Mido Entertainment

Mido Entertainment ድምፂ ተጋሩ | Voice Of Tegaru
Tdf Consists News, Music, Movie and Documentary in Tigrgna and other Lan

27/07/2025

Mamush Hayelom
❤ፊትኣውራሪ ሙዚቃ ትግራይ ❤ልጅ በላይ ሓየሎም (ማሙሽ)❤ ኣፃብዕቱ ዘየዕረፈሉ ጎበዝ ደርፊ ትግርኛ ዳርጋ የለን ካብ ሐዉ ሙላት ሓየሎም(ሰላም ጥራይ) ፣ ኣብርሃም ገ/መድህን ክሳብ ሰለሞን ሃይለ ፣ካብ ዳዊት ነጋ ፣ክሳብ ኣማኑኤል የማነ ፣ካብ ማህሌት ክሳብ ኤደን፣ ካብ ሸዊት መዝገቦ ክሳብ ራሄል ሃይለ ካብ ኣሚር ዳውድ ክሳብ ሰሎሞን ባይረ ፣ ካብ ታምራት ደስታ ፣ ጃኪ ጎሲ ክሳብ ተመስገን ገ/እግዚኣብሄር ወዘተ… ኮታስ ኣብ ድሕሪ መብዛሕቶም ፅቡቓት ደርፊታት ትግርኛ ንሱ አሎ ሙዚቃ ብስምዒትን ብኽእለትን ብተውህቦን ዝፃወት ፍሉይ ኣወሃሃዲ ሙዚቃ እዩ። ንባዕሉ ክገንን ጥራሕ ዘይኮነስ ንብዙሓት ፈረይቲ መወሃሃድቲ ክሕግዝን መንገዲ ከርእን ክእለቱ ዘይልገም ንትግራይ ብህያብ ዝተበርከተ ረዚን በዓል ሞያ፤ ክንዲ'ቲ ዝግብኦ ዘይተነግረሉ ወሓለ ከያኒ ልጅ በላይ ሓየሎም ሓው ድምፃዊት ንግስቲ ሓየሎም ፣ሓው ሙላት ሓየሎም ሎሚናት ሓየሎም እዩ ።
🙏🙏❤❤የቐንየልና ከያኒ Mamush Hayelom 🙏🙏

💥❖ለአብርሃም የተገለጠ ምስጢረ ሥላሴ ❖💥✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ💥❖ “በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።”  — ዘፍ...
13/07/2025

💥❖ለአብርሃም የተገለጠ ምስጢረ ሥላሴ ❖💥
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥❖ “በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።”
— ዘፍጥረት 18፥1

👉 መምሬ በኬብሮን ያለች ሲኾን አብርሃም ለእግዚአብሔር መሠዊያ የሠራባት የተቀደሰች ቦታ ናት (ዘፍ 13:18)
👉 በዕብራይስጥ "መምሬ" ማለት ጥንካሬ ወይም የሰባ ማለት ነው። ይኽም የተትረፈረፈ እና መለኮታዊ ጸጋን ያመለክታል።

💥❖ የተገለጡለት ሰዓቱ ቀትር (ስድስት) ሰዓት በዕንጨት ሥር በሰው አምሳል መኾኑ ቀደምት ሊቃውንት ሲያራቅቁት በአብ፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ በራሱም ፈቃድ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ ዘመኑ ሲፈጸም የአብርሃምን ባሕርይ ተዋሕዶ ፍጹም ሰው ኾኖ በስድስት ሰዓት በዕንጨት መስቀል ላይ ለቤዛ ዓለም የሚሰቀል መኾኑን ያጠይቃል ይላሉ፨

💥❖ ይኽነን ይዞ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በሕማማት ሰላምታው፦
"ለአብርሃም አብ ቀዳሚ ዘአስተርአይኮ ክርስቶስ
ቀትረ ታሕተ ዕፀ ድርስ
ተሰቀልከ ከመ እቡስ ስብሐት ለከ"
(ምስጋና የተገባኽ ጌታ ድርስ በሚባል የዛፍ ዐይነት ሥር በስድስት ሰዓት ለአባታችን አብርሃም ቀድሞ የተገለጥኽለት ክርስቶስ ሆይ እንደ በደለኛ ተሰቀልኽ) ይላል፨

💥 ሌላው ቀትር (እኩለ ቀን) የፀሐይ ግለት ይበረታል። እግዚአብሔርም በእሳት እንደተፈተነ ወርቅ እምነቱ ተፈትኖ የጠራውን አብርሃምን የጎበኘው በቀዝቃዛ ጊዜ ሳይኾን እንደ እሳት በሚያቃጥል ሰዓት ነው።

👉 ያልታዘዘው አዳምን በሠርክ ሰዓት እግዚአብሔር በአትክልት ስፍራ ሊጎበኘው ሲመጣ በዛፍ ውስጥ ተደበቀ። ታዛዡ አብርሃም ግን በቀትር (ከቀኑ 6 ሰዓት) በዛፍ አጠገብ ሳለ እግዚአብሔር ወደ ርሱ ሲመጣ ቢያየው ለመቀበል ሮጠ።

💥 እኩለ ቀን ፀሐይ በአናታችን ትክክል ከፍተኛው ልዕልናዊ ቦታዋ ላይ የምትደርስበት ሰዓት ሲኾን ሙሉ ብርሃን ሰጥታ ጥላን የምታባርርበት ሰዓት ላይ የክሕደት ጥላ ባላጣላበት አማናዊ ፀሐይ ሥሉስ ቅዱስ ተገልጸውለታል።

👉 በሐዲስ ኪዳንም በተመሳሳይ መልኩ ቅዱስ ጳውሎስን የመለሰው ከሰማይ የታየው ብርሃን በስድስት ሰዓት (ቀትር) ላይ ነበረ (የሐዋ 22:6)።

✍️ “ዐይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ”
— ዘፍጥረት 18፥2

👉 ሥላሴ በአምሳለ ዕደው ቆመው ቢያይ መሮጡ ድንቅ ነው። አርጅቶ 100 ዓመት መልቶት ከግዝረት ቁስል ያገገመ ሲኾን እስኪቀርቡ ሳይጠብቅ መሮጡ የመንፈስ ጥንካሬው፣ እንግዳ ማፍቀሩ፣ በመንፈስ የነቃ መኾኑን ያመለክታል (ዘፍጥረት 17፡24)።

👉 በዚኽ ደጉ አብርሃም አምላክን በመውደድ ፈጣን መንፈሳዊ ሩጫን ለሚሮጡ አብነት ነው።

✍️ “አራቱም እንስሶች፦ አሜን አሉ፥ ሽማግሌዎቹም ወድቀው ሰገዱ።”
— ራእይ 5፥14
✍️ “ሳበኝ፥ ከአንተም በኋላ እንሮጣለን፤ ንጉሡ ወደ ቤቱ አገባኝ” እንዲል
— መሓልይ. 1፥4

💥መላእክት ለእግዚአብሔር እንዲሰግዱና እንዲሮጡ አብርሃምም ሰው ሲኾን በግብሩ መልአክ ኾኖ ተገለጠ።
✍️ “እንስሶቹም እንደ መብረቅ ምስያ ይሮጡና ይመለሱ ነበር።”
— ሕዝቅኤል 1፥14

💥❖ ስላቀረበው ስግደት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ሰለዚኽ ነገር በድጓው ላይ፦
"ዮም አብርሃም ሰገደ ለፈጣሪሁ
ሶበ ነጸረ ዋሕደ በሥላሴሁ"
(ዋሕደ ባሕርይ የኾነ እግዚአብሔርን በአካላዊ ሦስትነቱ ባየው ጊዜ አብርሃም ዛሬ ለፈጣሪው ሰገደ) ይላል፨

💥❖ ከዚኽ በኋላ "አቤቱ በፊትኽስ ሞገስ አግኝቼ እንደኾነ ባሪያኽን አትለፈኝ ብዬ እለምናለኍ፤ ጥቂት ውሃ ይምጣላችኍ፤ እግራችኹን ታጠቡ፤ ከዚኽችም ዛፍ በታች ዕረፉ…" በማለት ተናግሯል፡፡

✔"በፊትኽ ሞገስን አግኝቼ" ብሎ አንድነታቸውን፤
✔"ውሃ ይምጣላችኍ፣ ዕረፉ፣ ትኼዳላችሁ" ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡

💥❖ ይኽቺ አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልለው ሦስትነቱ አንድነቱን ሳይከፍለው በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን እግዚአብሔር የተገለጠባት ዛፍ፤ አንድነት ሦስትነት በጐላ በተረዳ ነገር የታወቀባት ከሦስቱ አካል አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድን በድንግልና የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ መኾኗን፤ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ እንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ፦
"አንቲ ውእቱ ዕፀ ድርስ ዘለአብርሃም በርስአኒሁ
ዘብኪ አጽለለ እግዚአብሔር በሥላሴሁ"
(ለአብርሃው በእርጅናው ወቅት፤ እግዚአብሔርን በሦስትነት ያስጠለለብሽ የወይራ ዕንጨት አንቺ ነሽ) በማለት ሲገልጥ፦

💥❖ ዳግመኛም በዚኹ መጽሐፉ፡-
"እንቲ ውእቱ ዕፀት ዘነበርኪ ጥቃ ኀይመት፣
ዘብኪ አጽለሉ ሠለስቱ አጋዕዝት"
(ባንቺ ሦስቱ ጌቶች (ሥላሴ) የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ) በማለት በአንድነቱ ምንታዌ (ኹለትነት)፣ በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) ለሌለበት አምላክ የሦስትነቱ የአንድነቱ ምስጢር መገለጫ የሥላሴ ማደሪያ መኾኗን መስክሯል፡፡

