Sheger info

Sheger info Sheger info ማህበራዊ እና የመዝናኛ መረጃዎችን የሚቀስሙበት ገ?

16/08/2025

በአርቲስት ሸዋፈራው ደሳለኝ ምክንያት ብዙ ተመልካች ያለው
" ከትዳር በላይ " ትያትር ሊወርድ ነው ሲል ደራሲ እና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ በሰከነ መንገድ አስተያየት እንድትሰጡት ይህን ፅሁፍ አጋርቷል።
*************************************************
ባለፉት 6 ወራት በዓለም ሲኒማ ሲታይ የቆየው " ከትዳር በላይ " ትያትር ድንገት " ከመድረክ ሊወርድ ሦስት ሳምንት ቀረው " የሚል ማስታወቂያ መነገር መጀመሩ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል ፤ አስደንግጧል ። አንዳንዶችም እንደተለመደው ተመልካች ቀንሶ መስሏቸዋል ። እውነቱ ግን እንደሱ አልነበረም ። ትያትሩ በዓለም ሲኒማ ከፍተኛ ተቀባይነትና ተመልካች ካላቸው ጥቂት ትያትሮች መሐል አንዱ ነው ። ትያትሩ በመጪው ረቡዕ በ12:00 ሰዓት ታይቶ ለመቆሙ ምክንያቱ ተዋናይ ሸዋፈራው ደሳለኝ ነው ። የሸዋፈራው ጉዳይ ከዓመታት በፊት ( በአማተር ተዋኝነታችን ዘመን ) አርቲስት ስዩም ተፈራ ያለንን ያስታውሰኛል ። " ከቻላችሁ ስትሰሩ እንዳትተኩ አድርጋችሁ ስሩ ። እናንተ ስትቀሩ በቀላሉ ' በቃ እሱ ከቀረ እገሌ ግባ ' ከተባለባችሁ አስፈላጊነታችሁ ከማንም የተለየ አልነበረም ማለት ነው ። ' እሱ ከቀረማ እንበተን ' ለማስባል ስሩ ። " ይለን ነበረ ። ሸዋፈራው ለ " ከትዳር በላይ " ትያትር እንደዚያ ስዩሜ እኛን ይለን እንደነበረው አይነት ሆኖ ነው እሱ መቀጠል ሳይችል ሲቀር እሱን በሌላ ተዋናይ ከመተካት ትያትሩ እንዲቆም ያስወሰነው ። ይህ ሁኔታ ካሁን ቀደምም በሌሎች እጅግ ጥቂት ተዋንያንም አጋጥሟል ። እነሱ ገጸባህሪውን ሰቅለው ይሰሩትና ሌሎች ተዋንያን በቀላሉ ደፍረው ሊተኳቸው እንዳይገቡ የማድረግ አቅም አላቸው ። ሸዋፈራውም እንደዚያ ያለ ተዋናይ ነው ።

ሸዋፈራው በቀጣይ ላለበት ዓለም አቀፍ ጉዞ ትያትሩ ላይ እንደማይቀጥል ሲያሳውቅ ፕሮዲዩሰሯ ተዋናይት መስከረም አበራ የወሰነችው " ሸዋፈራው ካልሰራ ትያትሩ ደረጃው ወርዶ ከሚሰራ ከመድረክ ቢወርድ ይሻላል ። " የሚል ሆነ ። ሀሳቧ ገዢና ትክክል ነበረ ። እኔም በጣም ነው የደገፍኳት ። መቸም በዚህ ወቅት ትያትር ሙያ ውስጥ በመስከረም አበራ ልክ የተሰጠ አላውቅም ። እንደ ነጋዴና እንደተለመደውም ሸዋፈራውን በሌላ ተዋናይ ተክቶ መስራትና በገንዘብ መጠቀም ነው ከፊት ለፊት ያለው ሀሳብ ። ይህ ሳይታሰብ ቀርቶም አይደለም ። እንደ እውነት ሸዋፈራው የሚሰራውን ገጸባህሪ እሱ ሰቅሎ በሰራው ልክ የሚያመጣው ተዋናይ አልተገኘም ። ስለዚህ መስኪ የመረጠችው ትያትሩ ለጊዜው መውረዱን ነው ። መስኪ ለትያትሩ ደራሲነቴ ከፍተኛ ብር ነው የምትከፍለኝ ። ትያትሩ ሲቆም የእሷም ገቢ ፣ የእኔም ክፍያ ነው የሚቆመው ። የመስኪ ምርጫ ትያትሩ ከደረጃው ዝቅ ከሚል ማውረድን ነው ። ለሙያዋ ለማትደራደሪበት ማንነቷ መስከረም አበራን አመሰግናታለሁ ።

