Selom Media

Selom Media Selom Media is a Digital News Channel founded and owned by Fekadu Alemu that reports, analyses, & fact-checks professionally. "ተአማኒና ወጥ ማንነት ያለው ሚዲያ"

Welcome to Selom Media, a digital News channel owned by Fekadu Alemu that reports, analyses, and fact-checks to improve the quality, transparency, and credibility of news reporting on Ethiopia about everything. We are particularly concerned with the humanitarian crisis caused by political unrest, economic crisis, ethnic conflicts, and elections in Ethiopia and around the world. We also monitor, an

alyze, and comment on the professional practice of Ethiopian journalism, with a focus on news stories broadcast both locally and internationally. Strong Journalism, Great Ethiopia!

የጋዜጠኝነት ሙያ ውግንና ለሕዝብ እንዲሆን ሙያዊ አተገባበሩ እንዲሻሻል የበኩላችንን እንወጣለን፡፡

ወገን ሴንድ ( ) የአዲስ አመት የበዓል ስጦታ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ቀሩት። እርስዎስ፣ ተጠቅመዋል?  Unpaid advertisement. ከቀጥታ ምንዛሪው በተጨማሪ 9% ጭማሬ ጉርሻ ያገኛሉ።...
09/10/2025

ወገን ሴንድ ( ) የአዲስ አመት የበዓል ስጦታ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ቀሩት። እርስዎስ፣ ተጠቅመዋል? Unpaid advertisement.

ከቀጥታ ምንዛሪው በተጨማሪ 9% ጭማሬ ጉርሻ ያገኛሉ።

ለምሳሌ
£100 = 21,548 ብር በላይ
£500 = 107,740 ብር በላይ
£1000 = 215,481 ብር በላይ
ጉርሻው የሚቆየው ለጥቂት ቀናት ብቻ ነው።
መተግበሪያውን ከፕለይ ስቶር ወይም ከአፕ ስቶር በማውረድ ይጠቀሙ።

Get 9% BONUS

Get more for your money
On top of our competetive exchange rates, and free service, we are giving upto 9% Bonus* for a limited time.
Send money to Ethiopia, from the comfort of your home. You can deposit the money straight into their bank account, or they can pick it up from a branch.

Source:

Get a bonus on upto* 9% for every USD/EUR/GBP you send, in addition to our competitive exchange rates when you send money to your 'Wegen' using Wegensend. Wegensend is a fast, secure money transfer App that allows you to transfer money to Ethiopia with ease. T&C apply. See our site or Apps for detai...

የሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጋዜጠኞች፣ አርታኢ ትዕግስት ዘሪሁን እና ሪፖርተር ምንታምር ፀጋው፣ በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቁጥጥር ስር ከዋሉ 17 ቀን ሆናቸው፡፡ሴሎም ሚዲያ፥ ሎንደን፥ መስከ...
19/09/2025

የሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጋዜጠኞች፣ አርታኢ ትዕግስት ዘሪሁን እና ሪፖርተር ምንታምር ፀጋው፣ በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቁጥጥር ስር ከዋሉ 17 ቀን ሆናቸው፡፡

ሴሎም ሚዲያ፥ ሎንደን፥ መስከረም 09/17/25

የፌዴራል ፖሊስ፣ ጋዜጠኞቹን በቁጥጥር ስር ያዋላቸው፣ ያሰራጩት ዘገባ በሕግ የተከለከለ ይዘት ያለውና የሽብር ድርጊት ነው ብሎ እንደሆነ፣ ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ እንዲፈቅድለት፣ ባቀረበው ማመልከቻ ጠቁሟል፡፡

የሕክምና ባለሞያዎች፣ ለመንግስት ያቀረቡትን ጥያቄ ተከትሎ፣ የጤና ሚኒስቴር በሰርኩላር ያስተላለፈውን መፍትሄ፣ እንዴት እንደሚመለከቱት፣ የሕክምና ባለሞያ ቃለ መጠይቅ በማድረግ፣ ነሐሴ 24 በሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ ዜናው ተላልፎ ነበር፡፡

በዚሁ ዜና ምክንያት የፌዴራል ፖሊስ፣ ጋዜጠኞች ትዕግስት ዘሪሁን እና ምንታምር ፀጋውን፣ በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ፣ ምክንያቱን ዘርዝሮ፣ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው በመጠየቁ፣ ፍርድ ቤቱ ዘጠኝ ቀን ፈቅዶለት ነበር፡፡

በቀጣዩ ቀጠሮ፣ የፌዴራል ፖሊስ የፎረንሲክ፣ የገንዘብ ዝውውራቸውን እና ተጨማሪ ምርመራዎችን ለማድረግ ተጨማሪ ቀናት ጠይቋል፡፡

የፌዴራል ፖሊስን ምክንያትና ከጋዜጠኞቹ የቀረበውን መከራከሪያ ያዳመጠው፣ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ፣ ጋዜጠኞቹ በ50,000 ብር ዋስትና እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

በትዕዛዙ መሰረት፣ መስከረም 7/2018 ከሰዓት በኋላ፣ አስፈላጊው ፎርማሊቲ ተሟልቶ፣ ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ደርሶታል፡፡

ይሁንና፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የከፍተኛ ፍ/ቤቱን ውሳኔ በይግባኝ፣ ወደ ፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመወሰዱ፣ ለመስከረም 12/2018 ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
ጋዜጠኞቹም በእስር ላይ ናቸው፡፡

ሸገር 102.1 ራዲዮ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምሕረቱ በገዛ ፈቃዳቸው ከኃላፊነት መልቀቃቸውን አስታወቁ። ሴሎም ሚዲያ፥ ሎንደን /ነሐሴ 28/2017/25የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ...
03/09/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምሕረቱ በገዛ ፈቃዳቸው ከኃላፊነት መልቀቃቸውን አስታወቁ።

