ምንጊዜም ኢትዮጵያ- Mengizem Ethiopia

ምንጊዜም ኢትዮጵያ- Mengizem Ethiopia We’re here for one reason to provide fair and unbiased information to the community and is committed to separating news and views, while covering broad areas.

In addition, we do sponsored social media promotion on Facebook and Instagram.

36 ሰዎች ብቻ የሚኖሩባት ሀገርበሀገሪቱ 36 ሰዎች እና አራት ውሾች ብቻ ይኖሩባታል። ባውግስተን ዋና ከተማዋ ናት። የዓለማችን ትንሿ ሀገር የሞሊሲያ ሪፐብሊክ ጠባብ የቆዳ ስፋት ቢኖራትም ከ...
10/01/2025

36 ሰዎች ብቻ የሚኖሩባት ሀገር

በሀገሪቱ 36 ሰዎች እና አራት ውሾች ብቻ ይኖሩባታል። ባውግስተን ዋና ከተማዋ ናት።

የዓለማችን ትንሿ ሀገር የሞሊሲያ ሪፐብሊክ ጠባብ የቆዳ ስፋት ቢኖራትም ከሕዝቦቿ አንጻር ግን ሰፊ መሬት አላት።

ሕዝቦቿ ሞሊሲያን እንደ አንዲት ታዳጊ ሀገር ይቆጥራሉ። የራሷ መገበያያ ገንዘብ፣ የራሷ ሰማያዊ፣ ነጭ እና አረንጓዴ ቀለሞችን የያዘ ባንድራ እንዲሁም የሕዝብ መዝሙርም አላት።

ይህ ሁሉ እየሆነ የሚገኘው በዓለም ታላቋ ሀገር በአሜሪካ ውስጥ ነው። የሞሊሲያ ሪፐብሊክ በሀገረ አሜሪካ በኔቫዳ ግዛት ውስጥ ነው የምትገኘው።

የአሜሪካ መንግስትም ሆነ የተባበሩት መንግስታት እንደ ሀገር እውቅና ባይሰጣትም ሞሊሲያ ግን እንቅስቃሴዋ ሁሉ እንደ አንዲት ነጻ እና ሉዓላዊ ሀገር ነው።

የአሜሪካን መገበያያ ዶላርን ሳይሆን የራሷን “ቫሎራ” የተሰኘ ገንዘብ ትጠቀማለች። ሕዝቦቿ እንግሊዝኛን እና ኢስፒሬናቶ ቋንቋዎችን ይናገራሉ።

የሞሊሲያ ሪፐብሊክ የበርካታ ጎብኝዎችን ቀልብ መሳብ የቻለችም ሀገር ናት። በዓለም ላይ ካሉ ከፍተኛ የኑሮ ደረጃ ካላቸው ሀገራት መካከል ሞሊሲያ አንዷ ስትሆን ከፍተኛ የሀገር ውስጥ ምርት አላት።

ሆስፒታል እና አየር መንገድ ባይኖራትም የባሕር ኃይል፣ የባቡር ሀዲድ፣ የቱሪስት መስህብ ቦታዎች፣ ባንክ፣ የፖስታ አገልግሎት፣ የየሬዲዮ ጣቢያ እና የራሷ ሰዓት አቆጣጠር ያላት ሀገር ናት።

ሞሊሲያን መጎብኘት የሚቻለው በዓመት ውስጥ ለአንድ ወር ብቻ ሲሆን እሱም ጥቅምት ወይም ሚያዚያ ወር ላይ ነው። ጎብኝዎች ወደ ሀገሪቱ ለመግባት ከሞሊሲያ መንግስት ፈቃድ ማግኘት ይጠበቅባቸዋል።

ጎብኝዎች ፓስፖርታቸውን ለሀገሪቱ መንግስት ልከው ማህተም ካስመቱ በኃላ ወደ መጓዝ ይችላሉ።

ሞሊሲያ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንጆቹ 1977 ስትመሰረት የቩልድስተይን ግራንድ ሪፐብሊክ በመባል ትታወቅ ነበር።

አሁን ላይ የሞሊሲያ ሪፐብሊክን የሚያስተዳድሯት ፕሬዝዳንት ግራንድ አድሚራል ኮሌኔል ኬቨን ባወ (ዶ/ር) ይባላሉ።

04/01/2025

Please Share this Good Information with your family in Ethiopia?