💥❖ ከዚኽም ምስጢር የተነሣ አብርሃምም ሳራን “ሦስት መስፈሪያ የተሠለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፤ ለውሺውም እንጎቻም አድርጊ” በማለት የተገለጸለትን የሦስትነት የአንድነት ምስጢርን አጒልቶ ተናግሯል፡፡

💥❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ይኽነን ይዞ በሕማማት ሰላምታው ላይ፦
"ግናይ ለክሙ ሥሉስ ቅዱስ ነገሥተ ሰብዐቱ አብያት
እለ በላዕክሙ ውሣጤ ኀይመት
አሐደ ኅብስተ ትሥልስት"
(ከሦስት መስፈሪያ ዶቄት የተጋገረ አንድነት ያለው ኅብስትን በድንኳን ውስጥ የተመገባችሁ የሰባት ቤቶች (ሰማያት) ነገሥት ሆይ ለእናንተ መገዛት (ምስጋና) ይገባል) ይላል፨

💥❖ አብርሃምም በደስታ ኾኖ መዐር፣ ወተት፣ ያዘጋጀውን ጥጃ አመጣላቸው፤ እነርሱም ደስ ይበለው ብለው በግብር አምላካዊ ተመግበዋል፤ መላእክት ሎጥ ቤት፤ ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢት ቤት ተመገበ የተባለው አንድ ነው፤ እሳት ቅቤ በላ እንደማለት ብቻ ነው፨

💥❖ ይኸውም ወተትና መዐር መመገባቸው ኦሪትን ወንጌልን መሥራታቸውን ሲያጠይቁ ነው፤ መዐር የኦሪት፤ ቅቤ የወንጌል ምሳሌ ነው፨ ማር ለጊዜው ሲይዝ የሚለቅ አይመስልም፤ ግን ይለቃል ኦሪትም ስትሠራ የምታልፍ አትመስልም ነበር ግን በኽዋላ ዐልፋለች፨ ወተት የወንጌል ምሳሌ ነው፤ ይኽ ወተት ለጊዜው የሚለቅቅ ይመስላል በኽዋላ ሲያጥቡት አይለቅም ወንጌልም ለጊዜው ስትሠራ የምታልፍ ትመስል ነበር፤ በኽዋላ ግን ጸንታ የምትኖር ኾናለችና በማለት መተርጉማን ያራቅቁታል፡

💥 ከሦስቱ አንዱ እግዚአብሔር ወልድ አብርሃምን "የዛሬ ዓመት እንደዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለኍ፤ ሚስትኽ ሳራም ልጅን ታገኛለች" በማለት ዘመኑ ሲፈጸም እግዚአብሔር ወልድ ከቤተ አብርሃም ከተገኘች ከእመቤታችን የመወለዱንና፤ በሳራ የተመሰለች ወንጌል ምእመናንን እንደምታስገኝ በምስጢር ገልጾለታል፤ ቅዱስ ጳውሎስም አካላዊ ቃል በሰጠው ተስፋ መሠረት ከነገደ አብርሃም የመወለዱን ነገር ለዕብራውያን ሰዎች በጻፈው መልእክቱ ላይ "በሕይወታቸው ኹሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ኹሉ ነጻ እንዲያወጣ፤ በሥጋና በደም እንዲኹም ተካፈለ፣ የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም" በማለት ገልጾታል (ዕብ ፪፥፲፭-፲፮)፡፡

💥❖ ይኽቺ ሥላሴ የገቡባት ኀይመተ አብርሃም (የአብርሃም ድንኳን) የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፤ ይኸውም ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ኹሉ፤ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም፤ አብ ለአጽንኦ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ለመዋሐድ ዐድረዋል (ሉቃ ፩፥፴፭)፤ በመኾኑም አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ብቻ ናት፡፡

💥❖ ሊቁም በነገረ ማርያም ይኽነን ምስጢር ሲገልጽ "ወይእቲ ኀይመት ትትሜሰል በድንግል ወዕደው አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እሙንቱ፤ አብ አጽንኣ፣ ወወልድ ተሰብአ እምኔሃ፣ ወመንፈስ ቅዱስ ቀደሳ ከመ ትጹር አምላከ በከርሣ" (ያቺ ድንኳንም በድንግል ትመሰላለች፤ ሰዎቹም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፤ አብ አጸናት፣ ወልድም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾነ፣ መንፈስ ቅዱስ አካላዊ ቃል አምላክን ትሸከም ዘንድ ለያት) በማለት ተርጉሞታል፨

💥❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በሰላምታ መጽሐፉ ላይ መጽሐፉ፦ "ኀይመተ አብርሃም አብ ሰላም ለኪ፤
ዘኮንኪ ከመ ተድባብ ሰላም ለኪ"
(እንደ ጥላ የኾንሽ የአባት አብርሃም ድንኳን ሰላምታ ይገባሻል) በማለት አመስግኗታል፡፡

💥❖ ይኽ አብርሃም የተቀበለውን የተስፋ ቃል ሊቃውንት ሲተረጒሙት "ኦ አኃውየ በይነ መኑ እንከ ዘይቤ እግዚአብሔር ለአብርሃም አመ ከመ ዮም እገብእ ኀቤከ አኮኑ እግዝእትነ ማርያም ይእቲ ዘወፅአት እምነ ሥርው ለአዳም ..." (ወንድሞቼ ሆይ እግዚአብሔር አብርሃምን እንደዛሬው ኹሉ ወደአንተ ተመልሼ እመጣለኍ ያለው ስለማን ይመስላችኋል? ከአዳም ሥር ወጥታ፤ ከኖኅ አብራክ ተገኝታ፤ ወደ አብርሃም አብራክ ልትከፈል፤ ሥላሴ በአብርሃም ቤት በእንግድነት ተገኝተው፤ ከአብርሃም ዘር ከእመቤታችን የእግዚአብሔርን ልጅ ሰው መኾን ስለርሷ የተናገሩላት እመቤታችን ድንግል ማርያም አይደለችምን፤ ስለዚኽ እግዚአብሔር ስለ እመቤታችን ጥንታዊ የልደቷን አመጣጥ በየጊዜው ምልክት እንደሚሰጥ ልብ አድርገን ማስተዋል ይገባናል) በማለት አብራርተው ተርጒመዋል፡፡

💥❖ ሊቁ አባ ሕርያስቆስም በቅዳሴው በቊ ፴፪ ላይ "ተናግዶቱ ለአብርሃም" (የአብርሃም እንግድነቱ አንቺ ነሽ) በማለት ምስጢሩን ጠቅልሎ የገለጠውን ይኽነን ድንቅ ምስጢር፤ ሊቁ በነገረ ማርያም ላይ በስፋትና በጥልቀት፡-

♥ "ወዓዲ ኀይመት ዘአብርሃም ዘውስቴታ ተአንገደ እግዚአብሔር አኮ ከማሁ ዘኮነቶ ምጽላለ በእንተ ምዕር አላ ኮነቶ እመ ወተከድነ ሥጋሃ ወረሰዮ አሐደ ምስለ መለኮቱ"

(ዳግመኛም እግዚአብሔር (በሦስትነት) በዕንግድነት ያረፈባት የአብርሃም ድንኳን አንቺ ነሽ፤ ለጥቂት ጊዜ ብቻ መጠለያን፣ መጠጊያን የኾነቺው አይደለም፤ እናትን ኾናው ሥጋዋን ተዋሕዶ ከመለኮቱ አንድ አደረገው እንጂ) በማለት በአብርሃም ድንኳን ብትመሰልም እንኳ ክብሯ ከፍ ያለ፤ ለዘላለም የአምላክ ማረፊያውና እናቱ መኾኗን አብራርቶ ገልጧል፡፡

💥❖ ሊቅነትን ከንግሥና ጋር ያስተባበረው ዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ በመጽሐፈ ሥላሴ መጽሐፉ ላይ፦
👉 "ኦ ብእሲ ዘትትከሓድ አይኑ ዕለት ለአግዚአብሔር ሰገዱ ሎቱ ምስለ መላእክቲሁ በዕሪና እምነ ኩሉ ፍጡራኒሁ..."
(ሥላሴን የምትክድ አንተ ሰው ሆይ ከፍጡሮች ወገን በመላ እግዚአብሔርን ከመላእክቱ ጋር በአንዲት ዕሪና የሰገዱለት በማናቸው ዕለት ነው? በማናቸው ዕለት እግዚአብሔር ከፈጠራቸው መላእክቱ ጋር ተካክሎ እግሩን ታጠበ? በማናቸው ዕለት በሰው መጠለያ በታች ከፈጠራቸው መላእክት ጋር ተካክሎ ተጠለለ? በማናቸው ዕለት ከፈጠራቸው መላእክት ጋር ተካክሎ እግዚአብሔር በላ? በማናቸው ዕለት ከአዳም ልጆች ወገን ሰው ወደ ፈጣሪው በለመነ ጊዜ መላእክቱ ከፈጣሪያቸው ከእግዚአብሔር ጋር ተካክለው እንዲኽ አድርግ መቼ አሉ? አንተ ሥላሴን የካድኽ ከሓዲ ፍጡራን መላእክትን ፈጣሪ ከኾኑ ከሥላሴ ጋር በመተካከል እንዲሰገድላቸው ለምን ታመጣቸዋለኽ? ፈጡራን መላእክትን ፈጣሪ ከኾኑ ከሥላሴ ጋር ተካክለው በአብርሃም ቤት እንደተጠለሉ፤ እግራቸውን እንደታጠቡ፤ ዐብረው እንደበሉ አድርገኽ ለምን ታስተካክላለኽ? አንተ ከእኛ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አንድነት የኾንኽ ክርስቲያን አንዱ እግዚአብሔር ነው፤ ኹለቱ መላእክት ናቸው አትበል) በማለት አስፍቶ ይጽፋል፨