ሴሎም ሚዲያ፥ ሎንደን /ነሐሴ 28/2017/25

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ከሰባት አመታት ቆይታ በኋላ መሰናበታቸውን አስመልክቶ አስገራሚ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሀገሪቱ በአይ ኤም ኤፍ መሪነት በገበያ ላይ የተመሰረተ የምንዛሪ ተመን ስርዓትን በማሸጋገር ላይ ባለችበት ወቅት የሱ መልቀቅ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ወሳኝ ወቅት ላይ ነው።

አቶ ማሞ ምህረቱ ከሰባት አመታት ቆይታ በኋላ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ ማድረጋቸው ይታወሳል። ማሞ ሌሎች የሙያ እድሎችን ለመከተል መንግስትን ለመልቀቅ መወሰኑን አስታወቀ።

የዓለም ባንክ የቀድሞ ሰራተኛ የነበሩት ማሞ በመጀመሪያ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የፖሊሲ አማካሪነት የተዛወሩ ሲሆን በኢትዮጵያ የንግድ ድርጅት ዋና ተደራዳሪ በመሆን በእጥፍ አድጓል። እ.ኤ.አ. በ2019 በፋይናንሺያል ታይምስ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አስተዳደር የኢትዮጵያን ታላቅ የለውጥ እንቅስቃሴ ከሚመሩ ወጣት ቴክኖክራቶች መካከል አንዱ ተብሎ ተጠርቷል።

እ.ኤ.አ. ከሰኔ 2010 ጀምሮ የብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩትን ዶ/ር ይናገር ደሴን በመተካት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ሆነው ተሹመዋል። ማሞ ገዥነቱን ከመውሰዱ በፊት እ.ኤ.አ. በ2022 የተቋቋመው የመንግስት ኢንቨስትመንት ድርጅት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢኤች) ዋና ስራ አስፈፃሚ ነበሩ።

ጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ የአርቶዶክስ ንቅናቄ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የቀኖና ጥሰትና አድሎአዊ አሠራር ያወጣው መግለጫ (Coalition for the Church Inter...
30/08/2025

ጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ የአርቶዶክስ ንቅናቄ በቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የቀኖና ጥሰትና አድሎአዊ አሠራር ያወጣው መግለጫ (Coalition for the Church International Orthodox Movement)

ሴሎም ሚዲያ፥ ለንደን፥ ነሐሴ 24፥ 2017/25

አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፈሴሎም ሚዲያ/ ለንደን/ 11 ነሐሴ 17/25አርቲስት ደበበ እሸቱ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ድካም...
17/08/2025

አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፈ

ሴሎም ሚዲያ/ ለንደን/ 11 ነሐሴ 17/25

አርቲስት ደበበ እሸቱ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።

አርቲስት ደበበ እሸቱ በኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ዘርፍ የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን÷ በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በፊልም እና በጋዜጠኝነት ሙያ በርካታ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አቅርቧል፡፡

ተዋናይ፣ ኮሜዲያን እና አዘጋጅ ሆኖ ለረጅም ዓመታት ያገለገለው አርቲስቱ ÷ በቴአትር መድረኮች በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑ ሥራዎችን በማቅረብ ይታወቃል፡፡

አርቲስት ደበበ በሀገር ፍቅርና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ (በአሁኑ ብሔራዊ ቴአትር) መድረክ ላይ ለበርካታ ዓመታት በተዋናይነትና በአዘጋጅነት አገልግሏል።

አርቲስት ደበበ መጀመሪያ በቴአትር መድረክ የታየው በመንግስቱ ለማ ያላቻ ጋብቻ ሲሆን÷ በመቀጠልም በሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የተለያዩ ሥራዎችን አቅርቧል፡፡

አርቲስቱ ከተሳተፈባቸው ሥራዎች መካከል ያላቻ ጋብቻ፣ ሮሚዮና ዡልየት፣ ጠልፎ በኪሴ፣ ዳንዴው ጨቡዴ ፣ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ፣ ኦቴሎ፣ አንድ ዓመት ከአንድ ቀን፣ እናት ዓለም ጠኑ፣ በቀይካባ ስውር ደባ፣ የአዛውንቶች ክበብ፣ የወፍ ጎጆ ፣ የቬኒሱ ነጋዴ ፣ ማዕበል እና ሌሎች ይገኙበታል፡፡

17/08/2025

ፑቲን እና ትራምፕ ከጋዜጣዊ መግለጫ በኋላ የተለዋወጡት ሳቅ በሚሊየኖች ታይቷል

ሁለት ጋዜጠኞች በልዩ ሁኔታ በደህንነት አካላት ተይዘው የተሰወሩበት አለመታወቁን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋልሴሎም ሚዲያ/ለንደን፥ ነሐሴ 10፥ 2017/25አንጋፋው ጋዜጠኛ አብዱልሰ...
16/08/2025

ሁለት ጋዜጠኞች በልዩ ሁኔታ በደህንነት አካላት ተይዘው የተሰወሩበት አለመታወቁን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል

ሴሎም ሚዲያ/ለንደን፥ ነሐሴ 10፥ 2017/25

አንጋፋው ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ ከነሐሴ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የቤተሰቡ እና የቅርብ ዘመዶቹ እያፈለጉት ቢሆንም አሁን ድረስ ሊገኝ አልቻለም። ባለቤቱ እንደገለፀችው አብዱልሰመድ በዚያ ቀን ቃሊቲ ትራንስፖርት ባለሥልጣን የመንጃ ፈቃድ ፈተና እንዳለ ሄደ፤ ነገር ግን ከዚያ በኋላ በሥልክ ለማግኘት ቢሞክሩት አልተቻለም። ቤተሰቡ በፌደራል ወንጀል ምርመራና በተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች ለማጣራት ቢሞክሩም መረጃ ማግኘት አልተቻለም።

