Addisout.Com

Addisout.Com Provides Various Entertainment on music, short sketches & comedy Provide Information on Ethiopia Entertainment, Business,Politics and Travel

አንዱአለም ጎሳ ዛሬ ተፈቷል ! የጉድ ሃገር...
10/06/2025

አንዱአለም ጎሳ ዛሬ ተፈቷል ! የጉድ ሃገር...

ፓሪስ ይገባዋል...👏🏿👏🏿! ጭርሽ ፋይናል አይመስልምCongrats PSG...Well deserved Victory
01/06/2025

ፓሪስ ይገባዋል...👏🏿👏🏿! ጭርሽ ፋይናል አይመስልም
Congrats PSG...Well deserved Victory


------ኖሮው እያደረቀን የሬሳ ማድረቂያ አይገባንም-----በወተት ውስጥ የሬሳ ማድረቂያ.... በወተትና መሰል ምርቶች ላይ የአስከሬንማድረቂያ(Formaldehyde) የሚጠቀሙ ነጋዴዎች እንዳ...
27/05/2025

------ኖሮው እያደረቀን የሬሳ ማድረቂያ አይገባንም-----

በወተት ውስጥ የሬሳ ማድረቂያ....
በወተትና መሰል ምርቶች ላይ የአስከሬን
ማድረቂያ(Formaldehyde) የሚጠቀሙ ነጋዴዎች እንዳሉ ተገለጸ - ሸገር ሬዲዮ !


❤️❤️የሳቃችን ምንጭ አቡ ሱራፌል ብስራት ተሞሽሯል!❤️❤️  እንኳን ደስ ያለህ  ዘጠነኛው ሺ Surafel Bisrat
25/05/2025

❤️❤️የሳቃችን ምንጭ አቡ ሱራፌል ብስራት ተሞሽሯል!❤️❤️
እንኳን ደስ ያለህ
ዘጠነኛው ሺ Surafel Bisrat

ደሃ እና ጥቁር ጉዳን ከያዘህ አይለቅህም Really Yonatan Aklilu? የሚዳው መኪና፣ የሚኖርበት ቤት ሱፉ, የልጆቹ ልብስ, የሚስቱ ዊግ እያንዳንዱ ዛሬ አለኝ የሚለው ነገሩ ከደሃ እጅ...
24/05/2025

ደሃ እና ጥቁር ጉዳን ከያዘህ አይለቅህም Really Yonatan Aklilu?

የሚዳው መኪና፣ የሚኖርበት ቤት ሱፉ, የልጆቹ ልብስ, የሚስቱ ዊግ እያንዳንዱ ዛሬ አለኝ የሚለው ነገሩ ከደሃ እጅ ከተሰበሰበ ወይም ከተነጠቀ ብር እንደሆነ ዘንግቶት... This shall Pass

የ11 ዓመቷ ህፃን በዓምላክ ግርማ ገዳዮች የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው፡፡
23/05/2025

የ11 ዓመቷ ህፃን በዓምላክ ግርማ ገዳዮች የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው፡፡

ጠሚ አብይ ወደ ጠፍር ሊጓ ዙ ነው የሚለው የመሰረት ሚድያ ዜና እውነት ነው ወይስ ...🛰🚀 🛰
23/05/2025

ጠሚ አብይ ወደ ጠፍር ሊጓ ዙ ነው የሚለው የመሰረት ሚድያ ዜና እውነት ነው ወይስ ...🛰🚀 🛰



የባንክ ሹፌሮቹ ከህዝቡ 4 ሚልየን ብር የሚያወጣ የባንክ አካውንት እንዲያስከፍቱ እስከ ሰኔ አጋማሽ ድረስ ቀነ ገደብ ተሰጣቸው! Meseret Media _________________________...
20/05/2025

የባንክ ሹፌሮቹ ከህዝቡ 4 ሚልየን ብር የሚያወጣ የባንክ አካውንት እንዲያስከፍቱ እስከ ሰኔ አጋማሽ ድረስ ቀነ ገደብ ተሰጣቸው! Meseret Media
_________________________________________________________________
በዚህ አስተያየት ላይ....