✔❖በቤተ አብርሃም የገቡ ሥሉስ ቅዱስ ሆይ ዘወትር በቤተ ልቡናችን ውስጥ ግቡልን፨❖✔
[ለበለጠ ምስጢር "መልክአ ሥላሴ ንባቡና ትርጓሜው" መጽሐፌን ያንብቡ]፨
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ

️ #ስላሴ ማለት  ምን ማለት  ነው?✝️👉ስላሴ የሚለው ቃል ሰለሰ ሶስት አደረገ ካለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ሶስትነት ማለት ነው።✝️👉ቅድስት ስላሴ ለስላሴ ቅድስት ብለን እንቀ...
13/07/2025

️ #ስላሴ ማለት ምን ማለት ነው?
✝️👉ስላሴ የሚለው ቃል ሰለሰ ሶስት አደረገ ካለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ሶስትነት ማለት ነው።
✝️👉ቅድስት ስላሴ ለስላሴ ቅድስት ብለን እንቀጽላለን። ቅድስት ስላሴ ማለት ልዩ ሶስትነት ማለት ነው።
ይሕም ሶስት ሲሆን አንድ አንድ ሲሆኑ ሶስት ስለሚሆኑ ልዩ ሶስትነት ተብሏል ።
✝️👉ስለዚህ ነገር መጽሐፈ ቅዳሴያችን ስላሴ ሶስት ናቸው ስንል እንደ አብርሃም እንደ ይስሐቅ እንደ ያዕቆብ ማለታችን አይደለም ሶስት ሲሆኑ አንድ ናቸው እንጂ አንድ ናቸውም ስንል ቀዳሚ ሆኖ እንደ ተፈጠረው እንደ አዳም ማለታችን አይደለም አንድ ሲሆኑ ሶስት ናቸው እንጂ ። / ቅዳሴ ማርያም /
✝️👉ቅድስት ተብሎ በሴት አንቀጽ መጠራቱ ደግሞ እናት ለልጆ ስለምታዝን እና ስለምትራራ ስላሴም ለፍጥረታቸው ምሕረታቸው ዘለዓለማዊ ነው እና ቅድስት ይባላል ።
✝️👉በዚህ መሰረት ምስጢረ ስላሴ ማለት የአንድነት የሶስትነት ሚስጥር ማለት ነው። ይኸውም
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም ፤ በአካል ፤ በግብር ሶስት ሲሆኑ
በባሕርይ ፣ በሕልውና ፣ በመለኮት ደግሞ አንድ ናቸው።
✝️👉እነዚህ ባለ ድንቅ ነገር አንድ ሲሆኑ ሶስት ሶስት ሲሆኑ አንድ ይባላሉ ።
✝️👉ይህም ልዩ ሶስትነት ረቂቅ እና በሰው አእምሮ የማይመረመር ስለሆነ ሚስጥር ይባላል ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

✝️👉 በስም
✝️👉 በአካል
✝️👉 በግብር ነው።
እንደምን ነው ቢሉ
✝️👉አብ
✝️👉ወልድ
✝️👉መንፈስ ቅዱስ ነው።
እንደምን ነው ቢሉ
✝️👉 አብ የራሱ የሆነ
✝️ፍፁም መልክ
✝️ፍፁም ገጽ
✝️ ፍፁም አካል አለው።
✝️👉 ወልድ የራሱ የሆነ
✞ ✝️ፍፁም መልክ
✞ ✝️ፍፁም ገጽ
✞ ✝️ፍፁም አካል አለው።
✝️👉 መንፈስ ቅዱስም የራሱ የሆነ
✞ ✝️ፍፁም መልክ
✞ ✝️ፍፁም ገጽ
✞ ✝️ፍፁም አካል አለው።
እንደምን ነው ቢሉ
✝️👉 አብ ወላዲ፣አሥራፂ
✝️👉 ወልድ ተወላዲ
✝️👉 መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ ነው።
ይኸውም፦
✝️አብ ወልድን ቢወልደው መንፈስ ቅዱስን ቢያሠርፀው ነው እንጂ አይወለድም አይሠርፅምም።
✝️ወልድ ከአብ ቢወለድ ነው እንጂ አይወልድም አያሠርፅም አይሠርፅምም።
✝️መንፈስ ቅዱስም ከአብ ቢሠርፅ ነው እንጂ አይወልድም አይወለድም አያሠርፅምም።
እንደምን ነው ቢሉ
✝️👉 በአገዛዝ
✝️👉 በሥልጣን
✝️👉 በባሕርይ/በሕልውና/በሕላዌ
✝️👉 በመለኮት
✝️👉 በፈቃድ
✝️👉 በመንግሥትነት
✝️👉 ዓለምን አሳልፎ በመኖር አንድ ናቸው።
ይኸውም፦
✝️👉አብ አምላክ ነው ወልድ አምላክ ነው መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው ነገር ግን ሦስት አምላክ አይባልም አንድ አምላክ ይባላል እንጂ። ምክንያቱም፡- የሦስቱ ባሕርይ/ ሕላዌ፣ የሦስቱም አካላት መለኮት[አምላክነት] አንድ ብቻ ነውና። በዚሁ መሰረት ሥላሴ [እግዚአብሔር] በሥም ሦስት ስለሆነ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይባላል። በመለኮት ግን አንድ ብቻ ስለሆነ አንድ አምላክ አንድ ፈጣሪ አንድ እግዚአብሔር እንላለን።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
✝️👉እንድናመልከው ዘንድ የፈጠረን እግዚአብሔር ይመስገን።
የሥላሴ ጠብቆቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ፀንቶ ይኑር አሜን።
የቅድስት ስላሴ ይቅርታቸውና ሀብተ ረድኤታቸው አይለየ

 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስምሐምሌ ስድስት በዚች ቀን እንደ ርሱ ያሉ ኤልያስና ኄኖክ ወደ አሉባት ብሔረ ሕያዋን   ዕርገት ሆነ፣   አረፈች፣ ጳውሎስ የተባለ   በ...
13/07/2025



አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሐምሌ ስድስት በዚች ቀን እንደ ርሱ ያሉ ኤልያስና ኄኖክ ወደ አሉባት ብሔረ ሕያዋን ዕርገት ሆነ፣ አረፈች፣ ጳውሎስ የተባለ በሰማዕትነት ሞተ፣ የቅዱስ አብሮኮሮንዮስ እናት በሰማዕትነት ሞተች፣ የገርአልታው መታቢያቸው ነው፣ ሐዋርያው መታሰቢያ ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞



ሐምሌ ስድስት በዚች ቀን እንደ እርሱ ያሉ ኤልያስና ኄኖክ ወደ አሉባት ብሔረ ሕያዋን የዕዝራ ዕርገት ሆነ። ይህም ነቢይ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ የሚጽፍ ነበረ እርሱም ከሌዊ ወገን ነበረ። ከእግዚአብሔርም ጋራ ግሩም የሆነ ነገርን መናገር ጀመረ እንዲህም አለ ምድርን በፈጠርካት ጊዜ አዳምን ታስገኝ ዘንድ አዘዝካት አስገኘችውም።

ሁለተኛው የጥፋት ውኃ በጊዜው እንደ መጣና ሁሉን እንዳጠፋ ተናገረ ኖኅ አብርሃምና ዳዊት እንዴት እንደ ተመረጡ ደግሞ ተናገረ። ዳግመኛም ነፍስ ከሥጋዋ እንደምትወጣና ሰባት ቀኖች እንደምትዞር ከዚያም በኋላ እንደ ሥራዋ ወደተዘጋጀላት ቦታዋ እንደምትገባ ተናገረ።

ከዚያም ስለ ፍርድ ቀን ተናገረ። ከእግዚአብሔር ከጌትነቱ ብርሃን በቀር ፀሐይና ጨረቃ መብራትና ብርሃንም እንደሌሉ ተናገረ። ዳግመኛም በልቧ እጅግ በምትጨነቅ በምታዝንና በምትተክዝ ሴት አምሳል ጽዮንን አያት ልብሶቿም የተቀደዱ ነበሩ ልጇም ወደ ጫጕላው ቤት በገባበት ቀን እንደሞተ ነገረችው። ከዚህም በኋላ እርሷን ከማየቱ የተነሣ ፈርቶ በድንጋፄ እስከ ወደቀ ድረስ ፊቷ በድንገት እንደ መብረቅ በራ።

ደግሞም ዐሥራ ሁለት ክንፎችና ሦስት ራሶች ያሉት ንስር ከባሕር ሲወጣ ከክንፎቹም ውስጥ ራሶች ሲወጡ አየ እኒህም በየዘመናቸው ገዝተው የጠፉ ነገሥታት ናቸው። ደግሞም ስለ መድኃኒታችን ክርስቶስ መወለድ ተናገረ እንዲህም አለ። አንበሳ እያገሣ ከበረሀ ወጣ በሰው አንደበትም ሲናገር ንስሩንም ሲገሥጸው ሰማሁት አለ።

ዳግመኛም ስለ ክርስቶስ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ። በሌሊት ታላቅ ነፋስ ከባሕር ሲወጣ አየሁ ከማዕበሉ የተነሣ ባሕሩ ይታወክ ነበር ነፋሱም እንደ ሰው አምሳል ሁኖ ከባሕር ሲወጣ አየሁ። ደግሞም ከብዙ ኃይልና ክብር ጋር በሰማይ ደመና ማረጉን በአብ ቀኝ መቀመጡንም አይቶ ተናገረ።

ዳግመኛም በፈሳሹ ማዶ ያኖራቸው ዘጠኙ ነገድ እንደሚሰበሰቡ ተናገረ። ከዚህም በኋላ የነቢያት መጻሕፍትና የአባቶችን ትውልድ የያዙ መጻሕፍት ተደምስሰው መጥፋታቸውን በአሰበ ጊዜ ወደ በረሀ ገብቶ በጾምና በጸሎት ምሕላ ያዘ። ከእርሱም ጋር አምስት ጠቢባን ጸሐፊዎችን ወሰደ።