በተመሳሳይ ሁኔታ፣ ጋዜጠኛ ዮናስ አማረም ከነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ከቤተሰቡ እና ከሥራ ባልደረቦቹ ጋር ግንኙነት ተቋርጧል። በቤቱ የተካሄደ ማጣራት እንደሚያሳየው ከሆነ ጋዜጠኛው በሸገር ከተማ ኮዬ ፌጬ ኮንዶሚኒየም አካባቢ ሲገኝ ፊታቸውን በጭምብል የሸፈኑ ሰዎች መወሰዳቸውን ነገር ግን የወሰዱት ማን እንደሆኑ እና የት እንደተወሰዱ ዝርዝር መረጃ አልተገኘም።

የሁለቱም ጋዜጠኞች ጉዳይ በማህበረሰቡ ውስጥ ትልቅ ጭንቀት መፍጠሩን የዘገቡት መገናኛ ብዙሃን ቤተሰቦቻቸው እና በተለያዩ መንገዶች የሚያፈልጉ ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ተገልጿል።

በኢትዮጵያ ከሕግ ውጪ የሆኑ "የዘፈቀደ ግድያዎች" እና "ኢሰብአዊ ቅጣቶች" መቀጠላቸውን ከታማኝ ምንጭ መረጃ አግኝቻለሁ ሲል የአሜሪካ መንግሥት ገለጸሴሎም ሚዲያ/ ሎንደን/ ነሐሴ 07/2017...
13/08/2025

በኢትዮጵያ ከሕግ ውጪ የሆኑ "የዘፈቀደ ግድያዎች" እና "ኢሰብአዊ ቅጣቶች" መቀጠላቸውን ከታማኝ ምንጭ መረጃ አግኝቻለሁ ሲል የአሜሪካ መንግሥት ገለጸ

ሴሎም ሚዲያ/ ሎንደን/ ነሐሴ 07/2017

በኢትዮጵያ የመንግሥት ኃይሎች በዜጎች ላይ ከሕግ ውጪ የሆኑ ግድያዎችን እና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ታማኝ መረጃዎች ማግኘቱን የአሜሪካ መንግሥት ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ትግበራ ሪፖርት አመለከተ።

መንግሥት በጸጥታ ኦፕሬሽኖች ወቅት "ብዘዙ መከራና ስቃይ መፈጸሙን እና በባለስልጣናት ላይ ምንም ዓይነት ተጠያቂነት ማስፈን እንዳልቻለ ሪፖርቱ ያስረዳል።

በንጹሐን ዜጎች ላይ ተፈጽመዋል ተብለው ከጠቀሱት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መካከል የግሰለቦች "ስወራ"፣ "ስቃይ" እና "ኢሰብአዊ" ቅጣቶች ተካትተዋል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ200 በላይ ሀገራትን እና ግዛቶችን በተመለከተ በየዓመቱ የሚያወጣው ይህ ሪፖርት ይፋ የተደረገው በትላንትናው ዕለት ማክሰኞ ነሐሴ 6/2017 ዓ.ም. ነው።

ይህ ሪፖርቱት በአውሮፓውያኑ 2024 የነበረውን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ የሚዳስስ ሲሆን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ ይህን ሪፖርት የሚያጠናቅረው እንደ የሰብአዊ መብት ተቋማት ሪፖርቶች እና መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ያሉ "ታማኝ" የመረጃ ምንጮች በመጠቀም ነው።

ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት ውስጥ በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ውስጥ "በርካታ ከህግ እና ከፍርድ ውጪ የሆኑ ግድያዎች" መፈጸማቸውን ሪፖርቱ ይዳስሳል።

በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች እነዚህ ግድያዎች የተፈጸሙት "በግጭት አውድ" ውስጥ መሆኑን መረጃዎች እንደሚያመለክቱም ጠቅሷል።

በዋንኛነት በአማራ ክልል ተጥሎ የነበረውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የጠቀሰው ሪፖርቱ፤ የዚህ አዋጅ ተግባራዊነት ቢያበቃም "በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች [የሚፈጸሙ] በደሎች ቀጥለዋል" ብሏል። ሪፖርቱ፤ በሁለቱ ክልሎች "የተስፋፋ ህገ ወጥ የንጹሃን እና ባለስልጣናት ግድያ" መስተዋሉን የገለጸ ሲሆን "የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና የአማራ ፋኖ ታጣቂዎችም" እነዚህን ድርጊቶች ከፈጸሙት መካከል መሆናቸውን አስረድቷል።

በትግራይ ክልልም "የንጹሃንን ግድያን ጨምሮ ከህግ ውጪ ግድያዎች" መስተዋሉን ያሰፈረው ሪፖርቱ እነዚህ ድርጊቶች "በኤርትራ መከላከያ ሠራዊት እና የክልሉ ታጣቂዎች" የተፈጸሙ መሆናቸውን መረጃዎች እንደሚያመለክቱ ገልጿል።

የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ተቋማት እና የመገናኛ ብዙሃን መረጃዎችን በመጥቀስም፤ መንግሥት በሚያከናውናቸው "የጸጥታ ኦፕሬሽኖች" ወቅት "ስቃይ ውስጥ ተሳትፏል" ሲል ከስሷል።