"የግል ባንኮች ሰራተኞች ላይ ከዲስትሪክት ጀምሮ በየቀኑ እየተደወለ አንዳንዴም ወደ ቅርንጫፎች እየመጡ ሰራተኞቹ ማድረግ የማይችሉትን ትዕዛዝ በመሥጠት ያን ካላደረጉ ደግሞ ከደሞዛቸው ጀምሮ ብዙ ቅጣቶች እንደሚጠብቃቸው እያስፈራሩ ብቻም ሳይሆን እያደረጉትም ይገኛሉ" የሚል አስተያየት በፀሀፊው አቶ ፍቃዱ ኤርሱሞ ተንፀባርቋል።
_____________________________________________________________________

መሠረት ሚድያ Reports

በርካታ የግል ባንኮች ሰራተኞቻቸውን በአስገዳጅነት ህብረተሰቡን የባንክ አካውንት እንዲያስከፍቱ ተልዕኮ እየተሰጡ መሆናቸውን የሚገልፅ አንድ አስተያየት በትናንትናው እለት ማስነበባችን ይታወሳል።

ዛሬ የምናስነብባችሁ ደግሞ ባንኮች ውስጥ በሹፌርነት ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች እያንዳንዳቸው በድምሩ 4 ሚልየን ብር የሚሆን የባንክ አካውንት እንዲያስከፍቱ ስለታዘዙ ሹፌሮች ነው።

ጉዳዩ እንዲህ ነው፣

አዋሽ ባንክ Awash Bank እንደሌሎቹ ባንኮች ሁሉ ገንዘብ ለማሰባሰብ ሰራተኞቹን በከተማው ከማሰማራቱ ውጪ ሹፌሮቹም እያንዳንዳቸው 4 ሚልየን ብር deposit አስደርጉ መባላቸውን ሰማን።

"ሹፌሩ መኪናውን በአግባቡ መንዳት ትቶ ስለ ገንዘብ ማሰባሰብ ሲያስብ እና ሲጨነቅ ነው የሚውለው" ያሉን አንድ የተቋሙ ሰራተኛ ሁሉም ሹፌሮች እስከ ሰኔ አጋማሽ ግባቸውን እንዲመቱ (4 ሚልየን ብር ከህዝቡ deposit እንዲያስደርጉ) መታዘዛቸውን ተናግረዋል።

መሠረት ሚድያ የተመለከው አንድ የባንኩ ሰራተኞች የመልዕክት መለዋወጫ ግሩፕ ላይ የተፃፈ መረጃ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሲሆን "እያንዳንዱ የባንኩ አሽከርካሪ መኪና መንዳት ብቻ ሳይሆን ሀብት በማሰባሰብ ዘመዶቹን እና ጓደኞቹን ቡክ በማስከፈት አዳዲስ ደንበኞችን ማምጣት አለበት" ይላል።

መልዕክቱ አክሎም "አንድ አሽከርካሪ 4 ሚልዮን ብር ቢያመጣ የታለመውን እቅድ በቀላሉ ከግብ እናደርሳለን፣ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሰኔ አጋማሽ ድረስ በተሰጣችሁ እቅድ መሰረት እያንዳንዳችሁ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት እንድትተባበሩ" ይላል።

ደህና ኑሮ ይኖራሉ የሚባሉትን ጨምሮ በርካታ የህብረተሰብ ክፍል ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ በሆነበት በዚህ ወቅት አንድ ሹፌር በምን መልኩ 4 ሚልዮን ብር የሚያወጣ ቡክ ማስከፈት እንደሚችል ለበርካቶች ጭንቀትን ብቻ ሳይሆን አስደማሚ ሆኗል።

በዚህ ዙርያ ከባንኩ መረጃ ከደረሰን እናቀርባለን።

መረጃን ከመሠረት!

(መሠረት ሚድያ)- በርካታ የግል ባንኮች ሰራተኞቻቸውን በአስገዳጅነት ህብረተሰቡን የባንክ አካውንት እንዲያስከፍቱ ተልዕኮ እየተሰጡ መሆናቸውን የሚገልፅ አንድ አስተያየት በትናንትና....