ከዕንጨቱም አንጻር ቃል ጠርቶት ዕዝራ አፍህን ክፈት ብሎ ኅብሩ እሳት የሚመስል ውኃን የተመላ ጽዋን ሰጠው። ያንንም ጽዋ ጠጣ ያን ጊዜም ልቡናው ጥበብን አገሣ። ተገልጾለትም መጻሕፍትን ሁሉ ሰበሰበ ለእነዚያም ሰዎች ልዑል አምላክ ዕውቀትን ሰጣቸው። መጻሕፍትንም ሁሉ በየተራቸው ጻፉ። በዚያም አርባ ቀን ኖሩ እነዚያ ግን ቀን ቀን ይጽፋሉ ማታ ማታም ይመገባሉ እርሱ ግን ቀን ይጽፋል ማታም ዝም አይልም በእነዚያ አርባ ቀኖችም ሁሉ መጻሕፍት ተጻፉ።

ከዚህም በኋላ ልዑል እንዲህ ሲል ተናገረው የዕውቀት ምሥጢር የጥበብም ምሥጢር እንደ ፈሳሽ ውኃም ያለ ዕውቀት ላላቸው ታስተምራቸው ዘንድ ይህን ተመልከት እንዳለውም አደረገ። በአራተኛውም ዘመን ከሚቈጠሩ ከብዙ ሱባዔ በአምስተኛው ሱባዔ ይህ ዓለም ከተፈጠረ ከአምስት ሺ ዘመን በኋላ ጨረቃ ሠርቅ አድርጋ ጨለማዋን ባጣች በአሥረኛው ቀን በሦስተኛው ወር በዘጠና አንድ እንደእርሱ ያሉ ደጋግ ሰዎች ወዳሉበት ዕዝራን ወሰዱት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞



በዚህችም ዕለት ቅድስት ንስተሮኒን አረፈች። እርሷም ከኢየሩሳሌም ሰዎች ውስጥ ነበረች። እርሷም አስቀድማ ኃጢአተኛ ነበረች ከዚያም በኋላ ንስሓ ገብታ ወደ እግዚአብሔር በተቃጠለ ልብ ተመለሰች የሥጋን ፍላጐቶች ሁሉ ናቀች እመምኔት እስከ ሆነች ድረስ በበጎ ሥራ ሁሉ ትሩፋትንና ተጋድሎን አበዛች።

እኅቶችም ከገድል ብዛትና ምግብን ከመተው የተነሣ ሥጋዋ እንዳለቀ አይተው ሥጋሽን እንድትረጂ ጥቂት እህል በወጥ ብዪ አሏት። አብዝተውም ግድ ባሏት ጊዜ ልጆቼ ሆይ ወደ ቀድሞ ልማዴ እንዳልመለስ ጥቂት ወጥ ስለመብላት አትድከሙ ስለዚህ ወጥ አልበላም አለቻቸው። ከዚህ በኋላ በሰላም አረፈች።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞



በዚህችም ዕለት ጳውሎስ የተባለ ቅዱስ መርቄሎስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ ነው። እርሱም ሐዋርያትን አገልግሎአቸዋል። ወንጌልንም ለመስበክ ከእነርሱ ጋር ሔደ። የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስን መልእክቶች አደረሰ በመከራውም ጊዜ አገለገለው። ከእርሱም ጋር መከራ ተቀበለ ከእርሱም አልተለየም።

ወደ ሮሜ አገርም ከርሱ ጋር ገብቶ ቅዱስ ወንጌልን አስተማረ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን ከአረማውያን ብዙዎቹን መለሳቸው። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስም በሰማዕትነት በሞተ ጊዜ ይህ ረድእ መርቄሎስ መጥቶ ከመስቀል ላይ አወረደው በከበሩ ልብሶችም ከሽቱ ጋር ገነዘው። በሣጥንም አድርጎ ከምእመናን በአንዱ ቤት አኖረው።

የሐዋርያው ጴጥሮስ ደቀ መዝሙርም እንደሆነ በኔሮን ዘንድ ወነጀሉት ንጉሡም ወደ እርሱ አቅርቦ ጠየቀው እርሱም ለሐዋርያው ጴጥሮስ ደቀ መዝሙሩ እንደሆነ አመነ ደግሞም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕውነተኛ አምላክ እንደሆነ ታመነ።

ስለዚህም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ገረፈውም ዘቅዝቀው ሰቅለውም ከበታቹ ጢስን አጤሱበት። ከዚህም በኋላ ንጉሡ እንዴት ሁነህ መሞት ትሻለህ በምን አይነት ሞት ልግደልህ ንገረኝ አለው። ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰ እኔ ሕይወት በሆነ በክርስቶስ ስም መሞት እሻለሁ አንተ ግን በፈለግኸው ዓይነት ግደለኝ ፈጥነህም ወደ ፈለግኸው አድርሰኝ።

ያን ጊዜም ንጉሡ ኔሮን እንዲገርፉትና እንደ መምህሩ ጴጥሮስ ዘቅዝቀው እንዲሰቅሉት አዘዘ እንዲሁም አደረጉበት። የሰማዕታትንና የሐዋርያትን አክሊል ተቀበለ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞



በዚህችም ቀን የቅዱስ አብሮኮሮንዮስ እናት ገድለኛዋ ቴዎዳስያ በሰማዕትነት ሞተች፡፡ ከእርሷ ጋርም ሁለት መኳንንቶችና አሥራ ሁለት ሴቶች በሰማዕትነት ሞቱ።

ይህም እንዲህ ነው ይቺ ቅድስት ልጇ አብሮኮሮንዮስን ክርስቲያን ነው ብለው እንደወነጀሉትና ለሞት እስቲደርስ ጽኑዕ ሥቃይን እንዳሠቃዩት ሰማች። ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በዚያች ሌሊት ተገለጠለት ከሥቃዩም አዳነው ያለ ምንም ጉዳት ጤናማ ሆነ።

እኒህ ሁለቱ መኳንንትና ዐሥራ ሁለት ሴቶች ከእናቱ ጋር በአዩት ጊዜ እጅግ አደነቁ እንዲህ ብለውም ጮኹ እኛ በአብሮኮሮንዮስ አምላክ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን መኰንኑም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የክብር አክሊልን ተቀበሉ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞



ዳግመኛም በዚህች ዕለት የገርአልታው አቡነ አብርሃም መታቢያቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ሲሆኑ የትውል ሀገራቸው ትግራይ ነው፡፡ በሥርዓተ ገዳማትና በሥርዓተ ቀኖና ዐዋቂነታቸው ወደር የማይገኝላቸው አባት ናቸው፡፡ ከመጀመሪያዎቹ የኢትዮጵያውያን ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በስማቸው የተሠራው ገዳም በትግራይ ገርዓልታ የሚገኝ ሲሆን አጽቢ መንበርታ ደብረ ጽዮን አቡነ አብርሃም ገዳም ይባላል፡፡ ስለ አቡነ አብርሃም ከዚኽ ያለፈ ዝርዝር መረጃ ማግኘት አልተቻለም፡፡ በገዳማቸው ያሉ አባቶችም የጻድቁን የዕረፍታቸውን ቀን ከመጠቆም ያለፈ ነገር ለመናገር ገድሉ የላቸዉም፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞



በዚህች ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ መታሰቢያ ነው፡፡ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ የደረሰው አልዋሕ በሚባል አገር ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊያደርሰው አብረው ወደ አልዋሕ ሄዱ፡፡ ወደ ከተማው ለመግባት ምክንያት ፈለጉና ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ በርተሎሜዎስን ‹‹አትክልተኛ ባለሙያ ነው›› ብሎ የወይኑን ቦታ እንዲጠብቅለት ለአንድ ባለጸጋ መኰንን ባሪያ አድርጎ ሸጠው፡፡ ባለጸጋውም በርተሎሜዎስን በ30 እስቴታር ገዝቶት ሄደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ገንዘቡን ደብቆ ለቅዱስ በርተሎሜዎስ በድብቅ ሰጥቶት እንዲመጸውተው ነግሮት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፡፡ አልዋሕ ከገባ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ የወይን ቦታው አለቃ ሆኖ 40 ቀን ተቀመጠ፡፡ ወንጌሉን ባለመስበኩ በሀዘን እያለቀሰ ጌታችንን በጸሎት ጠየቀው፡፡ በገንዘቡ ገዝቶት ባሪያው ያደረገው ባለጸጋውም የወይኑን ቦታ ያይ ዘንድ እንደመጣ መርዘኛ እባብ ነድፎት ሞተ፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ሲያለቅስ በርተሎሜዎስ ግን ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ሄዶ ባለጸጋውን ሰው ከሞት አስነሣው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ሁሉ አምነው ተጠምቀዋል፡፡