ተመሳሳይ ምንጮች በመጥቀስም "የዘፈቀደ ወይም ህገወጥ ግድያ፣ ስወራ፣ ስቅይት ወይም የጭካኔ ተግባር፣ ኢሰብአዊ ወይም አዋራጅ አያያዞች ወይም ቅጣቶች" መፈጸማቸውን በሪፖርቱ አስፍሯል።

ሪፖርቱ፤ "ስቅይት በመፈጸም የሚከሰሱ የመንግሥት አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ አለመቻሉን" መረጃዎች እንደሚያሳዩ በመጥቀስም ወቅሷል። መንግሥት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የፈጸሙ "ባለስልጣናትን ለመለየት እና ለመቅጣት የወሰደው እርምጃ የተገደበ" እንደሆነም በሪፖርቱ ተካትቷል።

መንግሥት "ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያሉ የተወሰኑ ባለስልጣናት እንደተከሰሱ" መግለጹን ያስታወሰው ሪፖርቱ፤ እነዚህ እርምጃዎች በተመለከተ ያለው ዝርዝር መረጃ ትንሽ መሆኑን አስፍሯል።

በአዲስ አበባ ብዙ ሰዎች 'የቫይታሚን ዲ' እጥረት አለባችሁ የሚባሉት በስህተት ነው?BBC Amahricኸዲጃ እና ሪሐና እህትማማቾች ናቸው። ሁለቱም በተለያየ ምክንያት፣ በተለያዩ ቀናት ሐኪም ...
23/07/2025

በአዲስ አበባ ብዙ ሰዎች 'የቫይታሚን ዲ' እጥረት አለባችሁ የሚባሉት በስህተት ነው?

BBC Amahric
ኸዲጃ እና ሪሐና እህትማማቾች ናቸው። ሁለቱም በተለያየ ምክንያት፣ በተለያዩ ቀናት ሐኪም ጎብኝተው ሁለቱም የቫይታሚን-ዲ እጥረት አላባችሁት ተባሉ።

በሥራ ቦታ የሚያውቋቸው ሌሎች በርካታ ሰዎችም እንዲያ መባላቸውን ስለሚያውቁ ተገረሙ።

ኸዲጃ እና ሪሐና በሳምንት ዐርብ ከጁምዓ ስግደት በኋላ የቤተሰብ ፕሮግራም አላቸው። እየተገናኙ ይበላሉ፤ ይጨወታሉ።

በዚህ የቤተሰብ ጉባኤ የቫይቲምን-ዲ ነገር እንደ ዋዛ ተነሳ። "አለብሽ ተባልኩ" የሚለውን ተከትሎ "እኔም-እኔም-እኔም'' መባባል ሆነ።

"ከተሰበሰብነው ውስጥ ግማሻችን ቫይታሚን-ዲ አለባችሁ ተብለናል። ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል?" ትላለች ሪሐና።
"የእኛን አገር ሐኪሞች ብዙ አላምናቸውም። ድሮ ታይፎይድ አለባችሁ ይሉን ነበር፤ አሁን ደግሞ ቫይታሚን-ዲ እጥረት አለባችሁ ማለትን ፋሽን አድርገውታል" ትላለች ታላቅ እህቷ ኸዲጃ።

የጤና ባለሙያዎች ግን ነገሩ ወዲህ ነው ይላሉ።

"የአዲስ አበባ ሕዝብ 75% እጥረት አለበት"

ዓለም አቀፉ የምግብ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩት፣ ከጤና ሚኒስቴር ጋር ተባብሮ የሠራው ጥናት ውጤት አስደንጋጭ ነው።

ከኢትዮጵያ ሕዝብ ግማሹ እጥረት አለበት። ከአዲስ አበባ ሕዝብ ደግሞ ሦስት አራተኛው (¾) ቫይታሚን-ዲ አጥሮታል። ይህ ነገር ከኑሮ ውድነቱ ጋር የተያያዘ ይሆን?

አይደለም።

ይህ አሐዝ በተለይ 13 ወር ፀሐይ ለሚጠጣ ሕዝብ ስላቅ ይመስላል።ምክንያቱም የቫይታሚን-ዲ ዋና አከፋፋይ ፀሐይ ስለሆነች።
"አኗኗራችን ተለውጧል- ምርመራው ዘምኗል"
የሕክምና ባለሙያዎች የኑሮ ዘይቤያችን መቀየሩን አብዝተው ያወሳሉ።ከኮምፒውተር መምጣት ወዲህ እየጎበጥን ነው፤ ከዘመናይ ስልክ ወዲህ እየፈጠጥን ነው።

ይህ ነገር ጣጣ ይዞብን እየመጣ ነው። አያት ቅድመ አያቶቻችን ንቁ ነበሩ። የእኛ አኗኗር ፍዝ ሆኗል።የጤና ጣጣ ይዞብን ይመጣል።

ብዙ ሰው ጠዋት ተንደርድሮ ቢሮ ይገባል።ምሳ እዚያው ክበብ ውስጥ ይበላል። ሲመሽ ወደ ቤት ይነጉዳል።

ታዲያ ከፀሐይ ጋር በየት ይገናኛል? አኗኗራችን ተቀይሯል።

ተማሪ ትምህርት ቤት ይውላል፣ ካድሬ ቀኑን ሙሉ ስብሰባ ነው። ነጋዴው ሱቁ ቆሞ ይሸጣል። ከፀሐይ ጋር በየት በኩል ይገናኛል?

ለመሆኑ አዲስ አበቤ በሺህ በመቶ ሺዎች ለቫይታሚን ዲ የተጋለጠው ለዚህ ይሆን?