ለጠቅላላ ዕውቀት‼️

የመሬት መንቀጥቀጥ ደረጃ ዝቅተኛው በሬክተር ስኬል 0 ሲሆን ከፍተኛው 10 ነው::

ስለዚህ ዛሬ ሌሊት 9 .53 ላይ የተከሰተው 5.8 ነው። ከፍተኛ የሆነ መሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል ወደ ከፍተኛም ፊክተር ስኬር እየሄደ ነው😱 በረደን ወሰላማ ላኢላሂ🤲

አለማቀፍ ጂኦሎጂካል ሰርቬዮቹ የመሬት መንቀጥቀጥ ደረጃን በሬክተር ስኬል እንዲሁም ሊያስከትል የሚችለውን የጉዳት መጠን እንደሚከተለው አስቀምጠውታል።

1ኛ. መጠን ከ 1.0 እስከ 3.0: ይህን ያህል አይሰማም ግን ተመዝግቧል.

2ኛ. መጠን ከ 3.0 እስከ 3.9: ብዙ ጊዜ የሚሰማው ነው ነገር ግን ብዙም ጉዳት የለውም.

3ኛ. ከ 4.0 እስከ 4.9 መጠን: ጉልህ የሆነ የቤት ውስጥ እቃዎች መንቀጥቀጥ; አነስተኛ ጉዳት ሊደርስ ይችላል.

4ኛ ከ 5.0 እስከ 5.9 መጠን: በህንፃዎች እና ሌሎች ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል.

5ኛ. መጠን ከ 6.0 እስከ 6.9: ጠንካራ መንቀጥቀጥ እና ለከባድ ጉዳት ያስከትላል:

6ኛ. 7.0 እና ከዚያ በላይ መጠን: ከፍተኛ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛ ጉዳት እና ሰፊ ውድመት ሊያስከትል ይችላል።

አዲስ ዓመትን እንዲያከብሩ እስረኞችን ፈቶ የለቀቀው ፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለ፡**********************************************የዛምቢያ ፖሊስ አባል የሆነው መርማሪ ኢ...
03/01/2025

አዲስ ዓመትን እንዲያከብሩ እስረኞችን ፈቶ የለቀቀው ፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለ፡
**********************************************
የዛምቢያ ፖሊስ አባል የሆነው መርማሪ ኢንስፔክተር ቲተስ ፊሪ የተባለው ፖሊስ በቁጥጥር ስር የሚገኙ ተጠርጣሪዎቹን በዋና ከተማዋ ሉሳካ ከሚገኘው ሊዮናርድ ቼሎ ፖሊስ ጣቢያ ነው ፈቶ የለቀቃቸው፡፡

ለረጅም ሰአታት በጠጣው መጠጥ በአልኮል ተጽዕኖ ውስጥ የነበረው ኢንስፔክተሩ ድርጊቱን ከፈጸመ በኋላ ከህግ ለማምለጥ ጥረት አድርጓል፡፡

ባልጠበቁት ሁኔታ ከእስር ቤት እንዲወጡ የተፈቀደላቸው ታሳሪዎች በዝርፊያ ፣ ስርቆት እና አካላዊ ጥቃት በማድረስ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የሚገኙ ነበሩ፡፡

በአሁኑ ወቅት ሉሳካ የሚገኘው የሊዮናርድ ቼሎ ፖሊስ ጣቢያ ፖሊስ አባላት ያመለጡትን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል በአደን ላይ ይገኛሉ፡፡

የፖሊስ ቃል አቀባይ ሬ ሀሙንጋ ድርጊቱን የፈጸመው ኢንስፔክተር ቲተስ ፊሪ በአዲስ አመት ዋዜማ ተረኛ የእስረኞች ጠባቂ ከሆነችው የፖሊስ አባል የእስር ቤቶቹን ቁልፍ በሀይል እንደቀማት ተናግረዋል፡፡

በመቀጠልም ኢንስፔክተሩ የወንድ እና ሴት የእስር ቤት ክፍሎችን በመክፈት "ወደ አዲሱ አመት ለመሻገር ነፃ ሆናችኋል" በማለት ከእስር ቤቱ እንዲወጡ እንዳዘዛቸው ቃል አቀባዩ ገልጸዋል፡፡

በስካር መንፈስ ውስጥ ሆኖ ያልተጠበቀውን ድርጊት የፈጸመው መርማሪ ኢንስፔክተር ወዲያው ከአካባቢው ለመሸሽ ቢሞክርም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