በርተሎሜዎስም ወደ ሌሎች አገሮች ሄዶ አስተማረ፡፡ ጌታችን ወደ በርበሮች ዘንድ ሄዶ ወንጌልን እንዲሰብክ አዘዘው፡፡ ረዳት እንዲሆነውም እንድርያስን ከደቀ መዝሙሩ ጋር ላከለት፡፡ የሀገሪቱ ሰዎች ግን እጅግ ክፉዎች ነበሩ፡፡ በሐዋርያቱም ፊት በአስማት አስደናቂ ተአምራት እያሳዩ ትምህርታቸውን የማይቀበሏቸው ሁኑ፡፡ ይህን ጊዜ ጌታችን ሰውን ከሚበሉ አገር አንዱን ገጸ ከልብ ይታዘዝላቸው ዘንድ በሚያዙትም ነገር ሁሉ ከትእዛዛቸው እንዳይወጣ አዘዘው፡፡ ሐዋርያትም ወደ በርበሮች አገር ዳግመኛ በገቡ ሰዓት ይበሏቸው ዘንድ ኃይለኛ አራዊትን አውጥተው ለቀቁባቸው፡፡ ያ ገጸ ከልብም በአራዊቱ ላይ ተነሥቶ እየነጠቀ በላቸው፡፡ ይህንንም የተመለከቱት በርበሮች እጅግ ፈርተው በድንጋጤ ብቻ የሞቱ አሉ፡፡ በሐዋርያቱም እግር ሥር ወደቁ፡፡ ሐዋርያቱም አስተምረው ካሳመኗቸው በኋላ አጥምቀዋቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ እግዚአብሔርን ወደማያውቁ አገሮች ሄዶ ብዙ ተአምራትን እያደረገ አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ የከሃዲው ንጉሡ የአግሪጳን ሚስትም ትምህርቱን ሰምታ በጌታችን አመነች፡፡ ንጉሡ አግሪጳም በዚህ እጅግ ተቆጥቶ ቅዱስ በርተሎሜዎስን ብዙ ካሠቃየው በኋላ አሸዋ በተሞላ ትልቅ ከረጢት ውስጥ ከቶ ከነሕይወቱ ባሕር ውስጥ እንዲጥሉት አደረገ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን አውጥተው በክብር ቀብረውታል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ ይኽች ዕለት መታሰቢያ በዓሉ እንድትኾን አባቶቻችን አዘዋል፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

( እና )

 #ቁስቋም - እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወደደ ልጇን አዝላ ወደ ግብጽ የተሰደደችበት እለት ነወ ይህ በምስሉ የምንመለከተው ከመዐዲ ወደ ላዕላይ ግብጽ በጀልባ ከካይሮ በስተደቡብ 3...
13/07/2025

#ቁስቋም - እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወደደ ልጇን አዝላ ወደ ግብጽ የተሰደደችበት እለት ነወ

ይህ በምስሉ የምንመለከተው ከመዐዲ ወደ ላዕላይ ግብጽ በጀልባ ከካይሮ በስተደቡብ 320 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በላዕላይ ግብጽ የሚገኘው እመቤታችን ከተወደደ ልጇ እንዲሁም ከአረጋዊው ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ጋር ያረፈችበት ደብረ ቁስቋም ገዳም ነው።

ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዛሬዋ በዕረፍታቸው ዕለት ያደረጉት ተአምር ይህ ነው፡- ቅዱስ ጳውሎስ ኔሮን የሞት ፍርድ ፈርዶበት ሳለ ሊሰይፉት ሲወስዱት የኔሮን ወገን አንዲት ብላቴና ቅዱ...
12/07/2025

ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዛሬዋ በዕረፍታቸው ዕለት ያደረጉት ተአምር ይህ ነው፡- ቅዱስ ጳውሎስ ኔሮን የሞት ፍርድ ፈርዶበት ሳለ ሊሰይፉት ሲወስዱት የኔሮን ወገን አንዲት ብላቴና ቅዱስ ጳውሎስን አገኘችው፡፡ በጌታችንም አመነች፡፡ ስለ ጳውሎስም አለቀሰች፡፡ እርሱ ግን ‹‹መጎናጸፊያሽን ስጪኝ እኔም ዛሬ እመልስልሻለሁ›› አላትና ሰጠችው፡፡ ራሱ ወደሚቆረጥበት ቦታም ሄዶ ለሚሰይፈው ወታደር ራሱን አዘንብሎ ካዘጋጀለት በኋላ ፊቱን በመጎናጸፊያው ሸፈነው፡፡ ሰያፊውም የቅዱስ ጳውሎስን ራስ ቆርጦ በዚያች ብላቴና መጎናጸፊያ እንደተሸፈነ ጣለው፡፡ ሰያፊውም ለንጉሡ ሊነግረው በተመለሰ ጊዜ ያቺ ብላቴና አገኘችውና ‹‹ያ ጳውሎስ ወዴት አለ?›› አለችው፡፡ ወታደሩም ‹‹ራስ የሚቆረጥበት ቦታ ወድቋል፣ ራሱም በመጎናጸፊያሽ ተሸፍኗል›› በማለት ያደረገውንና የሆነውን ነገር ነገራት፡፡ እርሷም መልሳ ‹‹ዋሽተሃል፣ እነሆ ጴጥሮስና ጳውሎስ በዚህ ዘንድ አልፈው ሄዱ፤ እነርሱ የመንግሥት ልብሶችን ለብሰዋል፤ በራሳቸውም ላይ በዕንቁ የተጌጡ አክሊላትን አድርገዋል፤ መጎናጸፊያዬንም ሰጡኝ፤ አነኋት ተመልከት›› ብላ አሳየችው፡፡ ለሰያፊውና ከእርሱ ጋር የነበሩትም ወታደሮች ሁሉ አሳየቻቸው፡፡ አይተውም እጅግ አድንቀው ‹‹በጴጥሮስና በጳውሎስ አምላክ አመነናል›› እያሉ ስለ ጌታችን መስክረው እነርሱም ሰማዕት ሆኑ፡፡
+ + +

ክብርት እመቤታችን ለሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስለጌታችን ስም መከራን እንደሚቀበል አስቀድማ እንደነገረችው የሚናገር ተአምር ይህ ነው፡- ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በቆሮንቶስ መልእክቱ (2ኛ ቆሮ 12፡ 2) እንደተናገረው መላእክት እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ አሳርገውት ሳለ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ስለጸናች ስለክብርት እመቤታችን እንዲህ አለ፡- ‹‹እኔ ጳውሎስ ገና አብያተ ክርስቲያናትን በማፈራርስበትና የጌታን ደቀ መዛሙርት ለመግደል በማሳድድበት ጊዜ ይልቁንም በየመንደሩ እየገባሁ ሴቶችንም ወንዶችንም እየጎተትኩ ወደ ሥስር ቤት በምጨምርበት ወቅት እነሆ ከዚያ ምእመናንን እያደንኩ የምይዝበት የሥልጣን ደብዳቤ ይዤ ወደ ደማስቆ ስጓዝ ድንገት ከሰማይ የብርሃን ጸዳል አንጸባረቀብኝ፡፡ በዚኽም ጊዜ በምድር ላይ ወደቅሁና እነሆ በሰው ልጅ አንደበት ሊነገር ሊተረጎም የማይቻል ቃል ሰማሁ፡፡ ከእኔ ጋር ቆመው የነበሩ ሰዎች ድምፁን ከመስማት በቀር ማንንም አላዩም፡፡ በመሬትም ላይ ወድቄ እየተፍገመገምኩ ሳለሁ እኔን ጭንጋፍ የሆንኩ ሰው መላእክት መጥተው አጽናኑኝ፤ አንሥተውም እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ አሳረጉኝ፡፡ በዚያን ጊዜም የደም ግባቷ እንደፀሐይ የሚያበራ ድንግል ከሩቅ ስትመጣ ተመለከትኩ፡፡ ከእርሷም ጋር ብዙ ቅዱሳን መላእክት ከፊት ከኋላዋ ሆነው እየዘመሩ መጡ፡፡ ከእኔም ጋር ያለውን መልአክ ‹በዚህን ያህል ክብር ከብራ የምትመጣ ይኽች ማናት?› አልኩት፡፡ መልአኩም ‹ይኽች አንተ የምታሳድደው የናዝሬቱ የኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ማርያም ናት› አለኝ፡፡ በዚያን ጊዜም ወደእኔ መጣችና ሰላም ካለችኝ በኋላ ‹ሳውል ሳውል ልጄን የናዝሬቱ ኢየሱስን ለምን ታሳድደዋለህ? የሾለውን ብረት ብትረግጥ ለአንተ ይብስብሃል› አለችኝ፡፡ እኔም እየፈራሁና እየተንቀጠቀጥኩ ‹እመቤቴ ሆይ! ስለ ኃጢአቴ ምን አደርግ ዘንድ ይገባኛል? የሰው ደም እያፈሰስኩ ወንጀለኛ ሆኛለሁና አሁንም እመቤቴ ሆይ! ኃጢአቴን ይቅር በይልኝ እነሆ አንቺ የኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ እንደሆንሽ ተገልጦልኛልና› አልኩ፡፡ እርሷም ‹እነሆ ኃጢአትህ ይሠረይልህ ዘንድ ስለለመንኩልህ ኃጢአትን ይቅር ብሎሃል፡፡ አሁንም በሕይወተ ሥጋ ሣለህ ወደዚህ ትመጣ ዘንድ ልጄን ማለድኩት፡፡ እርሱም ‹እሺ ጥቂት ታገሺ አመጣዋለሁ› አለኝ፡፡ ‹ይልቁንም ልጄ ወዳጄ ሆይ አታዘግኝብኝ ፈጥኖ ልታመጣው እወዳለሁ በእርሱ የትምህርት ዘመን ስምህ እጅግ እንዲመሰገን ታውቃለህና› አልኩት፡፡ ልጄ ወዳጄም ‹አዎን እናቴ ሆይ! በአሕዛብና በነገሥታት በእስራኤልም መካከል የሞቴን መስቀል ተሸክሞ በጣፈጠ አንደበቱ በቀለጠፈ አነጋገሩ በታማኝነቱ የወንጌልን መንግሥት ያስተምር ዘንድ የተመረጠ አርበኛ አድርጌ እልከዋለሁ› አለኝ፡፡ ‹በስሜ ብዙ መከራ ይቀበል ዘንድ አለው› ብሎሃልና ስለዚህ በሥላሴ ስም ተጠመቅ፣ እነሆ አሁንም ቅዱሳኖች ሁሉ ታላቅ አቀባበል ያደርጉልሃል› አለችኝ፡፡›› (ባለ 270ው ተአምረ ማርያም ገጽ 335)

