፍትህ ፅ/ቤት አስታወቀ።

ሸውል ደምስስ የተባለው ግለሰብ በክስ አንድ በም/አ/ወ/ መቆርቆር ቀበሌ ልዩ ቦታው የገዛ ተብሎ ከሚጠራው መንደር በሚያዝያ ወር 2017 ዓ/ም በግምት ከጠዋቱ 4:00 ሲሆን ንብረትነቱ የአቶ ደምስስ ሀብቴ የዋጋ ግምቱ 17000 ብር የሚያወጣ ጊደር ሰርቆ ኮኪር ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጅማ ገበያ ወስዶ የሸጠ ሲሆን በክስ ሁለት ላይ በቀን 08/01/2018 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 8:00 ሰዓት አካባቢ በኮ/ገ/ጉ/ወ መንጎርጉር ቀበሌ ልዩ ስሙ አንበረዝ ተብሎ ከሚጠራው መንደር ንብረትነቱ የአቶ ሸለመ ዙቤር የዋጋ ግምቱ 16000 ብር የሚያወጣ ጊደር ከተለቀቀበት ሰርቆ ወደ ም/አ/ወ/መቆርቆር ቀበሌ ልዩ ስሙ የገዛ ተብሎ ወደ ሚጠራው አካባቢ ከመጣ በኃላ በክትትል ተይዟል።

በሁለት ተደራራቢ የስርቆት ወንጀል ክስ የቀረበበት ሲሆን ተከሳሽ ለችሎት ቀርቦ የቀረበበት የወንጀል ክስ መፈፀሙን አምኖ ስለአፈፃፀሙ በዝርዝር ለችሎት አስረድቷል።

የወረዳው ዓ/ህግም ተከሳሽ ባመነው መሠረት ጥፋተኝነቱ ይረጋገጥልኝ ያለ ሲሆን የም/አ/ወ/ፍ/ቤት በቀን 04/02/2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በወ/ስ/ስ/ህ/ቁ.134(1) መሠረት የተከሳሽን ጥፋተኝነት አረጋግጦ የግራ ቀኙ የቅጣት አስተያየት ከሰማ በኃላ በቀን 05/02/2018 በዋለው ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌሎችን ያስተምራል ያለውን በ 4 ዓመት ከ 3 ወር እዲቀጣ ተወስኗል።

መረጃው ያደረሰን የምሁር አክሊል ወረዳ ፍትህ ፅ/ቤት ነው።

ለፍትህ አካላት አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ ወንጀልን በጋራ እንከላከል!!!

ጥቅምት 06/2018ዓ.ም============= #በየመዋቅሩ ሁለንተናዊ ሰላም ለማስፈን እና ብልጽግና ለማረጋገጥ የወረዳው የጸጥታ መዋቅር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ።የምሁር አክሊል ወ...
16/10/2025

ጥቅምት 06/2018ዓ.ም
============= #በየመዋቅሩ ሁለንተናዊ ሰላም ለማስፈን እና ብልጽግና ለማረጋገጥ የወረዳው የጸጥታ መዋቅር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ።

የምሁር አክሊል ወረዳ ሚሊሻ ጽ/ቤት ከወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በየቀበሌ ለሚገኙ የሚሊሻ አባላት የደንብ ልብስ የማልበስ መረሃ ግብርና የተግባር ስልጠና ሰጠ።

የማህበረሰቡ ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ በወረዳው ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች የሚሊሻ ኀይል በመመልመልና በማሰልጠን ስምሪት በመስጠት እየሰራ እንደሚገኝ የምሁር አክሊል ወረዳ ሚሊሻ ጽ/ቤት ኀላፊ አቶ አንቄ ኑርጋ ተናግረዋል።

ይህ ኀይል በህዝባችን በሠላም እሴት ላይ ግንባር ቀደም በመሆን የምታገለግሉ፣ የጸጥታ መዋቅሩ አጋዥ መሆናችንን ከወዲሁ መገንዘብ ያስፈልጋል።

