Sheger info

Sheger info Sheger info ማህበራዊ እና የመዝናኛ መረጃዎችን የሚቀስሙበት ገጽ

በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ ስለ ተከሰተው እሳት አደጋ:- መረጃ ዛሬ ታህሳሥ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማ...
14/12/2025

በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ ስለ ተከሰተው እሳት አደጋ:- መረጃ

ዛሬ ታህሳሥ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ሕንፃ ቁጥር 2 ውስጥ ጥገና በሚሰራበት ቦታ ከብረት ብየዳ በተፈጠረ ፍንጣቂ አንዲት ትንሽ ክፍል ውስጥ እሳት ተከስቶ የነበረ ሲሆን ምንም አይነት ጉዳት ከማድረሱ በፊት ወድያውኑ እንዲጠፋ ተደርጓል። በክስተቱ ምክንያት በመንገደኞች መውጫ እና መግቢያ ላይ የተከሰተ ምንም አይነት መስተጓጎል አለመፈጠሩን ለማሳወቅ እንወዳለን ሲል አሳውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤

ሕፃናት በ12 ዓመታቸው ስማርት ስልክ እንዲጠቀሙ መፍቀድ የሚያስከትለውን ጉዳት ያውቃሉ? Sheger infoሕፃናት በ12 ዓመታቸው የሞባይል ስልክ (ስማርት ስልክ) እንዲይዙ እና እንዲጠቀሙ መ...
14/12/2025

ሕፃናት በ12 ዓመታቸው ስማርት ስልክ እንዲጠቀሙ መፍቀድ የሚያስከትለውን ጉዳት ያውቃሉ?
Sheger info

ሕፃናት በ12 ዓመታቸው የሞባይል ስልክ (ስማርት ስልክ) እንዲይዙ እና እንዲጠቀሙ መፍቀድ ልጆቹን ለድባቴ እንዲዳረጉ፣ ከመጠን በላይ ለሆነ ውፍረት ታጋላጭ እንዲሆኑ እና ለእንቅልፍ እጦት እንደሚዳርጋቸው አንድ ጥናት አመልክቷል።

አዳጊዎች በረጅም ጊዜ ሂደት የአዕምሮ ዕድገት እና ጤና በተመለከተ ከ2018 እስከ 2020 ባለው ጊዜ ከ10 ሺህ ሰዎች መረጃ በመሰብሰብ ነበር ጥናቱ በአሜሪካ ብሔራዊ የጤና እንስቲቲዩት ድጋፍ የተከናወነው።

በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የፊላደልፊያ የሕፃናት ሆስፒታል እና የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ በመሆን ነበር ሕፃናት የሞባይል ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ መፈቀድ የሚያስከትልው ጉዳት ምንድነው የሚለውን ጉዳይ ለመለየት እና የመፍትሔዎችን ለመጠቆም ጥናቱን ሲያከናውኑ የቆዩት።

ዩኒቨርሲቲዎቹ ዕድሜያቸው 12 ዓመት የሆኑ ሕፃናት ዘመናዊ ስልክ እንዲጠቀሙ መፍቀድ ከአእምሮ በሽታ እና ከመጠን በላይ ውፍረት ቀጥተኛ ግንኙነት እንዳለው በዚሁ በሠሩት ጥናት ማረጋገጥ ችለዋል።

ዘመናዊ ሞባይል እንዲጠቀሙ የተፈቀደላቸው ሕፃናት ከማይጠቀሙ ሕፃናት አንፃር የበለጠ ለድባቴ (ለድብርት የማገለጥ) እንዲሁም በቂ እንቅልፍ ያለማግኘት ችግር እንደሚያጋጥማቸው በጥናቱ ተጠቁሟል።

ዕድሜያቸው 12 ዓመት የሞላቸው እና ስልክ የማይዙ በጥናቱ የተሳተፉ ሕፃናት ዘመናዊ ስማርት ስልክ እንዲጠቀሙ ከተፈቀደላቸው አንፃር የተሻለ አዕምሯቸው ጤናማ እንደሆነም በጥናቱ ተረግጧል።

"የሕፃናት እና ጎልማሶች ወሳኝ ዓመታት ለመግራት መሠረታዊያን" የሚል መሐሐፍ ደራሲ የሆኑት ዶ/ር ሼሪል ጎንዛሌዝ እንደሚሉት፣ ሕፃናቱ የሚጠቀሟቸው የኤልክሮኒክስ መሣሪያዎች ታብሌትም ሆነ ዘመናዊ ስልክ ሌሎችም ቢሆን ውጤቱ ተመሳሳይ ነው።