የቅዱስ ጳውሎስ እመቤት የአምላክ እናት ክብርት እመቤታችን እኛንም ለልጇ መንግሥት የተዘጋጀን ታድርገን! ምልጃዋ አይለን!
+ + +

(የቤተክርስቲያኑ ፎቶ፦ ልዩ ስሙ አዲቃሾ በሚባለው ቦታ የሚገኘው የብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ ነው።)

የከበሩ ሐዋርያት የብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

🌹እንኳን አደረሳችሁ ሐምሌ 5 (፭) የፃድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው።     ➦ ሐምሌ 5 ለጻድቁ አባታችን ድንግል ማርያም የብርሃን ዐይን የተከለችለት እ...
11/07/2025

🌹እንኳን አደረሳችሁ ሐምሌ 5 (፭) የፃድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው።

➦ ሐምሌ 5 ለጻድቁ አባታችን ድንግል ማርያም የብርሃን ዐይን የተከለችለት እለት ነው! ይኸውም ጻድቁ አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዝቋላ ምድር ስለእትዮጵያ ሕዝብ ኃጢአት በባህር ቁልቁል ተዘቅዝቀው በመጸለያቸው #እግዚአብሔርም ይህን ጸሎታቸውን በመቀበል የኢትዮጵያን ሕዝብ እምርልሃለሁ ብሎ ስሙን ለጠሩ ዝክሩን ለዘከሩ የምሕረት ቃል ኪዳን ከሳቸው ጋር ካደረገ በኃላ ወደ ምድረ ከብድ ላከው። አባታችን #ገብረ #መንፈስ #ቅዱስም በምድረ ከብድ እንደ አምድ ተክል ሆኖ ሰባት አመት ቅንድቡን ሳይከድን፤ ራሱን ወደ ምድር ዝቅ ሳያደርግ እጆቹን እንደዘረጋ ወደ ሰማይ እየተመለከተ ሰባት አመት ቆዬ። በዚህ የሰውን ጸሎትና #የእግዚአብሔርን ምሕረት የምቃወም ጠላት ዲያብሎስ በአባታችን የጸሎት ጽናት በመቅናት ጸሎታቸውን ልያቋርጥ በቁራ ተመስሎ ወደ እሳቸው ጋ መጣና "ውኃ ጠምቶኛል ቀድተህ አጠጣኝ" ስላቸው አባታችንም "ጸሎቴን አቋርጬ አንተን ውኃ አላጠጣም ና ከአይኔ ጠጣ" ብሎ አዘዘው። በመጽሐፍ "ሳታቋርጡ ጸልዩ" ተብሎ እንደተጻፈ ( #1ኛ.ተሰሎንቄ.5፥17)። ቁራውም ከአይናቸው ልጠጣ እንደመጣ መስሎ አይናቸውን ወጋው! ጸሎት አቋርጦ በሁለት ዐይን ገሃነም ከምገቡ ጸሎትን ባለማቋረጥ በአንድ ዐይን መንግሥተ ሰማያት መግባትን ሽተዋልና። #ጌታችንም በወንጌሉ "ሁለት ዐይን ኖሮህ ገሃነም ከምትገባ አንድ ዐይን ኖሮህ ወደ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ይሻላል" ብሎአልና ( #የማርቆስ.ወ.9፥47።) አባታችን #ገብረ #መንፈስ #ቅዱስም በጽናታቸው ሰይጣንን ድል ነሱት። ከፈተና መዳን የምንችለው ፈተና ውስጥም መግባት ከገባንም መውጣት የምንችለው በጸሎት ስንተጋ ነውና #(ሉቃስ.ወ.22፥40)። #ጌታችን #አምላካችን #መድኃኑታችም #ኢየሱስ #ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ዲያብሎስን ድል እንዳደረገው ( #ማቴ.ወ 4፥1-11)። ጻድቁ ሰው ኢዮብም ከሰይጣን ጋር በመታገል ድል እምደነሳው #(መ.ኢዮብ 1) አባታችንም ዲያብሎስን በጸሎት ጽናት ድል ነስተውታል። ሐምሌ 5/፭ ቀን #እመቤታችን ለአባታችን የብርሃን ዐይን አምጥታ ተከለችለት።

የቅዱሳን መታሰብያቸው ከበረከት ጋር ለዘለዓለም ነውና የቅዱሳን ሀገር፣ የክርስትና መድና፣ ሀገሬ #እግዚአብሔር የሆነች እትዮጵያ #ቅዱሳንን ከማክበር በተጨማሪ #ቅዱሳን የምወለዱባት #ጻድቃን የምጠጉባት ሀገር ናት። ቅድስና ቅዱስ የሆነው #እግዚአብሔርን ቅዱስ እንደሆኔ በቅድስና ቅዱስ የምንሆንበት ሕይወት ነው። "እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" እንዳለን #(ኦ.ዘሌዋ 20፥7)። #ቅድስና የምታልፈውን አለም ንቆ የማታልፈውን ዘላለማዊ ሕይወት መናፈቅ ነው፤ #ቅድስና ራስን #ለእግዚአብሔር ነጥሎ ማውጣት, መለየት ነው። #ቅድስና አለም በሞቷ በምትገዛው ከካራን መውጣት #(ኦ.ዘፍጥረት.12፥1) ወተትና ማር የምታፈልቀው #የእግዚአብሔርን መንግሥት ከናአንን መናፈቅ ነው። የ #ቅዱሳን ሁሉ #አምላክ #ቅዱስ የሆነው #እግዚአብሔር ለእኛ ለኃጢአተኞችም የቅድስናን ሕይወት ያድለን። አሜን
የአባታችን በረከት ረድኤት ይደርብን ቃል ኪዳናቸው ይጠብቀን።አሜን አሜን አሜን 🤲🤲🤲

በዓታ ለማርያም እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከአባቷ ከኢያቄምና ከእናቷ ሐና ሐምሌ 30 ራእይ አይተው ነሐሴ 7 በብስራተ መልአክ በፈቃደ እግዚአብሔር እሑድ ተፀነሰች፥ በእናቷ ማህፀን ሳለ...
09/07/2025

በዓታ ለማርያም
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከአባቷ ከኢያቄምና ከእናቷ ሐና ሐምሌ 30 ራእይ አይተው ነሐሴ 7 በብስራተ መልአክ በፈቃደ እግዚአብሔር እሑድ ተፀነሰች፥ በእናቷ ማህፀን ሳለች ብዙ ተዓምራትን አድርጋለች የሞተውን ሳሚናስ ከሙት አስነስታዋለች ይህም ሳሚናስ የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ከአጎቱ ቤት ሄዶ የሞተው ለቀብር ሲወስዱት ከመንገድ ባሳረፉት ጊዜ ሐናም የአጎትዋ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ እርሷም እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነሥቶ ስብሐት ለኪ እሙ ለፀሐይ ጽድቅ ማርያም ሆይ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሐ ቤቱ ተፈሥሒ ደስ ይበልሽ ብሎ ሰገደላት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በእናቱ በኤልሳበጥ ማህፀን ሳለ ለእናታችን ማርያም እንደሰገደላት ሰላም ለኪ እንዳላት {ሉቃ1፥41} ይህም የሞተው ሳምናስ ከሞተበት ተነስቶ ሰገደላት ይህንን ታምራት ስትሰራ በሐና ማህፀን 9 ወር ተቀመጠች ግንቦት መባቻ ዕለት ግንቦት 1 ሊባኖስ በምትባል አካባቢ ተወለደች፥ በስምንተኛውም ቀን ስሟን ማርያም ብለው አወጡላት እናታችን ማርያም በእናት አባቷ ቤት 3 ዓመት ተቀመጠች።
መዝሙረኛው ዳዊት አባቷ በ { መዝ 44፥10-11} ላይ ልጄ ሆይ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን የአባትሽንም ቤት እርሺ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና እርሱ ጌታሽ ነውና" እንዳለ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ3 ዓመቷ የስለት ልጅ ናትና ቤተመቅደስ ወስደው ለካህኑ ለዘካርያስ ሰጧት ቀኑም የታህሳስ በዓታ ነበር። መልአኩ ፋኑኤል ከሰማይ በመሰቦ ወርቅ ህብስተ ሰማያዊ በብርሃን ጽዋ ስቴ ሕይወት ይዞ ረቦ ታያቸው እመቤታችንንም በአንዱ ክንፍ ጋርዶ በአንዱ ክንፉም አጎናፅፎ ህብስቱን አብልቷት ወይኑን አጠጥቷት እመቤቴ ሆይ! መንገድ ባስመታሁሽ ማሪኝ ብሎ የብርሃን መሶብ የብርሃን ጽዋ ይዞ ወደ ሰማይ ዐረገ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ህብስተ ሰማያዊ እየተመገበች ስቴ ሕይወት እየጠጣች ከንጹሓን ይልቅ ንጽሕት የሆንሽ አንቺ ነሽ ከማይነቅዝ ዕንጨት እንደ ተሠራ በወርቅ እንደተጌጠና ዋጋው ብዙ በሆነ በሚያበራ ዕንቁ እንደተለበጠ ታቦት በቤተ መቅደስ ውስጥ የኖርሽ የተመረጥሽ ድንግል ነሽ እንዳለ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ቁጥር 6 እንዲህ ሆና መላእክት ምግቧን እያመጡላት እየጎበኟት ከመላእክት ጋራ እየተጫወተች እየዘመረች 12 ዓመት በቤተ መቅደስ ተቀመጠች።
የእናታችን የድንግል ማርያም ምልጃ ጸሎት በረከቷ እረድኤቷ ቃል ኪዳኗ ከእኛ ከልጆቿ አይለየን እንዲሁ የአስራት ሀገሯ ከሆነች ከኢትዮጵያ ዘወትር አይለያት አይለየን አሜን።