ዶክተር ፍጹም አንድ ቁልፍ ምክንያት ያነሳሉ።

"በፊት ምርመራ አልነበረም። ስለዚህ ቫይታሚን-ዲ እጥረት እምብዛምም አይታወቅም ነበር ።አሁን ብዙ ሰው ለአጠቃላይ ጤና ምርመራ ሲሄድ እጥረት እንዳለበት ይነገረዋል . . . ።"

ዶክተር ፍጹም ጥላሁን በአሜሪካን አገር በሕክምና ሙያ ላይ ተሠማርተው ይገኛሉ።

ውስብስብ የሕክምና መረጃዎችን በሕዝብ ቋንቋ አውርዶ ማኅበረሰባዊ ግንዛቤ በመፍጠር ብዙ ሥራ በመሥራት ይታወቃሉ።

'ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሐኪም ቤት የሄደ አዲስ አበቤ ሁሉ ቫይታሚን-ዲ እጥረት አለብህ የሚባለው ለምንድነው?' ለሚለው ቁልፍ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተውናል።
"አኗኗራችን ተለውጧል- ምርመራው ዘምኗል"
የሕክምና ባለሙያዎች የኑሮ ዘይቤያችን መቀየሩን አብዝተው ያወሳሉ።ከኮምፒውተር መምጣት ወዲህ እየጎበጥን ነው፤ ከዘመናይ ስልክ ወዲህ እየፈጠጥን ነው።

ይህ ነገር ጣጣ ይዞብን እየመጣ ነው። አያት ቅድመ አያቶቻችን ንቁ ነበሩ። የእኛ አኗኗር ፍዝ ሆኗል።የጤና ጣጣ ይዞብን ይመጣል።

ብዙ ሰው ጠዋት ተንደርድሮ ቢሮ ይገባል።ምሳ እዚያው ክበብ ውስጥ ይበላል። ሲመሽ ወደ ቤት ይነጉዳል።

ታዲያ ከፀሐይ ጋር በየት ይገናኛል? አኗኗራችን ተቀይሯል።

ተማሪ ትምህርት ቤት ይውላል፣ ካድሬ ቀኑን ሙሉ ስብሰባ ነው። ነጋዴው ሱቁ ቆሞ ይሸጣል። ከፀሐይ ጋር በየት በኩል ይገናኛል?

ለመሆኑ አዲስ አበቤ በሺህ በመቶ ሺዎች ለቫይታሚን ዲ የተጋለጠው ለዚህ ይሆን?

ዶክተር ፍጹም አንድ ቁልፍ ምክንያት ያነሳሉ።

"በፊት ምርመራ አልነበረም። ስለዚህ ቫይታሚን-ዲ እጥረት እምብዛምም አይታወቅም ነበር ።አሁን ብዙ ሰው ለአጠቃላይ ጤና ምርመራ ሲሄድ እጥረት እንዳለበት ይነገረዋል . . . ።"

ኖርዌይ እና አዲስ አበባ
ኦስሎ ፀሐይ ብርቅ ናት።

አዲስ አበባ ፀሐይ መከራ ናት።

ብዙ አዲስ አበቤ ፀሐይን እንደ ደመኛ ነው የሚያያት። ታነጫንጫለች። መልስ ስጠኝ ከሚል የታክሲ ጭቅጭቅ ቀጥሎ ብዙ ሰው የሚነጫነጨው በፀሐይ ንዳድ ይመስላል።

በአንጻሩ የስካንዲኒቪያን ሰዎች መሳቅ የሚጀምሩት ፀሐይ ስትወጣ ነው። እዚያ ብልጭ ብላ ትሰወራለች። ለጥቂት ወራት ብቻ።

ሆኖም ከኦስሎ ሕዝብ ይልቅ የአዲስ አበባ ሕዝብ በብዙ እጥፍ በቫይታሚን-ዲ እጥረት ይሰቃያል።

እንዴት ይህ ሊሆን ይችላል? 13 ወር ሙሉ ፀሐይ እየወጣች?

ዶክተር ፍፁም ''ይህ ጥሩ ጥያቄ ነው" ብለው ይንደረደራሉ።

"ይህ የሆነው በሜላኒን ምክንያት ነው" ይላሉ።

ምንድነው ደግሞ ሜላኒን?

እኛ አፍሪካውያን እና ባለ ጥቁር ቆዳ ሕዝቦች ሜላኒን አለን።ፈረንጆቹ ግን የላቸውም።

ሜላኒን የተፈጥሮ ጥላ ነው። የቆዳ ዣንጥላ ማለት ነው።ለቆዳችን "የጨረር ባለሥልጣን" ሆኖ ያገለግላል።

በዚህ የተነሳ "ቫይታሚን-ዲ በቀላሉ ማምረት የሚችሉት በተለምዶ ፈረንጅ የምንላቸው ሰዎች ናቸው። ቆዳቸው ነጣ ያሉ ሰዎች።"

ጥቁር ቆዳ ግን 'ማገዶ ይፈጃል'። ፀሐይ በቀላሉ አይዘልቀውም።

ፈረንጆች ላይ ግን አልትራቫዮሌት ሰውነታቸው ላይ ሲያርፍ በቀላሉ ቆዳቸውን ሰርጎ ይገባል።

በሌላ አነጋገር ቫይታሚን ዲ ሰርጾ እንዳይገባ ይሄ ሜላኒን ደንቃራ ሆኖ ይቆማል።

ይህ ማለት ምን ማለት ነው?

ቫይታሚን-ዲ የማምረት አቅማችን አናሳ ነው ማለት ነው።

ዶክተር ፍጹም፣ "ይህ ማለት ግን ሜላኒን አያስፈልገንም ማለት እንዳልሆነ ልብ እንድንል አበክረው ያሳስቡናል።

ከቆዳ ካንሰር የሚጠብቀን ማን ሆነና።

"ዓሣ ማን አቅምሶን?!"

