Siltie Media Network

Siltie Media Network SMN የእውነት፣ የከፍታ፣ የአንድነትና የብዝሃነት ድምጽ ነው። ወቅታዊ መረጃ፣ መዝናኛ፣ ታሪክ፣ ባህል፣ ቴክኖሎጂ፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ...ርዕሰ-ጉዳዮች ይዳሰሳሉ።

 ❤
06/09/2025

03/09/2025
📌ግድቡ  ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአጠቃላይ ከ13 ተርባይኖች 5,150 ሜጋዋት ማመንጨት የሚችልበት አቅም ላይ ይገኛል። - እስካሁን ከ71 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር በላይ ውሃ ተይዟል። ቀ...
03/09/2025

📌ግድቡ

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአጠቃላይ ከ13 ተርባይኖች 5,150 ሜጋዋት ማመንጨት የሚችልበት አቅም ላይ ይገኛል።

- እስካሁን ከ71 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር በላይ ውሃ ተይዟል። ቀሪው 2.1 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በመጪዎቹ 7-10 ቀናት ውስጥ ይያዛል።

- በግድቡ የተያዘው ውሃ ወደኋላ ከ246 ኪሎ ሜትር በላይ ይተኛል፤ እስካሁን ባለው 240 ኪሎ ሜትር ላይ ተደርሷል። ርቀቱ ከአዲስ አበባ እስከ ሻሸመኔ ይሆናል።

ኢትዮጵያ ገንብታ ባጠናቀቀችው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አማካኝነት ኃይል እያገኘች ትገኛለች።

የኃይል ማመንጫ ግድቡ ነሐሴ 24/2017 ላይ 2530 ሜጋ ዋት በማመንጨት ኃይል መስጠት ችሏል።

- ግድቡ ተጠናቋል ሲባል ምን ማለት ነው ?

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋናው ግድብ በ1.8 ኪሎ ሜትር እርዝማኔና 145 ሜትር ከፍታ ተገንብቶ ተጠናቋል።

በአጠቃላይ ከ10 ሚሊየን ኪዩቢክ ሜትር ያህል ኮንክሪት (RCC) ሙሌት ተካሂዷል።

የግድቡ የስረኛው ክፍል 150 ሜትር ስፋት አለው። የላይኛው ክፍል ደግሞ 11 ሜትር ስፋት ሲኖረው ሁለት መኪኖችን ጎን ለጎን ማሳለፍ ይችላል።

ኃይል ማመንጨት የሚችሉ 13 ተርባይኖች ተከላ የተጠናቀቀ ሲሆን ከእነዚህ ተርባይኖች 5150 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት ይቻላል።

በግድቡ የውጨኛው ክፍል የሚታዩት የብረት አሸንዳዎች በግራ እና በቀኝ በኩል ላሉ ኃይል የሚያመነጩ ተርባይኖች ውኃ የሚተላለፍባቸው ሲሆን እያንዳንዳቸው 8.5 ሜትር ዲያሜትር ስፋት አላቸው። 300 ሜትር ኪዩብ በሰከንድ ማሳለፍ አቅም አላቸው።

በግራ የኃይል ማመንጫ 7 ተርባይኖች ሲኖሩ በቀኝ የኃይል ማመንጫ ደግሞ 6 ተርባይኖች ሙሉ ለሙሉ ተከላቸው ተጠናቋል።

ከዚህ ውስጥ 3ቱ የቅድመ ኃይል ተርባይኖች በመጠን አነስ ያሉ ሲሆን ቀሪዎቹ 10 ተርባይኖች እያንዳንዳቸው 400 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አላቸው።

ግድቡ ያመነጨው ኃይል በሁለት መስመሮች ማለትም በጣና በለስ አድርጎ በደብረ ማርቆስ እንደዚሁም በአሶሳ አድርጎ ወደ አዲስ አበባ ብሔራዊ የኃይል ቋት በመግባት ላይ ይገኛል።

ከዋናው ግድብ በተጨማሪ የህዳሴ ግድቡ የኮሬቻ ግድብ (Saddle Dam) ከዋናው ግድብ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።

ርዝመቱ 5.2 ኪሎ ሜትር እና 50 ሜትር ከፍታ ላይ ሆኖ ሙሉ ለሙሉ በ15 ሚሊየን ሜትሪክ ኪዩብ ድንጋይ የተሞላ ነው። የተያዘው ውሃ ሾልኮ እንዳያልፍ ከ30-40 ሴንቲ ሜትር ውፍረት ባለው ኮንክሪት ተለብጧል።