እስቲ ስለ ሸዋፈራው ደሳለኝ እናንሳ
****************************
" ወደ ማዶ " የተባለው አዲስ ስራችንን ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት ይዘን እንደምንዞር ካሳወቅንበትና እዚያ ትያትር ላይ ሸዋፈራው እንደሚተውን ከታወቀበት ማግስት ጀምሮ ፌስቡክ ላይ ተዋናዩ " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖትን ስለዘለፈ እሱ የሚሰራውን ትያትር እንዳታዩ " የሚል ቅስቀና ተጀመረ ። እጅግ የሚገርመው ብዙዎችን ያስቆጣው ንግግር ( " ኦርቶዶክስ እያለሁ የንሰሀ አባቴ ጸበል ይረጩኝ ነበረ ። ምን ልሁን ምን ላድርግ ግድ የላቸውም ። ብቻ ይረጫሉ ። ብር ይወስዳሉ ። አሁን ግን ከመንፈሱ ተረጭቼ በሀይልና በስልጣን እያገለገልኩ ነው ። እባካችሁ ወገኖቼ ጌታን ተቀበሉ ። ቀልድ አይደለም ። ከኢየሱስ ውጭ ሰውና አምላክ የለም ። አውቃለሁ ጊዜው የብዙ ችግር ወቅት ነው ። ግን ኢየሱስን ለተቀበለ ረፍትና ሰላም፣ ደስታና ፍሰሀ ሆኖለታል ። - መጋቢ ሸዋፈራሁ ደሳለኝ " የሚለው ) መጀመሪያ የወጣው ሁለት የፕቴስታንት የፌስቡክ ገጾች ላይ ነው ። ( ፖስቶቹ ከስር ይታያሉ ) ሲጀመር ሸዋፈራው መጋቢም አይደለም ። ሲቀጥል እነዚህ የፌስቡክ ገጾች አርቲስቱ የትም ቦታ ያልተናገረውን ፣ በጽሑፍ ያላሰፈረውን ፣ ለእነሱም ያልሰጣቸውን ሆነ ብለው ጋዜጣዊ መግለጫ በሚሰጥበት ዋዜማ ማውጣቸው ሰይጣናዊ እንጂ ሀይማኖታዊ ምክንያት የለውም ። አጋጣሚም አይደለም ።

ለ5 ወራት ገደማ " ከትዳር በላይ " ትያትር ሲታይ ያልነበረ ዘመቻ እንዴት " ወደ ማዶ " ትያትር ከፍ ባለ እና ከዚያ ቀደም በትያትር ጉዳይ ተደርጎ በማይታወቅ መልኩ ሸራተን ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጥ ተነሳ ? የሚለው ጥያቄ መልሱ የተለያዩ ወገኖች ሳያስቡትና ጥቂቶች ደግሞ ሆን ብለውና አቅደው የተቀናጁበት ሆኖ ነው የተገኘው ። እንግዲህ ሸዋፈራው የተከሰሰው በዚህ ከላይ በተገለጸው አባባል ከሆነ አንድም ቦታ ይህን ያለበትን ማስረጃ አለመቅረቡና እንዲቀርብ አለመጠየቁም አስገራሚና አስተዛዛቢም ነው ። እስቲ አንዳችሁ እንኳ ( በተለይ ይህን ጽሑፍ ያወጣችሁ ) " ነፍስ አባቴ ጸበል ሲረጩ . . . " ያለበትን የቪዲዮ ወይም የኦዲዮ ( መድረክ ላይ ሲሰብክም ሆነ በቃለመጠይቅ ) ማስረጃ አቅርቡና ሸዋፈራው ቀርቶ እኔ በተፈለገው መልኩ አማኒያኑን ይቅርታ ልጠይቅ ። ዋና የክሱ መነሻና ፍሬ ነገር ይህ ስለሆነ ማስረጃ ሆኖ መቅረብ ያለበትም ለዚሁ አባባል ነው ። " ሰርቀሀል " ተብሎ የተከሰሰ ሰው ፍ/ቤት ቢቀርብ " እንደውም ከስርቆቱም በላይ ሴት አስገድዶ ደፍሯል " ተብሎ ማስረጃ ሊቀርብበት አይችልም ። እስቲ ሸዋፈራው " አለ " የተባለው ማስረጃ ይቅረብ ። የለም ።