 #የሕግ  #ታቦት  #አንቺ  #ነሽ!  #የብዙኃንም  #ልጅ  #ነሽ!"✔️[አባ ጊዮርጊስ በእንዚራ ስብሐት ዘቀዳሚት 160]✔️✔️  #1ኛ. " #የሕግ  #ታቦት  #አንቺ  #ነሽ:- የማሕፀንሽ...
09/07/2025

#የሕግ #ታቦት #አንቺ #ነሽ! #የብዙኃንም #ልጅ #ነሽ!"
✔️[አባ ጊዮርጊስ በእንዚራ ስብሐት ዘቀዳሚት 160]✔️

✔️ #1ኛ. " #የሕግ #ታቦት #አንቺ #ነሽ:- የማሕፀንሽ ፍሬ በአምላክ ቀኝ የተቀረጸ የሕግ ታቦት አንቺ ነሽ።" የእግዚአብሔር ቀኝ ወልድ የማሕፀንሽ ፍሬ የሆነ በታቦትነትሽም ያደረብሽ አንች ነሽ:: ይህም አንችነትሽ የእግዚአብሔር ሥራ ውጤት ነውና "ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።" ተባልሽ [መዝ 87:5]::

✔️ #2ኛ. " #እግዚአብሔር #የሚጐበኝሽ:- እግዚአብሔር ዘወትር የሚጐበኛት የእስራኤል ርስትም አንቺ ነሽ።" እስራኤል የተባሉት እስራኤል ዘሥጋ እና እስራኤል ዘነፍስ ናቸው:: የሁሉም ርስት የሁሉም እናት ናትና የሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ይጎበኛታል:: በትውልድም ያስመሰግናታልና "ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤" አለች [ሉቃ 1:48]::

✔️ #3ኛ. " #ያማረች #ምድር #አንች #ነሽ:- እንደ ግብጽ ምድር ያልሆነች ያማረች ምድርም አንቺ ነሽ።" የግብፅ ምድር የጥላቻና የግፍ ምድር ናት እርሷ ግን ግፍና ጥላቻ የለባትምና እንደ ተቀደሰች ቦታ ልዩ ናት ያማረችና የከበረችም ናት:: "አንተ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ አለው።" እንዲል [ዘጸ 3:5] የእግዚአብሔር ማደሪያ ድንግል እንደዝያች ቅድስት ቦታ ያለ'ች ናት::

✔️ #4ኛ. " :- ፍጹም የበረሃ ሀገር ጤናማ ዝናብም አንቺ ነሽ።" በረድና ዲን የተመላ ጤነኛ ያልሆነ የመአት ዝናም አለ:: አንች ግን ጤናማ የምሕረት ዝናም ነሽ:: በርሃማውንም ቦታ የምታረሰርስ በቂ ዝናም አንች ነሽ:: ዝናምነትሽም ለዘላለም የማያስጠማ የሕይወት ውኃ ኢየሱስ ክርስቶስን የያዘ ነው:: [ዮሐ 4:14]

✔️ #5ኛ. " :- እረፍት ለሚያደርግ የምታምር የቤት ውስጥ ዙፋን አንት ነሽ።" ቤተመቅደስ ስለገባች ታቦት ተባለች:: አንድም እንደ ታቦት የእግዚአብሔር ቃል [ወልደ እግዚአብሔር] ስላደረባት:: የእረፍት ዙፋን:- እንደ ሰንበት ለእግዚአብሔርና ለፍጥረታት እረፍት የሆነች ድንግል ናትና ሰንበተ ሰንበታት ትባላለች:: ከዙፋንም በላይ አካሏን አካሉ አድርጎታልና ሴት ያላት እርሷ ትበልጣለች:: [ዘፍ 2:23][ዮሐ 19:26]

✔️ #6ኛ. " #የብዙኃን #ልጅ #ነሽ:- በጥበብ የተሠራሽ በተግሣጽም ያደግሽ ድንግል ሆይ የብዙኃን ልጅ ነሽ።" የብዙዎችን አምላክ ወልደሽ የብዙኃን እናት እንደሆንሽ ሁሉ በብዙኃን መላእክት ምክርና ትምህርት ያደግሽ የብዙዎች ልጅ ነሽ:: የሰማይ መላእክት እየመገቡሽና የምድር ካህናት እያመሰገኑሽ በመቅደሱ ያደግሽ የብዙዎች ልጅ አንች ነሽ:: አብርሃም እንደ ማለት ሁሉ ማሪሃም ማለትም "የብዙኃን" ማለት ነውና:: [ዘፍ 17:5]

የእግዚአብሔር ልዩ ታቦት የድንግል በረከትና ፍቅር ይደርብን!
✔️ ፍ ቅ ረ ፍ ቅ ር ዘ ፍ ቅ ር✔️

‹‹ራጉኤል›› የስሙ ትርጓሜ የብርሃናት አለቃ ማለት ነው። የብርሃናት አለቃ ሲባል ፀሐይን፣ ጨረቃን እና ከዋክብትን በማመላለስና ለሰው ልጆች፣ ለአዝርዕት፣ ለእንስሳት፣ ለአራዊት ሁሉ ብርሃንን...
09/07/2025

‹‹ራጉኤል›› የስሙ ትርጓሜ የብርሃናት አለቃ ማለት ነው።

የብርሃናት አለቃ ሲባል ፀሐይን፣ ጨረቃን እና ከዋክብትን በማመላለስና ለሰው ልጆች፣ ለአዝርዕት፣ ለእንስሳት፣ ለአራዊት ሁሉ ብርሃንን የሚመግብ ነው ማለት ነው።

ቅዱስ ራጉኤል በብርሃናት ላይ የተሾመ መልአክ ነው፤ በዚህም "መጋቤ ብርሃን" ይባላል

አንድም ራጉኤል ማለት የሚበቀል ማለት ነው።

የሚበቀል ነው ማለት በቀል የሚገባው ለጠላት ነው የሰው ልጅ ጠላት ደግሞ ዲያብሎስ ነው፤ ስለሆነም ቅዱስ ራጉኤል እግዚአብሔርን አምነው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው በፍርሐተ እግዚአብሔር አምልኮቱን ለሚፈጽሙ ሁሉ ጠላት ዲያብሎስን የሚያርቅላቸው ወደ እነርሱም ፈጥኖ በመድረስ የሚታደጋቸው ነው ማለት ነው።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ ሥጋዋ ወደ እፀ ሕይወት ሲነጠቅ (ሲያርፍ) አብሮ ለሄደውና ስጋዋን በእጣን ሲያጥን ለነበረው መልአከ

ለወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ /ፍቁረ እግዚ/ ኅብስትን የመገበ መልአክ ነው።

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል ወር በገባ በ1 መታሰቢያ በዓሉ ነው።

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል ጥበቃው አይለየን🙏

04/07/2025

🌹27 ጠብቀን🌹

📌መድኃኔዓለም ማለት== =የአለም መድሃኒት
📌 መድኃኔዓለም ማለት=== የሁሉ ቤዛ
📌መድኃኔዓለም ማለት ===የገዢዎች ሁሉ ገዢ
📌መድኃኔዓለም ማለት===የነገስታት ሁሉ ነጉስ
📌 መድኃኔዓለም ማለት ==የፍጥረታት ሁሉ ፊጣሪ ነው።

መድኃኒዓለም …………………
✞ጌታ ሆይ...................
✞ኢየሱስ ሆይ..................
✞መድኃኒዓለም ሆይ.........
✞አማኑኤል ሆይ............
✞ጎዶልያስ ሆይ..............
✞ኤልሻዳይ ሆይ..............
✞እግዚአብሔር ሆይ........

💒 ••••••>አማኑኤል ሆይ ሁሉይ ቻይ እንደሆንክ አዉቅ ሀሳብህም ሁሉ ይሆን ዘንድ ከቶ እንደማይከለከል በአለማት ላይ አንተ ብቻ እንደሰለጠንክ የሁሉ ፍጥረታት ስራ አስኪያጅ እንደሆንክ ያለጥርጥር በሙሉ ልቤ አምናለሁ፡፡🙏🙏
💒 ••••••>ዉዴ የህይወቴ አባት ካንተ ሌላ:-
☞ሳለቅስ እንባዬን የሚያብስ
☞ስወድቅ የሚያነሳኝ
☞ስራብ የሚያበላኝ
☞ስጠፋ የሚፈልገኝ
☞ስጨነቅ የሚደርስልኝ
☞አንገቴን ስደፋ ቀና የሚያደርገኝ
ካንተ በቀር ማንም እንደሌለኝ አዉቃለሁ፡፡🙏••••••>መድኃኒዓለም ሆይ:-
ሌት ተቀን እንደ ንስር እናት የምትጠብቀኝ እና የምታየኝ -አቤቱ እንዴት ባለ አንደበት ላመስግንህ....
በአንድ ነገር ተስፈ አለኝ እሱም አንተ ዘወትር ከኔጋ ነህ.