እስካሁን ከ71 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር በላይ ውሃ ተይዟል። አጠቃላይ ግድቡ የሚይዘው 74 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ነው፤ የሚቀረው ከ2.1 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ያልበለጠ ነው።

ቀሪው 2.1 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በመጪዎቹ 7-10 ቀናት ውስጥ ይያዛል።

በግድቡ የተያዘው ውሃ ወደኋላ ከ246 ኪሎ ሜትር በላይ ይተኛል። እስካሁን ባለው 240 ኪሎ ሜትር ላይ ተደርሷል። ርቀቱ ከአዲስ አበባ እስከ ሻሸመኔ ያልፋል።

የኮሬቻ (saddle dam) 74 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ለመያዝ ወይም የሚያመነጨውን 5150 ሜጋዋት ለማመንጨት የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን ለመያዝ በጣም አስፈላጊ ነው።

#ታላቁየኢትዮጵያህዳሴግድብ

📌ኢማም ሃጂ አብዱልሃዲ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤ...
02/09/2025

📌ኢማም ሃጂ አብዱልሃዲ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ባካሄደው የምስረታ ጉባኤና የስራ አስፈጻሚ ምርጫ ኢማም ሃጂ አብዱልሃዲ አህመድ ቡርሃንን የከፍተኛ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት አድርጎ ሰይሟል።

በመስራች ጉባኤው ከኢማም ሃጂ አብዱልሃዲ ባሻገር ኡስታዝ ባህጃ አብዱልጀሊል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚደንት፣ ሸይኽ ኡመር ሙስጠፋ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ጸሃፊ፣ አድርጎ ማጽደቁ ታውቋል።

በዚሁ መሰረትም መስራች ጉባኤው

1- ኢማም ሀጂ አብዱልሃዲ አህመድ - ፕሬዚደንት (ከኡለማዕ)
2- ኡስታዝ ባህጃ አብዱልጀሊል ምክትል ፕሬዚደንት (ከኡለማዕ)
3- ሸህ ኡመር ሙስጠፋ - ጸሃፊ (ከምሁራን)
4- ኡስታዝ ሳዲቅ ወጌቦ አባል ከኡለማዕ
5- ሸይኽ ሙስጠፋ ጀማል አባል ከኡለማ
6- ሸይኽ ሙክታር ሀሰን አባል ከኡለማ
7- ኡስታዝ ናስር ሙሐመድ አባል ከኡለማዕ
8- አባዝናብ አባዋሬ አባል ከስራ ማህበረሰብ
9- ሸይኽ አህመድ አበቴ አባል ከኡለማ
10- ኢስማኢል ሻሜቦ አባል ከወጣቶች
11- ዙበይዳ ሀቢብ አባል ከሴቶች ተመርጠው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።

በሌላም በኩል

1-ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን
2- ሀጂ ሽፋ ሙሐመድ
3- ሸይኽ አዩብ ሙሐመድ
4- ኡስታዝ ሰኢድ ጅላሉ
5- ሸይኽ ረሻድ ከድር
6- ሸይኽ አብዱሰላም ከድር
7- ሸይኽ ሙስጠፋ ሙሐመድ
8- ሁሴን ሙሐመድ
9- አብዱረሂም ሁሴን
10- መሐመድ ሱልጣን እንዲሁም
11- ሙንተሃ ሀያቱ ክልሉን ወክለው ለፌዴራል ተመርጠዋል።

በምርጫና መስራች ጉባኤው ላይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የህግና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ጽ/ቤት የህግ ጉዳዮች አማካሪ ወ/ሮ መቅደስ ማቴዎስ፣ የፌዴራልና የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምርጫ አስፈጻሚ አመራሮች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የስራ ሀላፊዎች፣ የዞንና የልዩ ወረዳ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ስራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል።

📌ታላቁ የህዳሴው ግድብ!!📌የኢትዮጵያ አዲስ ምዕራፍ!!
02/09/2025

📌ታላቁ የህዳሴው ግድብ!!
📌የኢትዮጵያ አዲስ ምዕራፍ!!