በመሆኑም ወላጆች ለልጆች ዘመናዊ ስልኮችን እና ታብሌቶች ሰጥቶ ዝም ከማለት የቅርብ ክትትል በማድረግ እና ለአለስፈላጊ ይዘት ተጋላጭነትን በመቀነስ በቂ እንቅልፍ እንዲያገኙ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ይላሉ።

ወላጆች እና ሞግዚቶች ለሕፃናት በስማርት ስልኮችን ገዝተው በመስጠት በማኅበራዊ ሚዲያ ሱስ እንዲጠመዱ ከማድረግ ለሕፃናት ጊዜ መስጠት እንዲጫወቱ ማድረግ ጊዜው አሁን ነው በማለት መክረዋል።

ሕፃናት በስማርት ስልክ ያላቸውን የዕይታ ጊዜን በመገደብ፣ ጤናማ የስማርት ስልክ አጠቃቀም ባህል ማዳበር ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ዶ/ር ሼሪል ጎንዛሌዝ አሳስበዋል።

EBC

አይ ሾው ስፒድ በአፍሪካ ዋንጫው ሊገኝ ነው ! ታዋቂው አሜሪካዊ " ስትሪምር " አይ ሾው ስፒድ ለቀጣዩ አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ሞሮኮ እንደሚገኝ አስታውቋል። በውድድሩ ወቅት ከሞሮኮ ቱሪዝም ቢ...
14/12/2025

አይ ሾው ስፒድ በአፍሪካ ዋንጫው ሊገኝ ነው !

ታዋቂው አሜሪካዊ " ስትሪምር " አይ ሾው ስፒድ ለቀጣዩ አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ሞሮኮ እንደሚገኝ አስታውቋል።

በውድድሩ ወቅት ከሞሮኮ ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመሆን የቀጥታ ስርጭት ለማድረግ መታሰቡ ተነግሯል።

የሞሮኮ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከዚህ በፊት አይ ሾው ስፒድ በአፍሪካ ዋንጫው እንዲገኝ ንግግር ላይ እንደነበር ሲገለፅ ነበር።

ተፅዕኖ ፈጣሪው " ስትሪመር " በአፍሪካ ዋንጫው እንዲገኝ የተፈለገው ውድድሩ አለም አቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ ለማስቻል በማለም መሆኑ ተነግሯል።

ከ7 ዓመታት በኋላ የሚደረገው ተጠባቂ ደርቢ16ኛ ሳምንቱ ላይ በደረሰው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በታይን ዌር ደርቢ ሰንደርላንድ ከ ኒውካስትል ዩናይትድ የሚገናኙበት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ ከ...
14/12/2025

ከ7 ዓመታት በኋላ የሚደረገው ተጠባቂ ደርቢ

16ኛ ሳምንቱ ላይ በደረሰው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በታይን ዌር ደርቢ ሰንደርላንድ ከ ኒውካስትል ዩናይትድ የሚገናኙበት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ከሰባት ዓመት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ የተመለሰው ሰንደርላንድ ጠንካራ ጅማሮ ያደረገ ሲሆን ዛሬም ለኒውካስትል ሌላ ፈተና እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

ከጨዋታ አለፍ ያለ ጉልበት የሚቀላቀልበት እና አንድ አንድ ጊዜ ለዳኞች ፈታኝ የሚሆነው ደርቢ 11 ሰዓት ላይ የሚጀመር ይሆናል፡፡

በሌላ ተጠባቂ መርኃ ግብር 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንችስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ ከ ከሜዳው ውጭ ከክሪስታል ፓለስ ይጫወታል፡፡

የፔፕ ጋርዲዮላ ስብስብ ልዩነቱን ለማጥበብ ወደ ሜዳ በሚገባበት ጨዋታ ከፓላስ ጠንካራ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡

በ26 ነጥብ 5ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ፓላስ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ለማግኘት ጥሩ ግስጋሴ ላይ የሚገኘ ቢሆንም በፕሪሚየር ሊጉ ከሲቲ ባደረጋቸው ያለፉት 10 ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም፡፡