የሥነ ምግብ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ይሁኔ አየለ በበኩላቸው ፀሐይ ብርቅ በሆነችበት በስካንዲኒቪያን የቫይታሚን እጥረት የሌለው በምክንያት ነው ይላሉ።

"የእነርሱ ዋና ምግባቸው ዓሣ ነው።ዓሣ ደግሞ በቫይታሚን-ዲ የበለጸገ ነው።''

ዓሣ ብላ ብሎ መምከር ለብዙ የአዲስ አበባ ሰው በቁስል ላይ እንጨት መስደድ ነው።

ምክንያቱም ዓሣ የሃብታም ምግብ ነው።

''ዓሣ ቤት'' ብዙ ሰው ምግቡን ደጋግሞ ፎቶ የሚያነሳው ለምን ሆነና።

ምን ተሻለ?

በዚህም በዚያም የአዲስ አበባ ሕዝብ ከቫይታሚን-ዲ እጥረት ማምለጥ አልቻለም፤ በዋናነት በሁለት ምክንያት።

አንደኛ፣ ከፀሐይ ንዳድ ሸሽቶ ቫይታሚን ዲ ያጥረዋል፣ ዓሣ ለመብላት ደግሞ ገንዘብ ያጥረዋል።

ምናልባት ለዚህ ይሆን 75 በመቶ የአዲስ አበባ ሕዝብ በቫይታሚን-ዲ እጥረት የሚሰቃየው?

ዶክተር ፍጹም ለዚህ አስደንጋጭ አሐዝ ሦስተኛ መላምት አላቸው።

የከተማው አየር በጭስ ታፍኗል፤ ከመኪና እና ከፋብሪካ በሚወጣ ጭስ (Smog) ከባቢ አየሩ ላይ ተሰግስጎ የፀሐይ ጨረርን እየገፋው ነው።

ይሄ ክፉ ጭስ ከተማዋን እንደ ብርድ ልብስ ይጋርዳታል። ይሄ ማለት ፀሐይ ቢነካንም ቀጥታ ጨረሩን አናገኘውም እንደማለት ነው።

የሥነ ምግብ ባለሙያው ዶክተር ይሁኔ ደግሞ ሌላም ምክንያት አለ ይላሉ።

''የምግብ ማበልጸግ ሥርዓት" በእንግሊዝኛ (food fortification) በሌላው ዓለም ይዘወተራል።በእኛ አገር ግን የለም።

ምን ማለት ነው ደግሞ እሱ?

በውጭው ዓለም የቫይታሚን እጥረት እንዳይከሰት ምግቦቻቸው ሆን ብለው ያበለጽጉታል። "ያ ልምድ በኢትዮጵያ አለመኖር ጎድቶናል" ባይ ናቸው፣ ዶክተር ይሁኔ።

ዶክተር ፍጹም፣ ከዶክተር ይሁኔ ሐሳብ ጋር ስምም ናቸው። እየኖሩትም ነው።

"እኔ በምኖርበት አሜሪካ ለምሳሌ ወተት ስትገዛ በቫይታሚን-ዲ የበለጸገ (Vitamin D fortified) የሚል ተጽፎባቸው ታያለህ።"

እጥረት እንደሚያጋጥም ስለሚታወቅ ነው እንዲያ የሚያደርጉት።

ቫይታሚን ዲ ምን ይሠራልናል? ቢቀርስ?
ካልሺየም የሚባለው እጅግ አስፈላጊ ንጥረ ነገር ወደ ሰውነታችን መግባት የሚችለው ቫይታሚን-ዲ ስናገኝ ነው።

አጥንት ያለ ካልሺየም ጨርቅ ነው። ካርቶን ነው። ይሳሳል-ይፈርሳል።

ቆመን ስንሄድ አይመስልም እንጂ ሸክላ ነን። በቀላሉ እንሰበራለን።ቆመን የምንሄደው በካልሺየም ብርታት ነው።

ሕጻናት በቂ ፀሐይ ካላገኙ እግራቸው ደጋን ይሆናል። እንደዚያው ሆነው ያድጋሉ።መቆም ይደክማቸዋል።

ዶክተር ይሁኔ በተለይ ልጆች ቡዳ እንዳይመታቸው እያሉ መሸፋፈን ይቅር ሲሉ አበክረው ይመክራሉ።

"ቅባት እየቀቡ፣ በጋቢ ጠቅልሎ ፀሐይ ማሞቅም ልክ አይደለም።"

ሽማግሌዎች በደንብ ፀሐይ ካላገኙ 'ወገቤን' ማለት ይጀምራሉ።ብዙ ሰው እርጅና ያመጣብኝ ጣጣ ነው ብሎ ይቀመጣል። ልክ አይደለም።

እጥረቱ ያለበት ሰው ሌላም ምልክት ያሳያል።

ቶሎ ቶሎ እንታመማለን። ቶሎ ቶሎ ጉንፋን ይይዘናል። ቶሎ ቶሎ ቶንሲል ያጠቃናል።

ጡንቻችን ይሟሽሻል። ድብርት ይመላለስብናል። የትከሻ እና የክንድ መዛል ይኖራል።

ብዙ ሰዎች መድኃኒት ወስጄም አልተሻለኝም ይላሉ። ዶክተር ፍጹም ለዚህ ምላሽ አላቸው።

"አንቲ ባዮቲክስ አይደለም። መድኃኒት ስለወሰድን ወዲያው አይሻለንም። ጊዜ ይወስዳል። የአጥንት ጥንካሬ ጊዜ ይፈጃል። መንቀሳቀስ አለብን።"