ኢንስፔክተሩ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸመ እስካሁን ቃሉን እንዳልሰጠ የተገለጸ ሲሆን ፖሊስ በበኩሉ ከእስረኞቹ መለቀቅ ጀርባ የስካር ስህተት ወይስ ድብቅ ዓላማ ያለው የተቀነባባረ ድርጊት የሚለውን ለማጣራት በምርመራ ላይ እገኛለሁ ብሏል፡፡
via አልአይን

🎙️🗣️ኒኮ ዊሊያምስ: "ወንድሜ ባይኖር እግርኳስ ተጫዋች አልሆንም ነበር።በልጅነቴ ከጓድኞቸ ጋር እንጠጣ እና እናጨስ ነበር።ወንድሜም ከእነዚህ መጥፎ ጓድኞች እንድርቅ ከመምክር ጀምሮ እስከ መ...
03/01/2025

🎙️🗣️ኒኮ ዊሊያምስ: "ወንድሜ ባይኖር እግርኳስ ተጫዋች አልሆንም ነበር።በልጅነቴ ከጓድኞቸ ጋር እንጠጣ እና እናጨስ ነበር።ወንድሜም ከእነዚህ መጥፎ ጓድኞች እንድርቅ ከመምክር ጀምሮ እስከ መደብደብ ድረስ እንዲሁም ልጆቹን አሳዶ ከእኔ እንዲርቁ ያደርግ ነበር።ይህን ሲያደርግ ሁሌም ለእናቴ እነግራት ነበር እሷም እሱን ነበር የምትደግፉው።ነገሩ አይገባኝም ነበር አይወዱኝም ብየ ነበር የማስበው።ካለ ወንድሜ ድጋፍ እዚህ ቦታ ፈፅሞ አልደርስም ነበር።አሁን ከየትኛውም ሰው በላይ የምሰማው ወንድሜን ብቻ ነው።ብቸኛው አማካሪየም እሱ ነው።አሁን ላይ ታላቅ ወንድሜን ኢኒያኪ ዊሊያምስን እንደ አባቴ ነው የማየው።"

ችርስ ለምርጥ ወንድሞቻችን!!❤️🥰

ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ የሚወርድ ከሆነ አዲዳስ ስፖንሰር ያደረገውን 900 ሚሊዮን ፓውንድ እንደሚሰርዝ ውላቸው ላይ ተቀምጧል።
02/01/2025

ማንችስተር ዩናይትድ ከሊጉ የሚወርድ ከሆነ አዲዳስ ስፖንሰር ያደረገውን 900 ሚሊዮን ፓውንድ እንደሚሰርዝ ውላቸው ላይ ተቀምጧል።

የጥበቃ ሠራተኛው የዩኒቨርሲቲ ሌክቸረር አጨ!!!ነገሩ የሆነዉ ኡጋንዳ ዉስጥ ነዉ በሌክቸረሯ ፍቅር የተማረከዉ የጥበቃ ሠራተኛ ለ2 አመታት በግቢዋ አጥር ዙሪያ ይመላለስ ነበር በዚህ ወቅት ሌክ...
02/01/2025

የጥበቃ ሠራተኛው የዩኒቨርሲቲ ሌክቸረር አጨ!!!

ነገሩ የሆነዉ ኡጋንዳ ዉስጥ ነዉ በሌክቸረሯ ፍቅር የተማረከዉ የጥበቃ ሠራተኛ ለ2 አመታት በግቢዋ አጥር ዙሪያ ይመላለስ ነበር በዚህ ወቅት ሌክቸረሯን ለማማለል አስቂኝ ቀልዶችንና የፍቅር ቃላትን እያቀረበ ያዝናናት ነበር።

እልል ብሎ በአደባባይ የታገብኛለሽ ጥያቄ ጠይቋታል ሌክቸረሯም አላሳፈረችዉም የታገብኛለሽ ጥያቄዉን ተቀብላ'ትምህርት ቤት ገብቶ እንዲማር አደርገዋለሁ::

የወደፊቱም የልጄ አባት ይሆናል ብላለች የአለም ሚዲያዎች ይህንን ክስተት እወነተኛ ፍቅር ብለዋል።

Address

Victoria Station
London
SW1V1JU

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ምንጊዜም ኢትዮጵያ- Mengizem Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ምንጊዜም ኢትዮጵያ- Mengizem Ethiopia:

Share