☑️🔴 መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የድንግል ማርያም ልጅ የአለም ሁሉ ቤዛ
☑️🔴 መድኃኔዓለም የገዢዎች ሁሉ ገዢ
☑️🔴መድኃኔዓለም የነገስታት ሁሉ ንጉስ
☑️🔴መድኃኔዓለም የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ
☑️🔴መድኃኔዓለም ከአለም በፊት የነበር
☑️🔴መድኃኔዓለም አለምን አሳልፎ የሚኖር
☑️🔴አልፋና_ ኦሜጋ ዘላለም የሚኖር

መድኃኔዓለም ሆይ አንተን የወደደች ነፍስ ምነኛ የታደለች ናት።በመስቀል ላይ ተሰቅለህ የከፈልኸውን እሰከ ሞት ድረስ የተገለጠ ፍቅር በልቦናዋ የምታስቀምጥ ነፍስ ምነኛ ትከብር።የእናትህን የምትወድና ሀዘኗን የምታስብ ነፍስ ምነኛ እድለኛ ትሆን።መድኃኔዓለም ሆይ የአንተን መታሰቢያ በየወሩ በ27 የምታደርግ ምን ያህል ባለሟልነት ታገኝ ይሆን።መድኃኔዓለም ሆይ አሁንም አንተ ብትወደን እንጂ እኛ እንወድሀለን ብለን ለመናገር አንደፍርም እና እንድንወድህ የአንተንና የናትህን ፍቅር በልቦናችን ላይ አሳድርብን።
አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ሐሜት በተናገረበት ድርሳኑ እንዲህ አለ፦ሐሜተኞችን ብቻ ሳይኾን ሌሎች ሰዎች ሲታሙ “እህ” ብለው የሚያደምጡትንም ጭምር ጆሮአቸውን እንዲዘጉ፣ “ወንድሙን በስውር የ...
03/07/2025

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ሐሜት በተናገረበት ድርሳኑ እንዲህ አለ፦

ሐሜተኞችን ብቻ ሳይኾን ሌሎች ሰዎች ሲታሙ “እህ” ብለው የሚያደምጡትንም ጭምር ጆሮአቸውን እንዲዘጉ፣ “ወንድሙን በስውር የሚያማን እርሱን አሳደድሁ" ብሎ የተናገረውንም ነቢይ እንዲመስሉት እመክራለሁ (መዝ.100፥5)፡፡

ባልንጀራዉን ለማማት ብሎ ወደ አንተ የመጣውን ስው እንዲህ በለው፡- “ስለ እርሱ መልካም ነገር የምትናገርለት አሊያም ደግሞ የምታመሰግነው ሰው አለህን? ይህን በጎ መዓዛ ያለውን ዘይት ለመቀበል ጆሮዬን እከፍታለሁ፡፡ ክፉ ንግግርን የምታወራ ከኾነ ግን ቃሎችህ ወደ ጆሮዬ እንዳይገቡ እከለክላቸዋለሁ፤ ይህን ፍግና ቆሻሻ ወደ ጆሮዬ ለማስገባት አልፈቅድምና፡፡

ወንድምህ ክፉ መኾኑን ብትነግረኝ ግን ምን ይረባኛል? ይልቁንም እንዲህ ስታደርግ ራሴን እንድጎዳና ያለኝን እንዳጣ ታደርገኛለህ፡፡ ስለዚህ ስለ ወንድማችን ጥፋት ከምናወራ ይልቅ ስለ ራሳችን ኃጢአት እንጨዋወት! የሠራናቸውን መተላለፎች እንዴት ይቅርታ እንደምናገኝባቸው እንጨነቅ፣ ስለ ራሳችን ሕይወት እንደዚህ ያለ ትጋትና ምክክር እናሳይ፡፡

እስኪ ንገረኝ! ስለ ራሳችን ጉዳዮች ምንም ሳናስብ የሌሎች ሰዎችን ኃጢአት ለመመርመር እንዲህ በመፈለጋችን የምናገኘው ይቅርታ ወይም የሚደረግልን ምሕረት እንደ ምን ያለ ነው?! 'ሰው ቤት እንዲሁ ዘው ብሎ ገብቶ መመርመርና ቤቱ ውስጥ ምን ምን እንዳለ መበርበር ወራዳና እጅግ አሳፋሪ ተግባር እንደ ኾነ ኹሉ፥ የሌላ ስው ሕይወት ምን እንደሚመስል መመርመርም እንደዚሁ የመጨረሻው የጨካኝነት ደረጃ ነው፡፡

ከዚህ ኹሉ የከፋው ደግሞ እንደዚህ ዓይነት ሕይወትን የሚኖሩና የራሳቸውን ጉዳይ የረሱ ሰዎች፥ ይህን ሐሜታቸውን የሚነግሩትን ሰው ለሌላ ሰው እንዳይናገር መለመናቸውና መማጸናቸው እነርሱ እንደዚህ መናገራቸው ግን ተግሣጽ እንደ ኾነና ተገቢ ሥራን እንደ ሠሩ አድርገው ማሰባቸው ነው፤ ይህን ለሌላ ስው እንዳይናገር የምትማጸነው ከኾነ፡ አስቀድመህ እነዚህን ነገሮች ከመናገር ልትቈጠብ አይገባህም ነበርን? ጉዳዩ በአንተ እጅ እያለ ምሥጢሩ የተጠበቀ ነበር፤ አሁን ካጋለጥከው በኋላ ግን ለምሥጢሩ መጠበቅ አብልጠህ የምትተጋ ኾንክ፡፡ የሰማህ ሰው ለሌላ ሰው እንዳይናገር የምትፈልግ ከኾነ አንተው ራስህ ቀድመህ አትንገረው፡፡ የጉዳዩን ምሥጢራዊነት ለሌላ ሰው ከገለጥክ በኋላ የነገርከውን ነገር ምሥጢር እንዳያወጣ ብለህ ብታስጠነቅቀውና ብታምለው ግን ግብርህ አፍአዊና ረብ የለሽ ነው፡፡

“ሐሜት ግን'ኮ ይጣፍጣል፡፡" በፍጹም! ጣፋጭስ አለማማት ነው፡፡ ምክንያቱም ሐሜተኛ ሰው ካማበት ጊዜ አንሥቶ ጠበኛ ነው፤ ተጠራጣሪ ነው፤ ይፈራል፤ ይጸጸታል፤ ከዚህም የተነሣ ምላሱን ይነክሳል (ይከነክኗል)፡፡ እንዲህ በፍርሐትና በረዓድ ተይዞ ሳለም ከዕለታት በአንዷ ላይ የተናገረው ነገር ወደ ሌሎች ሰዎች ይዛመታል፡፡ ታላቅ የኾነ መከራ እንደዚሁም ረብ የለሽና የማይገ'ባ ጠላትነትን ያመጣበታል፡፡ የጉዳዩን ምሥጢራዊነት ለሌላ ሰው የማይናገር ሰው ግን ዐረፍተ ዘመኑን ያለስጋትና እጅግ ደስ ብሎት ያሳልፋል፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፡- “የሰማኸው ቃል በአንተ ዘንድ ይሙት! እንዲህ ያደረግህ እንደ ኾነ የሚያገኝህ ክፉ ነገር እንደሌለ እመን” (ሲራ.19፡10)፡፡ “በአንተ ዘንድ ይሙት" ሲል ምን ማለት ነው? አጥፋው፤ ቅበረው! ከዚህ በላይ እንዲኼድ አትፍቀድለት! ምንም እንዳይንቀሳቀስ አድርገው፤ ከዚህ ኹሉ በላይ ግን ሰዎች ሐሜትን ሲለማመዱ ታግሠህ እንዳትስማቸው ተጠንቀቅ፡፡" አንተም ድንገት በኾነ ጊዜ ላይ ሐሜትን ብትስማ የሰማኸውን ቅበረው፤ የተነገረህን አስወግደው፤ ወደ መርሳት ባሕር ውስጥ ጣለው፤ ይህን ያደረግህ እንደኾነም ነገሩን እንዳልሰሙት ሰዎች ኾነህ የዚህ ዓለም ሕይወትህን በሰላምና በጸጥታ ታሳልፋለህ፡፡

ሐሜተኞች ከሚያሙአቸው ሰዎች በላይ እኛ እነርሱን [ሐሜተኞቹን] እንደምንጸየፋቸው ቢያውቁ ኖሮ ከዚያን ጊዜ ጀምረው እነርሱ ራሳቸው ይህን ክፉ ጠባይ በተዉ፣ ኃጢአታቸውን ባስወገዱ፣ ከዚያ በኋላም እኛን እንደ ታዳጊዎቻቸውና ረዳቶቻቸው አይተው ባመሰገኑን ነበር፡፡ እኛን ማመስገናቸው የወዳጅነታቸው ምልክት እንደ ኾነ ኹሉ ማማትና ስም ማጥፋትም አሁን ላዳበሩት ጠላትነት፣ ቂምና በቀል ጥንትና መሠረት ነበርና፡፡

ለሐሜት የሚሯሯጥና የሌሎች ሰዎችን ሕይወት በማጥናት የተጠመደ ሰው መቼም መች የራሱን ሕይወት መመልከት አይቻለውምና፥ የሰውን ምሥጢር ለማወቅ ከመጓጓትና በሌሎች ሰዎች ጉዳይ ዘው ብሎ ከመግባት ልማድ በላይ የራስህን ጉዳይየሚያስረሳ ምንም የለም፡፡ ምርምሩ ኹሉ በሌሎች ሰዎች ጉዳይ ጣልቃ መግባት ስለ ኾነ እርሱን የሚመለከቱ ኹሉም አስፈላጊ ነገሮች ለአደጋ የተጋለጡ ኾነው ይተ'ዋሉ፤ ችላም ይባላሉ፡፡ ሰው ትርፍ ጊዜዉን የገዛ ራሱን ኃጢአቶች እንደዚሁም እንዴት ሊያስወግዳቸው እንደሚገባው ቢያስብ መልካም ነው፤ መንፈሳዊ ምንድግናንም ገንዘብ ያደርጋል፡፡ ኹልጊዜ በሌሎች ሰዎች ጉዳይ የምትጠመድ ከኾነ ግን የራስህን ክፉ ግብሮች የምታስተውላቸው መቼ ነው?

(ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት፣ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ገጽ 79-96 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)

Address

London

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mido Entertainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mido Entertainment:

Share