 #ራሳቸው ተሰቅለው=ይላሉ ውረዱ!! #እኛ አይደለንም ወይ=መሬቱም መንገዱ #ውሎና አደሩ=መች ጠፋን ልካቸው!! #የኛ ንብረት ናቸው=ኮምፒውተር ስልካቸው።
02/09/2025

#ራሳቸው ተሰቅለው=ይላሉ ውረዱ!!
#እኛ አይደለንም ወይ=መሬቱም መንገዱ
#ውሎና አደሩ=መች ጠፋን ልካቸው!!
#የኛ ንብረት ናቸው=ኮምፒውተር ስልካቸው።

📌አፋልጉኝ!በስልጤ ዞን በሚቶ ወረዳ  ግ/ሾፎዴ ቀበሌ ነዋሪ የነበረው ወጣት ሻፊ ራመቶ ሀሚድ  ከ3 ዓመት በፊት ለስራ ብሎ ጅጅጋ እንደሄደና ለ1 ዓመት ያህል ስልክ እየደወለ እነደነበር ይነገ...
01/09/2025

📌አፋልጉኝ!
በስልጤ ዞን በሚቶ ወረዳ ግ/ሾፎዴ ቀበሌ ነዋሪ የነበረው ወጣት ሻፊ ራመቶ ሀሚድ ከ3 ዓመት በፊት ለስራ ብሎ ጅጅጋ እንደሄደና ለ1 ዓመት ያህል ስልክ እየደወለ እነደነበር ይነገራሉ ፋላጊ ቤተሰቦቹ አቶ ራመቶ ሀሚድ ስለሆነም ወጣት ሻፊ ራመቶ ሀሚድ ያገኘ ሰው ካለ ወይም ያለበትን የምታዉቁ በዚህ ስልክ ቁጥር ጥቆማ እንድትሰጡን ይላሉ ፋላጊ ቤተሰቦቹ
09-16-29-67-94
09-24-70-34-96

📌ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫበአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነውየአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የ2017 ዓ.ም ምርጫ...
31/08/2025

📌ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የ2017 ዓ.ም ምርጫ በታላቅ ስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ፣ የ2017 የከተማውን መጅሊስ የማዋቀር ሂደትና የምርጫ መርሃ ግብር በሰላማዊና ኢስላማዊ ስነ ስርዓቱን በጠበቀ መንገድ በስኬት ማጠናቀቁን በታላቅ ደስታ ይገልፃል።

መንግሥት የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም፣ የፌደራል መጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ በወሰነው መሰረት “ምርጫ ለፅኑ ተቋም” በሚል መሪ ቃል ህዝብ መሪውን በመስጂዱ በነፃነት ሊመርጥ ችሏል።

ቦርዱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ላለፉት አምስት ወራት ከ 5 ሺ በላይ የምርጫ ግብረ ሀይል አባላት በበጎ ፈቃደኝነት በማሳተፍ ፣ የከተማዋን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት በመገምገም እና የሀገራችንን ጥንታዊ የእስልምና ታሪክ የሚያንፀባርቅ ኢስላማዊ ስነ ስርዓቱን የጠበቀ፣ ፍትሐዊና ሰላማዊ ምርጫ ለማካሄድ ሌት ተቀን ሲሰራ ቆይቷል።

ይህንንም የተቀደሰ ዓላማ ለማሳካት በየደረጃው ማለትም በክፍለ ከተማ፣ በወረዳ እና በመስጂድ ደረጃ የምርጫ አስፈጻሚዎችን በመሾም እና ግብረ ኃይሎችን በማደራጀት እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የመጅሊስ ስራ አስፈፃሚዎችን በማስመረጥ ሰፊ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

የዚህ የተቀናጀ ጥረት ፍፃሜ የሆነው የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምሥረታ ጉባኤ፣ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወከሉ የዑለማዎች፣ የምሁራን፣ የሰራተኛ ማህበረሰብ፣ የወጣቶችና የሴቶች ተወካዮች በተገኙበት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

የምርጫው ሂደት ኢስላማዊ ሂደቱን የጠበቀ ግልጽ፣ ሰላማዊ እና ሁሉንም ያሳተፈ ሆኖ በላቀ ስኬት ተጠናቋል።

በዚህም መሰረት የምርጫው ውጤት እንደሚከተለው ይቀርባል፡-

1. አዲስ አበባን በፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሚወክሉ ተመራጮች
ከዑለማ ዘርፍ፡
1. ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ
2. ሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
3. ሸይኽ ሑሴን በሽር
4. ሸይኽ ማሕመድ ሑሴን
5. ሸይኽ አሕመድ ዛኪር

ከምሁራን ዘርፍ፡
1. ኤልያስ አወል
2. አምባሳደር ሸሪፍ ኸይሬ

ከሰራተኛ ማኅበረሰብ ዘርፍ፡
1. አብድልቃድር ማሂ

ከወጣት ዘርፍ፡
1. ኢብራሂም ሙሰማ

ከሴቶች ዘርፍ፡
1. ዘይነብ ነሩ

2. የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ተመራጮች
ከዑለማ ዘርፍ፡
1. ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ
2. ሸይኽ ሙሐመድ ሸሪፍ
3. ኡስታዝ ጋሊ አባቦር
4. ሸይኽ ዙበይር ሬድዋን
5. ሸይኽ ሑሴን ሰዒድ
6. ኡስታዝ ሰልሃዲን መለሰ
7. ሸይኽ ኑርሑሴን ሙስጠፋ