የሸራተኑ ጋዜጣዊ መግለጫ July 26 ሊሰጥ ሀሰተኛዎቹ ልጥፎች July 23 እና July 24 ሆን ተብለው በእነዚሁ የፕሮቴስታንት ፌስቡክ ገጾች ላይ ወጡ ። ከእነዚህ ልጥፎች ጀርባ መረጃ እንጂ ማስረጃ ስለሌለኝ ስማቸውን የማልጠራቸው ቀደም ሲል የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተከታይ የነበሩና ኋላ ላይ ፕሮቴስታንት ሆነው በጸረ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶነት ቆመው ሸዋፈራው የዚያ ጥፋት ተግባር ተባባሪ ያልሆነላቸው አካላት አሉበት ። እነሱ ብቻም ግን አይደሉም ። ኪነጥበቡ አካባቢ ያሉና አንዳንዶቹም ከዚሁ " ወደ ማዶ " ትያትር ጋር የቅርብና የርቀት ግንኙነትና ጥቅም ያላቸው ሆነው ከአዲስ አበባ እስከ ዋሽንግተን ዲሲ የክፋት መረብ ዘርግተው ሀሰተኛ መረጃ በመስጠት ሌሎችን ሊያሳስቱ የሞከሩ መሆኑ ደግሞ " ለምን ? " ያስብላል ። መቸም እንደ እኔ አይነት ባህሪ ላለው ሰው ከምጠላው ሰው ጋር ከመነጋገር የበዛ ድንጋይ መሸከም የለም ። ሕይወት ግን እንደዚያ ሆና ትመጣለች ።

በዚህ የተቃውሞ እንቅስቃሴ እጅግ የሚበዙቱ የተዋሕዶ ልጆች " ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ተነካች " ብለው እንደተነሱ አምናለሁ ። ጥቂቶች ግን በትያትሩ ዙሪያ ፣ ገንዘብና ጊዜያቸውን በማውጣት ጭምር የተሳተፉ ፣ በእውቀትም በአገልግሎትም የበረቱ ፣ በእምነታቸው ጥብቅ የተዋሕዶ ልጆች እንዳሉበት እያወቁ ይህን አድርገዋል ። እምነቴን ለገበያ ማቅረብ ማንነቴ ስላልሆነ እንጂ እኔ የካህን ልጅ ነኝ ። ስለ አባቴ ምንም ብዬ ስለማላውቅ እንጂ የእኔ አባት ለዓመታት ቤተክርስቲያኒቱን በኃላፊነት ያገለገለ ነው ። በልጅነቴ ከናዝሬት አዲስ አበባ ስመጣ አባቴን የማገኘው ቤተክህነት እየሄድኩ ነበረ ። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የልጅነት ትዝታዬ ናት ። ዝርዝሩ ብዙ ነው ።

እኔ ባለሁበት ቦታ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልትደፈር አትችልም ። ቤተክርስቲያኒቱ ችግር ውስጥ በገባች ጊዜ ሁሉ በእኔ ልክ ድምጽ የሚሆናት ፣ መነካቷ በእኔ ልክ የተሰማው ፣ በጀርባ ሳይሆን በፊትለፊት አቋሙን የገለጸ ጥቂት ነው ። ከ2/3 ዓመታት በፊት ቤተክርስቲያኒቱ በትርምስ ውስጥ ስትገባ ከጎኗ መቆም ነፍስን የማስያዝ ያህል ነበረ ። የዚያን ጊዜው ውጥረትና ትግል ሀይማኖታዊ ሳይሆን ፖለቲካዊ እንደሆነ ሳላውቅ ፣ በራሴ ላይ አደጋ መጥራት እንደሆነ ሳልገነዘበው ቀርቼ አልነበረም ። ቤተክርስቲያኗን የሚያመልኩባት ብቻ ሳይሆን የሚነግዱባት ፣ የገቢ ምንጫቸው የሆነችላቸው " አደጋ ቢደርስብንስ ? " ብለው በተሸሸጉ ወቅት እኔ ሳላመቻምች ከቤተክርስቲያኗ ጎን ቆሜያለሁ ። በዚያም ክብርና ኩራት ይሰማኛል ።