11 ሰዓት ላይ በሚደረገው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ አሁንም የማቲዮ ኮቫችቺ እና ሮድሪን ግልጋሎት በጉዳት የማያገኝ ሲሆን የጆን ስቶንስ መሰለፍም አልተረጋገጠም፡፡ በፓላስ በኩል መጠነኛ ጉዳት የነበረባቸው ጃን ፍሊፕ ማቴታ እና ኢስማይላ ሳር ለጨዋታው ዝግጁ ሆነዋል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል 3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አስቶን ቪላ ከሜዳው ውጭ ከዌስትሀም ዩናይትድ ሲጫወት፤ ቶተንሀም ከኖቲንግሀም ፎረስት እና ብሬንትፎርድ ከሊድስ ዩናይትድ ሌሎች ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡

የዳሰነች ወረዳ ባወጣው መግለጫ ውሳኔውን ለማሳለፉ በምክንያትነት የጠቀሰው "የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ ዳግም በሰዎች ላይ እየተገኘ መሆኑን" ነው። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሐቴ ...
14/12/2025

የዳሰነች ወረዳ ባወጣው መግለጫ ውሳኔውን ለማሳለፉ በምክንያትነት የጠቀሰው "የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ ዳግም በሰዎች ላይ እየተገኘ መሆኑን" ነው። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሐቴ በበኩላቸው ውሳኔው የተላለፈው አንድ ተጨማሪ ሰው በቫይረሱ እንደተያዘ መረጋገጡን ተከትሎ መሆኑን ለቢቢሲ ገልጸዋል።

የትናንቱ ታማሚ የተገኘው በዳሰነች ወረዳ እንደሆነ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ታደለ፤ "እርሱን አላውቅም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
bbc

ባለፉት ሶስት ዓመታት ብቻ 6 ቅርሶችን በዩኔስኮ ያስመዘገበችው ኢትዮጵያ‎‎ኢትዮጵያ ባለፉት ሦስት ዓመታት ብቻ ስድስት ቅርሶችን በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት ማስመዝገቧን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥ...
14/12/2025

ባለፉት ሶስት ዓመታት ብቻ 6 ቅርሶችን በዩኔስኮ ያስመዘገበችው ኢትዮጵያ


‎ኢትዮጵያ ባለፉት ሦስት ዓመታት ብቻ ስድስት ቅርሶችን በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት ማስመዝገቧን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር ተናግረዋል፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታት በዩኔስኮ ከተመዘገቡት ቅርሶች መካከል የ"ሔር ኢሴ" ባህላዊ ህግ፣ የሸዋል-ኢድ በዓል አከባበር፣ የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር፣ የመልካ ቁንጡሬ መካነ ቅርስ፣ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ተጠቃሽ ናቸው፡፡

ከሰሞኑ‎ በህንድ ኒውዴሊሂ በተካሄደው 20ኛው የተመድ ትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ስብሰባ ላይ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ጊፋታ" በማይዳሰስ የሰው ልጆች ወካይ የዓለም ቅርስነት ተመዝገቧል።

እነዚህ ውጤቶች መገኘት የቻሉት ኢትዮጵያ ለቱሪዝም ዘርፉ እና ለቅርሶች ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ በመሥራቷ እንደሆነ ይገለፃል።

ቅርሶቹ በዓለም ቅርስነት መመዝገባቸውና መረጃቸው በዩኔስኮ ድረ-ገፅ ላይ መቀመጡ ከዓለም ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ቱሪስቶችን ቁጥር በመጨመር ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያስገኛል።

‎ኅብረ ብሔራዊቷ ኢትዮጵያ የብዝኃ ማንነት እና ባህል ባለቤት እንደመሆኗ በቀጣይም የሚመዘገቡ ቅርሶች ስለመኖራቸው አቶ ኤልያስ ጠቁመዋል።

‎በ20ኛው የዩኔስኮ ስብሰባ የተሳተፉት አቶ ኤሊያስ ሽኩር፤ "ጊፋታ" ዓለም አቀፍ ቅርስ ሆኖ በፀደቀበት ቅፅበት በኢትዮጵያ ልዑክ በኩል የነበረው ደስታ ልዩ እንደነበር ለኤፍ ኤም 97.1 ተናግረዋል።

‎"ቅርሱን በተመለከተ ለአፅዳቂው ኮሚቴ ከቀረበው ሰነድ ጀምሮ በጥራት በመዘጋጀቱ እንደሚፀድቅ እርግጠኛ ብንሆንም በወቅቱ ይፋ ሲደረግ ግን ኢትዮጵያ ተጨማሪ ቅርስ በማስመዝገቧ እጅግ ተደስተናል" ብለዋል አቶ ኤልያስ።
‌‎
‎በአዳራሹ የታደሙ የሌሎች ሀገራት ተወካዮችም፤ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ቅርስ በማስመዝገቧ ደስታቸውን እንደገለፁለቸው አቶ ኤሊያስ አስታውሰዋል።