ከምሁራን ዘርፍ፡
1. ሺሃቡዲን ኑራ
2. ሼህ መሐመድ አሊ

ከማኅበረሰብ ዘርፍ፡
1. ኡስታዝ ኣዩብ ደርባቸው

ከወጣቶች ዘርፍ፡
1. መንሱር ኸድር

ከሴቶች ዘርፍ፡
1. ፈትህያ ሙሐመድ
2. ኑርያ ሙሐመድ

በኦዲትና ኢንስፔክሽን
1. ዶ/ር ዘይኑ ዙበይር
2. አቲ ሙሐመድ አብዶሽ
3. አቶ በረከት አብደላ

በተጨማሪም ጉባኤው የከፍተኛ ምክር ቤቱን ቁልፍ አመራሮች የሰየመ ሲሆን፣ በዚህም መሰረት፡-
1. ሸይኽ ሱልጣን ሐጅ አማን ኤባ - የከፍተኛ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት፣
2. ሸይኽ ሙሐመድ ሸሪፍ - ምክትል ፕሬዝዳንት፣
3. ሺሃቡዲን ኑራ - ዋና ጸሐፊ ሆነው ተመርጠዋል።

በመጨረሻም ምርጫ አስፈጻሚ ቦርዱ ለተመረጡት አባላትና አመራሮች በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን እያስተላለፈ፣ በቀጣይ የኃላፊነት ዘመናቸው የከተማችንን ሙስሊም ማኅበረሰብ በላቀ ኃላፊነትና ቅንነት እንዲያገለግሉ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

ለዚህ ታላቅ ስኬት የበኩላቸውን ላበረከቱት ለሰላም ሚንስቴር፣ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ለከተማዋ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባ ፖሊስና በየደረጃው ለሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች እንዲሁም ለመላው የአዲስ አበባ ሙስሊም ነዋሪዎች በአላህ ስም ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ ጉ/ከ/ም/ቤት

31/08/2025

😍

📌ክቡር ዶ/ር ሸይኸ ሱልጣን ሀጅ አማን ኤባ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆነዉ ዳግም ተመረጡ::
31/08/2025

📌ክቡር ዶ/ር ሸይኸ ሱልጣን ሀጅ አማን ኤባ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆነዉ ዳግም ተመረጡ::

📌የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው የምክር ቤት ምሥረታ እና የሥራ አስፈፃሚ ምርጫ ተከታዮቹን ሥራ አስፈፃሚዎች መርጧል።በዚህ መሰረትምኡስታዝ ጋሊ አባ...
31/08/2025

📌የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው የምክር ቤት ምሥረታ እና የሥራ አስፈፃሚ ምርጫ ተከታዮቹን ሥራ አስፈፃሚዎች መርጧል።

በዚህ መሰረትም
ኡስታዝ ጋሊ አባቦር
ሸኽ ሡልጣን አማን ኤባ
ሸኽ ሙሐመድ ሸሪፍ
ሸኽ ሑሴን ሰይድ
ሸኽ ዙቤር ሬድዋን
ሸኽ ኑሩ ሑሴን ሙስጠፋ
ኡስታዝ ሰላሃዲን መለስ ከዑለማኦች ዘርፍ የስራ አስፈፃ ሆነው የተመረጡ ሲሆን ኡስታዝ አዩብ ደርባቸው ደግሞ ከሰራተኛ እና ማህበረሰብ ዘርፍ የስራ አስፈፃሚ አባል ሆነው ተመርጠዋል።

📌በዛሬዉ ምርጫ ከአዲስ አበባ ወደ ፌደራል መጅሊስ  ያለፉ ዑለሞች ዝርዝር!1/ሸኽ ሀሚድ ሙሳ2/ሸኽ ኢልያስ አህመድ3/ሸኽ ሁሴን በሽር  4/ሸይኽ ማህሙድ  ሁሴን5/ ሸይኽ አህመድ ዛኪር
31/08/2025

📌በዛሬዉ ምርጫ ከአዲስ አበባ ወደ ፌደራል መጅሊስ ያለፉ ዑለሞች ዝርዝር!
1/ሸኽ ሀሚድ ሙሳ
2/ሸኽ ኢልያስ አህመድ
3/ሸኽ ሁሴን በሽር
4/ሸይኽ ማህሙድ ሁሴን
5/ ሸይኽ አህመድ ዛኪር

Address

London

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Siltie Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Siltie Media Network:

Share