ሌላው ሸዋፈራው " ስለሰራበት " ተብሎ ዘመቻ የተከፈተበት " ሳማ " ፊልም ነው ። እንደውም አንዱ ሰው " ዘመቻችን ግቡን መቷል ። ሳማ ፊልምን አስራ ምናምን ሰው ነው የመረቀው " ብሎ በደስታ ተሞልቶ ሲናገር አይቻለሁ ። የፊልም ስራን ለሚያውቅ ይህ የሚያስደስት ሳይሆን የሚያሳዝን ነው ። ፊልሙ አሁን ከሸዋፈራው ጋር ግንኙነት የለውም ። ፕሮዲዩሰሮቹ በሚሊየን የሚቆጠር ብር አውጥተው ፣ ለሸዋፈራውም የሚገባውን የሙያ ክፍያ ከፍለው ከተለያዩ ወራት ተቆጥረዋል ። አሁን ትርፉም ኪሳራውም የፕሮዲዩሰሮቹ ብቻ ነው ። እነዚህ ሰዎች የተዋሕዶ ልጆች ይሆናሉ ። በዚህ ሂደት ታዲያ ማን ነው እየተጎዳ ያለው ? ፊልሙን በሰላሙ ጊዜ ነው ሰርተው የጨረሱት ።

ሸዋፈራው ስሙንና ችሎታውን ሸጦላቸው ቤቱ ገብቷል ። እነሱ ላይ እንዲደርስ የተፈለገው ቢደርስ ደስታው የቱጋ ነው ? እውነት ለመናገር እንደ ክርስቲያን የሌላ ሰው ( የበደለን እንኳ ቢሆን ) መማሩ እንጂ ውድቀቱ ምኑ ያስደስታል ? ቅጣቱስ ቢሆን ( እነሱ ጉዳዩ ውስጥ በሌሉበት ሁኔታ ) ተመጣጣኝ ነው ወይ ? የሸዋፈራው ጉዳይ ለአባቶቻችን ቢሰጥ " ልጃችን ነው ። ተሳስቶ ወይም ንዋይ አታሎት ሄዶ ይሆናል ። ወደ ቤቱ እንዲመለስ እንጸልይለታለን " ይላሉ እንጂ " በድንጋይ ተወግሮ ይገደል " አይሉም ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለዘመናት ተቋም የመሰረተችና ሀገር የሰራችና የመናች ናት ። እንዴት ታዲያ ፍርድ ከተቋም ወርዶ ግለሰቦች እጅ ገባ ? ይሄ ሁሉ የሚሆነው ደግሞ አንድም ማስረጃ ባልቀረበበትና በማይቀርብበት መሆኑስ ?

እሺ ይሁን ደግሞ ። ሸዋፈራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንንም ሆነ አማኙን የሚያስቀይም ተግባር ፈጸመ እንበል ። መቸም የትኛውም ቅጣት ጥፋቱን የሚመጥን መሆን ይኖርበታል ። ልጃችሁ የቱንም ያህል ቢያጠፋ በሌባ ጎማ አትመቱትም ። እንኳን ይቅርታ በሚሰበክበት ፣ እንኳን " ግራህን ሲመታህ ቀኝህን ስጠው " ተብሎ በሚመከርበት ፣ እንኳን " አምላካችን ስለ እኛ ሀጢአት ሲል ተሰቀለ " ብለን በምናምንበት ቤት ውስጥ በዓለማዊ ጉዳይ እንኳን ማስጠንቀቂያ ይሰጥ የለም ? " እረፍ ። ተጠንቀቅ ። አትንካን " ይባላል ። ይህን አልሰማም ሲል መቸም ምንም ይሁን ። ሸዋፈራሁ ግን በአንዴ " ይሰቀል ! ይሰቀል ! " መባሉ እውነት ኦርቶዶክሳዊስ ፣ ፍትሐዊስ ነው ? እነ ትዝታው ሳሙኤል ያሉትን ሁሉ ብለው ፣ ያደረጉትን ሁሉ አድርገው በነጻነት ተንቀሳቅሰውና እቅዳቸውን አሳክተው ወደመጡበት በተመለሱባት ከተማ ፣ ብዙዎች ቤተክርስቲያኒቱን ለማፍረስ ብዙ ታትረው ምንም በማይደረጉበት ፣ አንዳንዴም ሹመትና ሽልማት በሚያገኙበት ሀገርና ከተማ ሸዋፈራው ላይ እየተደረገ ያለውን ህሊናችሁ ተቀብሎታል ? እኛ ሁላችንም ብንፈታተሽ ያልታሰርነው ፣ ያልተወገዝነው በንጽህናችን ነው ? ክርስትናስ በምን ይገለጻል ? በጥላቻ ? በአድማ ? በ " ይወገር " ?