‎ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ስለቱሪዝም በሰጡት ማብራሪያ "ቅርሶችን ወደ ቁርስነት መቀየር" መቻል እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎"ጊፋታ" በማይዳሰስ የዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ቅርሱ ዓለም አቀፍ ጥበቃ እንዲደረግለት፣ እንዲሁም ስለ ቅርሱ ታሪክ እና አጠቃላይ መረጃ በዩኔስኮ ድረገጽ እንዲቀመጥ የሚያስችለው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

‎የ"ጊፋታ" በዓልን ጠብቀው ለትውልድ ያስተላለፉ የወላይታ እናቶች እና አባቶች፣ ጥናት በማድረግ እና በመሰነድ በኩል ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ባህሉ እንዲተዋወቅ ያደረገው የዞኑ አስተዳደር ለቅርሱ መመዝገብ ሚናቸው ጉልህ እንደነበር ተነስቷል።

‎"ጊፋታ" በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበው ዩኔስኮ ያወጣውን አምስት መስፈርቶች በማሟላት ነው።


EBC

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በታጣቂዎች ተገ’ሉ።የኅዳር  ጽዮን ማርያምን በዓል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው በሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለ...
14/12/2025

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በታጣቂዎች ተገ’ሉ።

የኅዳር ጽዮን ማርያምን በዓል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው በሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ሻንቡ ከተማ መዳረሻ ሲደርሱ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ እና በርካታ የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞችና ወጣት የማኅበራት አገልጋዮች በታጣቂዎች ተወስደው የቆዩ ሲሆን ሌሎቹ ተፈትተው ቆይተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ኡፋ እና የስብከተ ወንጌል አገልጋይ የሆኑት ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል::

 #እንኳን ደስ ያለሽ!Sheger infoየICONIC AWARDS EAST AFRICA ሁለት ሽልማቶች አሸናፊ ቲክቶከር ዩቲ ናስ።
14/12/2025

#እንኳን ደስ ያለሽ!
Sheger info
የICONIC AWARDS EAST AFRICA ሁለት ሽልማቶች አሸናፊ ቲክቶከር ዩቲ ናስ።

ሽንሺቾ ?በከምባታ ዞን፣ በሽንሺቾ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ ዋና አስፓልት መንገድ ነገ ለሚካሄድ የሰርግ መልስ ፕሮግራም በድንኳን ተዘግቶ መዋሉን ፤ እስከ ምሽት ድረስም እንደዛው እንደ...
14/12/2025

ሽንሺቾ ?

በከምባታ ዞን፣ በሽንሺቾ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ ዋና አስፓልት መንገድ ነገ ለሚካሄድ የሰርግ መልስ ፕሮግራም በድንኳን ተዘግቶ መዋሉን ፤ እስከ ምሽት ድረስም እንደዛው እንደነበር ፤ በዚህም ምክንያት በርካቶች መጉላላታቸውን ተገልጸዋል።

መንገዱ በሁለቱም በኩል ማለትም በመሄጃውም በመምጫውም በኩል ተዘግቶ ስለነበር ተሽከርካሪዎች ማለፍ ሳይችሉ እንደቀሩና እንደተጉላሉ ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል።

አማራጭ መንገድ ተጠቅሞ ውስጥ ለውስጥ ሲሄድ የነበረ ጭድ የጫነ አይሱዙ ተሽከርካሪ የኤሌክትሪክ ገመድ በመንካቱ መቃጠሉን አክለዋል።

መንገዱ በርካታ ተሽከርካሪዎች የሚተላለፉበት ነው ፣ አምቡላንስም ሰዎች ይዞ ያልፋል መንገዱ በመዘጋቱ የሚፈጠረው ችግር ብዙ ነው ይሄ እንዴት አይታሰብም ሲሉ ጠይቀዋል።

ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት ምን አሉ ?