ሌላም ምክር አላቸው።

"ምርመራ ላይ ሰዎች የቫይታሚን-ዲ እጥረት አለብህ ሲባሉ ሁሉም ህመማቸው በእሱ ምክንያት የመጣ ይመስላቸዋል። ቫይታሚን-ዲ እጥረት ተጓዳኝ ችግር ነው እንጂ ዋና ችግር ላይሆን ይችላል።ሁሉም ህመማችን ከዚያ የመጣ ነው ማለትም አይደለም።"

ለምሳሌ ዘላቂ የኩላሊት እና የጉበት ህመምተኞች የቫይታሚን-ዲ እጥረት ምልክቶችን ያሳያሉ።

የአዲስ አበባ ሕዝብ ቫይታሚን-ዲ በስፋት እና በጥራት ያስፈልገዋል።

አለበለዚያ ዶክተር ይሁኔ እንደሚሉት "በአካሉ የበቃ፣ በአእምሮው የነቃ" የሚሉት ትውልድ አይፈጠርም።

 #ዜና  #ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የሆነየታጠቁ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎች፣ በራያ አካባቢ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን በኃይል ለመቆጣጠር ሲንቀሳቀሱ ከአካባቢው ሚሊሻዎች ጋር መጋጨታቸውን የዋዜማ ሬዲ...
22/07/2025

#ዜና #ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የሆነ

የታጠቁ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎች፣ በራያ አካባቢ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን በኃይል ለመቆጣጠር ሲንቀሳቀሱ ከአካባቢው ሚሊሻዎች ጋር መጋጨታቸውን የዋዜማ ሬዲዮ ዘግባል።

የክልሉን ፖሊስ ዩኒፎርም የለበሱ የታጠቁ ኃይሎች፣ ወደ ማይጨው፣ መሆኒ እና ጨርጨር ከተሞች እና ሌሎች የራያ አካባቢዎች በብዛት መግባታቸውን ምንጮች መናገራቸውን ዋዜማ ዘግባል። የጸጥታ ኃይሎቹ፣ የማይጨው ከንቲባ ጽሕፈት ቤትን በመቆጣጠር፣ በከባድ መሳሪያ ዙሪያውን እየጠበቁ ነው ተብሏል።

የታጠቁት የትግራይ ኃይሎች፣ በአላማጣ ከተማ የሠፈረው የፌደራል ፖሊስ ካምፑን ለቆ እንዲወጣ መጠየቃቸውንም ምንጮች ነግረውናል፡፡

አይ ኤም ኤፍ (IMF) ኢትዮጵያን አስጠነቀቀ፡ ከለጋሾች የሚሰጠውን ድጋፍ እየቀነሰ ባለበት የሪፎርም ሂደት አደጋ ሊገጥማት እንደሚችል አሰገንዝቧልሴሎም ሚዲያ፥ ለንደን፥ ሐምሌ 10፥ 2017/...
17/07/2025

አይ ኤም ኤፍ (IMF) ኢትዮጵያን አስጠነቀቀ፡ ከለጋሾች የሚሰጠውን ድጋፍ እየቀነሰ ባለበት የሪፎርም ሂደት አደጋ ሊገጥማት እንደሚችል አሰገንዝቧል

ሴሎም ሚዲያ፥ ለንደን፥ ሐምሌ 10፥ 2017/ ጁላይ 15፣ 2025

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር የብድር ስምምነት ማሻሻያ አጀንዳው ኢትዮጵያ ቁልፍ የፕሮግራም ግቦችን ብታሳካም ከለጋሾች የሚሰጠው ድጋፍ እየቀነሰ በመምጣቱን ምክንያት ሪፎርሙ ተግዳሮት ገጥሞታል ሲል አስጠንቅቋል።
አይኤምኤፍ ይዞት በወጣው ሰፊ ዘገባ መሰረት፥ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት የድጎማ ቅነሳ፣ የገንዘብ ማጠንከሪያ እና የታክስ ማሻሻያዎችን ጨምሮ ኢኮኖሚያዊ ማስተካከያዎችን በመተግበራቸው በመልካም ጎኑ አወድሷል።

ይሁንና እንደ ትይዩ የውጭ ምንዛሪ ገበያ እና ደካማ የጸጥታ ሁኔታዎች ያሉ ስጋቶች መጨመር እድገትን እንደሚያደናቅፉ እና የብድር መልሶ ማዋቀር ጥረቶችን ሊያወሳስበው እንደሚችሉ ሪፖርቱ ጠቁሟል።

ኢትዮጵያ በ2017/2025 ዓመት መጀመሪያ ላይ ከኦፊሴላዊ አበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ በተደረሰ ስምምነት ከቦንድ(holders) ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የብድር እፎይታ ትጠይቃለች። የአይኤምኤፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኒጄል ክላርክ "ከደህንነት ተግዳሮቶች እና ከለጋሾች ድጋፍ እየቀነሰ በመምጣቱ ከብድር እፎይታ ጊዜ ጋር በተገናኘ አመለካከቱ ለከፋ አደጋዎች ተገዢ ነው" ብለዋል።

ከአሥር ዓመታት በፊት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው የውጭ ዕርዳታ ከ12 በመቶው አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት ወደ 4 በመቶ ቀንሷል። አይኤምኤፍ በዚህ አመት ከአምስት ኢትዮጵያውያን አንዱ የምግብ ወይም የሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልገው ሲሆን የተባበሩት መንግስታት የምላሽ እቅድ በቂ ገንዘብ ያልተገኘለት እና ብዙ መርሃ ግብሮች በጊዜያዊ መገለል ላይ የተመሰረቱ ናቸው ብሏል።