ተቋሙ በ2017በጀት ዓመት ቀላል የማይባሉ የሠላም እሴት ሊያዛቡ የሚችሉ ጉዳዮች በመግባባት በመነጋገር እንዲፈቱ ከማድረግ፣ በሠላምና ጸጥታ ጉዳይ ግንዛቤ ማስጨበጥ፣ የሚሊሻ አባላት ማደራጀት፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ጥቅማ ጥቅም ከማስከበር፣ የዘማች ቤተሰብ መደገፍ እንዲሁም ሌሎችም ተግባራቶች መፈጸማቸው ጠቁመዋል።

ኀላፊው አክለው ለሀገርም ሆነ ለግለሠብ ሰላም እጅግ አስፈላጊና ግንባር ቀደም ከሆኑ ነገሮች ውስጥ ዋነኛና ተጠቃሹ ነው ብለው ሰላምን ለማስፈን ቁርጠኛ ሆኖ መስራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

በመድረኩ የተገኙት የምሁር አክሊል ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ተከስተ ትግስቱ የፀጥታ ሀይል አጋዥ ሆኖ በቀበሌ ደረጃ እየሰራ የሚገኘው የሚሊሻ አካል ከማህበረሰቡ ለየት የሚያደርገው ልብስ ለብሶ ከግለሰብ አንስቶ እስከ አካባቢ ድረስ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ማስከበር እንዳለበት ገልፀዋል።

የሀገር ሉአላዊነቷ በተደፈረ ጊዜ የሚሊሻ አባላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ለዚህ ኀይል የደንብ ልብስ ማልበስ፣ የስነ ልቦና እና የአካል ብቃት ስልጠና በዛሬው እለት መሠጠቱ ለቀጣይ ስራዎች አበረታች ነው።

ምክትል ኢንስፔክተሩ አክለው ሁሉም ማህበረሰብ ከፀጥታ አካላት ጎን በመሰለፍና የመረጃ ምንጭ በመሆን ወንጀልን በጋራ መከላከል ያስፈልጋል ሲሉ አሳስበዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች እንደገለጹት የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በየቀበሌው ሠላም እንዲሰፈን ለማድረግ የሚሊሻ ኃይል መልምሎ፣ ተቀናሽ ለሰራዊት አባላት እና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት አሳትፎ በሴክተሩ ተግባርና ኀላፊነት እንዲሁም በመመሪያና ደንብ ዙሪያ ስልጠና መስጠቱ ጥሩ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ የተጠናከረ ስራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸው አመላክተዋል።

በመጨረሻም የተሻለ አፈጻጸም ለነበራቸው ሚሊሻዎችና ለጽ/ቤቱ ባለሙያዎች የእውቅና መረሃ ግብር ተካሂዷል።

መረጃው የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የአንደኛ ሩብ ዓመት የዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀምና ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል...
15/10/2025

የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የአንደኛ ሩብ ዓመት የዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀምና ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል!!

ጥቅምት 5/2018 (ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የ2018 ዓ/ም በአንደኛው ሩብ ዓመት የፓርቲና የመንግስት ዋና ዋና የንቅናቄ ስራዎችና የነባራዊ ሁኔታ የግምገማ መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በመድረኩ በሩብ ዓመቱ የአመራሩ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት እንደነበር ተመላክቷል!

በግብርና፣በፀጥታ፣በስራ እድል ፈጠራ፣ በትምህርት ፣ገቢ፣ንግድና ሌሎችንም ተግባራት በሩብ አመቱ የተመሩበት አግባብና አፈፃፀማቸውን ጨምሮ የፓርቲ የአንደኛ ሩብ ዓመት ድጋፋዊ ክትትል ሪፖርትና በየደረጃው ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ይገኛል!!

በመድረኩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል ጨምሮ የዞን መዓከል ጠቅላላ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛል።

Address

Hawariyat
Wolkite

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት:

Share

Category