" እሁድ ታህሳስ 5 ለሚደረግ የመልስ ፕሮግራም ተብሎ ዋናዉ አስፓልት በድንኳን ከቅዳሜ ለሊት ጀምሮ ተዘግቷል።

ተለዋጭ ተብሎ በተዘጋጀዉ መንገድ እየሄደ ያለ ጭድ የጫና አይሱዙ መኪና ከመብራት ጋር ተገናኝቶ በተፈጠረ እሳት ሙሉ በሙሉ ወድሟል።

የመኪናዉ ሹፌር መኪናዉን ነፃ ወደ ሆነ ቦታ በመንዳት ዘሎ የወጣ ሲሆን በሰዉ ሕይወት ላይ ጉዳት አልደረሰም።

ከዚህ ባለፈ የመንገዱን መዘጋት ተከትሎ በተፈጠረ አለመግባባት ተኩስም ነበር። አሁን ላይ አንደኛው ድንኳን ተነስቷል። "

ሳዑዲ አረቢያ ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከ19,500 በላይ የህግ ተላላፊዎችን በቁጥጥር ስር አዋለች!ሪአድ — የሳዑዲ አረቢያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፣ ባለፈው ሳም...
14/12/2025

ሳዑዲ አረቢያ ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከ19,500 በላይ የህግ ተላላፊዎችን በቁጥጥር ስር አዋለች!

ሪአድ — የሳዑዲ አረቢያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፣ ባለፈው ሳምንት (ከዲሴምበር 4 እስከ ዲሴምበር 10) ባለው ጊዜ ውስጥ በፀጥታ ኃይሎች እና በተዛማጅ የመንግስት አካላት በተደረጉ የጋራ ፍተሻዎች 19,576 ህገወጥ ነዋሪዎች ተይዘዋል።

ይህ ሰፊ ዘመቻ በሶስቱ ዋና ዋና የህግ ጥሰት ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነበር፡

* 12,506 የመኖሪያ ፈቃድ ህግ ተላላፊዎች
* 4,154 የድንበር ደህንነት ህግ ተላላፊዎች
* 2,916 የሠራተኛ ህግ ተላላፊዎች

በዚሁ ጊዜ ውስጥ ድንበር ጥሰው ወደ መንግሥቱ ለመግባት ሲሞክሩ 1,418 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። ከተያዙት ውስጥ፡

* 57% ኢትዮጵያውያን
* 41% የመን አገር ዜጎች
* 2% ሌሎች ዜግነቶች

በተጨማሪም 24 ሰዎች መንግስቱን ለቀው ለመውጣት ሲሞክሩ ተይዘውበታል፣ እንዲሁም 16 ሰዎች ለህግ ተላላፊዎች የትራንስፖርት፣ የመጠለያና የስራ ዕድል በማመቻቸት ተሳትፈው ተይዘዋል።

ጠቅላላ 30,427 የሚሆኑ የውጭ ዜጎች

* 28,718 ወንዶች እና
* 1,709 ሴቶች

በአሁኑ ጊዜ ህጋዊ እርምጃዎች እየተወሰደባቸው ይገኛል።

ባለፈው ሳምንት በተከናወነው የህግ ማስፈጸሚያ ሂደት፡

* 12,365 ተላላፊዎች ከሀገር ተባርረዋል
* 21,803 ተላላፊዎች የጉዞ ሰነድ ለማግኘት ወደ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖቻቸው ተልከዋል
* 5,202 ተላላፊዎች የጉዞ ቦታ ማስያዣቸውን እንዲያጠናቅቁ ተመላክተዋል

የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ህገወጥ ግለሰቦች ወደ መንግሥቱ እንዲገቡ የሚያመቻች፣ የሚያጓጉዝ፣ መጠለያ ወይም ሌላ ማንኛውንም ድጋፍ የሚሰጥ ማንኛውም ሰው እስከ 15 ዓመት በሚደርስ እስራት፣ እስከ 1 ሚሊዮን የሳዑዲ ሪያል (SR1M) በሚደርስ ቅጣት፣ እንዲሁም ለትራንስፖርት ወይም ለመጠለያ አገልግሎት የዋሉ ንብረቶች በመውረስ እንደሚቀጣ አስጠንቅቋል።

የሳዑዲ አረቢያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር

የኢትዮጵያ 6ኛ የወርቅ ሜዳልያSheger info  በ4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ እየተካፈለ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን ስድስተኛ ወርቁን ትላንት በ 1500 እና በ800 ሜትር እና በ5...
14/12/2025

የኢትዮጵያ 6ኛ የወርቅ ሜዳልያ
Sheger info

በ4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ እየተካፈለ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን ስድስተኛ ወርቁን ትላንት በ 1500 እና በ800 ሜትር እና በ5000 ሜትር የእርምጃ ውድድር አስመዝግቧል፡፡