ኢትዮጵያ በውጭ ምንዛሪ ገበያ ሊበራሊላይዜሽን እድገት አሳይታለች ቢልም ሪፖርቱ ነገር ግን መዋቅራዊ ጉዳዮች አሁንም ቀጥለዋል፣ ለምሳሌ የ2.5% ማዕከላዊ ባንክ የኤፍኤክስ ሽያጭ ኮሚሽን፣ የተገደበ የኢንተርባንኮች ፍሰት እና ከፍተኛ የግብይት ወጪን ጨምሮ እንደማሳያ ተጠቁመዋል። እነዚህ ምክንያቶች ትይዩ የገበያውን ዓረቦን ወደ 15 በመቶ ገፋውታል ሲል አይኤምኤፍ ተናግሯል።

የዋጋ ግሽበት ከተጠበቀው በላይ በፍጥነት ወርዷል፣ በገንዘብ ፖሊሲ እና በክሬዲት ገደቦች በመታገዝ። ያም ሆኖ ግን ኢትዮጵያ ወደ ዘመናዊ የፖሊሲ ተመን ተኮር ማዕቀፍ የምታደርገውን ሽግግር እንድታፋጥን እና ተዓማኒነትን ለማጎልበት IMF አሳስቧል።

አይኤምኤፍ የፕራይቬታይዜሽን መዘግየቶች እና ከሚጠበቀው በላይ ከሚጠበቀው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ጋር የተያያዙ ስጋቶችን ጠቁሟል።

አይኤምኤፍ የተሻሻለ የኤክስፖርት እይታን ገልጿል፣ ወደ ውጭ የሚላኩ እቃዎች እና አገልግሎቶች አሁን በ2024/25 የበጀት ዓመት ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ውስጥ 12 በመቶ እንደሚደርሱ፣ ይህም በሁለተኛው ግምገማ ወቅት ከነበረው 9.6 በመቶ ደርሷል። ኢትዮጵያ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ከአይኤምኤፍ ጋር ባደረገችው ፕሮግራም 262 ሚሊዮን ዶላር ወጪ አድርጋለች።
ምንጭ፡ ሮይተርስ

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ስርጭት  አቁሟል ፤ውጥረቱ ከፍተኛ ነው በፌዴራል ፖሊስ እና ደህንነት ከባባ ተደርጓል ፤Verified by African History=====የብርቱካን ተመስገን የግፍ በደል ...
26/03/2025

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ስርጭት አቁሟል ፤ውጥረቱ ከፍተኛ ነው በፌዴራል ፖሊስ እና ደህንነት ከባባ ተደርጓል ፤

Verified by African History
=====
የብርቱካን ተመስገን የግፍ በደል ታሪክ ፤ በኢቢኤስ ቲቪ ለሕዝብ ይፋ መሆኑ ተከትሎ በሥልጣን ላይ የሚገኘው። የአገዛዝ ሥርዓት ከፍተኛ ውጥረት ላይ ይገኛል ።

ብርቱካን ተመስገንን በአዲስ አበባ ፌድራል ፖሊስ ቢሮ በእስር ላይ ትገኛለች ።የኢቢኤስ ቴሌቭዥን የፕሮግራሙ ዳይሬክተር ታሪኩ ሃይሌ ፣ ረዳት አዘጋጅ ህሊና እንዲሁም ቪዲዮ ኤዲተሩ ሃብታሙ በፌድራል ፖሊስ በቅድሚያ ታፈነው ተወስደው ከታሰሩ በኋላ ፤ ሌሎች ባለሙያዎች ከፕሮግራሙ ቀረጻ ጋር በተገናኘ ሙያዊ ስራቸው ያከናወኑ የቢሮ ሠራተኞች ተለይተው በፖሊስ መኪና ውስጥ እንዲገቡ ተደርጎ በጊቢው ውስጥ ታግተው ይገኛሉ።

ይህ መረጃ ይፋ እስከ ሆነበት ሰዓት ድረስ ከጠዋቱ ጀምሮ ወደ ኢቢኤስ ቢሮ እና ቅጥር ግቢ ወደ ውስጥ መገባት የሚቻል ሲሆን መውጣት ግን ክልከላ ተደርጎ የነበር ሲሆን ፤ ከምሳ ሰዓት በኋላ በጊቢው ውስጥ የነበሩ ሠራተኞች በሙሉ እንዲወጡ ተደርጎ በፌዴራል ፖሊስ እና ደህንነት የኢቢኤስ ቅጥር ጊቢ በከፍተኛ ሁኔታ ከበባ እና ጥበቃ ውስጥ ነው ያለው ።
የኢቢኤስ አዘጋጅ ሉላ ገዙ ታስራለች ተብሎ የተሰራጨው መረጃ እስካሁን ሰዓት ድረስ ሐሰት ነው ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኢቢኤስ የብርቱካን ተመስገንን ጉዳይ አስመልክቶ ሰጠ የተባለው መግለጫ ፤ በተቋሙ በተረጋገጠ የማኀበራዊ ትስስር ገጽ እንዲሁም በሚዲያው በግል የሰጠው አንዳችም መግለጫ እንደሌለ ለማወቅ ተችሏል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢቢኤስ ቴሌቪዥን በዛሬው ዕለት ሶስቱም ቻናሎቹ በኢትዮ ሳት ላይ ስርጭት አቁሟል። የስርጭቱ መቋረጥ ከላይ በተገለጸው ጉዳይ ይሆን ወይም በሌላ በግልጽ እስካሁን የታወቀ የለም ።

Address

United Kingdom, Regent Streets
London

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Selom Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Selom Media:

Share