እኔ ለማንም ጥብቅና ለመቆም አልመጣሁም ። እግዚአብሔር ምስክሬ ነው በዚህ ጉዳይ የእኔ ጥቅም ማግኘትና ማጣት አያሳስበኝም ። እንደ እኔ የግል ምርጫ ቢሆን እንደውም አንድ ሸዋፈራው ያለ አግባብ ፣ አጥፍቶም ቢሆን ( በየከሳሾቻችን ምህረት እየተደረገልን እንጂ ሁላችንም በየመጠኑ ጥፋተኞች ነን ) ከጥፋቱ ጋር ያልተመጣጠነ ቅጥቀጣ ከሚያርፍበት ስራው የትም ባይሰራና ቢቀር እመርጣለሁ ። ዘመኔን ሁሉ የኖርኩት ( ውስጡ የራሴ ጥቅም እያለበትም ) ከተገፉት ጎን በመቆም ነው ። አንድም ጊዜ በሰዎች በደል ያገኘሁት ክፍያ የለም ። አንድም ጊዜ ። አሁንም ይህ ነው ። " እንዲሰማልህ የምትፈልገውን ንግግር መጨረሻ ላይ ተናገረው " እንደሚባለው ሸዋፈራው ካሁን ቀደም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን በተመለከተ ምንም ብሎ ሊሆን ይችላል ። አሁን ለክስ የበቃበትንና " አለ " የተባለውን የቪዲዮና የኦዲዮ ማስረጃ ያላችሁ እስቲ ላኩልኝና ራሴን ወክዬ አደባባይ ወጥቼ ይቅርታ ልጠይቅ ።

07/08/2022

Sheger Info Media brings, social, economic, and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth by comment...

29/07/2022

Sheger Info Media brings, social, economic, and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth by comment...

አነጋጋሪው የጥቁር አንበሳ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ውሳኔ እና የተማሪ ቢኒያም ምላሽ !https://youtu.be/l8WRfTuW6zA
13/07/2022

አነጋጋሪው የጥቁር አንበሳ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ውሳኔ እና የተማሪ ቢኒያም ምላሽ !
https://youtu.be/l8WRfTuW6zA

Sheger Info Media brings, social, economic, and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth by commenti...

የአጥር ወፍ አትስማሽ! የፈጣሪ ፀጋ የሆነውን የእርግዝና ጊዜ ማስታወሻ የሚሆን ልዩ ቆይታ ከሸገር ኢንፎ ጋር አድርጊ !በዚህ ፕሮግራም ላይ መቅረብ የምትፈልጉ ነፍሰ_ጡር እናቶች በ 091324...
21/05/2022

የአጥር ወፍ አትስማሽ! የፈጣሪ ፀጋ የሆነውን የእርግዝና ጊዜ ማስታወሻ የሚሆን ልዩ ቆይታ ከሸገር ኢንፎ ጋር አድርጊ !በዚህ ፕሮግራም ላይ መቅረብ የምትፈልጉ ነፍሰ_ጡር እናቶች በ 0913242401 ወይንም በ0902007393 ላይ ይደውሉ!
https://youtu.be/5AyfzatgNHc

Sheger Info Media brings, social, economic, and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth by commenti...

በኬንያ ናይሮቢ በጠራራ ፀሀይ የታገተው ኢትዬጵያዊ የት ነው!https://youtu.be/ipUPO4UXsnc
13/05/2022

በኬንያ ናይሮቢ በጠራራ ፀሀይ የታገተው ኢትዬጵያዊ የት ነው!
https://youtu.be/ipUPO4UXsnc

Sheger Info Media brings, social, economic, and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth by commenti...

ተወዳጇ ተዋናይት ማክዳ አፈወርቅ! ያዘጋጀችው ልዩ ዝግጅት!https://youtu.be/ya3OlzFPiY0
02/05/2022

ተወዳጇ ተዋናይት ማክዳ አፈወርቅ! ያዘጋጀችው ልዩ ዝግጅት!
https://youtu.be/ya3OlzFPiY0

Sheger Info Media brings, social, economic, and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth by commenti...

እንኳን አደረሳችሁ! ልዩ የፋሲካ ዋዜማ ዝግጅት .. ልጁ በመታመሟ  ከእቅፉ ሳይለያት ከሚንከባከበው ከጠንካራው አባት ደረጀ እና ባለቤቱ ጋር!https://youtu.be/Igb5tMKcRN4
23/04/2022

እንኳን አደረሳችሁ! ልዩ የፋሲካ ዋዜማ ዝግጅት .. ልጁ በመታመሟ ከእቅፉ ሳይለያት ከሚንከባከበው ከጠንካራው አባት ደረጀ እና ባለቤቱ ጋር!
https://youtu.be/Igb5tMKcRN4

Sheger Info Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth b...

15/03/2022

Sheger Info Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth b...

15/03/2022

Sheger Info Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth b...

15/03/2022

Sheger Info Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience. Let us know what you think about the specific shows we put forth b...

Address

Trinity Road
London

Telephone

+251913242401

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sheger info posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sheger info:

Share