ወጣት የኦሎምፒክ ቡድኑ በወርቅ በተንበሸበሸበት ውሎ በ5000 ሜትር ሴቶች የእርምጃ ውድድር ህይወት አምባው በቀዳሚነት በማጠናቀ የወርቅ ሜዳሊያ ስታሸንፍ በ1500 ሜትር ሴቶች ሀና ነጋሳ ሌላኛውን ወርቅ ለኢትዮጵያ አስገኝታለች፡፡

በመድረኩ በ800ሜትር ሴቶች መርጋ ሂካ ተጨማሪ ወርቅ ለኢትዮጵያ አስመዝግባለች፡፡ በሴቶች ብስክሌት የጎዳና ላይ ውድድር ማህሌት ደስታ የብር ሜዳልያ ለኢትዮጵያ አስገኝታለች፡፡

በጎይቶም መኮንን በ3000 ሜትር ሴቶች ነሀስ ሌላኛው ሜዳልያ ለኢትዮጵያ ተመዝግቧል፡፡ እስካሁን የኢትዮጵያ ወጣት ቡድን 6 ወርቅ 4 ብር እና 4 ነሀስ ሜዳሊያዎችን አስመዝግቧል፡፡

“ሀላላ ኬላ” - 350 ዓመታትን የፈጀው ታሪካዊው የድንጋይ ካብየሀላላ ድንጋይ ካብ (ሀላላ ኬላ) የዳውሮ አባቶች በአገር በቀል ዕውቀት ድንጋይን በድንጋይ ላይ በማነባበር የገነቡት ግዙፍ እና...
14/12/2025

“ሀላላ ኬላ” - 350 ዓመታትን የፈጀው ታሪካዊው የድንጋይ ካብ

የሀላላ ድንጋይ ካብ (ሀላላ ኬላ) የዳውሮ አባቶች በአገር በቀል ዕውቀት ድንጋይን በድንጋይ ላይ በማነባበር የገነቡት ግዙፍ እና ረዥም የድንጋይ ግንብ ነው።

የሀላላ ካብ በ1 ሺህ 532 ዓ.ም በዳውሮ የመጀመሪያ ንጉሥ ስራው ተጀምሮ በ1 ሺህ 822 ዓ.ም ዳውሮን ይመሩ በነበሩት በንጉሥ ካዎ ሀላላ እንደተጠናቀቀ ይነገራል።

አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ 350 ዓመታት የወሰደ ሲሆን በንጉሥ ካዎ ሀላላ መጠሪያ "ሀላላ ኬላ" የሚል ስያሜን አግኝቷል።

"ሃላላ" የንጉሱ ስም ሲሆን “ኬላ” የሚለው ደግሞ የድንጋይ ካብ ማለት ነው።

የድንጋይ ካቡ አካባቢውን ከውጪ ወራሪ ኃይል ጦር ለመከላከል የተገነባ እንደሆነ የታሪክ ተመራማሪ ታዬ ጊምባቶ ገልጸዋል።

ሀላላ የድንጋይ ካብ በተለይም ዳውሮን ከውጪ ወራሪ ኃይል ፈረሰኛና እግረኛ ጦር ለመከላከል የተገነባ መሆኑን አቶ ታዬ አንስተዋል።

በሰባት ረድፍ አጠቃለይ ርዝመቱ 1 ሺህ 225 ኪ.ሜ የሚሸፍነው ሀላላ ኬላ፤ ከ2.5 እስከ 5 ሜትር ስፋትና ከ2.5 እስከ 3.8 ሜትር በላይ ከፍታ እንዳለው የታሪክ ተመራማሪው ገልጸዋል።

የድንጋይ ካቡ ከ500 በላይ ዕድሜ ቢኖረውም ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስበት ጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝም አቶ ታዬ ተናግረዋል።

ሀላላ ካብ የዳውሮ ህዝብ አንድነት ማሳያ መሆኑን እንዲሁም ካቡ በሚሰራበት ጊዜ እዛው እየዋሉ እያደሩ ህብረተሰቡ ስንቅ በማቀበል ስራውን ጨርሰው እንደወጡ ይህም ለቀጣይ ትውልድ ጥሎት ያለፈው አሻራ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል።

Address

Trinity Road
London

Telephone

+251913242401

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sheger info posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sheger info:

Share