ከንቲባ አዳነች አበቤ በአሜሪካ ሽር ብትን ሲሉ ታይተዋል። የሰራ ሰው እረፍት ያስፈልገዋል።እስቲ ፍቅራችሁን ግልጡላት...
15/05/2025

ከንቲባ አዳነች አበቤ በአሜሪካ ሽር ብትን ሲሉ ታይተዋል። የሰራ ሰው እረፍት ያስፈልገዋል።
እስቲ ፍቅራችሁን ግልጡላት...

ጌታቸው ረዳ እንዴት አደርክ!?😁😁😁 ቃለ መጠይቁን እንዴት አያችሁት?
13/05/2025

ጌታቸው ረዳ እንዴት አደርክ!?😁😁😁

ቃለ መጠይቁን እንዴት አያችሁት?

ሁሉም ለዋንጫ ደረሰ...Man Utd Vs Spurs --- Europa LeagueChelsea Vs Real Betis ---- Europa Conference League አርሰናል ብቻ ቀረ...ምን ይሻ...
09/05/2025

ሁሉም ለዋንጫ ደረሰ...
Man Utd Vs Spurs --- Europa League
Chelsea Vs Real Betis ---- Europa Conference League
አርሰናል ብቻ ቀረ...ምን ይሻላል
ሚኬል አርቴታ Mikel Arteta ይጫር አይጫር ?





ፖሊስ አንዱአለም ቤት ውስጥ ነበር ብሏል...ማነጀሩ ሌሊሳ ትናንት አንዱአለም ቤት እንዳልነበረ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ገልጾ ነበር !  ____________________________________...
12/03/2025

ፖሊስ አንዱአለም ቤት ውስጥ ነበር ብሏል...
ማነጀሩ ሌሊሳ ትናንት አንዱአለም ቤት እንዳልነበረ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ገልጾ ነበር !
_____________________________________________

በሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ አሟሟት ዙሪያ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!

ውዳሴ ህንፃ ላይ ነዋሪ የነበረችው ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ መጋቢት 01 ቀን 2017 ዓ/ም ከሌሊቱ 10፡00 ሠዓት አካባቢ ከቤቷ የማብሰያ ክፍል በኩል ካለው በረንዳ 5ኛ ፎቅ ላይ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ወድቃ ለህክምና እርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለበት ወቅት ህይወቷ አልፏል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃው ከደረሰው በኋላ የምርመራ ቡድን በማዋቀርና ቦታው ድረስ በመሄድ ተገቢውን የቴክኒክና የታክቲክ መረጃዎችን ያሰባሰበ ሲሆን የሟችንም አስከሬን ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለተጨማሪ ለምርመራ እንዲሄድ አድርጓል፡፡

ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ በወቅቱ ከበረዳ ላይ በወደቀችበት ሰዓት ፖሊስ በቤቱ ውስጥ የነበረውን ባለቤቷን ድምፃዊ አንዷለም ጎሳን በቁጥጥር ስር በማዋልም ምርመራ እያጣራ ሲሆን

በቀጣይ የመጨረሻውን የምርመራ ውጤትም ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ እያስታወቀ በተለያዩ ማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ከፖሊስ የወንጀል ምርመራ ውጤት በፊት የሚናፈሱ መረጃዎች ተገቢነት የሌላቸው ከመሆኑም ባሻገር በምርምራ ሒደቱ ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅህኖ በመገንዘብ የተሳሳተ መረጃ የሚያስተላልፉ እና የሚያሰራጩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ

Osoite

Tampere
33540

Hälytykset

Tiedä ensimmäisenä ja anna meille oikeus lähettää sinulle sähköpostitse uutisia ja promootioita Addisout.Com :ltä. Sähköpostiosoitettasi ei käytetä muihin tarkoituksiin, ja voit perua milloin tahansa.

Ota Yhteyttä Yritys

Lähetä viesti Addisout.Com :lle:

Jaa